id
stringlengths
8
14
url
stringlengths
36
42
title
stringlengths
8
90
summary
stringlengths
6
505
text
stringlengths
133
19.2k
news-53172629
https://www.bbc.com/amharic/news-53172629
"ወረርሽኙ መፍትሔ እስከሚያገኝ ስደተኞቹ በያሉበት በትዕግስት ይጠባበቁ" በጂዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ
በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች በሳኡዲ አረቢያ እስር ቤቶች ውስጥ በከፍተኛ ችግር ውስጥ ይገኛሉ።
ስደተኞቹ ለቢቢሲ በላኩት ተንቀሳቃሽ ምስሎች፤ ቁጥራቸው ከፍተኛ የሆኑ ስደተኞች በጠባብ እና ሞቃታማ ቦታ ላይ በአንድ ላይ ታጭቀው በአስከፊ ሁኔታ ላይ ሆነው ይታያሉ። ስሙ እንዲጠቀስ ያልፈለገ አንድ ወጣት ከሦስት ወራት ገደማ በፊት በየመንመመ በሁቲ አማፂያንና በሳኡዲ መካከል በነበረው ጦርነት ሕይወቱ አደጋ ላይ እንደነበር ያስታውሳል። በወቅቱ የሳኡዲ መንግሥት ወደ ግዛቱ እንዲገቡ ከፈቀደላቸው ስደተኞች መካለከል አንዱ የሆነው ይህ ወጣት፣ ከዚያ በኋላ አሁን ያሉበት ስፍራ መጣላቸውን ለቢቢሲ ተናግሯል። በእስር ቤቱ ውስጥ ስላለበት ሁኔታም "በሽንት ቤት ውስጥ ነው ያለነው፣ እዚያው እንበላለን፣ ከሽንት ቤት ውሃ እንጠጣለን። ውሃም በሦስት ቀን አንዴ ነው የሚመጣው። እየኖርንበት ያለው ቦታ ልንተኛበት ይቅርና ለማየትም የሚያስጠላ ነው። እላያችን ላይ ሰገራ እየፈሰሰብን ነው" በማለት ያሉበትን ሁኔታ ገልጾታል። በተለያዩ አሰቃቂ እስር ቤቶች ውስጥ ከሚገኙ ስደተኞች እስካሁን ሰባት ሰዎች የሞቱ ሲሆን፤ አንዱ በሳኡዲ የፀጥታ አካላት ነው የተገደለ" ሲል ከመካከላቸው የሞቱ ሰዎች ቢኖሩም እስከኣሁን የሚረዳቸው ሰው እንዳላገኙም ለቢቢሲ አስረድቷል። ወጣቱ አክሎም "በአንድ ቀን ሦስት ሰዎች ሞተውብን ዝም ብለው እንደ ቆሻሻ ተጥለዋል። አሁን ራሱ ሊሞት የደረሰ ሰው አለ። እኛን የሚረዳ ሰው ማን እንደሆነ አናውቅም፤ መፍትሔ አጥተናል። ይህንን የምትሰሙም እባካችሁ እርዱን። ከዚህ ሞት አውጡን” በማለት የእርዳታ ጥሪውን አሰምቷል። ቢቢሲ ያነጋገራቸውና በዚያው በሳኡዲ አረቢያ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ አስባባሪ የሆኑት አቶ መሀሪ በላይ ትናንት ረፋድ ላይ ስደተኞቹን ለመጎብኘት ባቀኑበት ወቅት፤ ስደተኞቹ አሁንም በተመሳሳይ ሁኔታ ውስጥ እንዳሉ መመልከታቸውን ተናግረዋል። "በእስር ቤቱ ያለው ቆሻሻ፣ ረሃብና ሁሉም ችግር የታወቀ ነው" የሚሉት አቶ መሀሪ፤ የታመሙት ህክምና እንዲያገኙ እንዲሁም ወታደሮች ጉዳት እንዳያደርሱባቸው ተነጋግረው መምጣታቸውን ይገልጻሉ። በእስር ላይ የሚገኙ ስደተኞች ለተለያዩ የጤና ችግር መጋለጣቸው እየተነገረ ነው "እኚህ ዜጎች ከየመን ሲመጡ፤ ልብስ የላቸው፣ ጫማ የላቸው፣ አንድ ቲሸርት ብቻ ለብሰው ነው የመጡት። አንድ ቲሸርት ለብሰው ለሦስት ወራት ያህል በአንድ እስር ቤት ቁጭ ሲሉ፤ በዚያ ላይ አሁን ባለው ከፍተኛ ሙቀት ተጨናንቀው እየደረሰባቸው ያለውን ጉዳት መገመት አያዳግትም" ይላሉ አቶ መሀሪ- ስለሁኔታው ሲገልጹ። በእስር ቤት የሚገኙት ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ከዚህ በተጨማሪም በቂ ምግብ በማያገኙበትና ለመታጠቢያ እንኳን ውሃ በሌለበት አስከፊ ሁኔታ ላይ በስቃይ ውስጥ እንደሚገኙ ጠቅሰዋል። በሳኡዲ ያለው የኢትዮጵያ ማኅበረሰብም እነርሱን ለመርዳት ጥረት እያደረገ እንደሆነም ነግረውናል። አቶ መሀሪ በጥይት የተመቱ እና እግራቸው ላይ ብረት የገባባቸው እንዳሉ ገልፈው፤ ጂዛን በሚባል ከተማ ያሉት ዜጎች ደግሞ ተላላፊ ይሁን አይሁን ባይታወቅም ሰውነታቸው እና ፊታቸው ላይ እብጠት ስለወጣባቸው፤ ማኅበረሰቡ ለህክምና የሚሆን ብር እያዋጣ መሆኑን ጠቁመዋል። "የእነዚህ ዜጎች ችግር የሚያበቃው ወደ አገራቸው መመለስ ሲችሉ ብቻ ነው" በማለት ወደ ኢትዮጵያ የሚመለሱበት መንገድ እንዲፈለግ ጠይቀዋል። ከቀናት በፊት የውጪ ጉዳይ ሚንስቴር በእስር ላይ የሚገኙ ስደተኞችን ወደ ኢትዮጵያ ለመመለስ ወይም ወደተሻለ ማቆያ ሥፍራ ለማሸጋገር ጥረት እያደረኩ ነው ብሎ ነበር። ይሁን እንጂ በጅዳ የሚገኘው የኢትዮጵያ ቆንስላ ዜጎችን ወደ አገር ቤት የመመለሱ ጥረት እንደሚዘገይ ትናንት አስታውቋል። ቆንስላው ረቡዕ ከሰዓት በፌስቡክ ገጹ ላይ ባወጣው መግለጫ፤ ስደተኞቹን ወደ አገራቸው መመለስን በተመለከተም፤ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እና የአፍሪካ ሕብረት ባወጧቸው ድንጋጌዎች የኮቪድ-19 ወረርሽኝ መፍትሄ እስኪያገኝ ድረስ ስደተኞች በያሉበት ይቆዩ ሲሉ መደንገጋቸውን በአስታውሷል። ጨምሮም በኢትዮጵያም በቂ የለይቶ ማቆያ ስፍራዎች አለመኖራቸውን በመጥቀስ፤ ስደተኞችን ከሳኡዲ የማስወጣቱ እንቅስቃሴ መስተጓጎሉን ገልጾ በእስር ቤቶች የሚገኙ ዜጎችም በትዕግስት እንዲጠባበቁም ቆንስላው ጠይቋል። በተያያዘም ቆንስላው በመግለጫው በጄዳ ሺሜሲ (የሴቶች እስር ቤት) በተፈጠረ ግርግር ምክንያት በርካታ ዜጎች ስለመጎዳታቸው መረጃ እንደደረሰው ገልጾ፤ ክስተቱ ለረዥም ጊዜ በእስር ቤት መቆየታቸውን በመቃወም ከእስር ቤት ለመውጣት ሲሞክሩ ከፖሊስ ጋር በመጋጨታቸው የተፈጠረ ነው ብሏል። በዚህም በአንዲት ስደተኛ ላይ መጠነኛ ጉዳት መድረሱንና ህክምና እንደተደረገላት መሆኑን የኢትዮጵያ መንግሥት ቆንስላ በመግለጫው አስፍሯል።
news-55112952
https://www.bbc.com/amharic/news-55112952
ኢራን የኑክሌር ሳይንቲስቷን ግድያ እንደምትበቀል ዛተች
የኢራኑ ፕሬዝደንት ሐሰን ሩሃኒ ለአገራቸው ዋነኛ የኑክሌር ሳይንቲስት ግድያ እስራኤልን ተጠያቂ በማድረግ፤ ግድያው የኢራንን የኑክሌር መረሃ ግብር ፍጥነት እንደማይቀንሰው ተናገሩ።
የኑክሌር ሳይንቲስቱ ሞህሲን ፋክሪዛዴህ ፕሬስደንቱ ጨምረውም በሳይንቲስቱ ሞህሲን ፋክሪዛዴህ ግድያ የኢራን ጠላቶች ምን ያህል በጠለቀ "በተስፋ መቁረጥና በጥላቻ" ውስጥ እንዳሉ ያሳ ነው ብለዋል። እስራኤል ከኢራን በኩል Iየቀረበባትን ክስ በተመለከተ ምላሽ ባትሰጥም፤ ቀደም ሲል ሞህሲን ፋክሪዛዴህ ኢራን በድብቅ ከምታካሂደው የኑክሌር ጦር መሳሪያ ግንባታ ጀርባ አሉ ስትከስ ነበር። ኢራን በዋነኛው የኑክሌር ሳይንቲስቷ ሞህሲን ፋክሪዛዴህ ላይ የተፈጸመውን ግድያ እንደምትበቀልም አሳውቃለች። ፋክሪዛዴህ ትናንት አርብ በዋና ከተማዋ ቴህራን አቅራቢያ ባልታወቁ ሰዎች በተፈጸመባቸው ጥቃት ሆስፒታል ተወስደው ነበር ህይወታቸው ያለፈው። የኢራን ሐይማኖታዊ የበላይ መሪ አያቶላህ አሊ ካሚኒ ወታደራዊ አማካሪ ሆሴን ዲጋን እንዳሉት ግድያውን በፈጸሙት ላይ ኢራን "በመብረቃዊ ጥቃት" እንደምትበቀላቸው ተናግረዋል። የምዕራባዊያን የስለላ ተቋማት እንደሚሉት ሳይንቲስቱ ፋክሪዛዴህ ኢራን በድብቅ እያካሄደች ነው ከሚሉት የኑክሌር ጦር መሳሪያ ግንባታ ፕሮግራም ጀርባ ያሉ ቁል ሰው ናቸው። ነገር ግን ኢራን እያካሄደች ያለው የኑክሌር መረሃ ግብር ለሰላማዊ ዓላማ አገልግሎት የሚውል እንደሆነ በተደጋጋሚ ገልጻለች። ግድያውን ተከትሎ የአገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሞሐመድ ጃቫድ ዛሪፍ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ "መንግሥታዊ የሽብር ተግባር" ያሉትን እንዲያወግዝ ጠይቀዋል። "ሽብርተኞች ታዋቂውን ኢራናዊ ሳይንቲስት ዛሬ ገደሉት" ሲሉም ሚኒስትሩ በትዊተር ገጻቸው ላይ ጽፈዋል። የሳይንቲስቱ መገደል የተሰማው ኢራን እያዳበረችው ያለው የዩራኒየም መጠን መጨመሩን በተመለከተ ስጋት እንዳለ መገለጹን ተከትሎ ነው። የዳበረ ዩራኒየም ለሰላማዊና ለወታደራዊ የኑክሌር ጦር መሳሪያ ግንባታ መረሃግብሮች ወሳኝ ግብአት መሆኑ ይታወቃል። ሳይንቲስቱን መገደል ይፋ የሆነው የኢራን መከላከያ ሚኒስቴር ትናንት አርብ ባወጣው መግለጫ ነበር። ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ባወጠው መግለጫ ላይ "የታጠቁ ሽብርተኞች በሚኒስቴሩ ውስጥ ያለው የምርምርና ጠፈጠራ ድርጅት ኃላፊ የሆኑትን ሞህሲን ፋክሪዛዴህ ይጓዙበት የነበረው መኪና ላይ ጥቃት ፈጽመዋል" በማለት ገልጿል። የሳይንቲስቱ ጠባቂዎች ከጥቃት ፈጻሚዎቹ ጋር የተኩስ ልውውጥ ማድረጋቸውንና በዚህም መካከል "ሞህሲን ፋክሪዛዴህ በጠና ቆስለው ወደ ሆስፒታል መወሰዳቸው" አብራርቷል። የህክምና ባለሙያዎች የሳይንቲስቱን ህይወት ለማትረፍ ያደረጉት ጥረት ሳይሳካ ቀርቶ ህይወታቸው ማለፉን የመከላከያ ሚኒስቴሩ ባወጣው መግለጫ ላይ ይፋ አድርጓል። በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኢራን አምባሳደር የሆኑት ማጂድ ታካት ራቫንቺ ግድያው ሆን ተብሎ በአካባቢው ቀውስ ለመፍጠር የተፈጸመና ግልጽ የዓለም አቀፍ ሕግ ጥሰት ነው በማለት በግድያው ውስጥ የእስራኤል እጅ ስለመኖሩ የሚያመለክቱ ማስረጃዎች እንዳሉ ተናግረዋል። የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ናታኒያሁ ከሁለት ዓመት በፊት ስለኢራን የኑክሌር ፕሮግራም ማብራሪያ በሰጡበት ጊዜ የኑክሌር ሳይንቲስቱን ስም በተለይ ጠቅሰው ነበር። ሆኖም ግን ግድያውን በተመለከተ አስካሁን ድረስ ከእስራኤል በኩል የተሰጠ ምንም አይነት አስተያየት የለም።
news-41815448
https://www.bbc.com/amharic/news-41815448
የሳዑዲው አልጋ ወራሽ ልዑል ሳዑዲ አረቢያ ወደ ለዘብተኛ የእስልምና ስርዓት መመለስ ትፈልጋለች አሉ።
የሳዑዲው አልጋ ወራሽ ልዑል ሞሃመድ ቢን ሳልማን፤ ሳዑዲ አረቢያ ወደ 'ለዘብተኛ የእስልምና ስርዓት መመለስ' የባህረ ስላጤዋን ሃገር ለማዘመን ቁልፍ ነው ብለዋል።
የሳዑዲው አልጋ ወራሽ ልዑል ሞሃመድ ቢን ሳልማን ይህን አስተያየት የሰጡት በሪያድ ሲካሄድ በነበረው የኢኮኖሚ ስብሰባ ላይ ነው። ልዑሉ በሰጡት መግለጫ ከአጠቃላይ የሳዑዲ ዜጎች ሰባ በመቶ የሚሆኑት እድሜያቸው ከሰላሳ ዓመት በታች መሆኑን ጠቁመው፤ እነዚህ ወጣቶች ''ሃይማኖታችን መቻቻል ሲል የሚገልፀውን'' አይነት ህይወት ይሻሉ ብለዋል። አልጋ ወራሹ ''አክራሪ የእስልምና ስርዓት አራማጆችን በቅርቡ አስወግዳለሁ" ሲሉም ቃል ገብተዋል። ይህ ሃሳባቸውን የተናገሩት በ500 ቢሊያን ዶላር ኢንቨስትመንት የምትገነባውን ከተማ እና የንግድ ቀጠና ካስተዋወቁ በኋላ ነበር። ኒዮም ተብላ የተሰየመችው ከተማ፤ በ26500 ስኩዌር ኪ.ሜ ላይ የምታርፍ ሲሆን በሳዑዲ አረቢያ ሰሜን-ምዕራብ አቅጣጫ ለግብፅ እና ለዮርዳኖስ ቅርብ በሆነ ቦታ ላይ ትገነባለች። ባለፈው ዓመት የ32 ዓመቱ አልጋ ወራሽ ልዑል ሞሃመድ በነዳጅ ላይ የተመሰረተውን የሳዑዲ ኢኮኖሚ ለመቀየር ባለ ብዙ ዘርፍ ማህበራዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ ለውጦችን ለማምጣት ራዕይ 2030 የተባለውን እቅድ አስተዋውቀው ነበር። በዚህ እቅድ ውስጥ የተለያዩ ማሻሻያዎች የተካተቱ ሲሆን በሳውዲ መንግሥት ስር የሚገኘውን ሳዑዲ አርማኮ የተባለውን ነዳጅ አውጪ ኩባንያን በከፊል ወደ የግል ይዞታ ማዞር ይገኝበታል። የሳዑዲ ኢኮኖሚ የተመሰረተው በተፈጥሮ የነዳጅ ሃብቷ ላይ ነው ምንም እንኳን ከወግ አጥባቂዎች ተቃውሞ ቢሰነዘርም፤ ከወር በፊት የልዑሉ አባት ንጉስ ሰልማን ሴቶች መኪና ማሽከርከር እንዲችሉ መወሰናቸው ይታወሳል። ከዚህ በተጨማሪም መንግሥት በመዝናኛ ዘርፉ መዋዕለ ንዋዩን ፈሰስ ማድረግ ይፈልጋል። ኮንሰርቶች በድጋሚ በሳዑዲ መደረግ ይጀመራሉ፤ ሲኒማ ቤቶች እንደገና ይከፈታሉ ተብሏል። አልጋ ወራሽ ልዑል ሞሃመድ እቅዳቸውን በሪያድ ይፋ ባደረጉበት ወቅት የበርካታ ባለሃብቶችን እና የሃገር ተወካዮችን ቀልብ መሳብ ችለዋል። ''ለተቀሩት ሃይማኖቶች፣ ባህሎች እና ከተለያዩ ዓለማት ለሚመጡ ሰዎች ክፍት ወደሆነው እና ከዚህ በፊት ወደ ነበርንበት- ለዘብተኛ የእስልምና ስርዓት ነው የምንመለሰው'' ብለዋል። ''ሰባ በመቶ የሚሆኑት ዜጎቻችን ከሰላሳ ዓመት በታች ናቸው። በሚቀጥሉትን ሰላሳ ዓመታት አፍራሽ የሆኑ ሃሳቦችን ማራመድ አንችልም። ምክንያቱም ይህ አካሄድ ወጣቱን በአንድ ጊዜ ሊያጠፋ ይችላል።'' አልጋ ወራሽ ልዑል ሞሃመድ ''ሳዑዲ አረቢያ እአአ ከ1979 በፊት እንደዚህ አልነበረችም'' ሲሉ በአጽንዖት ተናግረዋል። በኢራን በነበረው እሰላማዊ አብዮት እና ታጣቂዎች የመካን ትልቁን መስኪድ ከተቆጣጠሩ በኋላ ህዝባዊ መዝናኛዎች በሳውዲ ተከለከሉ እንዲሁም የሃይማኖት መሪዎች በዜጎች ህይወት ላይ ቁጥጥር ማድረግ እንደጀመሩ ይነገራል።
57326564
https://www.bbc.com/amharic/57326564
የእሳተ ገሞራ ፍንዳታ ግማሽ ሚሊዮን ሕዝብ የውሃ እጥረት እንዲገጥመው አደረገ
በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኦፍ ኮንጎ የተከሰተውን የእሳተ ገሞራ ፈንዳታን ተከትሎ ወደ ግማሽ ሚሊዮን የሚጠጋ ሕዝብ የንፁህ መጠጥ ውሃ እጥረት እንዲገጥመው ማድረጉን ድንበር የለሹ የህክምና ቡድን አስታወቀ።
የኮሌራ በሽታ ወረርሽኝ ሊቀሰቀስ እንደሚችል ከፍተኛ ስጋት መኖሩን ጠቅሶ በምስራቅ ጎማ ለሚገኙ ነዋሪዎች የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ጊዜ የማይሰጠው መሆኑን ገልጿል። ግንቦት 22 በኚራጎንጎ ተራራ በተከሰተ አሳተ ገሞራ ፍንዳታ ምክንያት የውሃ ማጠራቀሚያ እና ውሃ ማስተላለፊያ ቱቦወፐች ጉዳት ደርሶባቸዋል። በመቶ ሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎችም ወደ ቤታቸው መመለስ አልቻሉም። "የተፈናቀሉ ሰዎችን አስቸኳይ ፍላጎት ለማሟላት እየሠራን ቢሆንም በቂ አይደለም" ያሉት በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የቡድኑ ተልዕኮ ኃላፊ የሆኑት ማጋሊ ሩዳውት ናቸው። "ሰዎችን እንድንረዳ ሌሎች ሰብዓዊ ድርጅቶች አስቸኳይ ድጋፍ እንዲሰጡን እንጠይቃለን" ብለዋል። ድንበር የለሹ የህክምና ቡድን በአቅራቢያው በሚገኘው በሴክ ከተማ "ከ100,000 እስከ 180,000 የሚደርሱ ነዋሪዎች በአብያተ ክርስቲያናት፣ ትምህርት ቤቶች፣ መስጊዶች እና በጎዳናዎች በተጠለሉበት የህክምና አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን" አስታውቀዋል። ከጎማ 10 ኪ.ሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው የኚራጎንጎ ተራራ ከ10 ቀናት በፊት እሳተ ገሞራ በመከሰቱ የ32 ሰዎች ህይወት ማለፈፉን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስታውቋል። በዓለም ላይ በጣም ንቁ ከሆኑት እሳተ ገሞራዎች መካከል አንዱ ከፈነዳ ጀምሮ ብዙ የመሬት መንቀጥቀጦች ተከስተዋል። የአደጋ ተጋላጭነት ባለሙያዎችን እሳተ ገሞራው ያለበትን ደረጃ ለመገምገም ድሮን (አነስተኛ ሰው አልባ አውሮፕላኖች) አሰማርተዋል።
news-55099371
https://www.bbc.com/amharic/news-55099371
ሕይወታቸው ያለፈ ሰዎችን የሰውነት አካል ሲሰርቁ የነበሩ ዶክተሮች ተፈረደባቸው።
በቻይና በአደጋ ምክንያት ሕይወታቸው ያለፉ ሰዎችን የሰውነት የውስጥ አካል እያወጡ ሲሸጡ የነበሩ ዶክተሮችን ተባባሪዎቻቸው ጥፋተኛ ተብለው እስር መቀጣታቸው ተዘግቧል።
ተባባሪ ግለሰቦቹ እና የጤና ባለሙያዎቹ በአደጋ ምክንያት ሕይወታቸው ያለፈ ሰዎችን ቤተሰቦች የሟቾቹን አካል እንዲለግሱ በመጠየቅ ሕጋዊ ለማስመሰል ቅጽ በማስሞላት ሲያጭበረብሩ ነበር ተብሏል። በፈረንጆቹ 2017 እና 2018 እነዚሁ ሰዎች በቻይናዋ አንሁይ ግዛት የ11 ሰዎችን ጉበትና ኩላሊት አውጥተው በሕገ-ወጥ መንገድ ሸጠዋል። ቻይና ውስጥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሰውነት አካል ፈላጊዎች ቁጥር እየጨመረ የመጣ ሲሆን በበጎ ፈቃደኞች በኩል የሚገኘው የሰውነት አካል ደግሞ ከፈላጊዎች ቁጥር ጋር ሊጣጣም አልቻለም። የአገር ውስጥ መገናኛ ብዙሀን እንደዘገቡት የሰዎችን አካል ሲሸጥ የነበረው ቡድኑ በመኪና አደጋ ሕይወታቸው ያለፉ ሰዎችን ኢላማ አድርጎ ሲንቀሳቀስ ነበር። በአንሁይ የሚገኘው ሂዋያን ሆስፒታል የጽን ህሙማን ክፍል ኃላፊው ያንግ ሱክሱን የሟቾች ቤተሰቦችን በመቅረብ አንዳንድ የሰውነት ክፍሎችን ለመለገስ ፈቃደኛ አንዲሆኑ የማግባባት ስራም ይሰሩ ነበር ተብሏል። በዛውም ሐሰተኛ ዶሴ ላይ እንዲፈርሙ በማድረግ የሰውነት አካሎቹን በከፍተኛ ገንዘብ ይሸጡታል። የዚህ ቡድን ተግባር ሊጋለጥ የቻለው አንድ እናቱን በሞት የተነጠቀ ግለሰብ ባደረገው ማጣራት ነው። በፈረንጆቹ 2018 ላይ ሺ ዢያንድሊን እናቱ ከሞተች በኋላ አካሏ እንዲለገስ የፈረመበት ቅጽ ሲመረምር አንዳንድ ግራ የሚያጋቡ ነገሮችን ማስተዋል ቻለ። በመቀጠልም የሰውነት ክፍላቸውን የለገሱ ሰዎች የሚመዘገቡበት ማዕከል በመሄድ ሲያጣራ የእናቱ ስም አለመኖሩን ማረጋገጥ ችሏል። ወዲያውም ጉዳዩን ለመገናኛ ብዙሀን ይፋ አድርጓል። ከዚህ በኋላ ሺ ወደ ሆስፒታሉ በመሄድ የጽኑ ህሙማን ክፍል ኃላፊውን ለማናገር ሲሞክር ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ እንደሚከፍሉትና ምንም አይነት መረጃ ለሰዎች እንዳያወራ ጠየቁት። ሕገ-ወጥ ተግባር እየተፈጸመ እንደሆነ የተረዳው ሺ ወዲያውኑ ጉዳዩን ለፖሊስ ያሳወቀ ሲሆን ይህንን ወንጀል ሲፈጽሙ የነበሩት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው በፍርድ ቤት ጥፋተኛ ተብለዋል።
news-53900407
https://www.bbc.com/amharic/news-53900407
ሱዳን፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ወደ ሱዳን ሄዱ ማይክ ፖምፒዮም ካርቱም ገብተዋል
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ወደ ሱዳን ዛሬ ማለዳ ማምራታቸውን ጽህፈት ቤታቸው አስታወቀ።
ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ ከሱዳን ሉአላዊ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሌተናንት ጀኔራል አብደል ፈታህ አል ቡርሃን ጋር [ቀደም ያለ ጉብኝት] ጠቅላይ ሚኒስትሩ በካርቱም በሚኖራቸው ቆይታ ከሱዳን ሉዓላዊ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሌተናል ጄነራል አብዱል ፈታህ አልቡርሐንና ከጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሐምዶክ ጋር በአገራቱ የሁለትዮሽ ግንኙነት ላይ ውይይት ያካሂዳሉ ሲል ጽህፈት ቤታቸው ገልጿል። በተመሳሳይም አሜሪካው የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ማይክ ፖምፒዮ ታሪካዊ ጉብኝት ለማድረግ ዛሬ ማክሰኞ ከእስራኤል ጉዟቸው በማስከተል ሱዳን ገብተዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ወደ ሱዳን ሲጓዙ ከ15 ዓመታት በኋላ በአንድ የአሜሪካ ከፍተኛ ባለስልጣን የተደረገ የመጀመሪያው ጉብኝት ነው። ለዓመታት ተበላሽቶ የቆው የአሜሪካና የሱዳን ግንኙነት ባለፈው ዓመት ኦማር ሐሰን አልብሽር በሕዝባዊ ተቃውሞ ከስልጣናቸው ከተወደዱ በኋላ እየተሻሻለ መጥቷል። የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ በጉብኝታቸው የሱዳን መንግሥት ከፍተኛ ባለስልጣናት ከሆኑት ከጠቅላይ ሚኒስትሩና ከሉዓላዊ ምክርቤቱ ፕሬዝዳንት ጋር ውይይት እንደሚያደርጉ ተነግሯል። በአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና በሱዳን ባለስልጣናት መካከል የሚደረገው ውይይት ሱዳን ለምታደርገው ዴሞክራሲያዊ ሽግግር አሜሪካ በምትሰጠው ድጋፍ፣ ሱዳን ሽብርን ከሚደግፉ አገራት ዝርዝር ውስጥ ስለምትወጣበት ሁኔታና ሱዳን ከእስራኤል ጋር ስላላት ግንኙነት ላይ ያተኮረ ይሆናል ተብሏል። የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማይክ ፖምፒዮ ቀደም ሲል እስራኤል ውስጥ ጉብኝት በማድረግ ከከፍተኛ አገሪቱ ባለስልጣናት ጋር የተወያዩ ሲሆን የሱዳኑ ጉብኝታቸውም ያንን ተከትሎ የሚከናወን ነው። የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ወደ ሱዳን ባቀኑበት ዕለት የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማይክ ፖምፒዮ ወደ ካርቱም እንደሚገቡ መገለጹ በሁለቱ መካከል ውይይት ለማድረግ የሚያስችል እድል እንዳለ እየተነገረ ነው። በተለይ ደግሞ ከወራት በፊት በአሜሪካ አደራዳሪነት በኢትዮጵያ፣ በሱዳንና በግብጽ መካከል ሲካሄድ የነበረው የታላቁ ህዳሴ ግድብ ድርድር ጉዳይ በዚሁ አጋጣሚ ሊነሳ እንደሚችል ተገምቷል። ኢትዮጵያ ያለባትን የኤሌክትሪክ ኃይል እግር ለመቅረፍ ከፍተኛ ገንዘብ አፍስሳ ባለፉት በርካታ ዓመታት የስትገነባው በቆየውና ወደ መጠናቀቁ በተቃረበው ግዙፍ ግድብ ዙሪያ ሦስቱ አገራት መቋጫ ያላገኘ ድርድር ሲያደርጉ ቆይተዋል። በግድቡ የውሃ አሞላልና የሥራ ክንውን ዙሪያ መግባባት ያልቻሉት ኢትዮጵያ፣ ሱዳንና ግብጽ እየተጀመረ በተለያዩ ምክንያቶች ሲቆረጥ የቆየ ውይይትና ድርድር ሲያደርጉ መቆየታቸው ይታወሳል። በተለይ ከወራት በፊት ዋሽንግተን ውስጥ የአሜሪካ መንግሥትና የዓለም ባንክ ተሳታፊ የነበሩበት ድርድር ወደ መጠናቂያው በተቃረበበት ጊዜ ኢትዮጵያ ጥቅሜን የሚየስከብር አይደለም በማለት ከስምምነቱ እራሷን ማግለሏ ይታወሳል። በግድቡ ድርድር ጉዳይ ላይ የአሜሪካውን ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕን ጨምሮ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩና የአገሪቱ የገንዘብ ሚኒስትር ጉዳዩን በቅርበት ሲከታተሉት እንደነበረ ይታወቃል። የአሜሪካው የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ማይክ ፖምፒዮ የሱዳን ጉብኝት ከበርካታ ዓመታት በኋላ በአንድ የአሜሪካ ከፍተኛ ባለሥልጣን የተደረገ ቀዳሚ ጉብት ነው። ለሦስት አስርት ዓመታት ያህል ሱዳንን የመሩት ኦማር ሐሰን አልበሽር ከረዥም የስልጣን ዘመን በኋላ መነሳታቸውን ተከትሎ በአገሪቱ የተጀመረው የለውጥ እንቅስቃሴ በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ግንኙነት ለማሻሻል በር ከፍቷል። ሱዳን የአልቃኢዳ መሪ የነበረውን ኦሳማ ቢን ላደን አስጠግታ በማቆየትና የተለያዩ የሽብር ቡድኖችን በመደገፍና በአሜሪካዊያንና በአሜሪካ ጥቅሞች ላይ ከተፈጸሙ ጥቃቶች ጋር በተያያዘ በአሜሪካ ጥቁር መዝገብ ውስጥ ገብታ ቆይታለች። የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ኃላፊ ማይክ ፖምፒዮ ወደ ሱዳን የሚያቀኑት በእስራኤል፣ በባህሬንና በተባበሩት የአረብ ኤምሬቶች የሚያደርጉት የጉዞ ፕሮግራማቸው ውስጥ አንድ አካል ሆኖ ነው።
news-50876650
https://www.bbc.com/amharic/news-50876650
ደቡብ አፍሪካ፡ ታዳጊዎች ሲገረዙ የሞቱባቸው ትምህርት ቤቶች ታገዱ
ታዳጊ ወንዶች ሲገረዙ ሕይወታቸው ማለፉን ተከትሎ ደቡብ አፍሪካ በርካታ ባህላዊ ትምህርት ቤቶችን አገደች።
የአገሪቱ የሀይማኖትና ባህል ኮሚሽን፤ ቢያንስ 20 ታዳጊዎች ለመሞታቸው ተጠያቂ ናቸው ያላቸው በቁጥጥር ሥር እንዲውሉ ጠይቋል። ታዳጊ ወንዶች ለሳምንታት በተራራማ አካባቢ፣ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ እንዲቆዩ የሚያደርጉት ትምህርት ቤቶች፤ ታዳጊዎች ወደ ወጣትነት የሚሸጋገሩባቸው እንደሆኑ ይነገራል። በየዓመቱ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ እድሜያቸው ከ15 እስከ 17 የሚደርሱ ወንዶች፤ ጫካ ውስጥ ተገልለው እንዲቆዩ ተደርጎ፤ እንዴት በማኅበረሰቡ ዘንድ ሁነኛ ሰው መሆን እንደሚችሉ እንደሚማሩ ይነገራል። ሆኖም ግን በነዚህ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ምን እንደሚከናወን በግልጽ የሚታወቅ ነገር የለም። • ግርዛት የ21 ታዳጊ ወንዶችን ህይወት ቀጠፈ • የሴት ልጅ ግርዛት ምንድነው? የት እና ለምን ይፈጸማል? • የሴት ልጅ ግርዛት በከፍተኛ ደረጃ ቀነሰ 'ኡኩዋላኩዋ' የሚባለው ሂደት ከታዳጊነት ወደ ወጣትነት ለመሸጋገር አስፈላጊ መሆኑን እንደ ቋሳ እና ንዴቤሌ ያሉ ጎሳዎች ያምናሉ። ታዳጊዎች ከባህላዊ ትምህርት ቤቶቹ ሲወጡም ደማቅ አቀባበል ይደረግላቸዋል። በነዚህ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ሕይወታቸውን ያጡ፣ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው እንዲሁም በግርዛት ወቅት ጉዳት የገጠማቸው ታዳጊዎችም አሉ። አምና በመቶዎች የሚቆጠሩ ታዳጊዎች በብልታቸው ላይ በደረሰባቸው ጉዳት ሳቢያ እንዲሁም በቂ ውሀ ባለማግኘት ወደ ህክምና መስጫዎች ተወስደው ነበር። ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ግርዛት የሚካሄደው ታዳጊዎች ከትምህርት እረፍት በሚወስዱባቸው ወራት ነው። ከ15 እስከ 17 እድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ታዳጊዎች በባህላዊ የቀዶ ህክምና ባለሙያ አማካይነት ይገረዛሉ። ታዳጊዎቹም ስለ ግርዛቱ ምንም እንዳይናገሩ ተደርጎ ሂደቱ በሚስጥር ይከናወናል። እአአ ከ2012 ወዲህ ወደ 400 ታዳጊዎች ከግርዛት ጋር በተያያዘ ሞተዋል። አብዛኞቹ ታዳጊዎች የሚሞቱት በቂ ውሀ ባለማግኘት፣ ቁስላቸው ስለሚያመረቅዝና ተገቢውን ህክምና ስለማያገኙ ነው። አንዳንዶች ሂደቱን ኋላ ቀር እና አደገኛ ቢሉትም፤ የደቡብ አፍሪካ ሕገ መንግሥት የትኛወም ማኅበረሰብ ባህሉን እንዲያስቀጥል ይፈቅዳል። ባህላዊ ትምህርት ቤቶቹ በመንግሥት የሚታወቁ ሲሆኑ፤ አሁን ላይ የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ሀኪሞች ትምህርት ቤቶቹን እንዲጎበኙ እየከፈለ ነው። በመንግሥት ያልተመዘገቡ ትምህርት ቤቶችን መፈተሽ ግን አስቸጋሪ ነው። መንግሥት የሚደግፋቸው ጤና ጣቢያዎች የግርዛት አገልግሎት በመስጠት ሰዎች ከባህላዊ መንግድ ውጪ አማራጭ እንዲኖራቸው ለማድረግ ቢሞክሩም፤ የምዕራባውያን ባህል አራማጆች እንደሆኑ የሚያምኑ አሉ።
news-45743552
https://www.bbc.com/amharic/news-45743552
የላምፔዱሳው ኤርትራውያን እልቂት አምስተኛ ዓመት ተዘከረ
እአአ ጥቅምት 3፣ 2013 ላይ አብዛኞቹ ኤርትራውያን የሆኑ ስደተኞችን ጭና ከሊቢያ ወደ አውሮፓ ለመሻገር ስትጓዝ የነበረች መርከብ በላምፔዱሳ ደጃፍ ስትደርስ ሰጠመች። ከዚያን ዕለት ጀምሮ ኤርትራውያን ቀኑን በሀዘን ይዘክሩታል።
ከህሊና የማይጠፋው የላምፔዱሳ እልቂት ብዙ ስደተኞች ከአፍሪካ ወደ አውሮፓ ለመሻገር በሚያደርጉት ጉዞ ብዙ አደጋ ያጋጥማቸዋል፤ እንደዚህ ዓይነት አጋጣሚ የታየበት እና በዓለም መገናኛ ብዙሃን የተሰማ አደጋ ግን እምብዛም ነው። አምስት መቶ ስደተኞችን ጭና ከሊቢያ ባህር ዳርቻ የተነሳችው መርከብ ከ 25 ሰዓታት በላይ ያለ አንዳች ችግር ስትጓዝ ነበር። ላምፔዱሳ ደሴት ለመድረስ አንድ ኪሎሜትር ብቻ ሲቀራት ባልታወቀ ምክንያት ባጋጠማት ቃጠሎ የብዙ ኤርትራውያን ሕይወት ተቀጭቷል። በተለያዩ የዕድሜ ደረጃ የሚገኙ ሰዎች፤ ጨቅላ ህፃናትን የታቀፉ እናቶች፣ ዝምድና ያላቸው እና የአንድ አካባቢ ልጆች ጉዟቸውን በሰላም ለመጨረስ ለፈጣሪያቸው እየፀለዩ እና እየተሳሳቁ በሚጓዙበት ወቅት በቅፅበት ሁኔታዎች ተለወጡ። በዚያች መርከብ ውስጥ የነበረ እና በሕይወት የተረፈው አድሓኖም ሰመረ ስለዛች 'ጥቁር ቀን' ያስታውሳል። • ስለአዲሱ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ሥራ አስኪያጅ ጥቂት እንንገርዎ • የፍስሀ ተገኝ የቤተሰብ ፍለጋ ጉዞ ''የመርከቧ ካፒቴን 'ከዚህ በኋላ መሄድ ስለማንችል፤ እዚህ ሆነን እርዳታ መጠየቅ አለብን' በማለት ምልክት ለመስጠት አንሶላ አቃጠለ፤ እናም የመርከቧ ተጓዦች በድንጋጤ ለማምለጥ ሞከሩ፤ ከዚያም መርከቧ ሚዛኗን ስለሳተች አደጋው አጋጠመ'' በማለት ይናገራል። መርከቧ ገና ከሊቢያ ስትነሳ ጀምሮ ከልክ በላይ ብዙ ሰዎችን ጭና እንደነበር አድሓኖም ያስታውሳል። ከሌሊቱ 10 ሰዓት አደጋው ሲያጋጥም የነበረው ሁኔታ ምንም ግዜ ከዓዕምሮው የማይጠፋ መጥፎ ትውስታ እንደሆነ ይገልፃል። ''መርከቧ ወደ ቀኝ ከተገለበጠች በኋላ፤ አንድ ሰዓት ለሚሆን ጊዜ፤ ወደ መርከቧ ለመውጣት ስንሞክር መልሳ ትገለብጠናለች፤ ለአንድ ሰዓታት ያህል ተደጋጋሚ ሙከራ አድርገናል ግን አልሆነም፤ መርከቧ ሁላችንንም ይዛ ሰጠመች'' ይላል። 'እርዱን!' የሚለው ድምፅ እና ጩኸት በህይወት እስካለ ድረስ ለዘልዓለም ከዓዕምሮው የማይጠፋ እንደሆነ አድሓኖም ይናገራል። በአውሮፓ በር፡ በላምፔዱሳ ያጋጠመው እልቂት ሲታሰብ "እባካቹን ለቤተሰቦቼ ንገሩልኝ! መዋኘት አልችልም፤ ለቤተሰቦቼ ብቸኛ ነኝ የሚሉ ንግግሮች መቼም ቢሆን ከዓዕምሮዬ አይጠፋም፤ አስታውሳለሁ ሄለን የምትባል እናት 'ወይኔ ልጆቼ..........!' ስትል እስከአሁን ድረስ ድምፅዋ በጆሮዬ ያቃጭላል። 'ልጆቼ!.... ኧረ ልጆቼ!....' የሚሉ የሚረብሹ ድምፆችን መቼም ቢሆን አልረሳቸውም'' ይላል። በዚህ አደጋ ወንድሙን ያጣው የስዊድኑ ነዋሪ አቶ አዳል ንጉሰ በበኩሉ ገና በማለዳው ስለአደጋው የሰማው ከቢቢሲ ራድዮ ነበር። ከሁለት ቀን ቀደም ብሎ ሊቢያ የነበረው ወንድሙ ጉዞ ለመጀመር እንደተዘጋጁ ስለነገረው፤ በዚያችው መርከብ ሊኖር ይችላል በሚል እንደደነገጠ ይናገራል። ''ሊቢያ ደውየ ከአንድ ቀን በፊት ተጉዟል ባሉኝ ግዜ፤ ወንድሜ እዚያች መርከብ ላይ እንደሆነ ገባኝ'' በማለት ስለ ሁኔታው ያስረዳል። 'በሕይወት ያገናኙኝ ካልሆነም መርዶዬን ይንገሩኝ' በማለት የወንድሙን ፎቶ ይዞ ወደ ላምፔዱሳ አቀና። • በፖሊሶች መካከል በነበረ የተኩስ ልውውጥ ሕይወት ጠፋ • "ማንም ቢሆን ኢትዮጵያን ለብቻዬ ሰራኋት ሊል አይቻለውም" ጠ/ሚ ዐብይ ሳይውል ሳያድር ወደ ላምፔዱሳ ያቀናው አዳል ንጉሰ ከአደጋው የተረፉትን ሰዎች አግኝቶ "ይህን ሰው ታውቁታላችሁ?" በማለት የወንድሙን ፎቶ እያሳየ መወትወት ጀመረ። በሚጠይቃቸው ሰዎች ፊት ሀዘን ቢነበብም ጭንቅላታቸውን ወደ ግራ እና ቀኝ በመወዝወዝ አናውቀውም በማለት እንደነገሩት ያስታውሳል። በኋላ ላይ ግን ወደ ተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን (UNHCR) የወንድሙን ፎቶ ይዞ በመሄድ እንዲፈልጉለት ተስፋ ባለመቁረጥ ተማፀናቸው። ይሁን እንጂ በመጨረሻም "ወንድምህ በዚህች መርከብ ነበር፤ በህይወት መትረፍ ግን አልቻለም" የሚለውን መራር መርዶ ነገሩት፤ተስፋውም ጨለመ። • «የምታገለው ለማንም ብሔር የበላይነት አይደለም» አቶ በቀለ ገርባ • በእርጥብ ሳርና ቅጠል ጥቃትን ያስቆሙ አባቶች በወርሃ ጥቅምት 2013 ያጧቸውን ውዶቻቸውን ለማስታወስ ዘመድ አዝማድ ተሰባስበው ቀኑን ይዘክሩታል። አድሓኖምም እነዚያን 'እየመጣን ነው፤ ገብተናል' እያሉ የተለዩትን፣ በሰሀራ በርሃ አብረውት የተጓዙትን፣ በሊቢያ የችግሩ ተካፋዮች የነበሩትን፣ ከሁሉም በላይ ደግሞ እነዚያ በሞት አፋፍ ላይ ሆነው 'እኔ ለቤተሰቦቼ አንድ ነኝ. . .፣ . . . ለቤተሰቦቼ ንገሩልኝ፣ . . . እባካችሁ እየሞትኩኝ ነው፣ ወይኔ ልጆቼ!....' በማለት ሲጮኹ የነበሩትንና በአጭር የቀሩትን መንገደኞች ለማስታወስ ወደ ላምፔዱሳ ተጉዟል። "ከከተማዋ ከንቲባ ጋር በመገናኘት ከአሁን በፊት የተከልናቸውን 368 ችግኞች ኮትኩተናል፤ ከዚህ በተጨማሪ ችግኞቹ በሚገኙበት ቦታ ሐውልት እንድንሰራ ፈቃድ ጠይቀናል'' በማለት የአውሮፓ በር ተብሎ በሚታወቀው አካባቢ ፀሎት እንደሚያደርሱ እና አደጋው ወዳጋጠመበት ቦታ በአምስት መርከቦች በመሄድ የአበባ ጉንጉን እንደሚያስቀምጡ ነገሮናል።
42494639
https://www.bbc.com/amharic/42494639
የማህበራዊ ድረ-ገፅ ዘመቻዎች
የተለያዩ ጉዳዮች ወትዋችና አስታዋሽ ይፈልጋሉ። ለዚህም ነው የማህበራዊ ሚዲያ አራማጆች (አክቲቪስቶች) ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮችን አንስተው ትኩረት እንዲያገኙ ጥረት የሚያደርጉት።
ለዚህ ደግሞ መነሻ የሆነን ሃሳብ ሰሞኑን በማህበራዊ ድረ-ገፆች የህሊና እና የፖለቲካ እስረኞችን እናስታውስ በሚል የተካሄደው ዘመቻ ነው። የአራማጅነት የተለያዩ መልኮች እአአ 2011 በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መምህራንና ተማሪዎች የተቋቋመው የ'የለው ሙቭመንት' መሥራች ከሆኑት መካከል ወ/ት ሕሊና ብርሃኑ አንዷ ነች። ወ/ት ህሊና የሥርዓተ-ፆታ እና ሕግ መምህርት ስትሆን የእንቅስቃሴውን ጅማሬ እንዲህ ታስታውሳለች። "በኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ አስተናጋጅ የነበረችው አበራሽ ላይ የደረሰው ጥቃት እና እሱን ተከትሎ በተለየዩ መገናኛ ብዙሃን የተነሳው ውይይት ለእንቅስቃሴው መመስረት ሰበብ ሆኖናል።" እንዲህ አይነት ፆታን መሰረት ያደረገ ጥቃት ሲደርስ ሁሉም 'የአንድ ሰሞን ጀግና' ይሆናል የምትለው ወ/ት ሕሊና፤ ከዚያ በኋላ ሁሉም ወደ የዕለት ተግባሩ ሲገባ የሴቶቹ ጥቃት ይረሳል ስትል ትተቻለች። "ስለዚህ እኛ ቀጣይነት ያለው ውይይት እና ግንዛቤ ለመፍጠር በማሰብ መስራት ጀምረናል" ባይ ነች። 'ሴታዊት' በተሰኘው ሌላኛው እንቅስቃሴ ውስጥ የኮሙኑኬሽን አስተባባሪ የሆነችው ወ/ት ፍራኦል በላይ ደግሞ ሴታዊት በማህበረሰቡ ውስጥ አይነኬ የሚባሉ ነገሮች ላይ ውይይት ለመፍጠር እየሰራ ነው ስትል ለቢቢሲ ትናገራለች። "ውይይቱ ግን ቀጣይነት አንዲኖረው ክብረ በዓላትን ብቻ እየተከተልን ሳይሆን እኛ ራሳችን እያቀድን የተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻዎችን እናደርጋለን።" የዞን ዘጠኝ ጦማሪ የሆነው በፍቃዱ ኃይሉ በተከታታይ ያደረጓቸውን የማህበራዊ ድረ-ገፅ ዘመቻዎችን ያስታውሳል። "በዋናነት በአራት ጉዳዮች ላይ ተከታታይ ዘመቻዎችን አድርገናል። እነዚህም ሕገ-መንግስቱ ይከበር፣ ሀሳብን የመግለፅ ነፃነት ለሁሉም ይሁን፣ የመሰብሰብ እና የመደራጀት መብት ይከበር፣ ኢትዮጵያዊ ሕልም አብረን እናልም የሚሉ ነበሩ።'' የፌስ ቡክ ዘመቻዎችን ሲያካሂዱ ቡድን አቋቁመው ከቀን መረጣ እስከ ምስል ዝግጅት እንዲሁም ዘመቻውን የሚያግዙ የተለያዩ ጽሁፎች እና መሪ ቃሎችን በደንብ አብላልተው እንደሚዘጋጁ ይናገራል። ከዚህ በተለየ ደግሞ ሌሎች የማህበራዊ፣ ፖለቲካዊ እና አካባቢያዊ ለውጥን ለማምጣት ወይንም ንቃት ለመፍጠር የሚሰሩ አሉ። ከእነዚህ ዓይነት የማህበራዊ ድረ-ገፅ ዘመቻ አራማጆች መካከል በሰፊው የሚታወቁት 'ድምፃችን ይሰማ' እና አሁን ደግሞ 'የህሊና እስረኞችን እናስብ' በሚል እየተካሄደ ያለው ዘመቻ ነው። በዚህ ሳምንት የተጀመረው 'የህሊና እስረኞችን እናስብ' የፌስ ቡክ እንቅስቃሴን ሃሳብ ያመነጩት አቶ ጌታቸው ሽፈራው ዓላማው ''የተዘነጉ የፖለቲካ እና የሕሊና እስረኞችን ለአንድ ቀን ማስታወስ እና ፍትሕ እንዲሰጣቸው መወትወት ነው'' ይላሉ። ትኩረት የተነፈጋቸው ጉዳዮች በአገራችን በጣም አስፈላጊ ሆነው፤ ነገር ግን የተዘነጉ በርካታ ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች እንዳሉ እሙን ነው። ለአቶ ጌታቸው ደግሞ የህሊና እና የፖለቲካ እስረኞች ጉዳይ የተዘነጋ ነው። ''እስረኞቹ የማንነት ወይንም የሀይማኖት ጥያቄ በማንሳታቸው ብቻ በአንድ ጠባብ ክፍል ውስጥ በርካታ በደል ይደርስባቸዋል'' ይላሉ አቶ ጌታቸው። ''ይህ ደግሞ ባለፉት ሁለት ዓመታት በኦሮሚያ እና በአማራ ክልል በነበሩት ሕዝባዊ ተቃውሞዎች ተባብሷል። እነዚህ ታሳሪዎች የተለያየ በደል የደረሰባቸው ሲሆን ፍርድ ቤት ቀርበው ጉዳያቸውን እስኪያስረዱ ድረስ ማንም አይሰማቸውም'' ሲሉም ይናገራሉ። በጠባብ ክፍሎች የደረሰባቸውን በደል ህዝብ በሰፊው እንዲሰማላቸው፤ በዳዮች ተለይተው ቢቻል ዛሬ ባይሆን ነገ ለፍርድ እንዲቀርቡ መረጃው እንዲሰራጭ ማድረግ አልተቻለም ሲሉ አቶ ጌታቸው ይጨምራሉ። ስለዚህ በዚህ ሳምንት የተካሄደው ዘመቻ ስለ እስረኞች የሚያውቅ ሁሉ ያለውን መረጃ እንዲያካፍል፣ በደል ስለ ተፈፀመባቸውንና በደል ስለፈፀሙ ሰዎች መረጃ እንዲለዋወጥ፣ በደል የፈፀሙ እንዲጠየቁ፣ በደል የደረሰባቸውም የተቻለው ሁሉ እንዲደረግላቸው ለመመካከር አንደሆነ ገልፀዋል። ማህበራዊ ሚዲያን ለለውጥ በሥርዓተ-ፆታ ላይም ሆነ እንዲህ የእስረኞች መብት እንዲከበር የሚወተውቱ ወገኖች በጋራ የሚስማሙበት ነገር ቢኖር ማህበራዊ ሚዲያ ምንም እንኳን ጓዘ ብዙ ቢሆንም ሃሳባቸውን ወደ ብዙሃኑ ለማድረስ እንደ ድልድይ ሆኖ አገልግሏቸዋል። ''በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የያዝነው ሃሳብ መወያያ እንዲሆን እና ግንዛቤ እንዲፈጠር አጥብቀን እንሰራለን'' የምትለው ሕሊና የሚያነሷቸው ሃሳቦች ተገቢውን ተፅእኖ እንዲፈጥሩ በጥናት የተደገፈ ዘመቻዎችን እንደሚያካሂዱ ይናገራሉ። ፍራኦልም በበኩሏ ''ዋነኛ አላማችን በፌስ ቡክ ማህበረሰብ መካከል ውይይትን መፍጠር ነው። እድለኛ ከሆንን ትልልቅ የመገናኛ ብዙሃን ሃሳቡን ወስደው ለሰፊው ህዝብ ያደርሱታልም'' ብላለች። በማህበራዊ ድረ ገፅ ላይ የሚያነሱት ጉዳዮችን የተለያዩ ግለሰቦች ወደየራሳቸው እየወሰዱ ለሌሎች ያጋራሉ፣ ታሪካቸውን ያካፍላሉ እንዲሁም የፌስቡክ፣ ቲውተር እና ኢንስታግራም ገፅ ፎቶዎቻቸውን በዘመቻው መለያ ወይንም መሪ ቃል ይቀይራሉ። ይህ ደግሞ ውይይት የመፍጠር አላማቸውን እንደሚያሳካ ታምናለች። በርግጥ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሚነሱ ዘመቻዎችን የሚደግፍ እና የሚከተል ብቻ ሳይሆን የሚነቅፍም አለ የሚሉት ሕሊና እና ፍራኦል ከደጋፊዎቻችን ብቻ ሳይሆን ከነቃፊዎቻችንም እንማራለን ብለዋል። በፍቃዱ በበኩሉ ''ያካሄድናቸው ዘመቻዎች ውጤታማ ነበሩ ማለት እችላለሁ" ይላል። በእኛ ዘመቻዎች በርካቶች ተነቃቅተዋል። ተነቃቅተውም ያጋራናቸውን ነገሮች ተቀባብለዋቸዋል።'' በተለይ በሕገ-መንግሥት አንቀፆች ላይ ግንዛቤ ለመፍጠር እንደቻሉና ከምንም በላይ ለመንግሥት አካል ጋር ሃሳባቸው ደርሷል ብሎ ያምናሉ። አቶ ጌታቸውም ከዚህ የማህበራዊ ድረ-ገፅ ዘመቻ የበርካቶችን ተሳትፎ እና ውይይት እንደሚጠብቁ ይናገራሉ። ተግዳሮቶቹ ምን ምን ናቸው "የበይነ-መረብ (ኢንተርኔት) ተደራሽነት እና ፍጥነቱ አስቸጋሪ ቢሆንም በአሁኑ ሰዓት ጥሩ የተሳታፊዎች ምላሽ" የሚሉት አቶ ጌታቸው ችግሩን ለማህበራዊ ሚዲያዎች ዘመቻ እንደ ዋነኛ ተግዳሮት ያስቀምጡታል። አቶ በፍቃዱ በበኩላቸው በቂ ዝግጅት አለማድረግ፣ የማይጋብዙ መሪ ቃሎችን ማቅረብ፣ ሞገደኛ የሆኑ ቃላትን መጠቀም፣ ዘመቻው የሚካሄድባቸው ቀናት በሌላ አጀንዳ አለመያዛቸውን አለማረጋገጥ ተግዳሮቶች ናቸው ይላሉ። የሚነሱ የዘመቻ ሃሳቦችን በበጎ የማይመለከቱ አካላትም ከተግዳሮቶቹ መካከል ይጠቅሳሉ። ቢሆንም ግን የማህበራዊ ድረ-ገፅ አራማጅነት ሁሉም ሃሳቦች ተነስተው ውይይት በማካሄድ ግንዛቤ ተፈጥሮ ችላ የተባሉ ጉዳዮች ትኩረት እንዲያገኙ ለማድረግ እንዳስቻለ ያምናሉ።
52423333
https://www.bbc.com/amharic/52423333
የኢትዮጵያ አየር መንገድ 'የቻይና በረራዬን መቀጠሌ ትክክል ነበር' አለ
በአፍሪካ ትልቁ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የኮሮናቫይረስ ቻይና ውስጥ ከፍተኛ ደረጃ ላይ በደረሰበት ጊዜ ድርጅታቸው ወደዚያ ሲያደርግ የነበረውን በረራ አለማቋረጡ ትክክል እንደነበር ተናገሩ።
ዋና ሥራ አስፈጻሚው ተወልደ ገብረማሪያም ለቢቢሲ እንደተናገሩት በንግድ ግንኙነት ምክንያት ከቻይና ጋር ጥብቅ ቁርኝት ላላቸው የአፍሪካ አገራት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወሳኝ አገልግሎትን ሰጥቷል። ዋና ሥራ አስፈጻሚው አየር መንገዳቸው በቀጥታ በረራና በኮቪድ-19 ስርጭት መካከል ግንኙነት አለው ብሎ እንደማያምንም ተናግረዋል። ጨምረውም በጣም ጠበቅ ያለ የጉዞ ቁጥጥርና እገዳዎችን ባወጡ አገራት ውስጥ ሳይቀር ወረርሽኙ ጉዳት እያደረሰ መሆኑን አመልክተዋል። ነገር ግን በረራዎችን በማገድ በኩል በምጣኔ ሃብታዊ ሁኔታዎችና በሕዝብ ጤና መካከል ሚዛን መጠበቅ ከግምት ውስጥ መግባት እንዳለበት ገልጸዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቻይና ውስጥ በሽታው ተስፋፋፍቶ በነበረበት ወቅት ቤይጂንግና ሻግሃይን ወደመሳሰሉ ከተሞች በረራ ያደርጉ ከነበሩ የተወሰኑ አየር መንገዶች መካከል አንዱ ነበር። በሽታው በመላው ዓለም ከተሰራጨ በኋላ ክፉኛ ተጽዕኖውን ካሳረፈባቸው ዘርፎች መካከል የአየር ትራንስፖርት አንዱ ሲሆን የኢትዮጵያ አየር መንገድም ከፍ ያለ ኪሳራ እንዳጋጠመው ተነግሯል። አየር መንገዱ በአሁኑ ጊዜ ካለው አቅም በ10 በመቶ ብቻ እየሰራ ሲሆን ባለፉት ጥቂት ወራት ውስጥ ከ500 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ማጣቱን ሮይተርስ በቅርቡ ዘግቦ ነበር። አቶ ተወልደ የአየር ትራንስፖርት ዘርፉ በወረርሽኙ ምክንያት የገጠመውን ፈተና በተመለከተ ሲናገሩ፤ ድርጅታቸውን በዚህ የቀውስ ወቅት ይዞ መራመድ ፈታኝ ቢሆንም ጭነት በረራዎችን በመጨመር በመንገደኞች ጉዞ ያጣውን ገቢ ለማካካስ እየሞከረ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ በከፍተኛ ደረጃ ተስፋፍቶበት በነበረበት ወቅት ጥቂት ያማይባሉ አየር መንገዶች ወደ ቻይና ያደርጓቸው የነበሩ በረራዎችን አቁመው ነበር። በዚህም ሳቢያ በርካቶች ወረርሽኙን በመፍራት የኢትዮጵያ አየር መንገድም ወደ ቻይና የሚያደርጋቸውን በረራዎች እንዲሰርዝ ግፊት ሲያደርጉበት ቆይተዋል።
news-50923784
https://www.bbc.com/amharic/news-50923784
ስዊዲን፡ ስለ ሀብት ማውራት ነውር የሆነባት አገር
በስዊድኗ መዲና ስቶክሆልም ባለጸጎች በሚኖሩበት ኦስተርማልም፤ በግል መርከባቸው የሚንሸራሸሩ ሰዎችን ማየት ብዙ አያስገርምም። ከዚህ አካባቢ ብዙም የማይርቀው ስትራንድቫገን በቅንጡ መኖሪያ ህንጻዎች የተሞላ ነው።
እጅግ ውድ የኮስሞቲክስ ሱቆች፣ ጥቂቶች ብቻ የሚስተናገዱባቸው ሬስቶራንቶች ያሉበት አካባቢ ቢሆንም እንኳን፤ ስለ ሀብት ንብረቱ በዝርዝር ለማውራት ፍቃደኛ የሆነ ሰው ማግኘት ግን ቀላል አይደለም። የ30 ዓመቱ ሮበርት ኢንገማርሰን፤ ገንዘቡን ኢንቨስት ማድረግ እንደሚያስደስተው ገልጾ፤ "ምን ያህል ገንዘብ እንደማገኝ የምናገርበት ምክንያት ስለማይታየኝ አላወራም" ይላል። የ24 ዓመቱ ቪክተር ሄስ፤ ስዊድን ውስጥ ታዋቂ በሆነ ድርጅት ውስጥ ሊቀጠር መሆኑን ቢናገርም ደሞዙን ሲጠየቅ፤ "እሱማ ሚስጥር ነው" ሲል መልስ ሰጥቷል። • በዓለማችን ታሪክ ሀብታሙን ሰው ያውቁታል? ከጎርጎሮሳውያኑ 1990 ወዲህ በስዊድናዊያን ሀብታሞችና ድሆች መካከል ያለው ልዩነት እየሰፋ መጥቷል። ከሕዝቡ 20 በመቶው ከተቀረው ማኅበረሰብ አራት እጥፍ ገቢ ያገኛል። በብዙ አገራት መለኪያ ከፍተኛ ገቢ ማግኘት ስኬታማ ከሚያስብሉ መስፈርቶች አንዱ ነው። በስዊድናውያን ዘንድ ግን ስለ ሀብትና ንብረት ማውራት ነውር ነው። ቢቢሲ ይህንን ዘገባ ሲያጠናቅር ከወጣት ባለሀብቶች ጋር ቃለ ምልልስ ለማድረግ በተደጋጋሚ ቢሞክርም ውጤታማ አልሆነም። ባለጸጎቹ ስለ ቄንጠኛ ቤታቸው፣ ውድ መኪናቸው ኢ-መደበኛ በሆነ ንግግር መካከል ቢያወሩም፤ አደባባይ ወጥተው ሀብቴን እወቁልኝ ለማለት አይፈቅዱም። "ስለሀብቴ ማውራት ጉራ መንዛት እንደሆነ ይሰማኛል፤ ያን ማድረግ ደግሞ ምቾት አይሰጠኝም" ሲል አንድ ግለሰብ ለቢቢሲ ገልጿል። ስቶክሆልም ውስጥ ስለሀብት ማውራት ለምን አስነዋሪ ሆነ? ስቶክሆልም ውስጥ ከአስር ዓመታት በላይ የኖረችው ሎላ አኪንማዴ አከርስቶርም፤ ስለ ስዊድን ባህል መጽሐፍ አሳትማለች። ስዊድን ውስጥ ስለ ሀብት ማውራት "ምቾት አይሰጥም" ትላለች። ይህን ያህል ገንዘብ አለኝ ብሎ መኩራራት ወይም ስለ ወርሃዊ ደመወዝ ማውራትም ነውር እንደሆነ፤ "ስዊድናዊያን ስለ ገንዘብ ከማውራት ይልቅ ስለ ወሲብ ማውራት ይቀላቸዋል" ስትል ታስረዳለች። • የእኩልነት ዓለም ብለው የሚገልጿት የአውራምባውያኑ አምባ ለዓመታት አሜሪካ የኖረችው የ28 ዓመቷ ስዊድናዊት ጋዜጠኛ ስቲና ዳልግረን ተመሳሳይ አስተያየት ትሰነዝራለች። "አሜሪካ ውስጥ ይህን ያህል ገንዘብ አገኛለሁ ብትይ፤ ሰው ሁሉ ያሞግስሻል፤ 'ጎበዝ! በርቺ!' ይልሻል። ስዊድን ውስጥ የደመወዝሽን መጠን ብትናገሪ ግን ሰው 'ጤና የላትም እንዴ?' ብሎ በመገረም ያይሻል። ስዊድን ውስጥ ስለ ደመወዝ፣ ስለ ገንዘብ አይጠየቅም።" ስዊድን ውስጥ ስለ ገንዘብ ማውራት አስነዋሪ ባህል መሆኑን የሚገልጸው ቃል 'ጃንተላግን' ይባላል። ይህ ባህል አንድ ሰው ከማንም በላይ ነኝ ብሎ ማሰብ እንደሌለበት ያስገነዝባል። ጸሐፊዋ ሎላ እንደምትለው ይህ ያልተጻፈ ማኅበራዊ ሕግ፤ አንድ ሰው 'እዩኝ እዩኝ' እንዳይል፣ በህብረተሰቡ ዘንድ በተወሰነ ደረጃም ቢሆን እኩልነት እንዲሰፍን ያደርጋል። • ቢሊየነሯ የሀብታቸውን ግማሽ ለበጎ አድራጎት ለመስጠት ወሰኑ 'ጃንተላግን' የሚለው ቃል የተወረሰው በ1933 አክሰል ሳንደሞስ በተባለ ደራሲ ከተጻፈ ልብ ወለድ ነው። በመጽሐፉ ውስጥ ከሕግ ዝንፍ ማለት የማይቻልባት 'ጃንቴ' የምትባል ከተማ አለች። ባህሉ ከመጽሐፉ የተወሰደ ነው ቢባልም፤ ዶ/ር ስቴፈን ትሮተር የተባሉ ምሁር፤ ባህሉ ለዘመናት በኖርዲክ አገራት በተለይም በገጠራማ አካባቢዎች እንደነበረ ይገልጻሉ። "ማኅበረሰቡን መቆጣጠር የሚቻልበት መንገድ ነው፤ ስለ ሀብት አለማውራት ብቻ ሳይሆን የማያውቁትን ነገረ አለመዘባረቅንም ያካትታል።" ሎላ በበኩሏ፤ ስዊድን 'መደብ አልባ አገር ናት' የሚል ገጽታ ለመገንባት ቢሞከርም፤ ሀብታም ሰዎች ጓደኛ የሚያደርጉት ባለጸጎችን ነው። ሲሰባሰቡም ስላላቸው ገንዘብ ያለገደብ ያወራሉ። ስለዚህም የ'ጃንተላግን' ሕግ አንጻራዊ ነው ትላለች። ወጣት ስዊድናዊያን እና 'ጃንተላግን' ወጣት ስዊድናዊያን 'ጃንተላግን'ን መተቸት ጀምረዋል። ስለ ሀብትና ውጤታማነት በግልጽ መወራት እንዳለበትም ያምናሉ። የ22 ዓመቷ ጦማሪ ኒኮል ፋልሲያኒ የብዙ ወጣቶችን አመለካከት ትወክላለች። ሀብታሟ ጦማሪ ለሠርጓ የ20 ሺህ ዶላር ሻምፓኝ እንደተጠጣ የተናገረችው ያለምንም መሸማቀቅ ነበር። • ከግብር የሚሰወረው የዓለም ሃብት የት ነው? "ይህ ሀብትን የመደበቅ ባህል ቢጠፋ ደስ ይለኛል፤ ሁሉም ሰው እኩል ነው የሚለው አስተሳሰብ መልካም ቢሆንም፤ ጥሮ ግሮ ሀብት ያካበተ ሰው መኩራራት አለበት።" በኖርዌይ ዩኒቨርስቲ የሚያስተምሩት ኮርንሊዩስ ካፕሊን፤ የአመለካከት ለውጥ ለመምጣቱ ምክንያት የሆነው የማኅበራዊ ሚዲያ ገናናነት ነው ይላሉ። ወጣቶች ከእድሜ እኩዮቻቸው በተለየ ነጥረው ለመውጣት ስለእራሳቸው ጥሩ የሆነን ነገር ባጠቃላይ ያወራሉ። እንዲያውም 'ጃንተላግን' እንደ ስድብ እየተቆጠረም መጥቷል። ሎላ እንደምትለው፤ ወጣቶች ስኬታቸውን በአደባባይ ለማውራት አይፈሩም። ከተለያዩ አገሮች ወደ ስዊድን የሚያቀኑ ስደተኞች ቁጥር መጨመርም 'ጃንተላግን' እየጠፋ እንዲሄድ ምክንያት ሆኗል። ስለዚህም፤ ሎላ ስለ ገንዘብ ማውራት አስነዋሪ መሆኑ እየተሸረሸረ እንደሚሄድም ታምናለች። በተቃራኒው አንዳንድ ስደተኞች 'ጃንተላግን'ን መውረሳቸውን ይናገራሉ። ከሦስት ዓመታት በፊት ስቶክሆልም መኖር የጀመረችው የ35 ዓመቷ የቺሊ ተወላጅ ናታሊያ ኢርቢራ አንዷ ናት። "ቺሊ ውስጥ ጎበዝ ተማሪ ቆንጆ፣ ባለ መኪናና ባለቤት መሆንም ያኩራራል። እዚህ አገር ግን ሰዎች ስለስኬታቸው አይወሩም፤ በእኔ እምነት ራስን አለመካብ የሚበረታታ ባህሪ ነው።"
news-45623516
https://www.bbc.com/amharic/news-45623516
የናይጄሪያ የባህር ላይ ወንበዴዎች የስዊዘርላንድ መርከበኞችን አገቱ
በእቃ ጫኝ መርከብ ውስጥ ይሰሩ የነበሩ 12 የስዊዘርላንድ የመርከብ ድርጅት ሰራተኞች በናይጄሪያ የውሃ ክልል ውስጥ በባህር ወንበዴዎች ታግተዋል።
ማሶኢል የተባለው መርከብ ድርጅት እንዳስታወቀው ''ኤም ቪ ግላረስ'' የተባለው እቃ ጫኝ መርከብ ስንዴ ጭኖ ''ከሌጎስ'' ወደብ በመነሳት ወደ ''ሃርኮርት'' በመጓዝ ላይ እያለ ነበር ቅዳሜ ዕለት በወንበዴዎቹ ጥቃት የደረሰበት። የወንበዴው ቡድን አባላት ረጃጅም መሰላሎችን በመጠቀም ወደ መርከቡ እንደገቡና አብዛኛውን የመገናኛ መስመሮችን ከጥቅም ውጪ እንዳደረጉ ድርጅቱ 'ለኤኤፍፒ ገልጿል። • ለ10 ሰዓታት ባህር ውስጥ የቆየችው ሴት • የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችና ወላጆቻቸው ስጋት • ታላቁ ዲፕሎማት ኮፊ አናን ሲታወሱ 45 ደቂቃ በፈጀው የወንበዴዎቹ ጥቃት ከ19 የመርከቡ ሰራተኞች መካከልም 12ቱን አግተዋል። ከታገቱት መርከበኞች መካከል ሰባቱ ከፊሊፒንስ ሲሆኑ የተቀሩት ደግሞ ከስሎቬኒያ፣ ዩክሬይን፣ ሮማኒያ፣ ክሮሺያ እና ቦስኒያ መሆናቸውን ሮይተርስ የናይጄሪያ የባህር ጉዳዮች መስሪያ ቤትን እንደ ምንጭ ጠቅሶ ዘግቧል። የታጋቾቹ ቤተሰቦች ስለሁኔታው እንደተነገራቸውና ጉዳዩንም በቅርበት እየተከታተሉት እንደሆነ የመርከብ ድርጅቱ ቃል አቀባይ ገልጸዋል። በጉዳዩ የዓመታት ልምድ ያካበቱ የተባሉ ባለሙያዎች ታጋቾቹን ለማስለቀቅ እየጣሩ መሆናቸውንም ቃል አቀባዩ ጨምረው ተናግረዋል። የስዊዘርላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ከታጋቾቹ መካከል አንድም የስዊዘርላንድ ዜግነት ያለው ሰው አለመኖሩን ተናግዋል። በናይጄሪያ የውጪ ዜግነት ያላቸውን ሰዎች እንዲሁም ታዋቂ ናይጄሪያውንን አግቶ ማስለቀቂኣ ገንዘብ መጠየቅ የተለመደ ነው።
51166093
https://www.bbc.com/amharic/51166093
ኢትዮጵያን ጨምሮ ባፈለው ዓመት ኢንተርኔት በመዝጋት የከሰሩ ሃገራት
ባፈለው የፈረንጆቹ ዓመት ኢንተርኔት በመዝጋት የከሰሩ ሃገራትን ዝርዝር ይፋ ያደረገ አንድ ጥናት "ዓለም በዚህ ምክንያት 8 ቢሊዮን ዶላር ከስራለች" ብሏል።
ባለፈው የፈረንጆቹ ዓመት ኢንተርኔትን በአንድም ሆነ በሌላ ምክንያት የዘጉ ሃገራት ቁጥር ከምን ጊዜውም የላቀ ነው ሲል ኔትብሎክ የተባለው አጥኚ ድርጅት ይፋ አድርጓል። ጥናቱ ላይ እንደተጠቀሰው በተለያዩ ሃገራት 122 ጊዜ ኢንተርኔት የተቋረጠ ሲሆን በጠቅላላ 22 ሺህ ሰዓታትን እነዚህ ሃገራት ያለ ኢንተርኔት አሳልፈዋል ብሏል። ባለፉት 12 ዓመታት ጥናቱ ውስጥ የተካቱት መንግሥታት በሃገር ደረጃ ወይም በክልል ደረጃ ኢንተርኔትን ሆን ብለው አጥፍተዋል፤ ዋነኛው ዓለማው ደግሞ ተጠቃሚውን ፌስቡክ ከመሳሰሉ ከማህበራዊ ድር አምባዎች ለማገድ ነው። ድርጅቱ የኢንተርኔት አዘጋግ ሂደቱን በሁለት ይከፍለዋል። አንደኛው ሙሉ በሙሉ የኢንተርኔቱን ባልቦላ መቁረጥ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ማሕበራዊ ድር-አምባዎችን ከጥቅም ውጭ ማድረግ ነው። ፌስቡክ፣ ዋትስአፕ፣ ትዊተር፣ ዩቲዩብ እና መሰል ድር አምባዎች ቢታገዱም ተጠቃሚዎች 'ቪፒኤን' በመጠቀም ሊያገኟቸው ይችላሉ። ጥናቱ ይፋ ባደረገው መሠረት አብዛኛዎች የኢንተርኔት መቋረጦች ከተቃውሞ እና አለመረጋጋት እንዲሁም ምርጫ ጋር የተያያዙ ናቸው። የባልቦላው መዘጋት በተለይ 'በደሃ' ሃገራት በልማዳዊው ገበያ ላይ ያለው ተፅዕኖ ከፍተኛ መሆኑን ጥናቱ ደርሶበታል። ይህ ማለት ጥፋቱ ጥናቱ ላይ ከተቀመጠው በላይ ሊሆንም ይችላል ማለት ነው። የኢንተርኔት መዘጋቱ የሰው ልጅ የመናገር ነፃነትን የሚገፍ ነው የሚለው ድርጅቱ ኢንተርኔት መዝጋቱ ለበለጠ አመፅ እንደጋበዘ ታዝቤያለሁ ይላል። በዚህ ረገድ መካከለኛው ምስራቅና ሰሜን አፍሪቃ ኢንተርኔት በመዝጋት የሚስተካከላቸው አልተገኝም። ከሰሃራ በታች ያሉ ሃገራት ደግሞ ተከታዩን ደረጃ ይእዛሉ። እስያ በሶስተኛ ደረጃ የምትገኝ ሲሆን የደቡብ አሜሪካ ሃገራት በአራተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። ድርጅቱ ኢንተርኔት የዘጉ ሃገራትን ዝርዝር፤ ያጡትን ገንዘብ [በዶላር] እንዲሁም የኢንተርኔት ተጠቃሚዎችን ቁጥር ከዚህ እንደሚከተለው አስቀምጧል። ዚምባብዌ፣ ሞሪታኒያ፣ ፓኪስታን፣ ግብፅ፣ ካዛኪስታን፣ ቤኒን፣ ጋቦን፣ ኤርትራ እና ላይቤሪያ ሌሎች በዝርዝሩ ውስጥ የተካተቱ ሃገራት ናቸው። ከማሕበራዊ ድር-አምባ አንፃር ሲታይ ደግሞ ዋትስአፕ የተሰኘው መልዕክት መላላከያ ብዙ ሃገራት የዘጉት ሆኖ ተመዝግቧል። ፌስቡክ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ፤ ኢንስታግራም ትዊተር እና ዩቲዩብ ተከታትለው ይመጣሉ። ኢራቅ፣ ሱዳን፣ ሕንድ እና ቬንዝዌላ ኢንተርኔት በመዝጋታቸው ምክንያት 1 ቢሊዮንና ከዚያ በላይ ያጡ ሃገራት ሆነው ተመዝግበዋል። ይህም ምጣኔ ሃብታቸው ላይ ከፍተኛ ድቀት እንዳደረሰ የድርጀቱ መረጀ ያመለክታል። አራቱም ሃገራት ሕዝባዊ ተቃውሞን ለማብረድ ሲሉ ነው የኢንተርኔታቸውን ባልቦላ የቆረጡት። ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ ባለፈው የፈረንጆቹ ዓመት ኢንተርኔቷን ለ274 ሰዓታት ዘግታለች። በተለይ ወርሃ ሰኔ ላይ [አማራ ክልል እና አዲስ አበባ ላይ ከተከሰተው የባለሥልጣናት ግድያ ጋር በተያያዘ] ኢንተርኔት በሃገሪቱ ለተወሰኑ ቀናት ሙሉ በሙሉ ተቋርጦ ነበር። ከዚያ ባለፈ ሃገር አቀፍ የተማሪዎች ፈተና በሚኖርበት ወቅት ኢንተርኔት በበርካታ የሃገሪቱ ክፍሎች ተቋርጧል። ነገር ግን ኢንተርኔቱን የሚያስተዳድረው ኢትዮ ቴሌኮምም ሆነ መንገሥት ይፋዊ መግለጫ አልሰጡም። ከሃገር አቀፍ የኢንተርኔት መቋረጦች ባለፈ በተመረጡ አካባቢዎችም ተጠቃሚዎች ለቀናት ከኢንተርኔት ጋር ተቆራርጠው ቆይተዋል። ይህም ኢትዮጵያን ባላፈው ዓመት ብቻ 2 ቢሊዮን ብር ገደማ አሳጥቷታል።
news-55329587
https://www.bbc.com/amharic/news-55329587
ኮሮናቫይረስ፡ በኬንያ የመጀመሪያው ዙር ክትባት በጥር ወር ይደርሳል ተባለ
ኬንያ የመጀመሪያው ዙር የኮሮናቫይረስ መከላከያ ክትባት በሚቀጥለው፣ ጥር ወር እንደሚደርሳት አስታውቃለች።
የጤና ሚኒስትሩ ሙታይ ካግዌም ይህንኑ ማሳወቃውን የኔሽን አፍሪካ ጋዜጣ ዘግቧል። ሚኒስትሩ የኦክስፎርዱ አስትራዜኔካ የኮሮናቫይረስ መከላከያ ክትባት ለህዝቡ እናቀርባለን ብለዋል። አስትራዜኑካ የሚባለው ክትባት ከሞደርናና ፋይዘር ከተሰኙት የኮሮናቫይረስ መከላከያ ክትባቶች ጋር ሲነፃፀር ዋጋው ረከስ እንደሚልም ተናግረዋል። ነገር ግን የኦክስፎርዱ ክትባት በየትኛውም አገር እስካሁን እውቅና አላገኘም። ኬንያ በግሎባል ቫክሲን አሊያንስ ኢንሺዬትቭ በተባለው ድርጅት አማካኝነት 24 ሚሊዮን መጠን ብልቃጥ ክትባቶችን ያዘዘችው ባለፈው ሳምንት ነው። ይህም መጠን ከአገሪቷ ህዝብ መካከል 20 በመቶውን ይሸፍናል ተብሏል። የኬንያ መንግሥት 10 ቢሊዮን የኬንያ ሽልንግ (89 ሚሊየን ዶላር) ገንዘብ ለክትባቱ እንዳወጣም ተገልጿል። ክትባቱ ሲደርስ ቅድሚያ የሚሰጣቸው የጤና ባለሙያ ሰራተኞች፣ ፖሊሶች፣ አረጋውያንና መምህራን ይሆናሉ። ከዚህም በተጨማሪ ህዝብ በተጨናነቀበት አካባቢ የሚኖሩና እንዲሁም ከአንድ ወይም ሁለት በላይ ተደራራቢ ህመም ያለባቸውም እንዲሁ የመጀመሪያው ዙር ክትባት ተጠቃሚም ይሆናሉ ተብሏል። ኢትዮጵያም ኮቫክስ ከተሰኘው ዓለም አቀፍ የክትባት ድጋፍ ሰጪና እቅራቢ በኩል ለአገልግሎት ከሚቀርቡት የኮሮናቫይረስ ክትባት ለማግኘት ጥያቄ እንዳቀረበች የጤና ጥበቃ ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ ባለፈው ሳምንት ገልጸዋል። ሚኒስትሯ ጨምረውም ለአገልግሎት ብቁ ከሆኑ የክትባት ዓይነቶች መካከል ኢትዮጵያም እንድታገኝ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ተናግረው፤ በኮቫክስ በኩል ክትባቱን በፍጥነት ለማግኘትና በቅድሚያ መከተብ ለሚገባቸው ወገኖች እንዲደርስ እንደሚደረግ አስረድተዋል። የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ከተከሰተ አንድ ዓመት ሊሞላው ተቃርቧል። በአፍሪካ ከ2.3 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በበሽታው ሲያዙ ከ56 ሺህ በላይ ደግሞ ለሞት ተዳርገዋል። ከዚህ ውስጥ ደግሞ በኢትዮጵያ ከ117 ሺህ በላይ ሰዎች ቫይረሱ የተገኘባቸው ሲሆን ከ1 ሺህ 800 በላይም ህይወታቸውን አጥተዋል። ከ72 ሚሊዮን በላይ የምድራችን ነዋሪዎችም በበሽታው መያዛቸው የተረጋገጠ ሲሆን ከ1.6 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ሰዎች ደግሞ በወረርሽኙ ሰበብ ሕይወታቸውን ማጣታቸው የጆንስ ሆፕኪንስ ዩኒቨርሲቲ መረጃ ያሳያል።
news-53528520
https://www.bbc.com/amharic/news-53528520
የቀድሞውን የአል-በሽር መንግሥት ለመገልበጥ የሞከሩ ሰዎች የጅምላ መቃብር ተገኘ
እአአ 1990 ላይ የኦማር አል-በሽር መንግሥት ላይ መፈንቅለ መንግሥት ለማካሄድ የሞከሩ ሰዎች አስክሬን በጅምላ የተቀበረበት ስፍራ ተገኘ።
በጅምላ መቃብሩ የጦር አባላት ናቸው የተባሉ የ28 ሰዎች አስክሬን ተገኝቷል። ኦማር አል-በሽር ከመፈንቅለ መንግሥት ሙከራው አንድ ዓመት ቀደም ብሎ ነበር ስልጣን የያዙት። አል-በሽር ላይ የተሞከረው መፈንቅለ መንግሥት ከመክሸፉ በፊት መፈንቅለ መንግሥቱን ያሴሩ የጦር አመራሮች፤ በርካታ የጦሩ ዋና መሥሪያ ቤቶችን እና የጦር ህንጻዎችን በቁጥጥር ሥር ማዋል ችለው ነበር። ይሁን እንጂ መፈንቅለ መንግሥቱ ከከሸፈ በኋላ በቁጥጥር ሥር ውለው ተገድለዋል። የጅምላ መቃብሩ እንዴት ተገኘ? የሰዎቹ አስክሬን የተገኘው በሱዳኗ ኦማዱረማን ከተማ ነበር። ዐቃቢ ሕጉ ታጌለሲር አል-ቤብረ ለኤኤፍፒ ዜና ወኪል ሲናገሩ፤ የጅምላ መቃብሩ ፍለጋ በቀድሞ የሱዳን መሪ አል-በሽር የተፈጸሙ የወንጀል ድርጊቶች ምርመራ አካል ነው ብለዋል። "የጅምላ መቃብሩን ስፍራ ለማግኘት 22 ባለሙያዎች እና ሦስት ሳምንታት አስፈልገዋል" ብለዋል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕጉ። አል-ቤብረ ጨምረው እንደተናገሩት፤ የጅምላ መቃብሩን መቆፈር እና የሟቾቹን ማንነት የማጣራት ቀጣዩ ተግባራችን ነው ብለዋል። ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ መሰል የጅምላ መቃብር ስፍራ ሲገኝ ይህ ለሁለተኛ ጊዜ ነው። ባሳለፍነው ወር የአገሪቱ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ እንዳለው፤ እአአ 1998 ላይ ከውትድርና ስልጠና ካምፕ ለማምለጥ ሲሞክሩ የተገደሉ ተማሪዎች አስክሬንን የያዘ የጅምላ መቃብር ተገኝቶ ነበር። ባለፈው ዓመት በሕዝባዊ ተቃውሞ ከስልጣን የተባረሩት አል-በሽር ካርቱም በሚገኘው እስር ቤት ውስጥ ይገኛሉ። ኦማር አል-በሽር ላይ የሙስና ክስን ጨምሮ በርካታ ክስ ተመስርቶባቸዋል። የ76 ዓመቱ ኦማር አል-በሽር እአአ 1989 ላይ ወደ ስልጣን ባመጣቸው መፈንቅለ መንግሥት ላይ በነበራቸው ተሳትፎ ክስ ተመስርቶባቸው ከትናንት በስቲያ በመዲናዋ ካርቱም በሚገኘው ፍርድ ቤት ቀርበው ነበር። አል-በሽር በቀረበባቸው ክስ ጥፋተኛ ሆነው የሚገኙ ከሆነ የሞት ፍርድ ሊበየንባቸው ይችላል ተብሏል። አል-በሽር በሱዳኗ ዳርፉር ግዛት በተፈጸሙ የሰብአዊ መበት ጥሰቶች፣ የዘር ማጥፋት እና የጦር ወንጀሎች በዓለም አቀፉ የጦር ወንጀለኞች ይፈለጋሉ። የሱዳን የሽግግር መንግሥት ከወራት በፊት የቀድሞ መሪውን ለፍርድ ቤቱ አሳልፎ ለመስጠት ዝግጁ መሆኑን አስታውቆ ነበር።
news-53004399
https://www.bbc.com/amharic/news-53004399
የምግብ ቤት ባለቤቶቹ በማጭበርበር ወንጀል የ1 ሺህ 446 ዓመት እስር ተፈረደባቸው
ታይላንድ ውስጥ የሚገኝ አንድ ፍርድ ቤት ኅብረተሰቡን አጭበርብረዋል በሚል በሁለት የምግብ ቤት ባለቤቶች ላይ በእያንዳንዳቸው የ1ሺህ446 አመታት እስር በይኗል።
ለዚህም ምክንያቱ ባለፈው ዓመት ሌምጌት የተባለው የባሕር ምግብ አቅራቢ ምግብ ቤት በበይነ መረብ በኩል በቅድሚያ በሚደረግ ክፍያ የምግብ ማስተወወቅ ተግባር አከናውኖ እስከ 20ሺህ ከሚደርሱ ሰዎች 1.6 ሚሊዮን ዶላር የሚደርስ ገንዘብ ሰብስቦ አገልግሎቱን ባለማቅረቡ ነው። ከዚያም በመቶዎች የሚቆጠሩ ገንዘባችንን ተበላን ያሉ ሰዎች ክስ በማቅረባቸው ምግብ ቤቱ ባለቤቶች የሆኑት አፒቻት ቦዎረንባናቻራክ እና ፕራፓሶርን ቦዎረንባናቻራክ የተባሉት ግለሰቦች ተይዘው ፍርድ ቤት ከቀረቡ በኋላ ነው የረጅም ዘመን እስር የተፈረደባቸው። በታይላንድ ውስጥ በማጭበርበር ወንጀል ላይ ተሳትፈው የተያዙ ሰዎች ላይ በጣም ረጅም አመታት የእስር ቅጣት መጣል የተለመደ ሲሆን፤ በተለይ በርካታ ሰዎች ክስ ያቀረቡበት ጉዳይ ከሆነ ደግሞ ቅጣቱ ይከብዳል። በዚህ የማስተዋወቂያ ሽያጭ ምግብ ቤቱ ከባሕር ውስጥ እንስሳት የሚሰራን ምግብ በርካሽ እንደሚያቀርብ ገልጾ የበርካታ ሰዎችን ቀልብ መሳብ በመቻሉ ከአንድ ሚሊዮን ዶላር በላይ ገንዘብ ለመሰብሰብ ችሎ ነበር። በርካታ ሰዎች በኢንተርኔት አማካይነት ክፍያ ፈጽመው ስለነበረ ቀድመው ግዢውን የፈጸሙት ሰዎች የሚፈልጉትን ያገኙ ሲሆን፤ በኋላ ላይ የገዢው ቁጥር ከፍተኛ በመሆኑ ምግብ ቤቱ በሚፈለገው ፍጥነት ምግቡን ማቅረብ ባለመቻሉ ክፍያውን የፈጸሙ ሰዎች ተራቸው እስኪደርስ ለወራት መጠበቅ ነበረባቸው። ነገር ግን ከሚችለው በላይ የምግብ ትዕዛዝ የተቀበለው ምግብ ቤቱ በመጋቢት ወር ላይ "አልቻልኩም" ብሎ ድርጅቱን መዝጋቱን አስታወቀ። የአገሪቱ መገናኛ ብዙሃን እንደዘገቡት ምግብ ቤቱ ግዢውን ለፈጸሙ ሰዎች ገንዘባቸውን እንደሚመልስ አሳውቆ ከ818 ገዢዎች ውስጥ ለ375ቱ ገንዘባቸውን ተመላሽ አድርጓል። ነገር ግን ቀሪዎቹ በመቶ የሚቆጠሩ ሰዎች በድርጅቱ መጭበርበር ተፈጽሞብናል በሚል በባለቤቶቹ ላይ ክስ መስርተዋል። በዚህም ሁለቱ የምግብ ቤቱ ባለቤቶች በሐሰተኛ መልዕክት ሕዝብን ማጭበርበርን ጨምሮ በሌሎች ክሶች ተይዘው ታስረዋል። ክሱን የተመለከተው የታይላንድ ፍርድ ቤት በ723 ሰዎች ላይ በተፈጸመ ማጭበርበር ተከሳሾቹን ጥፋተኛ ሆነው ስላገኛቸው ትናንት ረቡዕ እያንዳንዳቸው ላይ የ1 ሺህ 446 ዓመታት እስር ወስኗል። ነገር ግን ተከሳሾቹ ጥፋተኝነታቸውን በማመናቸው ፍርድ ቤቱ የእስር ብይኑን በግማሽ ቀንሶላቸው እያንዳንዳቸው ላይ የ723 ዓመት እስር በይኗል። ነገር ግን በአገሪቱ ሕግ መሰረት ግለሰቦቹ የታሰሩት ቢበዛ ለ20 ዓመታት ነው። ከዚህ በተጨማሪም ምግብ ቤቱ ላይ የገንዘብ ቅጣት የተጣለበት ሲሆን ለቀሪዎቹ ደንበኞችም ገንዘባቸውን መልሶ ካሳም እንዲከፍል ተወስኖበታል። ከሦስት ዓመት በፊት ይኽው የታይላንድ ፍርድ ቤት አንድ በማጭበርበር ወንጀል የተከሰሰ ግለሰብ ላይ 13 ሺህ ዓመት እስር መፈረዱ ይታወሳል። ምንም እንኳን ፍርድ ቤቱ ይህንን ውሳኔ ያሳልፍ እንጂ የአገሪቱ ሕግ ሕዝብን በማጭበርበር የተከሰሱ ሰዎች የሚታሰሩበት ጊዜ ከ20 ዓመት እንዳይበልጥ ይገድባል።
news-55516800
https://www.bbc.com/amharic/news-55516800
ኮሮናቫይረስ ፡ ታዋቂው የቴሌቪዥን አቅራቢ ላሪ ኪንግ በኮቪድ-19 ተይዞ ሆስፒታል ገባ
ታዋቂው የቴሌቪዥን አቅራቢ ላሪ ኪንግ ኮሮናቫይረስ እንዳለበት በመረጋገጡ ሎስአንጀለስ ከተማ ውስጥ በሚገኝ ሆስፒታል ውስጥ ህክምና እየተደረገለት መሆኑን የአሜሪካ መገናኛ ብዙሃን ዘገቡ።
ላሪ ኪንግ ለላሪ ኪንግ ቤተሰብ ቅርብ የሆኑ ምንጮች ለኤቢሲ ኒውስና ቀድሞ ይሰራበት ለነበረው ሲኤንኤን ቴሌቪዥን እንደተናገሩት ላሪ ሆስፒታል ከገባ ከሳምንት በላይ ሆኖታል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የልብ ህመምን ጨምሮ በርካታ የጤና እክሎች ሲያጋጥሙት የነበረው ላሪ፤ ከ60 ዓመት በላይ በዘለቀው የቴሌቪዥን አቅራቢነት ሙያው በርካታ ሽልማቶችናና እውቅናዎችን አግኝቷል። የ87 ዓመቱ ላሪ ተወካዮች እስካሁን በይፋ ወጥተው ሆስፒታል ስለመግባቱና አሁን ስላለበት ሁኔታ ምንም አይነት መግለጫ ስላልሰጡ ዝርዝር መረጃ የለም። ላሪ ኪንግ መጀመሪያ ላይ እውቅናን ያገኘው በ1970ዎቹ በሬዲዮ ያቀርበው በነበረ ዝግጅቱ ነበር። ከዚያም ከ1985 እስከ 2010 (እአአ) በሲኤንኤን ቴሌቪዥን ላይ በተለያዩ መስኮች የዓለማችን ተጽእኖ ፈጣሪ ከሆኑ ታዋቂ ግለሰቦች ጋር በሚያደርገው ቃለ ምልልስ እውቅናን አትርፏል። ላሪ ኪንግ ከሬዲዮና ከቴሌቪዥን ሙያው በተጨማሪ በአሜሪካ ታዋቂ ለሆነው 'ዩኤስኤ ቲዴይ' ለተባለው ጋዜጣ ለ20 ዓመታት አምደኛ ሆኖ ጽሁፎችን ሲያርብ ቆይቷል። በቅርቡም በሩሲያ መንግሥት በሚተዳደረው የስርጭት ተቋም ስር ለሚቀርቡት 'ሁሉ' እና 'አርቲ' ለተባሉት ቴሌቪዥኖች 'ላሪ ኪንግ ናው' የተሰኘ ዝግጅትን ያቀርብ ነበር። ታዋቂው ቃለ መጠይቅ አድራጊ ላሪ ኪንግ ሙያውን እያከናወነ ባለበት ዘመን ውስጥ የስኳር፣ የልብ ህመምና የሳምባ ካንሰርን ጨምሮ በርካታ ከባድ የጤና ችግሮች ገጥመውት ነበር። በተጨማሪም ካሉት አምስት ልጆች ውስጥ ሁለቱ በልብ ህመምና በሳንባ ካንሰር በሳምንት ልዩነት ውስጥ ባለፈው የፈረንጆች ዓመት ሞተውበታል። ላሪ ኪንግ ከ30 ዓመት በፊት የልብ ህሙማን ሆነው የገንዘብ አቅምም ሆነ የጤና መድን የሌላቸውን ሰዎች የሚረዳ የበጎ አድራጎት ድርጅት በስሙ በማቋቋም ድጋፍ ሲያደርግ ቆይቷል።
44778467
https://www.bbc.com/amharic/44778467
ወደ አሥመራ ለመጓዝ ማወቅ የሚገባዎ 6 ነጥቦች
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለሃያ ዓመታት ተቋርጦ የነበረውን የአሥመራ በረራውን ማክሰኞ ሐምሌ 17/2010 ዓ.ም ሊጀምር መሆኑን አሳውቋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ በኤርትራ ያደረጉትን ይፋዊ ጉብኝት ተከትሎ የሁለቱ አገራት መሪዎች ከደረሱባቸው ስምምነቶች መካከል አንዱ የሆነው የአየር ግንኙነትን የመጀመር ውሳኔን ተከትሎ ነው ይህ ይፋ የሆነው። "ዛሬ ትግርኛ የለ፣ አማርኛ የለ! ቋንቋው ጠፍቶብኛል" ዐብይ አሕመድ ኢትዮጵያና ኤርትራ፦ ከእራት በኋላ ምን ተወራ? የኢትዮጵያ አየር መንገድ እንዳሳወቀው ከሁለት አስርት ዓመታት በኋላ ለሚያደርገው ለዚህ በረራ በአሁኑ ወቅት ተጠቃሽ ከሆኑት ዘመናዊ አውሮፕላኖቹ መካከል አንዱ የሆነው ቦይንግ 787ን እንደሚያበር አሳውቋል። • የጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ አዲስ ምዕራፍ በአሁኑ ወቅት ወደ ኤርትራ ለመጓዝ ያሰበ ሰው ምን ማድረግ ይጠበቅበታል? 1. ቪዛ ኢትዮጵያዊያን ኤርትራ ሲደርሱ ቪዛ ይሰጣቸዋል። በተመሳሳይ መልኩ ኤርትራውያን ኢትዮጵያ ሲገቡ የመዳረሻ ቪዛ ይሰጣቸዋል። ከቀናት በፊት በአዲስ አበባ የሚገኙ የኤርትራ ዲፕሎማቶች ''ለጉብኝት የሚሄዱ ኢትዮጵያዊያን አሥመራ ሲደርሱ ቪዛ ማግኘት ይችላሉ። ከጉዞ በፊትም የተጓዦች የፓስፖርት ኮፒ ወደ አሥመራ ይላካል'' ብለው ነበር። 2. የአውሮፕላን ቲኬት የኢትዮጵያ አየር መንገድ በመጀመሪያ በረራው ከአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ከጠዋቱ 3 ሰዓት በመነሳት በቀጥታ ወደ አሥመራ ጉዞ ያደርጋል። ለምሳሌ ሐምሌ 13 2010 ዓ.ም ጉዞውን ወደ አሥመራ አድርጎ ሐምሌ 18 ወደ አዲስ አበባ የሚመለስ ተጓዥ ለአየር ቲኬት 7106 ብር እንዲከፍል ይጠየቃል። የጉዞ ቲኬት ከኢትዮጵያ አየር መንገድ የሞባይል መተግበሪያ አሊያም ከአየር መንገዱ ድረ-ገጽ ላይ አሁን መግዛት ይቻላል። 1 ሰዓት ከ 10 ደቂቃ በሚፈጀው በረራ ጥቅም ላይ ይውላል የተባለው 787 ድሪም ላይነር ከ250 መንገደኞች በላይ የማሳፈር አቅም አለው። 3. የገንዘብ ምንዛሬ አሥመራ ላይ በብር መገበያየት አይቻልም። የኤርትራ መገበበያ ገንዘብ ናቅፋ ይባላል። 1 የአሜሪካን ዶላር በ15 ናቅፋ ይመነዘራል። 4. ሆቴል ከአዲስ አበባ ጋር ሲነጻጻር በአሥመራ በርካታ የሆቴል አማራጮች ላይገኙ ይችላሉ። በአሥመራ መሃል ከተማ ለአንድ ቀን አዳር በአማካይ ከ45 - 70 የአሜሪካን ዶላር ሊጠየቁ ይችላሉ። ይህን ያህል ዋጋ የሚጠየቅባቸው አብዛኛዎቹ ሆቴሎች ቁርስ የተካተተባቸው ሲሆን ነጻ የኢንተርኔት አገልግሎትም የሚሰጡ ናቸው። ከላይ ከተጠቀሰው ዋጋ የሚያንሱ የአንግዳ ማረፊያዎች (ፔኒሲዮኖች) በአሥመራ ከተማ ውስጥ ይገኛሉ። 5. ምግብ እና መጠጥ አማካይ በሆነ የአሥመራ ምግብ ቤት ውስጥ አንድ ጥብስ ከ100-125 ናቅፋ (6-8 የአሜረካ ዶላር) ድረስ ሊሸጥ ይችላል። የለስላሳ መጠጦች 8 ናቅፋ ገደማ ይጠየቅባቸዋል። በኤርትራ ''አሥመራ ሜሎቲ'' የሚባል አንድ የቢራ አይነት ብቻ ነው ያለው። ለአንድ አሥመራ ሜሎቲ ቢራ 18 ናቅፋ ይከፍላሉ። 6. የትራንስፖርት አገልግሎት ከአሥመራ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ እሰከ መሃል ከተማ ለመጓዝ የህዝብ አውቶብስ ወይም ታክሲዎችን መጠቀም ይችላሉ። የህዝብ አውቶብስ ከተጠቀሙ 2 ናቅፋ ብቻ የሚከፍሉ ሲሆን 4 ሰው የምትይዘውን ታክሲ ከመረጡ ግን 100 ናቅፋ ሊጠየቁ ይችላሉ። በኤርትራ ቆይታዎ ከአሥመራ በሰሜን ምሥራቅ አቅጣጫ 113 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የምትገኘውን ምፅዋንም መጎብኘት የሚሹ ከሆነ የህዝብ አውቶብስ በመያዝ ከሁለት ተኩል ጉዞ በኋላ መድረስ ይችላሉ። ከላይ የተጠቀሱት ዋጋዎች አማካይ ግምት ወይም ከሦስተኛ አካል የተገኙ ናቸው። ዋጋዎቹ ግብር ያካተቱ ቢሆንም በአንዳንድ ቦታዎች ላይ የዋጋ ልዩነት ሊኖር ይችላል። የትናንትናዋ እለት- በኢትዮ ኤርትራ ግጭት ቤተሰባቸው ለተለያየ?
news-51346478
https://www.bbc.com/amharic/news-51346478
ናይጄሪያ የቪዛ እገዳው እንዲነሳ የትራምፕን ማሻሻያ እቀበላለሁ አለች
አሜሪካ ናይጀሪያን ጨምሮ በስድስት አገራት ላይ የቪዛ እገዳ መጣሏን ተከትሎ ናይጀሪያ ያለባትን የፀጥታና ደህንነት ክፍተት ለማሻሻል እንደምትሰራ የሃገሪቱ ፕሬዚዳንት ሙሃመድ ቡሃሪ አስታውቀዋል።
በአፍሪካ በህዝብ ቁጥር አንደኛ የሆነችው ናይጄሪያ ከአሜሪካ ጋር "መልካም የሆነ ግንኙነት" እንዲኖራት እንደሚፈልጉም ምኞታቸውን ተናግረዋል። አዲሱን የቪዛ መስፈርቶች የሚያጠና አንድ ኮሚቴም ያቋቋሙ ሲሆን ለዚህም ሚኒስትር መድበዋል። • አሜሪካ ኤርትራን ጨምሮ በስድስት አገራት ላይ የቪዛ እገዳ ጣለች • "እናቴ ካልመጣች አልመረቅም" ኢዛና ሐዲስ ከማንችስተር ዩኒቨርስቲ ናይጄሪያን ጨምሮ ኤርትራ፣ ታንዛኒያ፣ ሱዳን፣ ኪርጊዝስታን እና ሚያንማር አሜሪካ ከምትሰጣቸው የተወሰኑ የቪዛ አይነቶችን እንዳያገኙ እገዳ ጥላባቸዋለች። የእነዚህ አገራት ዜጎች የተወሰኑ አይነት ቪዛዎችን ለማግኘት እንደማይችሉ ቢገለጽም የቱሪስት ቪዛ ግን ለማግኘት ይችላሉ ተብሏል። በ2018 አሜሪካ ከስምንት ሺ በላይ ለሚሆኑ ናይጄሪያውያን ቪዛ የሰጠች ሲሆን ይህም ቁጥር አሁን እገዳ ከጣለችባቸው አምስት ሃገራት ካገኙት ቪዛ ከሁለት ዕጥፍ በላይ ነው። በዚሁ ዓመት አሜሪካ ከ8 ሺህ በላይ ቪዛ ለናይጄሪያዊያን፣ 2 ሺህ ለሱዳናዊያን፣ 290 ለታንዛኒያዊያንና 31 ደግሞ ለኤርትራዊያን ሰጥታለች። "እነዚህ አገራት በብዙ መልኩ መተባበር ቢፈልጉም ከሃገራቱ የምንፈልገውን ዝቅተኛውን መስፈርት እንኳን ማሟላት ባለመቻላቸው እገዳው አስፈላጊ ሆኗል" በማለት ተጠባባቂ የአገር ውስጥ የደህንነት ሚንስትር ቻድ ዎልፍ አርብ ዕለት ለጋዜጠኞች ተናግረዋል። ቻድ ዎልፍ አክለውም እገዳ ከተጣለባቸው ሃገራትም ጋር የደህንነትና የፀጥታ መስፈርቱን የሚያሻሽሉበትን መንገድ ለመቀየስ አብረው እንደሚሰሩ ጠቅሰው በሂደትም ከእገዳ ዝርዝሩ እንዲወጡ ይደረጋል ብለዋል። አዲሱ የአሜሪካ የቪዛ ህግ ተግባራዊ የሚሆነው ከሃያ ቀናት በኋላ ሲሆን ለባለስልጣናት፣ በንግድ ለተሰማሩ ግለሰቦች እንዲሁም የቱሪስት ቪዛን በሚጠይቁ ሰዎች ላይ እንደማይተገበር የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ቢሮ ቅዳሜ ባወጣው መግለጫ አትቷል። • ለኢትዮጵያውያን ዲፕሎማቶች ቪዛ ስለማትጠይቀው ኳታር 5 ነገሮች • ፍልስጤማዊው የሃርቫርድ ተማሪ ወደ አሜሪካ እንዲገባ ተፈቀደለት "ናይጄሪያ ከአሜሪካም ሆነ ከዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጋር ያላትን መልካም ግንኙነት ማስቀጠል ትፈልጋለች፤ በተለይም በዓለም አቀፍ ደህንነትና ፀጥታ ዙሪያ አንደራደርም" በማለት የፕሬዚዳንቱ ቃል አቀባይ ፌሚ አዴሲና ተናግረዋል። ፕሬዝዳንት ትራምፕ ለመጀመሪያ ጊዜ የጉዞ እገዳ ያደረጉት በ2017 ነው። ያኔ በተረቀቀው መመሪያ መሰረትም ሰባት ከፍተኛ የእስልምና እምነት ተከታይ ህዝብ ቁጥር ያላቸው አገራት የአሜሪካን ቪዛ እንዳያገኙ ክልከላ ተደርጎባቸው ይገኛሉ። አሜሪካ ከዚህ ቀደምም በ2017 ለኤርትራዊያን የተወሰኑ የቪዛ ዓይነቶችን ከልክላ ነበር። ለመሆኑ አዲሱ መመሪያ ምንድን ነው? በአዲሱ መመሪያ መሰረት ከናይጄሪያ፣ ኤርትራ፣ ኪርጊዝስታንና ሚያንማር ለሚመጡ ዜጎች ቋሚ የመኖሪያ ፈቃድ ይዘት ያለው ቪዛ አይሰጣቸውም። ታንዛንያና ሱዳን ደግሞ በዲቪ ሎተሪ እንዲሳተፉ አይፈቀድላቸውም። በአዲሱ መመሪያ መሰረት ለጎብኝዎች፣ የንግድ ሥራ ለሚሰሩና ሕክምና ለሚያደረጉ ሰዎች የሚሰጠው ጊዜያዊ ቪዛ ግን ከእገዳው ጋር እንደማይገናኝ ባለስልጣኑ አረጋግጠዋል። እገዳው ከተጣለባቸው አገራት መካከል ኪርጊዝስታን እና ሱዳን በአብዛኛው ህዝባቸው የእስልምና ተከታይ ሲሆን፤ ናይጄሪያና ኤርትራ ደግሞ የእስልምና ተከታይ ቁጥር ህዝባቸው አምሳ በመቶ ነው። የጉዞ እገዳው ምንድን ነው? ፕሬዝዳንት ትራምፕ ስልጣን ላይ በወጡ በሰባተኛ ቀናቸው ነበር አወዛጋቢውን የጉዞ እገዳ የሚያትት መመሪያ የፈረሙት። እሳቤው የአሜሪካን ደህንነት ለመጠበቅ የግድ አስፈላጊ ነው በሚል ነበር። እገዳው ሰባት በአብዛኛው የእስልምና እምነት ተከታይ ባላቸው አገራት ላይ ያነጣጠረ ሲሆን ከፍርድ ቤትም ብርቱ ሙግት ገጥሞት ነበር። ፕሬዝዳንት ትራምፕ ባረቀቁት አወዛጋቢ መመሪያ መሰረትም የኢራን፣ ሊቢያ፣ሶማሊያ፣ ሶሪያ፣ የመን፣ ቬኒዙዌላ እና ሰሜን ኮሪያ የእገዳው ሰለባ ሆነዋል። ከእነዚህ አገራት ወደ አሜሪካ ለሚመጡ ዜጎች የቪዛ እገዳው ቢጣልም ለተማሪዎችና አለፍ ሲልም ከአሜሪካ ጋር የተለየ ቁርኝት አላቸው ለተባሉ ግለሰቦች እገዳው የተጣለባቸው አገራት ዜጎች ቢሆኑም ቪዛ የማግኘት ልዩ እድል እየተመቻቸላቸው ነው።
news-53216687
https://www.bbc.com/amharic/news-53216687
ትራምፕ የነጭን የበላይነት የሚሰብክ መልዕክት በትዊተር አጋሩ
አወዛጋቢው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ያጋሩት ተንቀሳቃሽ ምሥል የነጭን የበላይነት የሚሰብክ ነው።
አንድ ደጋፊያቸው ድምጹን ጎላ አድርጎ "የነጭ የበላይነት ለዘላለም ይኑር!" የሚል አውድ የሚሰጥ ቃል ሲናገር ይሰማል፤ እርሳቸው ባሰራጩት ቪዲዮ። መልዕክቱን ሲናገር የነበረው ሰው በፍሎሪዳ የጡረተኞች ሕንጻ ለዶናልድ ትራምፕ ድጋፍ ሲያደርጉ ከነበሩት ሰዎች አንዱ ነው። ዋይት ፓውር "White power" ነጭ አክራሪዎች የሚያዘወትሩት መፈክር ሲሆን ነጭ ከሌሎች ዘሮች ሁሉ የበለጠ ስለሆነ ነጭ ዘር ሌላውን ዘር መግዛት አለበት የሚል መልዕክትን ያዘለ ነው። በአንዳንድ የአሜሪካ ግዛቶች ይህ መልዕክት በእጅ ምልክት የሚገለጽ ሲሆን የነጭ የበላይነትን ሰባኪዎችና አክራሪዎች በአንድ እጃቸው ጣቶቻቸው የእንግሊዝኛውን "ደብሊው" (W) ሆሄን እንዲወክል በማድረግ ሌላኛውን ደግሞ የ"ፒ" (P) ሆሄን እንዲይዝ አድርገው የበላይነት ይሰብካሉ። ይህ ፕሬዝዳንቱ ያጋሩት ተንቀሳቃሽ ምሥል በፍሎሪዳው ሰልፍ ላይ የትራምፕ ደጋፊዎችና ተቃዋሚዎች ጸያፍ ስድብ ሲሰዳደቡ የሚያሳይ ነው። ተንቀሳቃሽ ምስሉን ማጋራታቸውን ተከትሎ ትራምፕ የዘረኝነት መልዕክቶችን በማፋፋም በነጭ አክራሪዎች አካባቢ ዳግም የመመረጥ እድላቸውን ለማስፋት እየሞከሩ ነው የሚል ትችት እየተሰነዘረባቸው ይገኛል። የትራምፕ ቃል አቀባይ ግን ትራምፕ ባጋሩት ቪዲዮ ውስጥ ይህ የነጭን የበላይነት የሚሰብከውን ድምጽ አልሰሙትም ነበር ብሏል። ዶናልድ ትራምፕ ይህን ቪዲዮ አሰናስለው በትዊተር ሰሌዳቸው በጻፉት መልዕክት የፍሎሪዳ ዘ ቪሌጅስ ነዋሪዎችን ለድጋፋቸው አመሰግነዋል። ዘ ቪሌጅስ በጡረታ ያሉ የሰሜን ምዕራብ ኦርላንዶ ነዋሪዎች ናቸው። የድጋፍ ሰልፉም የተደረገው እዚያው ነበር። በዚህ ትራምፕ በኋላ ላይ ከትዊተር ሰሌዳቸው ያስወገዱት ተንቀሳቃሽ ምሥል የነጭ የበላይነትን የሚሰብክ መፈክር እያሰማ የነበረው ሰው በጎልፍ ጨዋታ ላይ በምትዘወተር ጉርድ መኪና ቁጭ ብሎ ይታያል። ሰውየው ድምጹን ከፍ አድርጎ ከወዲያ ማዶ ለሚሰድቡት ሰዎች የአጸፋ መልስ እየሰጠ ይመስላል። ከወዲያ የሉ ሰዎች ሰውየውን ዘረኛ እያሉ ሲሰድቡት ይሰማል። ሌሎች ደግሞ ናዚ እያሉ ያወግዙታል። በጎልፍ መኪና ላይ የተቀመጠው ሰው "ነጭ ለዘላለም ይግዛ! የነጭ የበላይነት ይለምልም!" ሲል የመልስ ምት ይሰጣል። በአሜሪካ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ብቸኛው ጥቁር የሪፐብሊካን የምክር ቤት አባል ቲም ስኮት ከሲኤንኤን ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ቆይታ ትራምፕ ያጋሩት ተንቀሳቃሽ ምሥል "ጸያፍ ነው" ካሉ በኋላ ዶናልድ ትራምፕ ምሥሉን ከትዊተር ሰሌዳቸው በአስቸኳይ እንዲያነሱት ጠይቀዋል። ዶናልድ ትራምፕ አወዛጋቢና የዘረኝነት መንፈስ ያላቸውን መልዕክቶችን በትዊተር ሰሌዳቸው ላይ ሲያጋሩ ይህ የመጀመሪያቸው አይደለም። በ2017 በተመሳሳይ የእንግሊዝ ቀኝ አክራሪዎችን መልዕክት በማጋራታቸው ከዚያን ጊዜዋ ጠቅላይ ሚኒስትር ቴሬዛ ሜይ ጋር ቅራኔ ውስጥ ከቷቸው እንደነበር ይታወሳል። በ2019 ደግሞ የምክር ቤት ተመራጭ የሆኑትን አራት ሴቶች ማለትም ኢልሃን ኦማር፣ አሌክሳድሪያ ኦካሲዮ፣ ራሺዳ ጣላይብ እና አያና ብሬስሊን "ወደመጣችሁበት ሂዱና በወንጀል የተበከለውን አገራችሁን ችግር ፍቱ. . ." በሚል አሜሪካዊ እንዳልሆኑና መጤ እንደሆኑ የሚያሳስብ መልዕክት ጽፈውባቸው ነበር። ትራምፕ እንዲህ በስድብ የሞለጯቸው ሴት የምክር ቤት አባላት ከአራቱ ሦስቱ እዚያው አሜሪካ የተወለዱ ሲሆን አራቱም የአሜሪካ ዜግነት ያላቸው ናቸው። ከዚህም ሌላ በቅርቡ የጆርጅ ፍሎይድን በነጭ ፖሊስ በግፍ መገደል ተከትሎ የተነሳውን ተቃውሞ ለማብረድ ፖሊስ የኃይል እርምጃ እንደሚወስድ ትራምፕ የገለጹበት መንገድ ዘረኛ በመሆኑ ሲተቹበት ነበር። ዶናልድ ትራምፕ "ዘረፋ ሲጀመር ተኩሱም ይጀምራል" የሚለው አገላለጽን መጠቀማቸው ያስተቻቸው፤ ገለጻው በ1960ዎቹ መጨረሻ የማያሚ የፖሊስ ሹም ዋልተር ሄድሌይ ፖሊስ ጥቁሮችን እየለቀመ እንዲገድል መልዕክት ያስተላለፈበት በመሆኑ ነበር። ዶናልድ ትራምፕ ከእነዚህ ዘረኝነትን ከሚያባብሱ መልዕክቶች ሌላ የኮሮናቫይረስን "ኩንጉ ፍሉ" እያሉ መጥራታቸው ሲያስተቻቸው ቆይቷል። ይህ አገላለጻቸው በአሜሪካ የሚኖሩ የእስያ መልክ ያላቸው ዜጎች በሌሎች ጥቃት እንዲደርስባቸው እና እንዲገለሉ የሚያደርግ ነው። የዋይት ሐውስ አዲሷ ቃል አቀባይ ኬይሊ ማክኔኒ ግን ይህን አስተባብላለች። "ፕሬዝዳንቱ ኩንግ ፍሉ እያሉ ቫይረሱን የሚጠሩት ቫይረሱ ከቻይና ስለመጣ ብቻ ነው" ትላለች።
47314979
https://www.bbc.com/amharic/47314979
ትራምፕ አይኤስን ተቀላቅላ የነበረችውን አሜሪካዊት አላስገባም አሉ
ዶናልድ ትራምፕ አይኤስን ተቀላቅላ የነበረችውን አሜሪካዊት ተመልሳ ሀገሯን መርገጥ እንደማትችል ተናገሩ። በትዊተር ገፃቸው እንዳስነበቡት፣ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማይክል ፖምፒዮ፣ ሆዳ ሙታና የተባለችውን አሜሪካዊት ሀገሯ ተመልሳ እንዳትገባ ትእዛዝ አስተላልፈዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በበኩላቸው የ24 አመቷ ወጣት አሜሪካዊት እንዳልሆነች እና አሜሪካም እንደማትገባ ቀድመው ተናግረው ነበር። ቤተሰቦቿ እና ጠበቃዋ ግን ወጣቷ አሜሪካዊት እንደሆነች ይናገራሉ። ሆዳ ሙታና ቤተሰቦቿን ወደ ቱርክ ሃገር ለከፍተኛ ትምህርት እንደምትሄድ ነግራ አይኤስን ልትቀላቀል ወደ ሶሪያ ያቀናችው በ20 አመቷ ነበር። ሁኔታው ዜግነቷን ከተነጠቀችው የእንግሊዝ ተወላጇ ሸሚማ ቤገም ጋር ተመሳሳይነት አለው። • አይኤስን የተቀላቀለችው ተማሪ ወደ እንግሊዝ መመለስ እፈልጋለሁ እያለች ነው • አይ ኤስን ተቀላቅላ የነበረችው እንግሊዛዊት ዜግነቷን ልትነጠቅ ነው • "የኖርዌይ ፓስፖርቴን መልሼ ኢትዮጵያዊ መሆን እችላለሁ" አቶ ሌንጮ ለታ በቅርቡ ፕሬዝዳንት ትራምፕ በመጨረሻው ከአይኤስ ጋር በተደረገው ውጊያ የተማረኩትን፣ እንግሊዝን እና ሌሎች የአውሮፓ ሀገራት እንዲወስዷቸው እና ለፍርድ እንዲያቀርቧቸዉ ተናግረው ነበር። የሆዳ ሙታና ቤተሰብ ጠበቃ፣ ሀሰን ሺብሊ፣ ትራምፕ የአውሮፓ ሀገራትን ዜጎቻቸውን መልሰው እንዲወስዱ ተናግረው "በአሜሪካ ዜጎች ላይ ግን ለመቀለድ እየሞከሩ ነው" ሲሉ ኮንነዋል። አክለውም "የትራምፕ አስተዳደር ዜጎችን በተሳሳተ መንገድ ዜግነታቸውን ለመንጠቅ እየሞከረ ነው" በማለት ለኤቢሲ ኒውስ ተናግረዋል። ሆዳ ሙታና ህጋዊ የሆነ የአሜሪካ ፓስፖርት ያላት ዜጋ ስትሆን የተወለደችው በኒው ጀርዚ እኤአ በ1994 ነው። ጠበቃዋ ወጣቷ ፍትሀዊ የሆነ የፍርድ ስርዓት እንደምትፈልግና እስርም ከተፈረደባት ለመቀበል ዝግጁ እንደሆነች ተናግረዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ፖፒዮ ግን "ወጣቷ ህጋዊ የሆነ ፓስፖርትም ሆነ ፓስፖርት የማግኘት መብትም የላትም" ብለዋል። • ዜግነት ለመግዛት ምን ያህል ይከፍላሉ? • ፓስፖርት፡ የሰዎችን እንቅስቃሴ የወሰነ ሰነድ "ሆዳ ሙታና አሜሪካዊት አይደለችም፤ ወደ አሜሪካም አትገባም" በማለት ጨምረው አቋማቸዉን ገልፀዋል። ሆዳ ሙታና የአሜሪካ ፓሰፖርት ወደ ቱርክ ከመሄዷ በፊት አመልክታ እንደተሰጣት ለኒው ዮርክ ታይምስ ተናግራለች። ሶሪያ ከደረሰችም በኋላ ከሌሎች ሶስት ሴቶች ጋር የአሜሪካን ጨምሮ ሌሎች የምዕራብ ሀገራትን ፓስፖርቶች ሲያቃጥሉ በትዊተር ገፅዋ ላይ ምስል ለቅቃ ነበር። አስከትሎም የማህበራዊ ሚዲያ ገፆችዋ ላይ የእስላማዊ ታጣቂዎች አሜሪካውያንን እንዲገድሉ ገፋፍታለች። . ተንታኞች እንደሚሉት የአሜሪካ መንግስት መልስ አባትዋ የየመን ዲፕሎማት መሆኑ ላይ አመዝኗል። በአሜሪካ ከውጪ ሀገር ዲፕሎማቶች የሚወለዱ ልጆች ወዲያው የአሜሪካ ዜግነት አይሰጣቸውም ምክንያቱ ደግሞ በአሜሪካ ህግ ስር ስላልሆኑ ነው። ሆኖም ግን ጠበቃዋ ሁዳ ሙታና ስትወለድ አባትዋ የዲፕሎማትነት ሥራቸውን አቁመው እንደነበር ይናገራል። • 13 አስደናቂ የፓስፖርት እውነታዎች • "ፓስፖርት መስጠት አልተከለከለም" የኢሚግሬሽንና የዜግነት ጉዳዮች ተቋም የ18 ወር ወንድ ልጅ ያላት ሆዳ ሙታና አይኤስን መቀላቀልዋ እንደሚቆጫት እና በማህበራዊ ሚዲያ የእስላማዊ ቡድኑን እና አላማውን ለማስተዋወቅዋ ይቅርታ ጠይቃለች። ሆዳ ከኤቢሲ ኒውስ ጋር ባደረገችው ቆይታ " ምኞቴ ይህን ድርጊቴን ሙሉ ለሙሉ መሰረዝ ብችል የሚል ነው። ይፀፅተኛል። አሜሪካ እንደ አደጋ እንደማታየኝ ተስፋ አደርጋለሁ። እኔ እንደማንኛውም ሰው አንዴ የተሳሳትኩ ነኝ። ዳግም እንደማልሳሳት ተስፋ አደርጋለሁ።" ሆዳ ባሁኑ ወቅት በሰሜን ሶሪያ፣ በኩርዲሽ ሀይሎች ተማርካ በስራቸው በሚገኝ የስደተኞች መጠለያ ውስጥ ትገኛለች።
news-50198595
https://www.bbc.com/amharic/news-50198595
የስኮትላንድ እግር ኳስ ማህበር ታዳጊዎች ኳስ በቴስታ እንዳይመቱ ሊያግድ ነው
የስኮትላንድ እግር ኳስ ማህበር ከአንጎል ጤንነት ጋር በተያያዘ የወጣ ሪፖርትን ተከትሎ ከ12 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች ኳስ በቴስታ እንዳይመቱ እገዳ ለመጣል እያሰበ መሆኑ ተነገረ።
በግላስጎው ዩኒቨርስቲ የሚገኙ ባለሙያዎች እንደደረሱበት የቀድሞ እግር ኳስ ተጫዋቾች አንጎልን እያዳከመ ለሞት በሚያበቃ የአንጎል በሽታ የመጋለጥ እድላቸው ከሦስት ጊዜ በላይ ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል። የስኮትላንድ እግር ኳስ የበላይ አስተዳዳሪ ከህክምና ባለሙያዎች ጋር ከተነጋገረ በኋላ ያሉ አማራጮች ላይ ውሳኔ እንደሚሰጥ ተነግሯል። አሜሪካ ውስጥ ከአምስት ዓመት በፊት ጀምሮ ታዳጊ ህጻናት ኳስ በጭንቅላታቸው እንዳይመቱ እገዳ ተጥሏል። • ''ብሔርተኝነት'' እያጠላበት ያለው እግር ኳስ • የአውሮፓን እግር ኳስ የሚዘውረው ሃብታሙ 'ደላላ' በእግር ኳስ ጨዋታ ላይ በጭንቅላት (በቴስታ) ኳስ መምታት በአንጎል ደህንነት፣ በተለይም በህጻናት ላይ የሚኖረውን ውጤት በተመለከተ ባለሙያዎች የሚሰጡትን ምክር ተከትሎ ስኮትላንድ ውስጥ ክልከላ ሊቀመጥ እንደሚችል እየተነገረ ነው። አንድ ውስጥ አዋቂ እንዳሉት "ጉዳዩ ታዳጊዎች በእግር ኳስ ጨዋታ ወቅት ኳስ በጭንቅላታቸው የመግጨት አጋጣሚ ብቻ ሳይሆን በልምምድ ወቅት በተደጋጋሚ ኳስን በጭንቅላት መምታትን ይመለከታል" ብለዋል። የስኮትላንድ እግር ኳስ ማህበር ዋና የህክምና አማካሪ የሆኑት ዶክተር ጆን ማክሊን ባለፈው ሳምንት ለቢቢሲ ኳስን በጭንቅላት በመምታት በታዳጊ ተጫዋቾች ላይ የሚፈጠረውን ጫና ለመቀነስ እርምጃ እንዲወሰድ እንደሚፈልጉ ገልጸዋል። ዶክተሩ እንዳሉት "ከስኮትላንድና ከአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር ጋር በመሆን ተቀባይነት ያለው መመሪያ ለማዘጋጀት ሥራ ጀምረናል። " • አወዛጋቢው የእግር ኳስ ዳኞች ማስመሪያ • ቢጫና ቀይ ካርዶች እንዴት ወደ እግር ኳስ ሜዳ መጡ? "ለምሳሌም ለታዳጊዎች የሚሰጠውን ኳስ በጭንቅላት የመምታት ልምምድ የተወሰነ እንዲሆንና አንጎላቸው ለማገገም እንዲችል በሳምንት የሚሰጣቸው ስልጠና አንድ ጊዜ ብቻ እንዲሆን ማድረግን የመሰለ ቀላል እርምጃ ሊሆን ይችላል" ብለዋል። የስኮትላንድ እግር ኳስ ማህበር ውስጥ አዋቂ እንዳሉት የማህበሩ አመራር ቡድን ታዳጊዎች ኳስ በጭንቅላታቸው መምታትን በተመለከተ የቀረበውን የባለሙያ አስተያየት ይደግፈዋል ብለዋል። በግላስጎው ዩኒቨርስቲ ለተደረገው ጥናት መነሻ የሆነው የቀድሞው ዌስት ብሮም አጥቂ ጄፍ አስቴል ለህልፈት የተዳረገው በተደጋጋሚ በጭንቅላቱ ላይ በደረሰበት ጉዳት ሳቢያ ነው የሚል አስተያየት ከተሰነዘረ በኋላ ነው። በ2002 (እኤአ) አስቴል ከሞተ በኋላ፣ በጥናቱ መዘግየት ቤተሰቦቹ ቁጣቸውን በመግለጻቸው፣ በእግር ኳስ ማህበሩና በፕሮፌሽናል እግር ኳስ ተጫዋቾች ማህበር አነሳሽነት ጥናቱ ተደርጓል። የሟቹ እግር ኳስ ተጫዋች ሴት ልጅ የሆነችው ዳውን ጥናቱ ይፋ ከተደረገ በኋላ በውጤት "እንደደነገጠች" ተናግራለች።
52989989
https://www.bbc.com/amharic/52989989
በስህተት ቫይረሱ የለብህም የተባለው የመንዲው ወጣት ወደ ለይቶ ማቆያ ገባ
በኦሮሚያ ክልል፣ ምዕራብ ወለጋ ዞን መንዲ ከተማ ነዋሪ የሆነው ወጣት በስህተት ቫይረሱ የለብህም ከተባለ ከቀናት በኋላ የተነገረው ውጤት የሌላ ሰው መሆኑ ተገልጾ እሱን ጨምሮ ከእርሱ ጋር ንክኪ አላቸው የተባሉ በርካታ ሰዎች ወደ ለይቶ ማቆያ መግባታቸው ተነገረ።
ወጣቱ ህመም ተሰምቶት ወደ የግል የጤና ማዕክል ሁለት ጊዜ ሄዶ እንደነበረ የመንዲ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ገመቹ ጉዲና ለቢቢሲ ተናግረዋል። የበሽታውን ምልክት ማሳየቱን ተከትሎ ዓርብ ዕለት ወደ ሆስፒታላቸው መጥቶ እንደነበረ ዶ/ር ገመቹ ይናገራሉ። "እኛ ሆስፒታል እንደደረሰ ወደ ለይቶ ማቆያ አስገብተን፤ ናሙናው ለምርመራ ተላከ። ከዚያ ቅዳሜ ዕለት ቫይረሱ እንደሌለበት ተነገረን" ይላሉ። ዶ/ር ገመቺስ እንደሚሉት ከሆነ ግለሰቡ ቫይረሱ እንደሌለበት ለሆስፒታሉ ያስታወቀው የዞኑ ጤና ቢሮ ነው። ነገር ግን "ሰኞ ደግሞ የደረሳችሁ ውጤት የሌላ ሰው ነው አሉን። ስህተት እንደሆነና ግለሰቡ በሽታው እንዳለበት ነገሩን። ከዚያም መልሰን ወደ ለይቶ ማቆያ አስገባነው" ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል። በቅርቡ ወጣቱ በአንድ በርካታ ሰው በሚሰበሰብበት ማህበራዊ ሥነ ሥርዓት ላይ መታደሙንና ከበርካታ ሰዎች ጋር ንክኪ እንደነበረው የሚናገሩት ዶ/ር ገመቹ፤ በዚህም ሳበያ ከወጣቱ ጋር ንክኪ ሳይኖራቸው አይቀርም ተብለው ወደ ለይቶ ማቆያ የገቡ ሰዎች ቁጥር ከፍተኛ መሆኑን ጠቀስዋል። "በከተማ ውስጥና በሆስፒታላችንም ከእርሱ ጋር ንክኪ የነበራቸውን ሰዎች ለይተናል። ከመጀመሪያው ጀምሮ የወጣቱን ቤተሰብ ጨምሮ ከእሱ ጋር ግንኙነት የነበራቸውን በፍጥነት ለይተናል። ሰኞ ዕለትም ከእሱ ጋር ንክኪ የነበራቸው ተጨማሪ 30 ሰዎችን ወደ ለይቶ ማቆያ አስገብተናል። 15 የጤና ባለሙያዎችም ተለይተዋል" ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል። ወጣቱ "ምልክት ሳያሳይ ከብዙ ሰዎች ጋር ንክኪ ስለነበረው በከተማው ውስጥና እኛ ጋርም ያለው ስሜት ጥሩ አይደለም" የሚሉት ዶ/ር ገመቹ፤ በቫይረሱ ስጋት ወደ ሆስፒታላቸው የሚመጡ ታካሚዎች ቁጥር መቀነሱንም ተናግረዋል። በበሽታው መያዙ ከተረጋገጠው ወጣት ጋር ንክኪ አላቸው ተብለው ወደ ለይቶ ማቆያ እንዲገቡ የተደረጉ ሰዎች ቁጥር ወደ 300 እንደሚጠጋ ዶክተሩ አስታውሰዋል። ጨምረውም "ከሰዎቹ ብዛት አንጻር በለይቶ ማቆያው ብዙ ያልተሟላላችወ ነገር አለ። በቂ ቦታ፣ ምግብና ውሃም እጥረት ይፈጠራል። የጤና ባለሙያዎችም በበሽታው ተይዘው ሊሆን ይችላል" ሲሉ ያላቸውን ስጋት ተናግተዋል።
55260304
https://www.bbc.com/amharic/55260304
ኮሮናቫይረስ፡ ኢትዮጵያ ነፃ የኮቪድ-19 ምርመራ መስጠት መጀመሯን አስታወቀች
የኮቪድ-19 ምርመራ ማድረግ ለሚፈልጉ ኢትዮጵያውያን ነፃ ምርመራ ማድረግ እንደሚችሉ የጤና ሚኒስቴር እና የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታውቀዋል።
በአዲስ አበባ በሚገኙ በተመረጡ 34 የጤና ጣቢያዎች እና ሆስፒታሎች ከክፍያ ነፃ ናሙና በመስጠትም ምርመራ ማድረግ ይችላሉም ተብሏል። የጤና ማዕከላቱንም ዝርዝር የጤና ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በማህበራዊ ሚዲያዎቻቸው አውጥተዋል። ነፃ የኮቪድ-19 ምርመራ ይሰጥባቸዋል ተብለው ከተጠቀሱትም መካከል ሚኒልክ ሆስፒታል፣ አቤት ሆስፒታል፣እንጦጦ ፋና የጤና ማዕከል፣ ህዳሴ የጤና ማዕከል፣ ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል፣ የካቲት 12 ሆስፒታል፣የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ይገኙበታል። ከአዲስ አበባ ውጭ ባሉ የጤና ማዕከላት የነፃ ምርመራን በተመለከተ የተባለ ነገር የለም። በአዲስ አበባ በሚገኙ የጤና ማዕከላት ውስጥ የኮሮናቫይረስ ምርመራ ለማድረግ 1 ሺህ 250 ብር ክፍያ የሚጠየቅ ሲሆን፤ አንዳንድ የጤና ተቋማትም 1 ሺህ 500 ብር ያስከፍላሉ። አገሪቷ ከዚህ ቀደም የኮሮናቫይረስ ምልክት የሚያሳዩና፣ከህመምተኞች ጋር ንክኪ ያላቸውን ብቻ ነበር በነፃ የምትመረምረው። በአሁኑ ወቅት አገሪቷ አስገዳጅ አድርጋው የነበረው የጭምብል ማጥለቅ መመሪያ ላላ ብሏል። የአፍሪካ በሽታዎች መከላከልና ቁጥጥር ማዕከል፣ ሲዲሲ ባወጣው መረጃ መሰረት በአፍሪካ ከፍተኛ የህሙማን ቁጥር ከተመዘገባቸው አገራት መካከል አንዷ ኢትዮጵያ መሆኗን ነው። ኢትዮጵያ እስካሁን ባለው ወደ 1.7 ሚሊዮን የላብራቶሪ ምርመራ ያከናወነች ሲሆን፣ 114 ሺህ 834 ህሙማንንም መዝግባለች። ከነዚህም ውስጥ 1 ሺህ 769 ዜጎቿንም በኮሮናቫይረስ እንዳጣች የጤና ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። የጤና ሚኒስትሯ ሊያ ታደሰ በዛሬው ዕለት እንደተናገሩት በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌንየም ሜዲካል ኮሌጅ ሲኒየር አንስቴቲስት የሆኑት አቶ ገብረሥላሴ አባዲ በኮቪድ-19 መሞታቸውንም ገልፀዋል።
news-49969117
https://www.bbc.com/amharic/news-49969117
ግሬግ ስኩፍ ፡ ሕገ ወጥ ስብሰባ አካሂደዋል የተባሉት አሜሪካዊ ፓስተር ከሩዋንዳ ተባረሩ
ሰኞ ዕለት ከጋዜጠኞች ጋር 'ሕገ-ወጥ' ስብሰባ በማድረጋቸው በኪጋሊ በቁጥጥር ሥር ውለው የነበሩት አወዛጋቢው አሜሪካዊው ፓስተር ከሩዋንዳ ተባረሩ።
ግሬግ ስኩፍ [በቀኝ በኩል] የታሰሩት በኪጋሊ ከጋዜጠኞች ጋር እያወሩ በነበረበት ወቅት ነው ወንጌላዊ ግሬግ ስኩፍ ትናንት በቁጥጥር ሥር የዋሉት ከጋዜጠኞች ጋር ሕገ ወጥ ስብሰባ በማካሄዳቸው እንደሆነ ፖሊስ አስታውቆ ነበር። ፓስተሩ የራዲዮ ጣቢያቸውና ቤተክርስትያናቸው በመዘጋቱ የሩዋንዳን መንግሥትን ተችተዋል። • ሩዋንዳ 700 አብያተ ክርስትያናትን ዘጋች • የአእምሮ ጤና ሰባኪው ፓስተር ራሱን አጠፋ 'ዘ አሜዚንግ ግሬስ' የተባለው የራዲዮ ጣቢያቸው ሴቶችን እንደ 'ሰይጣን' አድርጎ የሳለ ሰባኪን ማቅረቡን ተከትሎ ከሥርጭት የታገደው ባሳለፍነው ዓመት ነበር። በአገሪቷ ካሉ እና በድምፅ ብክለት፣ እንዲሁም ሕግ ባለማክበራቸው ከተዘጉ በመቶዎች ከሚቆጠሩ ቤተ ክርስትያናት መካከል የእርሳቸውም አንዱ ነበር። ግንቦት ወር ላይ የራዲዮ ጣቢያቸውን ለማስከፈት የአገሪቷ መንግሥት ሚዲያዎች ላይ የሚያሳድረውን ተፅዕኖ በመቃወም ያቀረቡት ክስ ውድቅ ተደርጎባቸዋል። "ግሬግን በቁጥጥር ሥር አውለን፤ ለሩዋንዳ የምርመራ ቢሮ አሳልፈን ሰጥተናቸዋል" ሲሉ የፖሊስ ቃል አቀባዩ ጆን ቦስኮ ካቤራ፣ ለኤ ኤፍ ፒ የዜና ወኪል ተናግረው ነበር። የሃገሪቱ የኢሚግሬሽን መምሪያ ዳይሬክተር፤ ወንጌላዊው በሩዋንዳ ለመስራት የሚያስችላቸው የሥራ ፍቃድ ጊዜው ካለፈ ወራት መቆጠሩን ጠቅሶ፤ ግለሰቡ የመኖሪያ ፍቃድ ስለሌላቸው ከሩዋንዳ እንዲባረሩ ተደርገዋል ብሏል። ቃል አቀባዩ አክለውም "ግለሰቡ በቁጥጥር ሥር የዋሉት በሕዝብ መገልገያ ቦታ ከጋዜጠኞች ጋር ሕገ ወጥ ስብሰባ በማካሄዳቸው ነው፤ በአገሪቷ ሕግ በሕዝብ መገልገያ ቦታ ያለ ፍቃድ ስብሰባ ማካሄድ የተከለከለ ነው" ሲሉ የታሰሩበትን ምክንያት ያስረዳሉ። ግሬግ ሰኞ ዕለት ከመታሰራቸው በፊት ለሚዲያ በሰጡት የፅሁፍ መግለጫ ላይ የሩዋንዳ መንግሥት በሚፈፅማቸው የአህዛብ ድርጊቶች 'ከፈጣሪ ጋር በተቃርኖ ቆሟል' ብለዋል። "የክርስቲያን ራዲዮ ጣቢያዎች በሕገ ወጥ መንገድ እየተዘጉ ነው፤ 7 ሺህ ቤተክርስትያናት በሕገ ወጥ መንገድ ተዘግተዋል፤ ኮንዶም በትምህርት ቤት ውስጥ ለህፃናት ይተዋወቃል፤ ርኩሰትን ያበረታታል" ይላል መግለጫው። • ቀብር አስፈጻሚዎች ከሞት አስነሳሁ ያለውን ፓስተር ሊከሱ ነው አክለውም በትምህርት ቤት ውስጥ ስለ ሰው ልጅ የዝግመተ ለውጥ አመጣጥ የሚሰጠውን ትምህርት፤ የፅንስ ማቋረጥ ሕግን ማቅለል በተመለከተም የሩዋንዳን መንግሥት ይተቻሉ። "መንግሥት ሕዝቡን ገሃነም ሊያስገባው ነው እንዴ?" ሲሉም ይጠይቃሉ። ፓስተር ግሬግ ከዚህ ቀደምም በሩዋንዳ ያለውን ሃሳብን በነፃነት መግለፅን በተመለከተ አበክረው ይጠይቁ ነበር። ባለፈው ዓመት በራዲዮ ጣቢያቸው በተላለፈው ዝግጅት ላይ አንድ የአገሪቷ ፓስተር "ሴቶች የሰይጣን አደገኛ ፍጥረቶች ናቸው፤ ሁል ጊዜም ከፈጣሪ እቅድ በተቃርኖ ይሄዳሉ" ማለታቸውን ተከትሎ "በአገሪቷ ውስጥ መከፋፋልን ይሰብካል" በሚል በመንግሥት ተከሰው ነበር። ፓስተር ግሬግ እና ቤተሰቦቻቸው ከጎርጎሮሳዊያኑ 2003 አንስቶ ኑሯቸውን በሩዋንዳ ማድረጋቸውን ድረ ገፃቸው ላይ የሰፈረው መረጃ ያመለክታል።
news-47905829
https://www.bbc.com/amharic/news-47905829
የሱዳን ተቃዋሚ ሰልፈኞች ወታደሩ ያስቀመጠውን ሰዓት እላፊ ጣሱ
በትናንትናው ዕለት ሱዳንን ለሰላሳ ዓመታት ያስተዳድሩት አል በሽር በወታደሩ ከስልጣን መውረዳቸውን ተከትሎ የተጣለውን የሰዓት እላፊን በመተላለፍ ሱዳናውያን ምሽቱን ጎዳና ላይ አሳልፈዋል።
ለረዥም ወራት ተቃውሞ ሲቀርብባቸው የነበሩት የቀድሞው የሱዳን ፕሬዝዳንት ከስልጣን ተነስተው በቁጥጥር ስር የዋሉት ትናንት ሐሙስ ዕለት ነበር። ተቃዋሚ ሰልፈኞች ግን የወታደሩ ምክር ቤት የአል በሽር አስተዳደር ውስጥ የነበረ ነው ሲሉ ተቃውመዋል። እንደ አዲስ ያገረሸው ተቃውሞ በወታደሩ እና በተቃዋሚ ሰልፈኞቹ መካከል ግጭት እንዳያስነሳ ተሰግቷል። • ለሰዎች መገደል ምክንያት የሆነውን የጥላቻ ንግግር፣ ህግ ይገድበው ይሆን? • "የአማራ ልዩ ኃይል ሕዝብን የሚጎዳበት ምክንያት የለውም" አቶ ገደቤ • ትውስታ- የዛሬ 20 አመት ኢትዮጵያ ሞባይል ስልክን ስትተዋወቅ በተጨማሪም የተለያዩ የደህንነት ኃይሎችና ሚሊሻዎች እርስ በእርሳቸው ጦር እንዳይማዘዙ ስጋት አለ። የተባበሩት መንግሥታትም ሆነ የአፍሪካ ሕብረት በሀገሪቱ መረጋጋት እንዲሰፍን ጥሪ አቅርበዋል። የ75 አመቱ አል በሽር ከስልጣን የመውረዳቸውን ዜና ተከትሎ የነበረው የደስታ እና የፈንጠዚያ ስሜት የተቃውሞ ሰልፉ አስተባባሪዎች በጦር ሠራዊቱ ዋና መስሪያ ቤት ደጃፍ የመቀመጥ አድማው እንዲቀጥል መናገራቸወን ተከትሎ ተቀዛቅዟል። "ይህ የቀደመው ሥርዓት ቅጣይ ነው" ብላለች ሳራ አብደልጃሊል የሱዳናውያን ባለሙያዎች ማህበር አባል " ስለዚህ በሰላማዊ ተቃውሟችን መግፋትና መታገል አለብን።" ትናንትና በሀገሪቱ ቴሌቪዥን በተነበበው መግለጫ ላይ ከምሽቱ አራት ሰዓት እስከ 10 ሰዓት ድረስ ሰዓት እላፊ መታወጁ ተገልጦ ነበር። በመግለጫው "ዜጎች ለራሳቸው ደህንነት ሲሉ ህጉን እንዲያከብሩ ይጠይቃሉ" አክለሎም "የጦር ኃይሉ እና ደህንነቱ ሰላምና ፀጥታን ለማስከበርና የዜጎችን ደህንነት ለማስከበር ሥራቸውን ያከናውናሉ" ተብሏል። በካርቱም ጎዳናዎች ላይ የወጡ ተቃዋሚ ሰልፈኞች አል በሽርን ከሰልጣን ለማውረድ የተጠቀሙባቸውን መፈክሮች "ይውረድ፣ ይውረድ" በማለት እንደገና ድምፃቸውን ከፍ አድርገው እያሰሙ ነው። አል በሽር ዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት በዳርፉር ውስጥ በተፈጸሙ በጦር ወንጀሎችና በሰብአዊ መብት ጥሰት የእስር ማዘዣ ቆርጦ የሚፈልጋቸው ግለሰብ ናቸው።
news-56648233
https://www.bbc.com/amharic/news-56648233
ብራዚል በአንድ ቀን 4ሺህ ዜጎቿን በኮሮናቫይረስ አጣች
ብራዚል ለመጀመርያ ጊዜ በ24 ሰዓት 4ሺህ ሰዎች በኮሮና ምክንያት መሞታቸውን ይፋ አደረገች፡፡
ምክንያቱ ደግሞ አዲሱ ዓይነት የኮቪድ ተህዋሲ ዝርያ መከሰቱ ሳይሆን አይቀርም ተብሏል፡፡ በአሁኑ ሰዓት በብራዚል ሆስፒታሎች ከሚችሉት ታማሚ በላይ እያስታመሙ ሲሆን በአንዳንድ ከተሞች ሰዎች አልጋ ወረፋ እየተጠባበቁ ተራ ሳይደርሳቸው ሞት እየቀለባቸው ነው ተብሏል፡፡ የሰው ሰራሽ መተንፈሻ መሣሪያዎች እጥረትም ተከስቷል፡፡ ወረርሽኙ ከመጣ ወዲህ ብራዚል የሞቱባት ዜጎች ቁጥር 337ሺህ የደረሰ ሲሆን ይህም በዓለም ሁለተኛው አስፈሪ ቁጥር ነው፡፡ በዚህን ያህል ቁጥር ዜጎቹ የሞቱበት ከአሜሪካ ሌላ የለም፡፡ በአሜሪካ ከግማሽ ሚሊዮን ዜጎች በላይ ሕይወታቸውን አጥተዋል፡፡ ፕሬዝዳንት ቦልሶናሮ ይህ ሁሉ ዜጋ ሞቶባቸውም ዘጋግቶ ቤት የመቀመጥ እርምጃን ተቃዋሚ ሆነው እንደፀኑ አሉ፡፡ እሳቸው እንደሚሉት ዜጎች ከቤት እንዳይወጡ ቢደረግ የምጣኔ ሀብት ቀውስና መዘዙ ከኮቪድ-19 የባሰ ሕዝቡን ይጨርሳል፡፡ ፕሬዝዳንት ቦልሶናሮ ባለፈው ማክሰኞ ለደጋፊዎቻቸው ንግግር ባደረጉ ጊዜ የእንቅስቃሴ ገደብ ያስቀመጡ የክልል ገዢዎችን ወቅሰዋል፡፡ ‹‹ቤት መቀመጥ ትርፉ መወፈርና ድብርት ነው፡፡ ቤት መቀመጥ ትርፉ የሥራ አጥ ቁጥርን ማብዛት ነው›› ሲሉ ተናግረዋል፡፡ በዚህ ንግግራቸው እሳቸው በሚመሯት ብራዚል በ24 ሰዓት 4ሺህ ዜጎች የመሞታቸውን ነገር ሳያነሱ አልፈውታል፡፡ በብራዚል እስከዛሬ በተህዋሲው የተያዙት ሰዎች ቁጥር 13 ሚሊዮን አልፏል፡፡ በደቡብ አሜሪካዊቷ አገር ብራዚል በመጋቢት ወር ብቻ 66ሺህ ዜጎች ከዚሁ ተህዋሲ ጋር በተያያዘ ሕይወታቸው አልፏል፡፡
news-54285516
https://www.bbc.com/amharic/news-54285516
ኮሮናቫይረስ ፡ የያዘዎት ጉንፋን ወይስ ኮቪድ-19 መሆኑን እንዴት መለየት ይችላሉ?
ኢንፍሉዌንዛ፣ ጉንፋን እና ኮቪድ-19 መነሻቸው የተለያዩ ቫይረሶች ቢሆኑም፤ ምልክታቸው ተመሳሳይ ነው። አንዳቸውን ከሌላቸው ለመለየትም ያስቸግራል።
በኮሮናቫይረስ የሚያዙ ሰዎች ከሚያሳዩት ምልክት መካከል ሙቀት መጨመር፣ የማያቋርጥ ሳል፣ የስሜት ህዋሳት አልሠራ ማለት ይጠቀሳሉ። ትኩሳት አለዎት? ሙቀት ከ37.8 በላይ ሲጨምር ሰውነት ኮሮናቫይረስን ወይም ሌላ ህመም እየተዋጋ ነው ማለት ነው። ስለዚህም ቴርሞሜትር ካለዎት ሙቀትዎን ይለኩ። ከሌለዎ ደግሞ ደረትዎ ወይም ጀርባዎ ላይ ትኩሳት እንዳለዎ በአይበሉባዎ ይፈትሹ። ትኩሳት የኮሮናቫይረስ ብቻ ሳይሆን የጉንፋንና የሌሎች ህመሞችም ምልክት ነው። ትኩሳት ካለዎት ኮቪድ-19 ቢመረመሩ ይመከራል። ያስልዎታል? ኢንፍሉዌንዛ ወይም ጉንፋን ሲይዝዎ ያስልዎታል። ጉንፋን ድንገት ይከሰትና የጡንቻ ህመም፣ ብርድ ብርድ ማለት፣ ራስ ምታት፣ የጉሮሮ መድረቅ፣ ድካም፣ የአፍንጫ መታፈን ያስከትላል። ህመሙ ከኢንፍሉዌንዛ በላይ ነው። ኢንፍሉዌንዛ የሚሰማን ቀስ በቀስ ሲሆን፤ ህመሙም ቀለል ይላል። ሳል፣ ማስነጠስ፣ የጉሮሮ መድረቅ እና የአፍንጫ ፈሳሽ ምልክቶቹ ናቸው። ትኩሳት፣ ብርድ ብርድ ማለት፣ የጡንቻ ህመምና ራስ ምታት ላይገጥምዎ ይችላል። ኮሮናቫይረስ ሲይዝዎ ከአንድ ሰዓት በላይ ያስላሉ። በ24 ሰዓት ውስጥ ሁለቴ ወይም ሦስቴ የማያቋርጥ ሳልም ያስከትላል። የማያቋርጥ ሳል ከገጠመዎ ኮቪድ-19 እንዲመረመሩ ይመከራል። መቅመስና ማሽተት አለመቻል ማሽተት ካቃተዎ ወይም ጣዕም መለየት ካልቻሉ የኮሮናቫይረስ ምርመራ ማድረግ አለብዎት። ቀለል ያለ ብርድ ይዞዎት ሊሆን ቢችልም መመርመሩ አይከፋም። በሌላ በኩል ማስነጠስ የኮሮናቫይረስ ምልክት አይደለም። ትኩሳትና ሳል ከሌለዎ ወይም የስሜት ህዋስዎ እንደ ወትሮው እየሠሩ ከሆነ መመርመር አያስፈልግዎትም። ሆኖም ግን ሲያስነጥሱ ቫይረሱን ሊያስተላልፉ ስለሚችሉ ሶፍት ይጠቀሙና እጅዎን በሳሙና ይታጠቡ። እጅ ከመታጠብ በተጨማሪ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል ማድረግና አካላዊ ርቀት መጠበቅም አይዘንጉ። አፍንጫዎን ያፍንዎታል? የአፍንጫ ፈሳሽ የኮሮናቫይረስ ምልክት እንዳልሆነ ባለሙያዎች ይናገራሉ። ኮቪድ-19 ያለባቸው ሰዎች መጠነኛ ወይም የተባባሰ ምልክት ሊያሳዩ ይችላሉ። ምልክት የማያሳዩ ሰዎች በሽታውን ሊያስተላልፉ ይችላሉ። በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች በሁለት ሳምንት ውስጥ ምልክቱን ያሳያሉ። በእርግጥ ብዙሀኑ በአምስተኛው ቀን የበሽታው ምልክት ሊታይባቸው ይችላል። ትንፋሽ የሚያጥርዎ ከሆነ በሽታው ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሷል ማለት ነው። በአጠቃላይ አንዳች የኮቪድ-19 ምልክት ሰውነትዎ ላይ ካስተዋሉ ሳያንገራግሩ ወደ ህክምና መስጫ ይሂዱ።
53915676
https://www.bbc.com/amharic/53915676
ሞባይል፡ 'የኮምፒውተር ተህዋስ' የተገጠመላቸው የቻይና ሥልኮች ኢትዮጵያና ሌሎች የአፍሪካ አገራት ውስጥ ተሽጠዋል
የኮምፒውተር ተህዋስ [ማልዌር] የተገጠመላቸው በሺዎች የሚቆጠሩ የቻይና ስሪት የሆኑ ስልኮች አፍሪካ ውስጥ መቸብቸባቸው ተሰምቷል።
አፕስትሪም የተሰኘ አንድ ተቋም ነው ይህን ይፋ ያደረገው። ቢያንስ በ53 ሺህ ይህ ተህዋስ የተገጠመላቸው የቴክኖ ስልኮች ኢትዮጵያ፣ ካሜሩን፣ ግብፅ፣ ጋና እና ደቡብ አፍሪካ ውስጥ መሸጣቸው ተነግሯል። የስልኮቹ አምራች የሆነው ትራንዚሽን የተሰኘ ኩባንያ ተህዋሱ የተገጠመው ከእኔ እውቅና ውጪ በአከፋፋዮች ነው ይላል። አፕስትሪም የተሰኘው የመሰል ተህዋሶች አጋላጭ ድርጅት በዚህ አይስማማም። "ይህ ማልዌር [የኮምፒውተር ተህዋስ] ሚሊዮኖችና ገቢያቸው አናሳ የሆኑ ሰዎች በሚገዙት ስልክ ላይ መሰል ተህዋስ ያለ ተጠቃሚዎች መገጠሙ ኢንዱስትሪው ምን ያክል የሰዎችን ግላዊነት እየተጋፋ እንዳለ የሚያሳይ ነው" ይላሉ የአፕስትሪም ባለሙያ የሆኑት ጄፍሪ ክሊቭስ። 'ትሪያዳ' የተሰኘው ተህዋስ አንድሮይድ ተንቀሳቃሽ ስልኮች ላይ የሚገጠም ሲሆን 'ኤክስሄልፐር' የተባለ ኮድ ተጠቅሞ ከተጠቃሚዎች እውቅና ውጪ ያሻውን የሚያደርግ ነው። ይህ ማልዌር ብዙ ጊዜ ተጠቃሚዎች ሳያውቁ አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶችን የሚቀላቀል ነው። ይህ ተህዋስ ሞባይል ስልክዎ ላይ ያለዎትን ገንዘብ [የአየር ሰዓት] ያለ ፈቃድዎ የሚወስድ ነው። በርካታ የአፍሪካ አገራት ውስጥ የበይነ መረብ ክፍያ የሚፈፀመው በአየር ሰዓት ነው። አፕስትሪም የተሰኘው ተቋም ቢያንስ 200 ሺህ ስልኮች ያለፈቃዳቸው 'ሰብስክራይብ' ካደረጓቸው አገልግሎቶች እንዲወጡ አድርጓል። ትራንዚሽን ሆልዲንግስ የተሰኘው ተንቀሳቃሽ ስልክ አምራች ኩባንያ ቻይና ውስጥ ካሉ ግዙፍ ኩባንያዎች አንዱ ሲሆን አፍሪካ የምርቶቹ ቁጥር አንድ ገዢ ናት። ቴክኖ፤ ችግሩ ያረጀና ያፈጀ ነው። ከሁለት ዓመት በፊት ቀርፌዋለሁ ይላል። ለቢቢሲ ጉዳዩን የተመለከተ የጽሑፍ መግለጫ የላከው ድርጅቱ፤ "ቴክኖ ደብለዩ2 ስልኮች ያላቸው ሰዎች መሰል ችግር እንዳያጋጥማቸው መጫን የሚችሉት መተግበሪያ [አፕሊኬሽን] አለ። ወደ ቴክኖ ሱቆች መጥተው እርዳታ መጠየቅም ይችላሉ" ይላል። ከወራት በፊት አንድ ሌላ ድርጅት ተመሳሳይ ችግር ያለባቸው ዩኤምኤክስ የተሰኙ የቻይና ምርት የሆኑ ስልኮች ላይ ማግኘቱ አይዘነጋም። ይህ ስልክ አሜሪካ ውስጥ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ሰዎች በመንግሥት መከፋፈሉ ይታወሳሉ። በፈረንጆቹ 2016 ራያን ጆንሰን የተሰኙ ተመራማሪ 700 ሚሊዮን አንድሮይድ ተንቀሳቃሽ ስልኮች ማልዌር እንደተገጠመባቸው ይፋ አድርጎ ነበር። ማልዌር ማለት ስልኮችና ሌሎች የቴክኖሎጂ ውጤቶች ላይ ከተጠቃሚዎች እውቅና ውጪ የሚገጠመው ተህዋስ ሲሆን መረጃ ከመመዝበር አልፎ ስልኮችንና ኮምፒውተሮች ከጥቅም ውጪ ሊያደርግ ይችላል።
news-57067389
https://www.bbc.com/amharic/news-57067389
አገራት ፍልስጥኤምና እስራኤል ግጭቱን እንዲያረጋጉ ጠየቁ
በእስራኤላውያን እና ፍልስጥኤማውያን መካከል የተፈጠረውን ውጥረት ለማርገብ እንደ አሜሪካ፣ አውሮፓ ሕብረት እና ዩናይትድ ኪንግደም ያሉ የተለያዩ አገራት አፋጣኝ እርምጃ እንዲወሰድ እየጠየቁ ነው።
ለውጥረቱ መነሻ የሆነው በምስራቅ እየሩሳሌም በሚገኘው የሼክ ጃራ ክፍል የፍልስጥኤማዊያን ቤተሰቦችን የማፈናቀል አደጋ መጋረጡ ነው። በመቶዎች የሚቆጠሩ ፍልስጥኤማዊያን ሰልፈኞች ብሎም ከ 20 በላይ የእስራኤል ፖሊሰች ባለፈው ሶስት ቀናት በነበሩ ግጭቶች ተጎድተዋል። እሁድ ምሽት ፍልስጥኤማዊያን ሰልፈኞች በእስራኤል ፖሊስ ላይ ድንጋይ ወርውረዋል። ፖሊስ ደግሞ በአፀፋው ስልፈኞችን ለመበተን ሙከራ አድርጓል። ትናንት ሰኞ ዕለት የፍልስጥኤም ታጣቂዎች ወደ እየሩሳም ሮኬቶችን መተኮሳቸው ደግሞ ነገሮችን ይበልጥ አባብሶታል። በምላሹ የእስራኤል ወታደሮች በጋዛ ሰርጥ የሚገኙ ኢላማዎች ላይ የአየር ጥቃቶችን ፈጽመዋል። የፍልስጥኤም የጤና ኃላፊዎች እንደሚሉት ደግሞ እስራኤል ጋዛ ውስጥ በወሰደችው የአየር ድብደባ እርምጃ ህጻናትን ጨምሮ 20 ሰዎች ሕይወታቸው አልፏል። እስራዜል ደግሞ ጋዛን ይመሩ የነበሩ ሶስት የሀማስ ቡድን አባላትን በድብደባው ገድያለው ብላለች። ሰኞ ዕለት በቅዱሱ የእየሩሳሌም አካባቢ ከእስራኤል ፖሊሶች ጋር በተፈጠረው ግጭት በመቶዎች የሚቆጠሩ ፍልስጤማውያን መጎዳታቸውን ተከትሎ ሃማስ የአጸፋ ምላሽ እንደሚወስድ አስጠንቅቋል። የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ደግሞ ሀማስ 'ቀዩን መስመር ተላልፏል' እስራኤልም ብትሆን ለሚደርሰው ነገር በሙሉ በከፍተኛ ኃይል ምላሽ ትሰጣለች ብለዋል። የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ኃላፊው አንቶኒ ብሊንከን ሀማስ የሮኬት ተኩሱን በፍጥነት እንዲያቆምና ሁለቱም ወገኖች ነገሮችን ለማበብረድ ጥረት እንዲያደርጉ ጠይቀዋል። የዋይት ሀውስ ቃል አቀባይዋ ጄን ሳክ በበኩሏቸው ፕሬዝደን ጆ ባይደን እየሆነ ያለው ነገር በእጅጉ እንዳሳሰባቸውና ግጭቱ በፍጥነት እንዲቆም ጥሪ ማቅረባቸውን አስታውቀዋል። የዩናይትድ ኪንግደም የውጭ ጉዳይ ኃላፊው ዶሚኒክ ራብ ደግሞ በትዊተር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት ''በሮኬት የሚፈጸሙት ጥቃቶች መቆም አለባቸው፤ የንጹሀን ዜጎች ኢላማ መሆንም መቆም አለበት'' ብለዋል። የአውሮፓ ሕብረት የውጭ ፖሊሲ ኃላፊ ጆሴፍ ቦሬልም በጉዳዩ ላይ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። ''በዌስትባንክ፣ ጋዛ እና ምስራቃዊ እየሩሳሌም እየጨመረ የመጣው ግጭት በፍጥነት መቆም አለበት'' ብለዋል። የተባበሩት መንግስታት በበኩሉ ትናንት ሰኞ ዕለት በጉዳዩ ላይ አስቸጓይ ስብሰባ አካሂዷል። ነገር ግን እስካሁን ድረስ ምንም አይነት መግለጫ አላወጣም። ትናንት በተከበረው ዓመታዊው የእየሩሳሌም የባንዲራ ቀን ሲደርስ ባንዲራ የያዙ ወጣቶች በሙስሊም አካባቢዎች ያልፋሉ ተብሎ ነበር። ይህም የሚካሄደው እስራኤል ምስራቅ እየሩሳሌምን የያዘችበትን ቀን ለመዘከር ነው። በርካታ ፍልስጤማዊያን ይህንን ድርጊት ትንኮሳ ነው ይሉታል። ሊፈጠር የሚችለውን የጸጥታ ችግር ከግምት ውስጥ በማስገባትም ይህ ቀን በዚህ ቦታ እንዳይካሄድ ተወስኗል።
news-55513634
https://www.bbc.com/amharic/news-55513634
ተዋናይ፣ ደራሲና አዘጋጅ ባዩሽ ዓለማየሁ
ተዋናይት፣ ደራሲ እና አዘጋጅ ባዩሽ ዓለማየው ታኅሣስ 23 ቀን 2013 ዓ. ም. ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች።
ተዋናይት፣ ደራሲ እና አዘጋጅ ባዩሽ ዓለማየው በተለይም በአገር ፍቅር ቴአትር ቤት ለበርካታ ዓመታት በተውኔት ሥራዎቿ የምትታወቀው ባዩሽ የመድረክ ቴአትር አዘጋጅም ነበረች። ባዩሽ ከምትታወቅባቸው ሥራዎች መካከል "ነቃሽ" የተባለው ቴአትር ይጠቀሳል። በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት የባህልና ቴአትር አዳራሽ የቀረበው ይህ ቴአትር የሕክምና ተቋማት ውስጥ ስለሚከሰቱ ሴራዎች ይተርካል። የአስክሬን ዘረፋ፣ የመድኃኒት ሽያጭና ሌሎችም ቴአትሩ የሚያጠነጥንባቸው ርዕሰ ጉዳዮች የተመልካችን ቀልብ ስበው ነበር። ከባዩሽ በተጨማሪ ፋንቱ ማንዶዬና ሌሎችም አንጋፋ ተዋንያንን ያሳተፈው ቴአትሩ ከ28 ዓመታት በኋላ በድጋሚ ወደ መድረክ እንዲመለስ መደረጉም ይታወሳል። ባዩሽ አጫጭር ተከታታይ ድራማዎችና ትረካዎችም ሠርታለች። ከሥራዎቿ መካከል ነቃሽ፣ ትዳር ሲታጠን፣ የስለት ልጅ፣ ሰማያዊ ዐይን፣ የቬኑሱ ነጋዴ እና ሰዓት እላፊ ተጠቃሽ ናቸው። የታዋቂው ተርጓሚ እንዲሁም ደራሲ መስፍን ዓለማየሁ ልጅ የሆነችው ባዩሽ በሬድዮ ትረካም ትታወቃለች። በዚህም በሬድዮ ፋና ላይ "ፓፒዮ" የተሰኘውን ትርጉም ልብ ወለድን መተረኳ ይታወሳል። በ1990ዎቹ ገደማ በኢትዮጲያ ቴሌቪዥን ስመ ገናና በነበሩ አጫጭር ተከታታይ ድራማዎች ላይ በመተወን የታወቀችው ባዩሽ፤ ከድርሰት ሥራዎቿ ውስጥ ረመጥ፣ ፎርፌ እና ገጽ ሁለት ተጠቃስ ናቸው። ተዋናይ፣ ደራሲና አዘጋጅ ባዩሽ ታማ ሆስፒታል እስከምትገባ ድረስ በአገር ፍቅር ቴአትር ቤት በድጋሚ ሊታይ በነበረው "ሰዓት እላፊ" በተሰኘው የቴዎድሮስ ተክለአረጋይ ቴአትር ላይ ለመተወን በልምምድ ላይ እንደነበረች ተነግሯል። ባጋጠማት ህመም ምክንያት በየካቲት 12 ሆስፒታል በህክምና ስትረዳ ቆይታ ታህሳስ 23 ቀን 2013 ዓ. ም 11 ሰዓት ገደማ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቷን ቤተሰቦቿ ገልጸዋል። ስለባዩሽ የሚያውቋት በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ያሉት መዓዛ ወርቁ መድረክ ላይ የምደነቅባት ተዋናይት (ሥራዎቿን ዘርዝሬ አልጨርሳቸውም። ገብቷት ተመችቷት የምትኖርበት መድረክ።) በሥራዎቼ የማምናት የእኔ የምላት ተዋናይት፤ አቋራጩ - የቲቪ፣ ወፌ ቆመች እና ህይወት መሰናዶ የሬዲዮ ድራማዎች ላይ አፌን ያስከፈተችኝ ሙሉ ሴት። አገር ፍቅር ቲያትር ቤት የሴት ደራሲ ነበረኝ ካለ ከባዩሽ ሌላ ማንን እንደሚጠራ አላውቅም። ቆንጆ ቆንጆ አጫጭር ልቦለድ ፅሁፎቿን ለሬዲዮ ራሷ ተርካ ሰጥታናለች - ታሪክ የገባት ሀሳብ ያላት ደራሲ! አደንቃታለሁ አከብራታለሁ እወዳታለሁ። በህልፈቷ እጅግ አዝኛለሁ። እኔ በህይወት እስካለሁ አልረሳትም። ታሪኳ በኢትዮጵያ ኪነጥበብ ታሪክ ጥሩ ቦታ እንዲቀመጥ እመኛለሁ። ** ያሬድ ሹመቴ ከድንቅ ተዋናይነቷ በላይ ፊቴ ድቅን የሚለው በጎነቷ ነው። በአገር ፍቅር ቴአትር ቤት እንደመስራቷ የእርዳታ ማስተባበር ሥራዎች በምንሰራባቸው ጊዜያት እህል ጭኖ ለማራገፍ የቆመ መኪና ስታይ ድንገት ነገሯን ሁሉ ትታ ወደ ሸክም እርዳታ ትገባለች። ከያኒ ባዩሽ አለማየሁ ገና ብዙ በምትሰራበት እድሜዋ አጥተናታል። እንግዲህስ ምን እንላለን? ቸር አምላክ ከደጋጎቹ ወገን ያኑራት። ** መሰረት መብራቴ የኔ ምስኪን በመጨረሻም ወደማይቀረው ቤትሽ ሄድሽ። ባዩሽ አለማየሁ ፀሐፌ ተውኔት፣ አዘጋጅ፣ ምርጥ ተዋናይት! የብርቱና የጠንካሬ ሴት ተምሳሌት! አይጠገቤ ጨዋታሽ፣ አክብሮትሽ እና መልካም ሰብዕናሽ ሁሌም በልባችን ይኖራል። ** ወሰንሰገድ ገ/ኪዳን ባዩሽ፤ ከምርጥ ሴት ተዋናዮች ተርታ የምትጠቀስ ነበረች፤ ለመድረክ ትወና የተሰጠች የጥበብ እመቤት ነበረች፤ ድንቅ ተዋናይ ነበረች። ** ውድነህ ክፍሌ የኛ አንደኛ፤ መድረክን እየናፈቁ መለየት ልብ ይሰብራል። ደራሲ፣ አዘጋጅና ተዋናይት ባዩሽ አለማየሁ። ነፍስሽ በሰላም ትረፍ።
news-50322622
https://www.bbc.com/amharic/news-50322622
የሞት ፍርድ ተፈርዶበት የነበረው ኬንያዊ የሕግ ዲግሪውን አጠናቀቀ
የሞት ፍርድ ተፈርዶበት የነበረ ኬንያዊ ከለንደን ዩኒቨርስቲ የሕግ ዲግሪውን ከሰሞኑ አግኝቷል።
ናይሮቢ በሚገኘው ኪማቲ እስር ቤት የምርቃት ሥነ ሥርዓት ተዘጋጅቶለት የነበረው ዊልያም ኦኩሙ ከፍተኛ ደስታ እንደተሰማው ለፎከስ ኦን አፍሪካ ራዲዮ ገልጿል። "ይህ የሚያሳየን ከቆሻሻም ቢሆን መልካም ነገር እንደሚገኝ ነው" በማለት ተናግሯል። •የሴቶች ዘብ የነበሩት ዶ/ር ቦጋለች ገብሬ •የኢትዮጵያዊቷ ህክምና መቋረጥ በደቡብ አፍሪካ አነጋጋሪ ሆነ አክሎም "ምን ዓይነት ደስታ ውስጥ እንዳለሁኝ ሊገልፅልኝ የሚችል የእንግሊዝኛ ቃል የተፈጠረ አይመስለኝም" ብሏል። በሠላዎቹ እድሜ ላይ የሚገኘው ዊልያም ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር ነበር ከእስር የተፈታው፤ የሕግ ዲግሪውም ሕይወቱን እንደቀየረ ገልጿል። እስር ቤትም ውስጥ በነበረበት ወቅት ያገኘው እውቀት ራሱንም ሆነ ሌሎች እስረኞች ለመከላከል እንደጠቀመው አስረድቷል። •"እስሩ አብንን ለማዳከም ያለመ ነው" ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) የሕግ ትምህርት ለመማርም ያነሳሳው ጉዳይ የሞት ፍርድ የተፈረደበት ሕጉን ባለመረዳቱና በሂደቱም ወቅት ትክክለኛ ጠበቃ ባለማግኘቱ መሆኑንም ገልጿል። ከሁለት ዓመታት በፊት የኬንያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተፈረደበት የሞት ቅጣት ከኬንያ ሕገ መንግሥት ጋር የማይጣጣም መሆኑንም ገልፆ ነበር። ዊልያም የሞት ቅጣት ተፈርዶበት የነበረው የዝርፊያ ወንጀልን ለመፈፀም ኃይልን በመጠቀሙ ሲሆን፤ ለራሱም ጥብቅና በመቆም የሞት ቅጣቱ የከፋ ነውም ሲል አስረድቷል። ዳኛውም ቅጣቱን ወደ አስር ዓመታት አቅልለውለታል፤ እስሩንም ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር ላይ አጠናቆ ተፈትቷል። በኬንያ እስር ቤቶች ከአምሳ ሺህ በላይ እስረኞች ያሉ ሲሆን፤ ብዙዎቹ ደግሞ ቀለል ያለ ወንጀል የፈፀሙ እንደሆነ ተገልጿል። ድህነትና አለመማር ተደራርበው እስረኞች ትክክለኛ የሕግ ውክልና እንዳያገኙ አድርጓቸዋል ተብሏል።
news-54040198
https://www.bbc.com/amharic/news-54040198
ትግራይ ፡ ምርጫው "እንዳልተደረገ የሚቆጠር፣ የማይጸናና ተፈጻሚነት የሌለው ነው" የፌዴሬሽን ምክር ቤት
በትግራይ ክልል በመጪው ረቡዕ ሊካሄድ የታቀደው ምርጫ ከአገሪቱ ሕገ መንግሥት ጋር የሚቃረን በመሆኑ "እንዳልተደረገ የሚቆጠር፣ የማይጸናና ተፈጻሚነት የሌለው ነው" ሲል የፌዴሬሽን ምክር ቤት በሙሉ ድምጽ መወሰኑ ተገለጸ።
ምክር ቤቱ ዛሬ [ቅዳሜ] ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባው ላይ በትግራይ ክልል የሚካሄደውን የምርጫ እንቅስቃሴን በተመለከተ የሕገ መንግሥት ትርጉምና የማንነት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበለት የውሳኔ ሐሳብ ላይ መወያየቱ ተገልጿል። በዚህም መሠረት የትግራይ ክልል ምርጫን በሚመለከት ያሳለፈው ውሳኔ፣ እንዲሁም እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ከአገሪቱ የበላይ ሕግ ጋር የሚቃረን በመሆኑ ተፈጻሚነት እንደሌለው ገልጿል። በዚህም ምክር ቤቱ በቀረበለት የውሳኔ ሐሳብ መሰረት በትግራይ ክልል ምርጫ ለማካሄድ የሚደረገው እንቅስቃሴ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 9(1) መሰረት እንዳልተደረገ የሚቆጠር፣ የማይጸናና ተፈፃሚነት የሌለው ነው በማለት፣ ተቀባይነት የለውም ብሏል። በምክር ቤቱ ስብሰባ ላይ "ሕገ ወጥ አካላት በሚፈፅሙት ድርጊት ምክንያት በሕዝቡ ላይ ጉዳት ሊደርስበት አይገባም ብሎ የሚያምን መሆኑና በቀጣይም ምክር ቤቱ ለትግራይ ሕዝብ ካለው ውግንና አንጻር ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዳት እንዳይደረስ ችግሮችን በሰላማዊና ሕጋዊ መንገድ ለመፍታት እየተደረገ ያለው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት መግባባት ላይ ተደርሷል" ብሏል። በኢትዮጵያ በዚህ ዓመት ሊካሄድ ዕቅድ ተይዞለት የነበረው ምርጫ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ መከሰቱን ተከትሎ ምርጫውን ለማካሄድ የሚያስችል አመቺ ሁኔታ የለም በማለት የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባቀረበው ጥያቄ መሰረት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የፌዴሬሽን ምክር ቤት ምርጫው ለሌላ ጊዜ እንዲተላለፍ መወሰናቸው ይታወሳል። በዚህም የፌደራልና የክልል ምክር ቤቶች ቀጣዩ ምርጫ እስኪካሄድ ድረስ በሥራቸው ላይ እንዲቆዩ ተወስኖ የነበረ ቢሆንም የትግራይ ክልል በተናጠል ምርጫውን እንደሚያካሂድ አሳውቆ የተለያዩ ተግባራት ሲያከናውን ቆይቷል። ክልሉ ምርጫውን እንዲያስፈጽምለት ብሔራዊውን የምርጫ ቦርድ ጠይቆ የነበረ ቢሆንም፣ ቦርዱ በተናጠል ምርጫውን ለማካሄድ የቀረበውን ጥያቄ ባለመቀበሉ፤ የትግራይ ክልል የራሱን የምርጫ ኮሚሽን አቋቁሞ የምርጫ ዝግጅት በማድረግ ድምጽ ለመስጠት ቀናት ብቻ ቀርተውታል። ምርጫን በሚመለከት በፌዴሬሽን ምክር ቤት የተላለፈው ውሳኔ በመላው አገሪቱ የሚገኙ ክልሎች ተግባራዊ የማደረግ ግዴታ ቢኖርባቸውም፣ የትግራይ ክልል ከዚህ ውሳኔ ውጪ በሚቃረን ሁኔታ ምርጫ ለማካሄድ እንቅስቀሴ እያደረገ መሆኑን ለምክር ቤቱ በቀረበው የውሳኔ ሃሳብ ላይ ተጠቅሷል። የፌዴሬሽን ምክር ቤት ባካሄደው በዚህ አስቸኳይ ስብሰባው ላይ የትግራይ ክልል መንግሥት ያወጣው የምርጫ አዋጅ ከሕገ መንግሥቱ ጋር የሚቃረን መሆኑን፣ በዚህም ክልሉ የምርጫ ኮሚሽን ማቋቋሙ ሕገ መንግሥቱ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሰጠውን ስልጣን እንደሚቃረን ገልጿል። በዚህም የትግራይ ክልል ምክር ቤት፣ አስፈፃሚ አካላት እና የምርጫ ኮሚሽን ምርጫን በሚመለከት ያወጣው የምርጫ አዋጅ የተላለፉ ውሳኔዎችና የፈፀሟቸው ተግባራት ከሕገ መንግስቱ ጋር የሚቃረኑ በመሆናቸው፣ በሕገ መንግስቱ አንቀጽ 9(1) መሰረት "እንዳልተደረጉ የሚቆጠሩ፣ የማይፀኑ እና ተፈፃሚነት የሌላቸው ናቸው" በማለት የፌዴሬሽን ምክር ቤት በሙሉ ድምጽ ውሳኔ አስተላልፏል። ከዚህ በተጨማሪ የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ፣ የራያ ራዩማ ዴሞክራሲዊ ፓርቲ እና የወልቃይት ጠገዴ ማንነት አስመላሽ ኮሚቴ ለምክር ቤቱ ያቀረቧቸውን ቅሬታዎች በመጥቀስ "የትግራይ ክልል እያካሄደ ካለው ሕገ ወጥ ምርጫ ጋር ተያይዞ በዜጎች ላይ እየደረሰ ያለው የሰብዓዊ መብት ጥሰትና በሕገ መንግሥቱ የተረጋገጡ የፖለቲካ ፓርቲዎች መብት አለማክበር ተቀባይነት የሌለውና ሊታረም የሚገባው" መሆኑን ምክር ቤቱ አመልክቷል። በትግራይ ክልል ምርጫ ለማካሄድ 2̌.7 ሚሊዮን ሰዎች መመዝገባቸውና ለምርጫው የሚያስፈልጉ ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን የክልሉ ምርጫ ኮሚሽን መግለጹ ይታወቃል። በዚህም መሰረት የድምጽ መስጫው ቀን ረቡዕ ጳጉሜን 04/2012 ዓ.ም እንደሚሆን መገለጹ ይታወሳል።
53831785
https://www.bbc.com/amharic/53831785
ጠቅላይ አቃቤ ሕግ ኬንያዊው ጋዜጠኛ ከእስር እንዲወጣ አዘዘ
ጠቅላይ አቃቤ ሕግ ኬኒያዊው ጋዜጠኛ ያሲን ጁማ በአስቸኳይ ከእስር እንዲወጣ ትዕዛዝ ሰጠ።
ያሲን ጁም ከአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ በኋላ ከአቶ ጃዋር መሐመድ መኖሪያ ቤት በቁጥጥር ሥር ከዋሉት መካከል አንዱ ነው። ከዚህ ቀደም የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ነሐሴ 1 በዋለው ችሎት ያሲን ጁማን ጨምሮ የ11 ሰዎች የዋስትና መብት ተከብሮላቸው በዋስ እንዲወጡ ብይን ሰጥቶ ነበር። ይሁን እንጂ ፖሊስ ያሲን ጁማን በሌላ የወንጀል ደርጊት ጠርጥሬያለሁ በማለቱ ያሲን ጁማ በእስር ቆይቷል። ባሳለፍነው ሳምንት ደግሞ ያሲን ጁም በፖሊስ ቁጥጥር ስር ሳለ በኮሮናቫይረስ መያዙ ተነግሯል። የያሲን ጁማ ጠበቃ የሆኑት አቶ ከድር ቡሎ ለቢቢሲ እንደተናገሩት፤ ያሲን በኮቪድ-19 በመያዙ በኢትዮጵያ የሚገኘው የኬንያ ኤምባሲ ጋዜጠኛው ተለይቶ የሚቆይበት ቦታ ሲያዘጋጅ ከእስር እንደሚወጣ ለቢቢሲ ተናግረዋል። ያሲን ጁማ ከእስር እንዲለቀቅ የጋዜጠኞች መብት ተከራካሪ ድርጅቶች ጥሪ ሲያቀርቡ ቆይተዋል። ከአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ በኋላ ከያሲን ጁማ በተጨማሪ የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትዎርክ እና የአሥራት ሚዲያ ጋዜጠኞችም በቁጥጥር ሥር ውለዋል። ከእነዚህም መካከል የኦኤምኤኑ ጋዜጠኛ መለሰም ከዚህ ቀደም የዋስትና መብቱ ተጠብቆለት ከእስር እንዲወጣ ቢወስንም ፖሊስ በሌላ የወንጀል ድርጊት ጠርጥሬዋለሁ በማለቱ ከእስር ሳይለቀቅ ቀርቷል። የአስራት ሚዲያ ጋዜጠኞች ደግሞ 'አመፅ ቀስቃሽ መልዕክት በጣቢያው ሲቀርብ ሠራተኞች ነበራችሁ' ተብለው ነው በቁጥጥር ሥር የዋሉት። በእስር ላይ የሚገኙት ጋዜጠኞቹ ሙሉጌታ አንበርብርና በላይ ማናዬ እንዲሁም የካሜራ ባለሙያው ምስጋናው ከፈለኝ ሲሆኑ ከስምንት ወር በፊት የሚዲያ ተቋሙን የለቀቀው ዮናታን ሙሉጌታም እንደሚገኝበት ከጣቢያው መስራቾች አንዱ የሆኑት አቶ ጌታቸው ሽፈራው ለቢቢሲ ገልጸው ነበር።
news-54169233
https://www.bbc.com/amharic/news-54169233
ቤተሰብ፡ የፈለጉትን ሰው ማግባት የማይፈቀድላቸው ናይጄርያውያን
ናይጄርያውኑ ጥንዶች እንዳይጋቡ ቤተሰቦቻቸው መወሰናቸውን ተከትሎ ራሳቸውን ያጠፉት በዚህ ወር መባቻ ነበር።
ቤተሰቡ ጋብቻውን አንቀበልም ያለው ከጥንዶቹ የአንደኛቸው ቤተሰብ የዘር ግንድ የሚመዘዘው በባርነት ከተሸጡ ሰዎች በመሆኑ ነበር። ጥንዶቹ ራሳቸውን ከማጥፋታቸው በፊት “ጥንታዊ አመለካከት ተመርኩዘው እንዳንጋባ ከለከሉን” ብለው ጽፈው ነበር። በ30ዎቹ መግቢያ ላይ የነበሩት ጥንዶች ቤተሰቦች የሚኖሩት ኦኪጃ በተባለች ግዛት ነው። በኦኪጃ እንደ ጎርጎሮሳውያኑ በ990ዎቹ የባርያ ንግድ ተከልክሏል። ነገር ግን የኢግቦ ማኅበረሰብ አባላት የሆኑ ከባርነት ነጻ የወጡ ግለሰብ፣ የልጅ ልጆች ከሌሎች የኢግቦ ተወላጆች ጋር ትዳር እንዲመሰርቱ አይፈቀድም። ራሳቸውን ያጠፉት ጥንዶች “ሁሉም ሰው የተፈጠረው እኩል ነው፤ ታዲያ የሰው ልጆች አንዱን ከሌላው ለምን ያበላልጣሉ?” ብለው ነበር። ብዙ የኢግቦ ጥንዶች ተመሳሳይ መድልኦ ይፈጸምባቸዋል። የ35 ዓመቷ ፌቨር ከሦሰት ዓመት በፊት ትዳር ለመመሥረት እየተዘጋጀች ነበር። ለአምስት ዓመት አብራው የነበረችው ፍቅረኛዋ ቤተሰቦች፤ የፌቨር ቅድመ አያቶች በባርነት ተሸጠው እንደነበሩ ሲያውቁ ግን ጋብቻውን ተቃወሙ። መጀመሪያ ላይ ፍቅረኛዋ ከሷ ጎን ነበር። የቤተሰቦቹ ጫና ሲበረታበት ግን ሐሳቡን ለውጦ ተለያት። ፌቨር “በጣም ከፍቶኝ ነበር። እጅግ ተጎድቻለሁ” ትላለች። “ደንቦቹን መሻር እንችላለን” የባርያ ቤተሰቦች የሚገለሉት ከትዳር ብቻ አይደለም። ከባህላዊ አስተዳደር፣ ማኅበረሰባቸውን ወክለው ለሕዝብ እንደራሴነት ከመወዳደርም ይታገዳሉ። መማር እና መሥራት ቢችሉም ከሌላው ማኅበራዊ ግንኙነት መገለላቸው ከውጪ አገራት ከመጡ የክርስትና ሰባኪዎች ጋር እንዲቀራረቡ አድርጓቸዋል። ቤተሰቦቻቸው ባርያ የነበሩ ሰዎች ምንም ያህል ስኬታማ ቢሆኑ ማኅበረሰቡ የበታች አድርጎ ይወስዳቸዋል። 2017 ላይ የ44 ዓመቷ ኦጌ ማዱግው ማኅበረሰቡ ውስጥ ያለውን ኋላ ቀር መድልኦ ለማስወገድ ማኅበር መሥርተዋል። ላለፉት ሦስት ዓመታት በደቡብ ምዕራብ ናይጄርያ አምስት ግዛቶች እየተዘዋወሩ ስለ እኩልነት ሲያስተምሩ ነበር። “አሜሪካ ውስጥ ጥቁሮች የሚደርስባቸው እንግልትና እዚህ በባርያ ቤተሰቦች ላይ የሚደርሰው ስቃይ አንድ አይነት ነው” ይላሉ። ኦጌ የባርያ ቤተሰብ ባይሆኑም መድልኦውን እያዩ ስላደጉ ማስቆም ይፈልጋሉ። በተለያዩ ግዛቶች ሲዘዋወሩ ይህን አግላይ ልማድ ለመግታት ከባህላዊ መሪዎች ጋር ተገናኝተዋል። “ሰዎች ተሰባስበው እነዚህን ደንቦች እንዳወጡት ሁሉ እኛም ተሰባስበን መሻር እንችላለን” ሲሉ ጉዟቸውን ይገልጻሉ። ኢግቦ ውስጥ የባርያ ቤተሰቦች በሁለት ይከፈላሉ። ኦሁ እና ኦሱ ይባላሉ። ቅድመ አያቶቻቸው በሰዎች የተገዙት ኦሁ፤ ቅድመ አያቶቻቸው በአማልክት የተመሩት ደግሞ ኦሱ ተብለው ይጠራሉ። በካሊፎርንያ የአፍሪካ ጥናት መምህሩ ኦጎ ንዌክጂ “ኦሱ ከባርነትም የከፋ ነው” ይላሉ። ኦጎ እንደሚያስረዱት፤ ባርያዎች ከባርነት ቀንበር መላቀቅ ቢችሉም ኦሱ በሚል ለሚመደቡ ሰዎች ግን ይህ አይሠራም። ለልጅ ልጆቻቸውም ይሸጋገራል። ኦሱዎች ላይ የሚደርሰው መገለል ከኦሁ የባሰ ነው። ኦሁዎች የሚገለሉት በማኅበራዊ የተዛባ አመለካከት ነው። በሌላ በኩል ኦሱዎችን አለማግለል በአማልክት ያስቀጣል ተብሎ ይታመናል። ፌቨር ልታገባው የነበረው ግለሰብ ቤተሰቦች “ኦሱ ካገባህ ትሞታለህ” ብለው አስፈራርተውት ነበር። እሱም “እንድሞት ትፈልጊያለሽ?” ብሏት እንደነበር ታስታውሳለች። ሕጉን ማስፈጸም አልተቻለም የማኅበረሰቡ ፍርሀት መድልኦን የሚቀርፍ ሕግ እንዳይተገበር ምክንያት ሆኗል። 1956 ላይ ኦሁዎች አና ኦሱዎች እንዳይገለሉ በኢግቦ ሕግ አውጪዎች ቢደነገግም ማስፈጸሙ ከባድ ነው። የካቶሊክ ቄስ አንቶኒ ኦቢና “አንዳንድ ጥንታዊ ልማዶችን ለማስቀረት ሕገ መንግሥት በቂ አይደለም። ሥር ነቀል ለውጥ ያስፈልጋል” ይላሉ። ኦጎ ሲያስተምሩ ኦሱዎችን በተመለከተ ያሉ ልማዶች ስለሚቀረፉበት መንገድ ይጠቁማሉ። በመቶዎች በሚቆጠሩ በጎ ፍቃደኞች የሚከናወነው ሥራቸው ቀላል አይደለም። ቢሆንም በየማኅበረሰቡ ያሉ ባህላዊ መሪዎች እኩልነትን እንዲያሰፍኑ የማሳመን ጥረታቸውን እንደቀጠሉ ነው። ትግላቸውን የሚደግፉ እንዳሉ ሁሉ “ባህላችንን አንቀይርም” ብለው የሚቃወሟቸውም እንዳሉ ኦጎ ያስረዳሉ። በደቡብ ምዕራብ ናይጄሪያ ምን ያህል የባርያ ቤተሰቦች እንዳሉ መረጃ የለም። ባለው መድልኦ ሳቢያ ግጭቶች የሚቀሰቀሱባቸው ቦታዎች አሉ። አንዳንድ የባርያ ቤተሰቦች የራሳቸው ማኅበርና አስተዳደር ፈጥረዋል። ለምሳሌ ከ13 ዓመት በፊት በሊሞ ግዛት ኦሱዎች ‘ኒንጂ’ ወይም ከአንድ ማህጸን የተባለ ቡድን ተቋቁሟል። የቡድኑ አባላት መካከል ትዳር ይመሠረታል። ከሀብታም ኦሱዎች የተወለደችው ኦግዲማ “ሰዎች ካንቺ ጥቅም ሲፈልጉ ይመጡና ከኦሱ ጋር ትዳር አንመሠርትም ይላሉ” ትላለች። ከአሥር ዓመት በፊት የምክር ቤት መቀመጫ ለማግኘት ስትወዳደር መገለል እንደገጠማት ታስታውሳለች። እሷን በመቃወም ፊርማ ሲሰባሰብ ነበር። የዩርባ ተወላጅ የሆኑት የፓርቲዋ መሪም ሊደግፏት አልቻሉም። በዮሩባ እና ሀውሳ ማኅበረሰቦች የባርያ ቤተሰቦችን ማግለል የተለመደ አይደለም። እንደ ማሊና ሴኔጋል ባሉ አገሮች ግን መድልዎ ይስተዋላል። ቄስ አንቶኒ እንደሚናገሩት፤ አንዳንድ ከባርያ ቤተሰብ ልጆች ጋር የተጋቡ ሰዎች ጥቃት እንዳይደርስባቸው ተከላክለዋል። የኖሊውድ ሚና አመለካከቱ እንደ ቺንዋ አቼቤ ባሉ አፍሪካውያን ደራሲያን ሥራዎችም እንደሚንጸባረቅ ኦግዲማ ታምናለች። ‘ቲንግስ ፎል አፓርት’ የመሰሉ መጻሕፍትን የሚያነቡ ናይጄርያውያን ወጣቶች ስለ ኦሱዎች ምን አይነት አመለካከት ሊኖራቸው እንደሚችል ትጠይቃለች። በኢንጉ ግዛት ቄስ የሆኑት አሎይሰስ አግቦ የኖሊውድ ፊልሞች ተጽዕኖ ያሳድራሉ ብለው ያምናሉ። “መሠረተ ቢስ ብለን ችላ ያልናቸው አመለካከቶች አሁን እውነት መስለው በቴሌቭዥን መርሀ ግብሮች እየመጡ ነው። ባህላችንን እያሳዩ ይመስላቸዋል። ማኅበረሰቡ ላይ የሚያሳድረውን ጫና አያስቡም” ይላሉ። እንደ ‘ብላክ ላይቭስ ማተር’ አይነት ለጥቁሮች መብት የሚሟገቱ ንቅናቄዎች የሰውን አመለካከት ይቀይራል ብላ ኦግዲማ ተስፋ ታደርጋለች። ሁለት ኃይማኖት አንድ ትዳር!
50640404
https://www.bbc.com/amharic/50640404
ከኢትዮጵያ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ እስከ አውስትራሊያ ሰደድ እሳት
በምስራቅ አፍሪካ ቆፈናም ማለዳ፣ አልቃሻ ተሲያት፣ ጨፍጋጋ ምሽት የሰሞኑ ክስተቶች ናቸው። በኢትዮጵያም ወቅቱን ካልጠበቀ ዝናብ ሰብሎችን ለመታደግ እዚህም እዚያም ርብርብ ተደረገ ሲባል እንሰማለን።
በሕንድ ውቅያኖስ የዲፖሌ ክስተት ባለፉት 60 ዓመታት ከታየው ከፍ ያለ መሆኑን ተመራማሪዎች ይናገራሉ የምስራቅ አፍሪካ ሰማይ ዝናብ አርግዟል፤ ያለማቋረጥ ይዘንባል። በዚህም የተነሳ በሶማሊያ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል፤ በደቡብ ሱዳን ከተሞች ሙሉ በሙሉ በውሃ ተውጠዋል። • የአየር ጸባይ ለውጥ ላይ የሚመክረው ስብሰባ ምን ይዞ ይሆን? በኢትዮጵያ፣ ኬኒያና ታንዛኒያ እና ሌሎች ጎረቤት ሀገራት ያለማቋረጥ የጣለ ዝናብ ባስከተለው ጎርፍ የመሬት መንሸራተት ተከስቶ እስካሁን ድረስ በአጠቃላይ 250 ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል። ተመራማሪዎች ቀጠናው በዚህ ዓመት ከባድ ዝናብ አስተናግዷል ይላሉ። ይህም ሊሆን የቻለው በሚቲዎሮሎጂካል ክስተቶች መሆኑን በመናገርም ለዚህም ምክንያቱ የሕንድ ውቅያኖስ ዲፖሌ ነው ሲሉ ያስረዳሉ። ግን ይህ ሳይንቲስቶች ስም ጠቅሰው፣ ማስረጃ ነቅሰው ኢንዲያን ዲፖሌ ያሉት ነገር ምንድን ነው? ሶስት ነገሮችን ከእነርሱ ማስረጃ ውስጥ መዝዘናል። 1.የሕንድ ውቅያኖስ ዲፖሌ ምንድን ነው? የሕንድ ውቅያኖስ ዲፖሌ (IOD) ሚቲዮሮሎጂካዊ ክስተት ሲሆን ውቅያኖሱን በሚጎራበቱና በምድር ወገብ አቅራቢያ ባሉ ሀገራት የዝናብ ስልትን ይቀይራል። ይህም ከምስራቅ አፍሪካ እስከ ኢንዶኔዢያ ድረስ የተለጠጠ ሲሆን የአየር ጠባዩ እስከ አውስትራሊያ ድረስ ርቆ ይስተዋላል። አይ ኦዲ ፖዘቲቭ ሲሆን በሕንድ ውቅያኖስ በስተምዕራብ ያለ ውሃ ይሞቃል። ይህም ከምስራቅ አፍሪካ ራቅ ብሎ መሆኑ ነው፤ ይህ ከተለመደው በላይ የውቅያኖስ መሞቅ ከፍተኛ ትነት እንዲከሰትና ከባድ ዝናብ እንዲከሰት ሰበብ ይሆናል። • ለ12 ቀናት በሰዋራ ሥፍራ የቆዩት አውስትራሊያዊት በሕይወት ተገኙ ይህ በእንዲህ አንዳለ በሕንድ ውቅያኖስ በስተምስራቅ ያለ ውሃ፣ ከጃቫ እና ሱማትራ ባህር ዳርቻ ራቅ ብሎ፣ ከተለመደው ጊዜ በተለየ ይቀዘቅዛል። ይህ ደግሞ በተቃራኒው ተጽዕኖ ይፈጥራል። አንድሪው ተርነር በዩኬ በሚገኘው ሬዲንግ ዩኒቨርስቲ የዘርፉ ባለሙያ ናቸው፤ ለቢቢሲ ሲያስረዱ "ሕንድ ውቅያኖስ ዲፖሌ ሲከሰት፣ የዝናብ መጠኑ ከውሃው መሞቅ ጋር ይሄዳል፤ ስለዚህ በምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ከተለመደው ከፍ ያለ ዝናብ ያገኛሉ ማለት ነው" " በሌላ በኩል ደግሞ በምስራቅ ህንድ ውቅያኖስ፣ የባህር ወለል የሙቀት መጠን ከተለመደው በላይ ቀዝቃዛ ስለሚሆን አካባቢው ከተለመደው ያነሰ የዝናብ መጠን ያገኛል" ብለዋል። የሕንድ ውቅያኖስ ዲፖሌ በፓስፊክ ውቅያኖስ ላይ ከሚከሰተው ኤልኒኖ ጋር ተነጻጻሪ ነው፤ ለዚህም አንዳንዴ የሕንድ ኒኖ በመባል ይታወቃል፤ ነገር ግን አንደ ኤልኒኖ ተጽዕኖው የገዘፈ አይደለም። 2. የሕንድ ውቅያኖስ ዲፖሌ እ.ኤ.አ. በ2019 አየል ብሎ ታይቷል ካለፉት 60 ዓመታት በተለየ ሁኔታ ፖዘቲቭ አይኦዲ ጠንክሮ ታይቷል። ኔጋቲቭ የሆነው ሲመጣ ደግሞ ውሃው በምስራቃዊ አፍሪካ ዳርቻዎች ከተለመደው በላይ መቀዝቀዝ፣ በኢንዶኔዢያ አካባቢ ደግሞ መሞቅ ይጀምራል። የኬኒያዋ ምዕራብ ፖኮት ግዛት በመሬት መንሸራተትና በጎርፍ ከተመታች በኋላ ለማገገም እየጣረች ትገኛለች።፣ በመቶዎች የሚቆጠሩ ቤቶች ጎርፍ ይዟቸው ሄዷል። በግዛቲቱ የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከ50 በላይ እንደሚሆን ተነግሯል። • “ኦዲፒ ዋጋ የተከፈለባቸውን ጥያቄዎች ወደ ጎን መተው አይገባውም” ፕ/ር መረራ ጉዲና እንደ ዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል መረጃ ከሆነ በደቡብ ሱዳን ከ600 ሺህ በላይ ሰዎች በጎርፍ ምክንያት የመኖሪያ ቀያቸውን ለቅቀው እንዲሰደዱ ሲሆኑ፣ ይህ እጣ የ273 ሺህ ሶማሊያውያንም ነበር። በሌላ በኩል አውስትራሊያ ደግሞ ለሌላ ድርቅ እና ሰደድ እሳት እየተዘጋጀች ነው። ይህም ሕዳር ጀምሮ እስከ የካቲት ይቀጥላል ተብሏል። ነገር ግን ሞቃታማው አየር አስቀድሞ የሰደድ እሳት እንዲከሰት ያደረገ ሲሆን በዚህም የተነሳ 4 ሰዎች ሲሞቱ ከ500 በላይ ቤቶች ተቃጥለዋል። የአውስትራሊያ የረዥም ጊዜ አየር ጠባይ ትንበያ ባለሙያ የሆኑት አንድሪው ዋትኪንስ እንደሚሉት ከሆነ "በአሁን ሰአት ያለውና ተጠባቂው ሁኔታ የሚያሳየን እስካሁን ድረስ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ጠንካራ የሆነ ፖዘቲቭ ዲፖሌ መመዝገቡን ነው" ነገር ግን ይህ የአየር ጠባይ ድርቅ እያመጣ ይሆን ብላ በስጋት ከምትጨነቀው ህንድ ፊት ስጋቷን ገለል ያደረገ ነው። ለዚህ ደግሞ ምክንያቱ በተወሰኑ ሀገሪቱ ክፍል በዚህ አየር ጠባይ ምክንያት የምታገኘው የዝናብ መጠን ከፍ ስለሚል ነው። 3. የዓለም ሙቀት መጨመር የሕንድ ውቅያኖስ ዲፖሌ ክስተቶችን ቶሎ ቶሎ እንዲመጡ ያደርጋል ዶ/ር ተርነር እንደሚሉት ከሆነ በአይኦዲ ምክንያት የሚከሰቱ ከባድ የአየር ንብረት ጠባይ ለውጦች የግሪን ሀውስ ልቀት በጨመረ ቁጥር በተደጋጋሚ የመከሰት ፍጥነታቸው እንደሚቀጥል ይናገራሉ። " በህንድ ውቅያኖስ ምዕራብ የሚገኙ የአፍሪካ ሀገራት በተደጋጋሚ እንዲህ አይነት አየር ጠባይ እንደሚመለከቱ፣ ጎርፍና ከባድ ዝናብ ደግሞ የተለመደ ይሆናል። ዝናቡ በሰብል ላይ ጥፋት ያደርሳል፤ ጎርፉ መሰረተ ልማት ያወድማል" ይላሉ። • መሬት መንሸራተትና ጎርፍ በደቡብ ኢትዮጵያ ጥፋት አደረሰ " በሌላ በኩል ደግሞ በምስራቅ ህንድ ውቅያኖስ የሚገኙት ሀገራት፣ በኢንዶኔዢያ ምዕራብ የሚገኙ ደሴቶች የዝናብ መጠን በመቀነሱ ምክንያት ድርቅ ሊመዘገብባቸው ይችላል።"
news-56417952
https://www.bbc.com/amharic/news-56417952
"የተፈጸመው ጥቃት አደገኛና ከባድ ወንጀል ነው" የአማራ ክልል
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙት በሰሜን ሸዋ ዞን አጣዬና በክልሉ የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ጅሌ ጥሙጋ አካባቢዎች በንጹሐን ላይ የተፈጸመው ጥቃት አደገኛና ከባድ ወንጀል ነው ሲል የክልሉ መስተዳደር ገለጸ።
የአማራ ክልል መስተዳደር ክስተቱን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ በጥቃቱ የሰዎች ህይወት መጥፋቱንና ንብረት መውደሙን ጠቁሞ "በንጹሐን ላይ የተፈፀሙው ይህ ጥቃት በፍጹም ተቀባይነት የሌለው አደገኛና ከባድ ወንጀል ነው" ብሏል። ባለፈው አርብ ምሽት ከሦስት ሰዓት ጀምሮ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን፤ ኤፍራታና ግድም ወረዳና አጣዬ ከተማ ውስጥ በታጣቂዎች በተፈጸመ ጥቃት የሰላማዊ ሰዎች ሕይወት ማለፉን ነዋሪዎችና የአካባቢው ባለሥልጣን ለቢቢሲ ገልጸው ነበር። የኤፍራታና ግድም ወረዳ የሠላምና የሕዝብ ደኅንነት ጽ/ቤት ኃላፊ እንዲሁም ምክትል አስተዳዳሪ የሆኑት አቶ ሰለሞን አልታየ እስከ ቅዳሜ ረፋድ ድረስ የአራት ሰዎች ሕይወት ማለፉን መመልከታቸውን የተናገሩ ሲሆን፤ ከዚያ በኋላ ከአካባቢው የሚወጡ መረጃዎች የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከዚህም ከፍ እንደሚል እያመለከቱ ነው። የክልሉ አስተዳደር ባወጣው መግለጫ ላይ እንዳመለከተው ለተፈጠረው ግጭት ምክንያቱ ሐሙስ መጋቢት 9/2013 ዓ.ም ምሽት "ጅሌ ጥሙጋ ውስጥ በግለሰቦች መካከል በተፈጠረ ጠብ ምክንያት አንድ ሰው ህይወት መጥፋት" ለው ብሏል። ይህንንም ተከትሎ በአገር ሽማግሌዎችና በሐይማኖት አባቶች አማካይነት እርቅ ተፈጽሞ እንደነበር ጠቅሶ ነገር ግን "የኦነግ ቡድንና እሱን መሰል ተባባሪ የሆኑ አካላት እርቀ ሰላም ወርዶ መፍትሔ ያገኘውን ክስተት ምክንያት በማድረግ" ጥቃቱ መፈጸሙን ገልጿል። በዚህም ከአርብ መጋቢት 10/2013 ዓ.ም ጀምሮ "አርሶ አደር ይይዘዋል ተብሎ በማይጠበቅ ከባድና የቡድን መሣሪያ በመታገዝ የተደራጀና ብዛት ያለው የታጠቀ ኃይል በአጎራባቹ የሰሜን ሸዋ ዞን አጣየ ከተማና አካባቢው ሰላማዊ ዜጎች ላይ ነውረኛ የሆነ ጥቃት ተፈጽሟል" ብሏል። ክልሉ እሁድ እለት ባወጣው መግለጫ ላይ ግን በክስተቱ ጉዳት የደረሰባቸውን ሰዎች መጠን አልገለጸም። ጥቃቱ በአጣዬ ከተማ ዙሪያ ቀበሌ 01፣ 02 እና 03 እንዲሁም በኤፍራታና ግድም ወረዳ በሚገኙ አላላ እና ማጀቴ ቀበሌዎች አርብ ምሽት መጀመሩንና የከተማው ነዋሪ ላይ ከባድ ድንጋጤን ፈጥሮ እንደነበር ቢቢሲ ያናገራቸው የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል። በአካባቢው ከባድ የተኩስ ድምጽ መሰማት የጀመረው ቀደም ብለው ከነበሩት ቀናት ጀምሮ እንደነበር የአካባቢው ነዋሪዎችና ኃላፊው ለቢቢሲ ገልጸው፤ ነገር ግን ይህ ሁኔታ ከሠርግና ከሌሎች ባላህላዊ ሥነ ሥርዓቶች ጋር የተያያዘ ሊሆን እንደሚችል በማሰብ ችላ ተብሎ መቆየቱን አስረድተዋል። አርብ ምሽት የነበረው ተኩስ ግን ከነፍስ ወከፍ የጦር መሳሪያ ከፍ ያለና ከባድ እንደነበር ምክትል አስተዳዳሪው አቶ ሰለሞን አልታየ ገልጸው፤ የተከፈተውን ተኩስ ተከትሎ የአጣዬ ከተማ 01 ቀበሌ "ሙሉ በሙሉ በታጣቂዎቹ መያዙን" ለቢቢሲ ተናግረው ነበረ። ጥቃቱን ለመከላከል በወረዳው ባለው የፀጥታ ኃይል በኩል ሙከተራ ተደርጎ ከአቅማቸው በላይ በመሆኑ ለሚመለከታቸው የበላይ አካላት ቢያሳውቁም፤ አሁን የደረሰውን ጉዳት ቀድሞ መቆጣጠር አለመቻሉን ተስፋ በመቁረጥ ስሜት ለቢቢሲ ተናግረዋል። የተከሰተውን የጸጥታ ችግር ተከትሎም ከክልሉና ከፌደራል መንግሥት ተጨማሪ ኃይል ተጠይቆ ወደ አካባቢው መግባቱን ነዋሪዎችና ኃላፊው ገልጸዋል። የክልሉ መንግሥትም በመግለጫው "በንጹሃን ላይ እየፈፀመ ያለውን ጥቃት ለማስቆም ጥቃቱ ከጀመረበት ሰዓት ጀምሮ ከፌዴራል መንግሥት ጋር በመሆን ተጨማሪ የፀጥታ አካላትን ወደ ሥፍራው በማሰማራት ጥቃቱን ለመቆጣጠርና ንጹሐን ዜጎችን ለመታደግ አስፈላጊውን ሁሉ እየሠራ ይገኛል" ብሏል። ጥቃቱን የፈጸሙት ታጣቂዎች በከባድና በዘመናዊ መሳሪያ የተደገፉ መሆናቸውን አቶ ሰለሞን ገልጸው፤ "ለደኅንነቱ ስጋት ያደረበት ነዋሪ ሊደርስ ከሚችል ጉዳት ለመሸሽ ከተማውን ለቆ እየወጣ ነው" ሲሉ ቅዳሜ ዕለት ተናገረው ነበር። ያነጋገርናቸው ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የማጀቴ ነዋሪዎችም ከአርብ ሌሊት ከ6:00 ጀምሮ ቢቢሲ ነዋሪዎችን እሰካናገረበት ቅዳሜ እኩለ ቀን ድረስ ተኩስ እንዳለ የገለጹ ሲሆን፤ በስልክ በተደረገው በቃለ ምልልስ ወቅትም ከጀርባ የተኩስ ድምጽ ይሰማ ነበር። ጥቃቱን ተከትሎ በአካባቢው የስልክ ኔትወርክ ተቋርጦ እንደነበር የሚገልጹት ነዋሪዎች፤ ይህም መረጃ እንዳይለዋወጡ እንዳደረጋቸው ገልፀዋል። ጥቃቱን በማን እንደተፈጸመ በግልጽ የታወቀ ነገር ባይኖርም የአካባቢው አስተዳደርና ነዋሪዎች የችግሩ ፈጣሪና ጥቃት ፈጻሚው 'ኦነግ ሸኔ' ነው ይላሉ። የክልሉ መንግሥትም በመግለጫው ጥቃቱ የተፈጸመው "የኦነግ ቡድንና እሱን መሰል ተባባሪ" ባላቸው ኃይሎች መሆኑን ገልጾ፤ "በንጹሐን ላይ የፈፀሙት ጥቃት በፍጹም ተቀባይነት የሌለው አደገኛና ከባድ ወንጀል ነው" ብሏል። ጨምሮም በአጣየና በአካባቢው የተፈጸመውን ዝርዝር ጥቃት እንዲሁም የደረሰውን ሰብአዊና የንብረት ጉዳት መንግሥት በፍጥነት መረጃውን አጣርቶ ለሕዝቡ ይፋ የሚያደርግ ገልጿል። በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ውስጥ የሚገኘው ኤፍራታና ግድም ወረዳ በክልሉ ውስጥ ካለው የኦሮሞ ብሔረሰብ ልዩ ዞን ጋር ይዋሰናል። ከዚህ ቀደምም በተለያዩ ጊዜያት በወረዳው ውስጥ በሚገኙ አካባቢዎች በተፈጸሙ ጥቃቶችና ግጭቶች በሰውና በንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን ቢቢሲ ያናገራቸው የማጀቴ ከተማ ነዋሪ አስታውሰዋል።
news-53231191
https://www.bbc.com/amharic/news-53231191
ሕንድ አዲስ የኮሮና ክትባትን በሰው ላይ ልትሞክር ነው
በአገራቸው በምርምር ላይ የቆየውን የመጀመሪያው ክትባት ፍቃደኛ በሆኑ ሕንዳዊያን ላይ ከቀናት በኋላ ሙከራ ማድረግ እንደሚጀመር ተገለጸ።
ቁጥራቸው ምን ያህል እንደሆኑ ያልተገለጹት እኒህ ሕንዳዊያን ክትባቱ የሚሰጣቸው በሐይድራባድ በሚገኝ ባራት ባዮቴክ በተሰኘ የጥናት ድርጅት ነው። ክትባቱ በእንሰሳት ላይ በተደረገ ሙከራ ምንም የጎንዮሽ ጉዳት ያላስከተሉ ከመሆኑ በላይ የተፈጥሮ በሽታን የመከላከያ ኃይል ቫይረሱን የሚከላከሉ ህዋሶችን እንዲያመርት አስችሎታል። በመላው ዓለም በቤተ ሙከራ ደረጃ ያሉ 120 የክትባት ምርምሮች ሲኖሩ ከነዚህ ውስጥ ስድስቱ በሕንድ ነው እየተካሄዱ የሚገኙት። ይህ ክትባት የሚመረተው ከራሱ ከኮቪድ-19 ሲሆን ቫይረሱ በቤተ ሙከራ ውስጥ ተዳክሞና መጠኑ ቀንሶ ነው ወደ ክትባትነት የሚለወጠው። የሕንድ የመድኃኒት ቁጥጥር አስተዳደር ለባራት ባዮቴክ ምርምር ተቋም የምዕራፍ አንድና ምዕራፍ ሁለት ሙከራዎችን በሰው ላይ እንዲያደርግ የፈቀደው በእንሰሳት ላይ የተደረገው ሙከራ አመርቂ ውጤት ማስገኘቱን ከመረመረ በኋላ ነው። እነዚህ ሁለት ምዕራፎች የተከፈሉ ሙከራዎች ትኩረት የሚያደርጉት የክትባቱ ፈዋሽነት ላይ ሳይሆን ክትባቱ በሰው ልጅ ላይ ጉዳት ያስከትላል ወይስ አያስከትልም በሚለው ላይ ነው። አዲሱ ሕንድ የሰራችው ክትባት ኮቫክሲን የሚል ስም የተሰጠው ሲሆን በቤተ ሙከራ የተዘጋጀው ደግ ከብሔራዊ የሕንድ ቫይሮሎጂ ኢንስቲትዩትና ከካውንስል ኦፍ ሜዲካል ሪሰርች ጋር በመተባበር ነው። ይህ ተቋም ከዚህ ቀደም ኤችዋን ኤንዋን ለተሰኘ ቫይረስ 4 ቢሊዮን ጠብታ ክትባት በመላው ዓለም አምርቶ ያሰራጨ ነው። ሕንድ የዓለም ትልቋ የመድኃኒት አምራች አገር ናት።
news-53517112
https://www.bbc.com/amharic/news-53517112
ከሰሀራ በታች አፍሪካ ውስጥ ከ10 ሺህ በላይ የጤና ባለሙያዎች በኮሮናቫይረስ ተይዘዋል ተባለ
የዓለም ጤና ድርጅት ከሰሀራ በታች ባሉ አገራት ውስጥ ከ10 ሺህ በላይ የጤና ባለሙያዎች በኮቪድ-19 ወረርሽኝ መያዛቸውን አስታወቀ።
ድርጅቱ እንዳለው ወረርሽኙ በከፍተኛ ሁኔታ እየተሰራጨ ያለው የጤና ባለሙያዎች የደኅንት መጠበቂያ መገልገያዎችና አልባሳት (ፒፒኢ) በበቂ ሁኔታ ስላልተሟላላቸው ነው። የዓለም ጤና ድርጅት ጨምሮም አፍሪካ ውስጥ በኮሮናቫይረስ የሚያዙ የጤና ባለሙያዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱ በጣም እንዳሳሰበው ገልጿል። በዓለም አቀፍ ደረጃ በበሽታው ከተያዙ ሰዎች መካከል የህክምና ባለሙያዎች አስር በመቶውን ይይዛሉ። በዚህም ሳቢያ የጤና ባለሙያዎች ለአካላዊ እንዲሁም ለሥነ ልቦናዊ ጉዳትም መጋለጣቸው ተነግሯል። በከፍተኛ ሁኔታ የጤና ባለሙያዎች ለበሽታው የተጋለጡባቸው የአፍሪካ አገራት ደቡብ አፍሪካ፣ አልጄሪያ፣ ጋና፣ አይቮሪ ኮስት፣ ካሜሩን፣ ዛምቢያ እና ኬንያ መሆናቸውን ድርጅቱ አመልክቷል። ለወረርሽኙ በዋነኛነት እየተጋለጡ የሚገኙት ነርሶች መሆናቸው የተቀሰው ድርጅቱ፤ እነዚህ የጤና ባለሙያዎች ለሰዓታት ለህሙማን የህክምና ድጋፍ ይሰጣሉ ብሏል። የዓለም ጤና ድርጅት እንዳለው፤ ከደኅንት መጠበቂያ መገልገያዎች አልባሳት (ፒፒኢ) እጥረት በተጨማሪ ሆስፒታሎች በተገቢው ሁኔታ የጥንቃቄ እርምጃ አለመውሰዳቸው የጤና ባለሙያዎችን ለቫይረሱ ተጋላጭ አድርጓል። ባለሙያዎቹ ተገቢውን ስልጠና ሳያገኙ በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎችን እንዲያክሙ እንደሚደረጉም ድርጅቱ ተናግሯል። በአህጉሪቱ እስካሁን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 700 ሺህ በላይ የደረሰ ሲሆን ከ16 ሺህ የሚበልጡ ሰዎች ደግሞ በበሽታው ሳቢያ ሕይወታቸውን አጥተዋል።
news-50905757
https://www.bbc.com/amharic/news-50905757
ፈረንሳይ ኩሽና ውስጥ ተሰቅሎ የተገኘው ሥዕል ብሔራዊ ሐብት ነው አለች
በአንዲት ፈረንሳዊት አዛውንት ኩሽና ውስጥ የተገኘው ጥንታዊ ስዕል የሥነጥበብ ባለሙያዎችን ሲያስደንቅ ቆይቶ አሁን ላይ የፈረንሳይ መንግሥት ብሔራዊ ቅርስ ነው በማለት ወደ ሌላ ሃገር እንዳይላክ እገዳ ጥሏል።
ሥዕሉ ለበርካታ ዓመታት በኩሽና ውስጥ ከማብሰያ ምድጃ በላይ ግድግዳ ላይ ተንጠልጥሎ ቆይቷል። በእውቅ ጣሊያናዊ ሰዓሊ ተስሎ የነበረው እና ለረዥም ዓመታት ጠፍቶ የቆየው ይህ ሥዕል በአንዲት አዛውንት ፈረንሳዊት ሴት ኩሽና ውስጥ ከተገኘ በኋላ ሪከርድ በሆነ በ24 ሚሊዮን ዩሮ ዋጋ በጨረታ መሸጡ ይታወሳል። ይህ የሥዕል ሥራ ከሁለት ወራት በፊት ነበር በሰሜናዊ ፈረንሳይ ነበር የተገኘው። 24 ሚሊዮን ዩሮ ከፍሎ የገዛው አካል ማን እንደሆነ በአጫራቾቹ በይፋ ባይነገርም፤ የፈረንሳይ መገናኛ ብዙሃን ግን ሥዕሉን የገዙት የጣሊያን የጥንት የሥዕል ሥራዎችን በመሰበሰብ የሚታወቁ ነዋሪነታቸው በአሜሪካ የሆኑ ሁለት የቺሊ ዜጎች መሆናቸውን ዘግበዋል። የፈረንሳይ መንግሥት ይህን የሥዕል ሥራ መልሶ ከግለሰቦች እጅ ለመግዛት የሚያስፈልገውን ገንዘብ ምንጭ እስኪያገኝ ድረስ ለ30 ወራት ሥዕሉ ከሃገር እንዳይወጣ ወስኗል። ሥዕሉ ለበርካታ ዓመታት በኩሽና ውስጥ ከማብሰያ ምድጃ በላይ ግድግዳ ላይ ተንጠልጥሎ ቆይቷል። አንድ የሥዕል ባለሙያ እና አጫራች ሥዕሉን ከተመለከተ በኋላ ባለቤቶቹ የሥዕሉን ዋጋ ለማስተመን ባለሙያዎችን እንዲያማክሩ ሲወተውት ነበር ተብሏል። ባለቤቶቹ ግን ሥዕሉ እድሜ ጠገብ ሃይማኖታዊ ምልክት ያለው ሥዕል ከመሆን ባለፈ ብዙ ዋጋ ያለው የጥበብ ሥራ መስሎ አልታያቸውም። በሥዕሉ ላይ የተደረጉ ጥልቅ ምርምሮች ሥዕሉ የጣሊያናዊው ሰዓሊ ሶኒ ዲ ፔፖ መሆኑን አረጋግጠዋል። በጣሊያን ፍሎረንስ የተወለደው ሶኒ ዲ ፔፖ በ13ኛው ክፈለ ዘመን መጨረሻ ላይ እና በ14ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ የሥዕል ሥራዎችን ሰርቷል። ይህ የጥበብ ሥራ በመጠን አነስተኛ ሲሆን 20 ሲ.ሜትር በ26 ሴንቲ ሜትር ያክላል። ሥዕሉ የአንድ የሥዕል ሥራ አካል ሲሆን የተቀሩት ሥዕሎች ሎንደን እና ኒው ዮርክ በሚገኙ የሥዕል ማሳያ ማዕከል ውስጥ ይገኛሉ።
news-54187169
https://www.bbc.com/amharic/news-54187169
የዝነኛዋ የጥቁር መብት ታጋይ ጀግኒት ሮዛ ፓርክስ መኖርያ ቤት ለዕይታ ቀረበ
በ1950ዎቹ እና 60ዎቹ በአሜሪካ የጥቁር መብት ተጋድሎ ውስጥ ስሟ ከፍ ብሎ የሚነሳው የጀግኒት ሮዛ ፓርክስ መኖርያ ቤት በጣሊያን ኔፕልስ ሮያል ፓላስ ውስጥ ለዕይታ ቀርቧል፡፡
ጀግኒት ሮዛ ፓርክስ በአለባማ ግዛት በ1955 ከሥራ ወደ ቤቷ አውቶቡስ ተሳፍራ ስትመለስ ለነጭ ወንበሯን እንድትለቅ ስትጠየቅ እምቢኝ በማለቷ ታሪክ መሥራት ችላለች፡፡ ከዚህ እምቢተኝነቷ በኋላ ከአክራሪ የነጭ አሜሪካዊያን የሞት ዛቻ ስለደረሳት መኖርያዋን ከመንገመሪ ወደ ሰሜናዊ አሜሪካ ሚቺጋን፣ ዲትሮይት አዘዋውራ ነበር፡፡ በዲትሮይት ከዘመዶቿ ጋር ትኖርበት የነበረው አነስተኛ የእንጨት/ ጣውላ ቤት ነበር፡፡ ይህ ሮዛ ፓርክስ የኖረችበት ቤት ከብዙ የሕግ ሙግት በኋላ ከአሜሪካ ወደ ጣሊያን ተዛውሮ ነው አሁን ለሕዝብ በመታየት ላይ ያለው፡፡ የአሜሪካ ኮንግረስ ጀግኒት ሮዛ ፓርክስን ‹‹የጥቁሮች መብት ቀዳማዊት እመቤት›› ሲል ነው የሚያሞካሻት፡፡ ያኔ፣ በታኅሣሥ 1፣ 1955 የአላባማ ግዛት ዋና ከተማ መንገምሪ የአውቶቡስ ወንበሯን ለፈረንጅ እንድትለቅ በተጠየቀች ጊዜ አሻፈረኝ በማለቷ ለእስር ተዳርጋ ነበር፡፡ የሷ እምቢተኝነት ያቀጣጠለው አመጽ እነ ማርቲን ሉተር ኪንግ ጁኒየር የመሩትን አውቶቡስ ያለመሳፈር ተቃውሞን ቀሰቀሰ፡፡ ይህ ሰላማዊ ተቃውሞ ጥቁሮች ከሥራ ወደ ቤት፣ ከቤት ወደ ሥራ ሲሄዱ አውቶቡስ እንዳይሳፈሩና ከዚያ ይልቅ በእግር እንዲንቀሳቀሱ ወይም ሌሎች አማራጮችን እንዲጠቀሙ ነበር፡፡ ይህም ውጤት አስገኝቶ የአውቶቡስ ባለቤቶችን ለኪሳራ ዳርጓቸዋል፡፡ ከአንድ ዓመት በኋላ የፌዴራል ፍርድ ቤት ጥቁሮች የአውቶቡስ ወንበራቸውን ለነጮች እንዲለቁ የሚያዘው ሕግ ኢ-ሕገ መንግሥታዊ ነው ሲል ውሳኔ አስተላልፏል፡፡ ይህም በአሜሪካ የዘር መድሎ ትግሉ ውስጥ ግዙፍ ድል ያመጣ ክስተት ነበር፡፡ ይቺ ጀግኒት ሮዛ ፓርክስ የኖረችባት ቤት በ2008 የዲትሮይት ከተማ ማዘጋጃ ቤት ለልማት ሊያፈርሳት አቅዶ ነበር፡፡ ነገር ግን የሮዛ ፓርክስ የወንድሟ ሴት ልጅ ሮሂ ማካሊ ቤቱን በ500 ዶላር ገዝታ ለአርቲስት ራየን ሜንዶዛ በስጦታ መልክ አስተላልፋዋለች፡፡ አርቲስት ራየን በበኩሉ ቤቱ እንዳይፈርስ በሚል እንቅስቃሴ ቢያደርግም ስላልተሳካለት የመኖርያ ቤቷን ከፊል ገጽታ ነቅሎ በ2016 ወደ በርሊን በመውሰድ በራሱ ስቱዲዮ ውስጥ ለሕዝብ እንዲታይ አድርጓል፡፡ በ2018 የሮድ አይላንድ ብራውን ዩኒቨርስቲ ቤቱን ለአውደ ርዕይ ለማቅረብ መዘጋጀቱን ገልጾ ነበር፡፡ ሆኖም ከሮዛ ፓርክስ ቤተሰብ በገጠመው የሕግ ክርክር ሐሳቡ ሳይሳካ ቀርቷል፡፡ በመጨረሻ አርቲስቱ ራየን ሜንዶዛ ቀድሞ ይሰራበት ከነበረው ሞራ ግሪኮ ፋውንዴሽን ጋር ግንኙነት በመፍጠር ቤቱ በጣሊያን፣ ኔፕልስ ሮያል ፓላስ ውስጥ ለአውደ ርዕይ እንዲቀርብ አስችሏል፡፡ በአውደ ርዕዩ ላይ አንድ ሙዚቃ ለ8 ደቂቃ ከ46 ሰከንድ ደጋግሞ እንዲጫወት ተደርጓል፡፡ ይህም ባለፈው ግንቦት ፖሊስ አንገቱን ቆልፎ ለገደለው ጆርጅ ፍሎይድ መታሰቢያ እንዲሆን ነበር፡፡ ጆርጅ ፍሎይድ ‹‹መተንፈስ አልቻልኩም›› እያለ በነጭ ፖሊስ ማጅራቱ ተቆልፎ የተያዘው ለ8 ደቂቃ ከ46 ሰኮንድ ነበር፡፡ ጆርጅ ፍሎይድ ከተገደለ ወዲህ ተመሳሳይ ዘረኛ ግድያዎች እዚያም እዚህም የተሰሙ ቢሆንም የጥቁሮች የነጻነትና የእኩልነት ትግል ከቅርብ ጊዜ ወዲህ መነቃቃትን አሳይቷል፡፡ ጆርጅ ፍሎይድን ማጅራቱን ቆልፎ የገደለው ነጭ ፖሊስ መኮንን ዴሪክ ቾቪን ባለፈው ሳምንት ፍርድ ቤት ቀርቦ ነበር፡፡
48277802
https://www.bbc.com/amharic/48277802
ቻይናዊው ለውሾቹ ባወጣው ስም ምክንያት ዘብጥያ ወረደ
በምስራቃዊ ቻይና የሚኖር ባን የተባለ ወጣት ለሚያሳድጋቸው ሁለት ውሾች ባወጣላቸው "ሕገ ወጥ" ስም ምክንያት ዘብጥያ ወረደ።
በቤይጂንግ የሚታተም አንድ ጋዜጣ እንደዘገበው፤ ባን ውሾችን እያዳቀሉ በማርባት የሚታወቅ የ30 ዓመት ወጣት ሲሆን፤ ሰኞ እለት ሁለት የሚያሳድጋቸው ውሾችን ፎቶ አንስቶ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ካጋራ በኋላ ስማቸውን 'ቼንጉዋን' እና 'ዤግዋን' እንዳላቸው ይገልጻል። የውሾቹ ስም የማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች መነታረኪያ ሆነ። የማንዳሪን ቋንቋ ተናጋሪዎች እንደሚሉት፤ የውሾቹ ስም መንግሥት እና የመንግሥት ሠራተኛ ማለት ነው። ቼንጉዋን በከተሞች አካባቢ ተቀጥረው የሚሠሩ እና ቀላል ወንጀሎችን ለመከላከል ላይ ታች የሚሉ ሲሆኑ፤ ዤግዋን ደግሞ መደበኛ ያልሆኑ እንደ በጎ ፈቃደኛ ያሉ የማኅበረሰብ ሠራተኞች ናቸው። • "ልዩ ነዳጅ መኖሩን አልደረስንበትም" የማዕድን፣ የፔትሮሊየምና የተፈጥሮ ጋዝ ሚኒስቴር • እናት አልባዎቹ መንደሮች • ''ኢትዮጵያን ወደተሻለ ስፍራ ሊወስዳት የሚችል ሌላ መሪ የለም'' የሶማሌ ክልል ፕሬዝዳንት ጋዜጣው እንዳተተው፤ ወጣቱ ለውሾቹ ይህንን ስም ያሸከማቸው ለቀልድ ቢሆንም የአካባቢው አስተዳደር ከዚህ ስም ውስጥ የሚፈለቀቅ ደስታ ወይም ቀልድ አልታያቸውም፤ በይበልጥ ደግሞ ቼንጉዋን ከሚለው ስም። የዪንግዡዎ ፖሊስ "ይህ የሕግ አስከባሪ አካላትን መዝለፍ" ነው በማለት በግለሰቡ ላይ ምርመራ የጀመሩት ወዲያውኑ ነው። አክለውም የቻይናን ሕግ አንስተው፣ አንቀፅ ጠቅሰው ዘብጢያ ያወረዱት ሲሆን፤ 10 ቀናትም እዚያው ማሳለፍ አለበት ብለዋል። አንድ የፖሊስ ኃላፊ እንዳሉት፤ የግለሰቡ የማኅበራዊ ሚዲያ ፅሁፍ "ዜጎች ላይና የከተማዋ አስተዳደር ስሜት ላይ ጉዳት የሚያደርስ" ነው። ባንም በድርጊቱ መፀፀቱ የተገለፀ ሲሆን፤ ጋዜጣው እንደዘገበው "ሕጉ መኖሩን አላውቅም ነበር፤ ሕገ ወጥ መሆኑንም አላወቅኩም" ብሏል። የማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች በበኩላቸው ነገሩ የሳቅ ጅረት ሆኖላቸው ሲሳለቁ፤ አንዳንዶቹም የትኛው ሕግ እንደሚያስቀጣቸው አልያም እንደማያስቀጣቸው ሲከራከሩ ተስተውሏል።
news-53089295
https://www.bbc.com/amharic/news-53089295
ኮሮናቫይረስ ውሸት ነው ያሉ የሩሲያ ቄስ አንድ ገዳምን ተቆጣጠሩ
ኮሮናቫይረስ ውሸት ነው፣ የለም ያሉ አንድ አክራሪ የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቄስ አንድ የሴቶች ገዳምን በቁጥጥር ሥር አውለዋል።
አባ ሰርጌ ሮማኖቭ አባት ሰርጌ ሮማኖቭ ከየካትሪንበርግ ከተማ ወጣ ብላ የምትገኝን የሴቶች ገዳም የተቆጣጠሩት ማክሰኞ ዕለት ነው። የሰውየውን ወደ ገዳሙ መግባት ተከትሎ በርካታ መነኮሳት ገዳሙን ለመልቀቅ ተገደዋል። አሁን የታጠቁ ፖሊሶች ለገዳሙን ጥበቃ እያደረጉለት ይገኛሉ። አባት ሰርጌይ ለቤተ ክርስቲያኒቱ አስተዳዳሪዎች እንደተናገሩት ገዳሙን ከእርሳቸው እገታ ነጻ ማውጣት የሚቻለው እርሳቸውን ጨምሮ ገዳሙን ሙሉ በሙሉ ሲያጋዩት ብቻ ነው። እኚህ አወዛጋቢ ቄስ ባለፈው መጋቢት ከማንኛው የሰበካ አገልግሎት ታግደው ቆይተዋ። በግንቦት ወር ደግሞ የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ደረጃቸውን የሚገልጸውን ትልቅ መስቀል እንዳያጠልቁ ተከልክለዋል። የሩሲያ ቤተክርስቲያን በእርሳቸው የወደፊት እጣ ፈንታ ላይ የሚወስን አንድ ጉባኤ ጠርታ የነበረ ሲሆን እርሳቸው ላይ ስለሚወሰደው እርምጃ እየመከረ ሳለ ነው አባት ሰርጌይ ጥለው ወጥተው ገዳም የተቆጣጠሩት። ይህ እርምጃ የተወሰደባቸው ምዕመናን ማንኛውንም በመንግሥት የሚሰጡ የማኅበረሰብ ጤና ምክሮችን ተግባራዊ እንዳያደርጉ በመስበካቸው ነው። አባት ሰርጌይ ይህ ሐሰተኛ ያሉት የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ የሰይጣን ቅንብር ነው፤ የቤተክርስቲያኒቱ አስተዳዳሪዎች ከመንግሥት ሰዎች ጋር መሥራታቸውን ጌታ እየሱስ የሚወደው ተግባር አይደለም። አባት ሰርጌይ ሰሬድኒዩራልስክ ደብሪቱን የቆረቆሯት እንደ አውሮጳዊያኑ በ2000 ሲሆን በሺህዎች የሚቆጠሩ ምዕመናን የእርሳቸውን ሰበካ ለመስማት ወደዚህች ገዳም ሲጎርፉ ነበር። በበሽታው ምክንያት የሩሲያ ባለሥልጣናት በመጋቢት 13 ሁሉኑም የእምነት ቦታዎች ዘግተው የነበረ ሲሆን ገና በዚህ ወር ነው አብያተ ክርስቲያናት እንዲከፈቱ የፈቀዱት። አገሪቱ እስከ ትናንት ሐሙስ ድረስ ግማሽ ሚሊዮን ሰዎች በተህዋሲው ተይዘውባታል። በጠቅላላ የሟቾች ቁጥር ደግሞ 7,660 አልፏል። አንዳንድ የኅብረተሰብ ጤና አዋቂዎች ቁጥሩ ከዚህ በእጥፍ እንደሚልቅ ይገምታሉ። በአሁኑ ሰዓት አባት ሰርጌይ የተቆጣጠሩት ገዳም በታጠቁ ፖሊሶች ከበባ ላይ ሲሆን አንድ ጋዜጠኛ ግን ሾልኮ በመግባት አግኝቷቸዋል። "አገረ ስብከቱ እንዳልሰብክ ከለከለኝ፣ እንዳልናገር ከለከለኝ። ነገር ግን ጌታ እንድናገር ባርኮኛል" ብለውታል ወደ ውስጥ ሾልኮ ለገባው ጋዜጠኛ። አባት ሰርጌይ ቄስ ከመሆናቸው በፊት ፖሊስ የነበሩ ሲሆን ከዚያ ወዲያ ሰው በመግደል ተጠርጥረው 13 ዓመት በእስር አሳልፈዋል። የእርሳቸው ተከታዮች ግን "አባታችን ደርጊቱን አልፈጸሙም" ይላሉ። እኚህ ቄስ በሕጋዊ መንገድ ስማቸውን ወደ ኒኮላይ ሮማኖቭ የቀየሩ ሲሆን ይህንንም ያደረጉት ለመጨረሻው የሩሲያ ንጉሥ ዳግማዊ ኒኮላስ መታሰቢያና ክብር በሚል ነው። ይህ ንጉሥ የተቀበረውም እርሳቸው ከቆረቆሯት ደብር በቅርብ ርቀት ላይ ነው። እርሳቸውን ጨምሮ በርካታ ቀሳውስት በሩሲያ አዲስ የተሀድሶ እንቅስቃሴ ጀምረዋል በሚል ይተቻሉ። የቀደምት ነገሥታት አፍቃሪዎች በሚልም ይጠራል እንቅስቃሴያቸው። የአባት ሰርጌይ እንቅስቃሴም የዚህ አካል ተደርጎ ነው የሚታየው። አባት ሰርጌይ ከዚህ ቀደም በርካታ አወዛጋቢ ስብከቶችን ያደረጉ ሲሆን ከእነዚህ ስብከቶቻቸው መካከል ፑቲንን የሚቀናቀን የኢየሱስ ጠላት በሩሲያ ይነሳል፣ አርማጌዶንም ይካሄዳል የሚለው ይገኝበታል።
news-53879105
https://www.bbc.com/amharic/news-53879105
ፍሬዲ ብሎም፡'የዓለማችን የእድሜ ባለፀጋ' ደቡብ አፍሪካዊ በ116 ዓመታቸው አረፉ
የዓለማችን በዕድሜ ትልቁ ሰው ይሆናሉ ተብለው የታሰቡት ደቡብ አፍሪካዊ በ116 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።
እኝህ የእድሜ ባለፀጋ ፍሬዲ ብሎም፤ በምስራቅ ኬፕ ግዛት በጎርጎሮሳዊያኑ ግንቦት ወር 1904 እንደተወለዱ የግል መረጃቸው ያሳያሉ። ይህ ግን በዓለም ድንቃ ድንቅ መዝገብ የተረጋገጠ አይደለም። በጎርጎሮሳዊያኑ 1918 በተከሰተው በስፓኒሽ ጉንፋን ወረርሽኝ (የኅዳር በሽታ) ምክንያት በአስራዎቹ የዕድሜ ክልል ላይ እያሉ ጠቅላላ ቤተሰባቸውን አጡ። የሚገርመው ከወረርሽኙ ያመለጡት ፍሬዲ፤ ለበርካቶች ሞት ምክንያት ከሆኑት ሁለት የዓለም ጦርነቶችና እና ከአፓርታይድ ጭፍጨፋም ተርፈዋል። ከሁለት ዓመታት በፊት ረዥም እድሜ ለመቆየታቸው ሚስጥሩ ምንድን ነው ? ተብለው የተጠየቁት የዕድሜ ባለፀጋው ለቢቢሲ ሲናገሩ "ምንም የተለየ ሚስጥር የለውም" ብለዋል። " አንድ ነገር ብቻ ነበር። ይህም ከፈጣሪ የተሰጠ ፀጋ ነው። ሁሉም ኃይል ያለው እሱ ነው። እኔ ምንም የለኝ። በማንኛውም ጊዜ ልሞት እችል ነበር፤ ግን እርሱ ጠበቀኝ" ብለዋል። ፍሬዲ አብዛኛውን ጊዜያቸውን ያሳለፉት ሰራተኛ ሆነው ነው። ታታሪና ጠንካራ ሰራተኛ ነበሩ። መጀመሪያ ላይ በእርሻው ዘርፍ ከዚያም የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪውን ተቀላቅለዋል። ጡረታ የወጡትም በ80ዎቹ ዕድሜ ላይ እያሉ ነው። ምንም እንኳን ከበርካታ ዓመታት በፊት ከመጠጥ ጋር ቢለያዩም መደበኛ አጫሽ ነበሩ። ሆኖም የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝን ተከትሎ የአገሪቷ መንግሥት የእንቅስቃሴ ገደብ ሲጥል ሲጋራ መግዛት ጭንቅ ሆኖባቸው ነበር። በዚህ ጊዜም በ116ኛው ልደታቸው ጋዜጣ ጠቅልለው የራሳቸውን ሲጋራ ሰርተው አጭሰዋል። ይህም ብቸኛው የሚያዝናናቸው ተግባር እንደሆነ የ86 ዓመቷ ባለቤታቸው ግንቦት ወር ላይ ለሰንደይ ታይምስ ተናግረው ነበር። እኝህ የዕድሜ ባለፀጋ ቅዳሜ ዕለት በተፈጥሯዊ ምክንያት በኬፕ ታውን ማረፋቸውን ቤተሰቦቻቸው ተናግረዋል። "ከሁለት ሳምንት በፊት አያቴ እንጨት እየፈለጠ ነበር። በጣም ጠንካራ ሰው ነበር። ልበ ሙሉ ነበር።" ሲል አንድሬ ኔዶ ለኤኤፍፒ የዜና ወኪል ተናግሯል። "በቀናት ውስጥ ግን ያ ልበ ሙሉውና ጠንካራው ሰው በአንዴ ኩምሽሽ አለ" ይላል አንድሬ። ሕልፈታቸው ከዘመኑ ኮቪድ-19 ወረርሽኝ ጋር እንደማይገናኝ ግን ቤተቦቻቸው ያምናሉ።
43862014
https://www.bbc.com/amharic/43862014
የአሜሪካ ከፍተኛ ባለስልጣን በኤርትራ ያልተለመደ ጉብኝት እያደረጉ ነው
ከበርካታ ዓመታት በኋላ በአሜሪካ መንግሥት ከፍተኛ ባለስልጣን ወደኤርትራ የተደረገ ጉዙ እንደሆነ የተነገረለት ጉብኝት በአንድ የውጪ ጉዳይ ባለስልጣን እየተደረገ ነው።
የአሜሪካ ከፍተኛ ባለስልጣን ከሶማሊያው ፅንፈኛ እስላማዊ ቡድኖች ጋር ግንኙነት አላት ተብላ በማዕቀብ ስር ወደምትገኘው ኤርትራ ያልተለመደ ጉብኝት እያደረጉ ነው። በአሜሪካ የውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት የሆኑት ዶናልድ ያማሞቶ ከኤርትራ ባለስልጣናት ጋር ለመገናኘት ወደ አስመራ ያቀኑት ሃገሪቱ የተጣለባት ማዕቀብ እንዲነሳላት ድጋፍ እየፈለገች ባለበት ወቅት ነው። የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ጥበቃ ምክር ቤት የጦር መሳሪያን ጨምሮ ማዕቀቡን የጣለው ከስምንት ዓመታት በፊት የተካሄደን ምርመራ ተከትሎ ኤርትራ አልሸባብን ጨምሮ ሌሎች በሶማሊያ ያሉ ታጣቂ ቡድኖችን ትደግፋለች በሚል ነበር። ነገር ግን የኤርትራ መንግሥት ይህንን እንዳልፈፀመ ሲያስተባብል ቆይቷል። የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የአፍሪካ ጉዳዮች ዋና ምክትል አምባሳደር ዶናልድ የማማቶ ከረጅም ግዜ በኃላ በኤርትራ ላይ ጉብኝት በማድረግ ላይ ናቸው። ለሦስት ቀናት በሚቆየው የአማባሳደር ዶናልድ ያማሞቶ ጉብኝት ከከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናት ጋር በሁለትዮሽ ግንኙነት ጉዳዮች ላይ እንደሚመክሩ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያቤት ያወጣው መግለጫ ያመላክታል። በተባበሩት መንግሥታት አጣሪ ቡድን ምርማራ መሰረት የፀጥታው ምክር ቤት በኤእርትራ ላይ የጣለው ማዕቀብ ለሁለት ጊዜ እንዲራዘም ተደርጓል። በዚህም ምክንያት ኤርትራ ከምዕራባዊያን ሃገራት በተለይ ደግሞ ከአሜሪካ ጋር ግንኙነቷ ሻክሮ ቆይቷል። የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በበኩላቸው አገራቸው ከኢትዮጵያ የገባችበት ለ20 ዓመት የቆየ ዕልባት ያላገኘ የድንበር ውዝግብ ላለመፈታቱ በተደጋገሚ አሜሪካንን ተጠያቂ ሲያደርጉ ይስተዋላል። የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት የሆኑት የዶናልድ ያማሞቶ ጉብኝት ኢትዮጵያንና ጅቡቲን የሚያካትት የአፍረካ ቀንድ ሃገራት ጉዞ ቢሆንም፤ የኤርትራው ጉብኝታቸው ግን የበርካቶችን ቀልብ ስቧል። አምባሳደር ያማሞቶ በአስመራ ከሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ሠራተኞች ጋርም የሚወያዩ ሲሆን፤ ቀጥሎም በጅቡቲ ለሁለት ቀናት በሚካሄደው የአሜሪካና የጅቡቲ የሁለትዮሽ ውይይት ላይ የሚሳታፉ የአገሪቱ ልኡካን ቡድንን መርተው ወደዚያው እንደሚያቀኑ መረጃዎች ያመለክታሉ። በመቀጠልም አምባሳደሩ ወደ ኢትዮጵያ በማምራት ከከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር በሁለትዮሽ ግንኙነት ጉዳዮችና በኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ይወያያሉ ተብሏል። ለመጀመርያ ግዜም ከአዲሱ ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አሕመድ ጋር ተገናኝተው ይመክራሉ ተብሎም ይጠበቃል። አምባሳደር ያማሞቶ ከሁለት ዓመት በፊት በኤርትራና ኢትዮጵያ ያለው አለመግባባት ለመፍታት እቅድ እንደነበራቸው ለጋዜጠኞች መናገራቸው ይታወሳል። በዚሁ ጉብኝታቸው ሁለቱ አገሮችን ለማግባባት ይጥራሉ የሚል ግምት በብዙዎች ዘንድ ያለ ሲሆን፤ እስከአሁን በዚህ ጉዳይ ላይ ይምከሩ አይምከሩ በውል ማረጋገጥ አልተቻለም። ላለፉት ሃምሳ ዓመታት የኤርትራ ጉዳይ ሲከታተሉ መቆየታቸውን የሚናገሩት ፕሮፌሰር ፍስሃፅየን መንግስቱ የአምባሳደር ያማሞቶ የአስመራ ጉብኝት የተለያየ ትርጉም ሊሰጠው እንደሚችል ይናገራሉ። "አንደኛ አሜሪካ በቀጣናው ያላትን ጥቅም ለማስጠበቅ ነው። ሁለተኛ፣ የኤርትራ መንግስት በፀጥታው ምክርቤት የተጣለበትን ማእቀብ ለማስነሳት ከአሜሪካ ጋር መልካም ግንኙነት እንዲኖረው ስለሚፈልግ ይመስለኛል" ብሏል። ከኢትዮጵያ ጋር ያለው ግንኙነት ሊሻሻልል ይችላል ወይ? የሚለውን ሲመልሱ " የኤርትራ መንግስት ለኤርትራ ህዝብ ያልጠቀመ ለኢትዮጵያ ሊጠቅም አይችልም" ይላሉ። በኤርትራ ያለው የፖለቲካ ሁኔታ ተስፋ እንደሌለው ይናገራሉ። "በውጭ ተፅዕኖ የሚመጣ ለውጥ ዘላቂ ኣይደለም። እንደ እኔ አስተያያት ዘላቂ መፍትሄ በኤርትራ ያለው ሁኔታ ሲያገኝ ብቻ ነው" ይላሉ።
54223308
https://www.bbc.com/amharic/54223308
ቤንሻንጉል ጉሙዝ፡ መንግሥት የዜጎችን ደህንነት እና ሰላም እንዲጠብቅ ኢሰመጉ ጥሪ አቀረበ
በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከሰሞኑ በደረሰው ጥቃት በርካታ ሰዎች መገደላቸውን፣ የአካል ጉዳት የደረሰባቸውና አስገድዶ መሰወር (እገታ) እንደተፈፀመባቸው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ፣ ኢሰመጉ በትናንትናው ዕለት፣ መስከረም 9፣ 2013 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።
በክልሉ፣ ነሃሴ 29 እና 30 እንዲሁም ጳጉሜ 1 እና 2 ቀን ባሉ ቀናት ጥቃቶቹ እንደተፈፀሙ ያስታወሰው መግለጫው በመተከል ዞር ስር አስተዳደር ባሉት ጉባ፣ ዲባጢ፣ ቡለን እና ወንበራ ወረዳዎች በርካታ ነዋሪዎች ኢላማ እንደተደረጉም በስፍራው ከሚገኙ እማኞች ሰበሰብኩት ያለውን መረጃ ዋቢ አድርጓል። በነዚህ አካባቢዎች ንፁኃን ሰዎች በቀስት፣ በስለት እና በጦር መሳሪያ በታገዙ እጅግ አሰቃቂ ብሎ የጠራው ሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ተፈፅሟል ብሏል። በነዚህ በርካታ ቀበሌዎች ላይ ጥቃቱን ያደረሱት ማንነታቸው ያልታወቁ ታጣቂዎች እንደሆኑ አስፍሮ በርካቶችም ባለው ስጋት ምክንያት ከመኖሪያ ስፍራቸው እንደሸሹ ኢሰመጉ አስታውቋል። ጥቃቱ የደረሰባቸው አካባቢዎች ከዚህ ቀደምም ተደጋጋሚ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች የደረሱበት እንደሆነ ያስረዳው የኢሰመጉ መግለጫ በፌደራል መንግሥትም ሆነ በክልሉ መንግሥት በዘላቂነት ችግሩን ለመቅረፍ ስራዎች እንዳልተሰሩ ጠቁሟል። የክልሉም ሆነ የፌደራል መንግሥት አልፎ አልፎ ከሚወስዷቸው የህግ ማስከበር ስራዎች በዘለለ ችግሩን ከስር መሰረቱ ባጤነ መልኩ ወደ ዘለቄታዊ መፍትሄ አልሄዱም ብሏቸዋል። ከዚህም በተጨማሪ ከዚህ ቀደም በደረሱ ጥቃቶች ላይ ኃላፊነታቸውን ባልተወጡ በተለያየ ደረጃ ላይ ባሉ አስተዳደሮች ላይ ተገቢው እርምጃ ባለመወሰዱ ምክንያት እንዲህ አይነት ጥሰቶች እንደገና ለመድረሳቸው ምክንያት መሆኑን ኢሰመጉ እንደሚያምን አስፍሯል። "በየደረጃው ያሉ የፀጥታ ኃይሎች እና የመንግሥት የፍትህ ተቋማት ችግሩ እንዳይከሰት አስቀድሞ የመከላከል ከተከሰተም በኋላ በአፋጣኝ ሕጋዊ እርምጃ በመውሰድ የማስተካከል ህገ መንግሥታዊ ኃላፊነታቸውን በሚገባ ባለመወጣታቸው ንፁኃን ሰዎች የተደጋጋሚ ጥቃቶች ሰለባ እንዲሆኑ እንዳደረጋቸው ለመረዳት ችለናል" ብሏል። ይህንንም ችግር ለመቅረፍ ኢሰመጉ የመፍትሄ ኃሳብ ያላቸውን አቅርቧል። ጥቃቱን የፈፀሙት ለፍትህ እንዲቀርቡ፣ ተጎጂ ግለሰቦች ሰብዓዊ እርዳታ እንዲደረግላቸው እና ተገቢው የሞራል እና የገንዘብ ካሳ እንዲሰጣቸው ኢሰመጉ ጠይቋል። ከዚህም በተጨማሪ የክልሉና የፌደራል መንግሥት የፀጥታ ኃይሎች የጀመሩትን ህግ የማስከበር እንቅስቃሴ አጠናክረው በመቀጠል ጠንካራ ህጋዊ እርምጃዎችን በመውሰድ እንደሚገባም አስፍሯል። "የዜጎችን በህይወት የመኖር የአካል ደህነነት ነፃነት እንዲሁም ሰላም እና ደህንነቱ በተጠበቀ በማንኛውም አካባቢ የመኖር ህገ መንግሥታዊ መብቶቻቸውን በምልዓት እንዲያረጋግጡ" ኢሰመጉ አሳስቧል። የክልሉም ሆነ የፌደራል መንግሥት እነዚህን ተደጋጋሚ ጥቃቶች አስቀድሞ መከላከል የሚያስችል መዋቅር መዘርጋት እንደሚያስፈልግ ያሳሰበው መግለጫው ለተደጋጋሚ ሰብዓዊ ጥሰቶቹ ዘላቂ መፍትሄ ሊበጅለት ይገባል ብሏል። ከሰሞኑም የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ባወጣው መግለጫ ላይ በመግለጫው ላይ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጳጉሜ 1/2012 ዓ.ም እንዲሁም ከመስከረም 4 አስከ መስከረም 10/2013 ዓ.ም መካከል ባሉት ቀናት ውስጥ ቢያንስ ሁለት ጥቃቶች ማጋጠማቸውን ከክልሉ መንግሥት ለማረጋጥ መቻሉን አመልክቷል። ይህንንም ተከትሎ ቢያንስ በሁለት ዙር በተፈጸሙ ጥቃቶች ባልታጠቁ ሰላማዊ ሰዎች ላይ ግድያዎች መፈፀማቸውን እንዲሁም በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች መፈናቀላቸውን በስፍራው ከሚገኝ አንድ መንግሥታዊ ምንጭ መረዳት እንደቻለ ኮሚሽኑ መግለፁ የሚታወስ ነው። በክልሉ ሰላምና መረጋጋት እንዲኖር በመከላከያ ሠራዊት፣ በፌዴራል ፖሊስ እና በክልል የጸጥታ ኃይሎች ሰላምን ለማስጠበቅ እየተደረገ ያለውን ጥረት እንደሚያበረታታም አስታውቋል። ከዚህም በተጨማሪ በደቡብ ክልል በኮንሶ ዞን ካራትና ኮልሜ ወረዳዎች እና በአሌ ልዩ ወረዳ መካከል ባሉ አዋሳኝ ቀበሌዎች በተከሰተው ግጭት በርካታ ሰዎች ተገድለዋል፣የአካል ጉዳት ደርሷል እንዲሁም ቤት ንብረታቸው ወድሟል። በዋነኝነት ለዓመታት ሲንከባለል የመጣው የወሰን አካለል ጋር በተያያዘ በሚነሱ ግጭቶች የሰዎች ህይወትን መጥፋት እያስከተለ ነው፤ ከባለፈው ዓመት ኃምሌ ጀምሮም ግጭቱ እንዳልበረደ አስታውሷል። እነዚህን ግጭቶች በተመለከተ ኢሰመጉም መንግሥት መሰረታዊና ዘለቄታዊ መፍትሄ እንዲያበጅም ለመንግሥት ጥሪ አቅርቧል።
news-52705131
https://www.bbc.com/amharic/news-52705131
ኮሮናቫይረስ፡ 'በፈጣሪ ይሁንታ ይህም ይታለፋል' ከቫይረሱ ያገገሙት
በመላው ዓለም ወደ 5 ሚሊዮን ገደማ ሰዎችን የያዘው ኮቪድ-19፤ ዛሬ ላይ ስርጭቱ በምዕራባውያን አገራት እየቀነሰ የመጣ ቢመስልም በአፍሪካ ግን አስፈሪነቱ እንደቀጠለ ነው።
የቫይረሱን ስርጭት ለመቆጣጠር የሚደረገው ጥረት ቀላል አይደለም። ከበሽታው ጋር ተያይዘው የሚወጡ ዜናዎችም ለሰሚ ጆሮ የሚያስደስቱ አይደሉም። በዚህ ሁሉ መካከል ግን በሽታውን ድል ነስተው የሚድኑ ሰዎች ታሪክ ለሌሎች መጽናኛ ሆነዋል። ከእነዚህም መካከል የአምስት ሰዎችን ታሪክ ልናጋራችሁ ወደድን። ኒሃሪካ ማሃንደሩ "አሁን መተንፈስ በመቻሌ እድለኛ እንደሆንኩ ይሰማኛል" ትላለች ከኮቪድ-19 ያገገመችው ኒሃሪካ ማሃንደሩ። ከዩናይትድ ኪንግደም ተነስታ እጮኛዋን ለመጎብኘት ወደ ስፔን ካቀናች በኋላ ነበር በቀናት ልዩነት ራስ ምታት እና ትኩሳት ጨምሮ ሌሎች የበሽታውን ምልክቶች ማሳየት የጀመረችው። ብዙም ሳትቆይ ህመሟ ተባብሶ ከከባድ ሳል በኋላ መተንፈስ አቃታት። ይህ ተከትሎ ከዚህ ቀደም የጤና እክል ያልነበረባት የ28 ዓመት ሴት ባርሴሎና ወደሚገኝ ሆስፒታል እንድትገባ ተደረገ። • የዓይን እማኞች በመቀለ በፀጥታ ኃይሎች ስለተገደለው ወጣት ምን ይላሉ? "የነበርኩበት ሁኔታ በጣም ከባድ የሚባል ነበር። መተንፈስ ያቅተኝ ነበር። ጉሮሮዬ እየተዘጋ የሚሄድ አይነት ስሜት ነበር የሚሰማኝ። ይሄ ስሜት በጣም አስፈሪ ነበር" ትላለች ኒሃሪካ። ሆስፒታሉ በበሽተኞች ተጨናንቆ ስለነበረ ወደ ቤት እንድትመለስ ተደረገች። በቀጣይ ቀን በኮቪድ-19 መያዟን የምርመራ ውጤቷ አረጋገጠ። ፓራሲታሞል፣ ሃይድሮክሲክሎሪኪን እና አንቲባይቶኪስ መድሃኒቶችን ስትወስድ እንደነበረ ትናገራለች። አሁን ላይ ከበሽታው ያገገመችው ወጣት "ለተደረገልኝ እንክብካቤ የጤና ባለሙያዎችን በጣም ላመሰግናቸው እወዳለሁ" ትላለች። 'በመልካም ስሜት ከተሞላን ቫይረሱን እናሸንፈዋለን' ጋፋር ማርሁን "በፈጣሪ ይሁንታ ይህም ያልፋል። ሁሉም ነገር ወደ ቀደመ ነገር ይመለሳል" ይላል ጋፋር ማርሁን። የ26 ዓመቱ የአውቶብስ ሹፌር በባህሬን በኮቪድ-19 ተይዞ ህክምና ያገኘው የመጀመሪያው ሰው ነው። ጋፋር ከባለቤቱ ጋር ወደ ኢራን ተጉዞ ከተመለሰ በኋላ ነበር በቫይረሱ መያዙን ያወቀው። ባለቤቱ ግን በኮቪድ-19 አልተያዘችም። ጋፋር እንደሚለው፤ በዱባይ አድርጎ ወደ ባህሬን ሲመለስ አውሮፕላን ላይ 'በተደጋጋሚ ሲያስል' ከነበረ መንገደኛ ቫይረሱ ሳይዘው እንዳልቀረ ይገምታል። "በመልካም ስሜት ከተሞላን ቫይረሱን እናሸንፈዋለን። እኔ በበሽታውም ተይዤ ደስተኛ ነበርኩ። የጤና ባለሙያዎች ሁሉ በዚህ ሲደነቁ ነበር" ይላል። "በቅድሚያ በባህሬን በቫይረሱ መያዙ የተረጋገጠ ሰው እኔ በመሆኔ ተወግዤ ነበር" የሚለው ጋፋር፤ ለሁለት ወራት ልጆቹን አለመያቱን ይናገራል። ከቫይረሱ ሙሉ ለሙሉ አገግሚያለሁ ያለው ጋፋር ልጆቼን እስካይ በጣም ጓጉቻለሁ ብሏል። ጃያንታ ራንሲንግሄ በስሪ ላንካ በኮቪድ-19 መያዛቸው ከተረጋገጡ እና ካገገሙ ሰዎች የመጀመሪያዎቹ ውስጥ አንዱ ነው። ጃያንታ ራንሲንግሄ በስሪ ላንካ በኮቪድ-19 መያዛቸው ከተረጋገጠ እና ካገገሙ ሰዎች የመጀመሪያዎቹ ውስጥ ይካተታል። የ52 ዓመቱ አስጎብኚ አገሩን ሊጎበኙ ከመጡ 4 ጣሊያናዊያን ጎብኚዎች ጋር አብሮ ከሰነበተ በኋላ በቫይረሱ መያዙ ተረጋግጧል። "የካቲት 9 ላይ በቫይረሱ መያዜ ሲነገረኝ፤ ለህይወቴ ሰጋሁኝ። የምሞት መሰለኝ" ይላል የ52 ዓመቱ ጎልማሳ። • በኮሮናቫይረስና በነዳጅ ዋጋ መውደቅ ስጋት የተደቀነባት ሳዑዲ አረቢያ የጤና ባለሙያዎች ጃንያታ መደናገጥ እንደሌለበት ለማረጋጋት ሲሞክሩ፤ ባለቤቱ እና ሁለት ልጆቹ ደግሞ ''ቫይረሱን ልታጋቡብን ትችላላችሁ'' በሚሉ ጎረቤቶች የተለያዩ ጥቃቶች እየተሰዘሩባቸው ነበር። እንደውም ከጎረቤቶቻቸው መካከል አንዷ መኖሪያ ቤታቸውን በእሳት ለማጋየት ሰዎች ስታስተባብር ነበር። የጤና ባለሙያዎች እና ባለስልጣናት ስለበሽታው መረጃ በመስጠት ሊታደጓቸው ችለዋል። ለ18 ቀናት በጤና ተቋም የሰነበተው የ52 ዓመቱ ጎልማሳ፤ መጋቢት 12 ላይ ወደ መኖሪያ ቤቱ ተመልሷል። "ከካንሰር ጋር መኖር ከቻልኩ፤ ከኮቪድ-19 ጋር መቆየት አይከብደኝም" በአንጀት ካንስር የሚሰቃየው የቢቢሲ ዜና አንባቢ ጆርጅ አላጊአህ በአንጀት ካንስር የሚሰቃየው የቢቢሲ ዜና አንባቢ ጆርጅ አላጊአህ የኮሮናቫይረስ ምልክቶች ይታዩበት ነበር። የካንስር ህመምተኛ የሆነው ጋዜጠኛ፤ የኮሮናቫይረስ ምልክቶችን ማሳየቱን ተከትሎ ባደረገው ምርመራ በቫይረሱ መያዙ ተረጋግጧል። "ለስድስት ዓመታት የካንስር ህመምተኛ ሆኜ ቆይቻለሁ። ከካንስር ጋር መኖር ከቻልኩ፤ ከኮቪድ-19 ጋር መቆየት አይከብደኝም ብዬ ራሴን አሳምኜ ነበር" ይላል ጆርጅ። የ64 ዓመቱ የቀደመ የጤና እክል ስለነበረው በኮቪድ-19 ሳቢያ ህይወቱ አደጋ ላይ ነው ተብሎ ተገምቶ ነበር። ይሁን እንጂ ጆርጅ ከቫይረሱ አገግሟል ምንም እንኳ ባለቤቱ የቫይረሱን ምልክት ማሳየት ብትጀምርም። ታይገር ዪ ታይገር ዪ የ21 ዓመት ተማሪ ነው። ነዋሪነቱም የቫይረሱ መነሻ ነች ተብላ በምትገመተው ዉሃን ቻይና ነው። 'በቫይረሱ እንዴት እንደተያዝኩ አላውቅም' የሚለው ታይገር፤ በቅድሚያ ያሳይ የነበረው ምልክት፤ የጡንቻ ህመም፣ የምግብ ፍላጎት መቀስ እና ትኩሳት ነበሩ። ከዚያም ያስመልሰው እና ተቅማጥ ተከተለ። "በህይወቴ በጣም የታመምኩበት ጊዜ ሳይሆን አይቀርም። እንዲህ አይነት ስሜት ተሰምቶኝ አያውቅም" ብሏል የ21 ዓመቱ ወጣት። "ማስመለሱ በጣም ህመም ነበረው። ሳለቅስ ነበር። የምሞት መስሎኝ ነበር። የምበላው ምግብ ሁሉ ይወጣ ነበር። እንደዛም ሆኖ ሆዴ በጣም ይወጠር ነበር። እያንዳንዱ የሰውነቴ ክፍል ህመም ነበረው" በማለት የነበረውን ሁኔታ ያስታውሳል። በዉሃን የሆስፒታሎች አልጋ በቫይረሱ ህመምተኞች ተጨናንቀው ስለነበረ፤ ወደ ሆስፒታል በመሄድ ህክምና ማግኘት አልቻለም ነበር። ራሱን ለይቶ ለ10 ቀናት መድሃኒት እየወሰደ ከቆየ በኋላ ለውጥ ማሳየት ጀመረ። "ስለ ሁኔታው ማሰብ አልፈልግም። እጅግ አስቀያሚ ነገር ነው" የሚለው ታይገር፤ ከበሽታው ለመዳን የቤተሰቦቹ አስተዋጽኦ ከፍ ያለ መሆኑን ይናገራል።
news-54232907
https://www.bbc.com/amharic/news-54232907
የዓለም መነጋገርያ የሆኑት አፈትልከው የወጡት ዶሴዎች ይዘት ምንድነው?
አፈትልከው የወጡ ዶሴዎች የዓለማችን ግዙፍ ባንኮች ወንጀለኞች ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር እንዲያደርጉ መፍቀዳቸውን አረጋግጠዋል።
2 ትሪሊየን ዶላር ልውውጥ የተመዘገበባቸው የፋይናንስ ሰነዶችም የዓለም መነጋገሪያ ሆነዋል። እነኚህ የፊንሴን (FinCEN) ዶሴዎች ወደ ምዕራቡ ዓለም ገንዘባቸውን ማንቀሳቀስ እንዳይችሉ ማዕቀብ ተጥሎባቸው የሚገኙ ግለሰቦች እና ቡድኖች እውቅ ባንኮችን ተጠቅመው ገንዘባቸውን ሲያንቀሳቅሱ እንደነበር አጋልጠዋል። ፊንሴን (FinCEN) የአሜሪካ የፋይናንስ ወንጀል ተቆጣጣሪ ኔትዎርክ ሲሆን፤ የፋይናንስ ወንጀሎችን የሚከላከል የአሜሪካ የግምዣ ቤት አካል ነው። ከአሜሪካ ውጪ ጭምር በአሜሪካ ዶላር የሚደረጉ ግብይቶች ሪፖርት ይቀርቡለታል። ከ2500 በላይ የሚሆኑትን የፊንሴን ዶሴዎች የባንክ ደንበኞች ሚስጢራዊ የገንዘብ ዝውውሮችን የያዙ ናቸው። ዶሴዎቹ ለበዝፊድ ኒውስ የተላኩ ሲሆን ከዚያም በ88 አገራት ለሚገኙ ለ108 መገናኛ ብዙሃን ድርጅቶች ተጋርተዋል። በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጠኞች ዶሴዎቹን መነሻ በማድረግ ጉዳዩ በጥልቀት በመመርመር ባንኮች ሕዝቡ እንዲያውቅ የማይፈልጉትን እውነታ ይፋ አድርገዋል። አንድ ሰው ከሕገ-ወጥ እንቅስቃሴዎች ትርፍ ለማግኘት ካሰበ ቀድሞ መዘጋጀት ያለበት የሚያገኘውን ገንዘብ ሕጋዊ አስመስሎ ማቅረብ መቻል ነው። ይህ ማለት በሙስና ወይም በእጽ ዝውውር የተገኘን ሕገ-ወጥ ገንዘብ ሕጋዊ አድርጎ በባንክ ማስቀመጥ ማለት ነው። ባንኮች በበኩላቸው ከደንበኞቻቸው የሚቀበሉት ሕገ-ወጥ ገንዘብ አለመሆኑን የማጣራት ግዴታ አለባቸው። በአንድ ባንክ ሕገ-ወጥ ገንዘብ ሕጋዊ መስሎ ተቀምጦ ቢገኝ ባንኩ ብዙ ሕጎችን ተላልፎ ይገኛል ማለት ነው። ባንኮች የደንበኞቻቸውን ማንነት ማወቅ ግድ ይላቸዋል። በስርዓታቸው ውስጥ አጠራጣሪ የገንዘብ እንቅስቃሴ ሲያስተውሉ ለሚመለከተው የመንግሥት አካል ማሳወቅም ይኖርባቸዋል። ማሳወቅ ብቻ ግን በቂ አይደለም። የገንዘብ እንቅስቃሴው ሕገ-ወጥ መሆኑን ካረጋገጡ የገንዘብ እንቅስቃሴውን ማገድ ይኖርባቸዋል። የምርመራ ጋዜጠኞቹ ቡድን አባል የሆኑት ፈርገስ ሼኤል ይፋ የተደረጉት ዶሴዎች “በመላው ዓለም ሕገ-ወጥ ገንዘብ ሲንቀሳቀስ የነበረው በባንኮች እውቅና ነው” ብለዋል። በሕገ-ወጥ መንገድ ሲዘዋወር ነበር የተባለው እና አፈትልከው በወጡት ዶሴዎች ከተረጋገጠው 2 ትሪሊዮን በላይ መሆኑም ተጠቅሷል። ዶሴዎቹ ምን አጋለጡ? በዓለማችን በግዙፍነቱ 6ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው እና መቀመጫውን በዩናይትድ ኪንግደም ያደረገው HSBC (ኤችኤስቢሲ) ባንክ አጭበርባሪዎች የተሰረቀ ገንዘባቸውን በመላው ዓለም እንዲያንቀሳቅሱ ፈቅዷል። ባንኩ የደንበኞቹ የገንዘብ ምንጭ ከአሜሪካ መንግሥት እየተነገረውም የገንዘብ ዝውውሩ እንዲደረግ ፈቅዷል። የአሜሪካው JP Morgan (ጄፒ ሞርጋን) ባንክ በተመሳሳይ በአሜሪካው ኤፍቢአይ ከሚፈለጉ ቡድኖች መካከል የአንዱ ቡድን የሆነ ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ እንዲንቀሳቀስ ፈቅዷል። የሩሲያው ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን አጋር እንደሆኑ የሚታመኑ ማዕቀብ የተጣለባቸው ግለሰብ ባርክሌይስ ባንክን በመጠቀም ገንዘባቸውን በምዕራቡ ዓለም እንዲያንቀሳቅሱ ፈቅዷል። የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች ማዕከላዊ ባንክ ከኢራን ጋር ግነኙነት ያለው ድርጅት ገንዘብ እንዲያንቀሳቅስ መፍቀዱን አረጋግጧል። የጀርመኑ Deutsche Bank (ዶቼ ባንክ) የተደራጁ የወንጀል ቡድኖች፣ አሸባሪዎች እና እጽ አዘዋዋሪዎች ሕገ-ወጥ ገንዘብን ሕጋዊ አስመስለው እንዲጠቀሙ ፈቅዷል ይላል። ከዚህ በተጨማሪም ስታንዳርድ ቻርተርድ ባንክ (Standard Chartered) ሽብርን የሚደግፉ ሰዎች ገንዘባቸውን ጆርዳን ወደሚገኝ ባንክ ለአስርት ዓመታት ሲያስተላልፍ መቆየቱን አረጋግጧል።
news-53089288
https://www.bbc.com/amharic/news-53089288
በህዳሴ ግድብ ድርድር በቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ መስማማት እንደተቻለ ተገለጸ
በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ በሦስቱ አገራት መካከል ሲካሄድ በሰነበተው ድርድር በበርካታ ቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ከስምምነት መደረሱ ተገለጸ።
የኢትዮጵያ ውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር ስለድርድሩ ሂደት ባወጣው መግለጫ ላይ እንዳለው አብዛኞቹ ቴክኒካዊ ጉዳዮች በድርድሩ መፍትሄ እንዳገኙ የገለጸ ሲሆን ነገር ግን ለድርድሩ መቋጫ ለማበጀት ሕጋዊ ጉዳዮች ላይ ገና መስማማት እንደሚያስፈልግ አመልክቷል። ለዚህም የአገራቱ የቴክኒክና የሕግ ቡድን አባላት ከሚኒስትሮቹ ስብሰባ በፊት ተጓዳኝ ምክክር ማድረጋቸው የተገለጸ ሲሆን ይህም ቡድን የደረሰበትን ውጤት ለሦስትዮሹ የሚኒስትሮች ስብሰባ ማቅረቡ ተነግሯል። ባለፉት ሰባት ቀናት በኢትዮጵያ፣ በሱዳንና በግብጽ መካከል በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ደረጃ የውሃ አሞላልና ዓመታዊ የውሃ ልቀት ላይ ታዛቢዎች ባሉበት በቪዲዮ ግንኙነት ድርድር ሲካሄድ ሰንብቶ በተለያዩ ቁልፍ ጉዳዮች ላይ መነጋገራቸውም ተገልጿል። ሚኒስቴሩ ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ ያላትን ዘላቂ መብት ለማረጋገጥ የሚደረገው ድርድር ጥንቃቄን እንደሚፈልግ ገልጾ፤ ለዚህም ድርድሩ የግብጽና የሱዳን መንግሥታት የሁሉንም አገራት ሉአላዊነትና የጋራ ጥቅም ያከበረ አርቆ ለሚመለከት ዘላቂ ትብብር የበኩላቸውን ማድረግ እንደሚጠበቅ አመልክቷል። በድርድሩ ላይ ኢትዮጵያ የመርሆች ስምምነትን መሰረት አድርጋ ግድቡን በውሃ የመሙላትና ሥራውን የማካሄድ መብት እንዳላት ግልጽ ማድረጓን ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ገልጿል። በዚህም ኢትዮጵያ ሦስቱም አገራት እያደረጉት ካለው በመመሪያዎችና ደንቦች ላይ እያካሄዱት ካለው ድርድር ለሁሉም በሚጠቅም መልኩ ስምምነት ላይ ተደርሶ እንዲጠናቀቅ ጽኑ ፍለጎት እንዳላት አመልክቷል። በዚህ ሂደት የሱዳን ተደራዳሪዎች ጠቅላይ ሚኒስትራቸውን ማነጋገር ስለፈለጉ ድርድሩ ለአንድ ቀን እንደተቋረጠ የተነገረ ሲሆን የሱዳኑ ውሃ ሚኒስትር ጠቅላይ ሚኒስትራቸውን ማነጋገር ስለፈለጉ ድርድሩ በዛሬው እለት አይኖርም። የሱዳን ተደራዳሪዎች ስለድርድሩ ሂደት ከጠቅላይ ሚኒስትራቸው ጋር ለመወያየትና መመሪያ ለመቀበል በመጠየቃቸው የትናንቱ ድርድር ከዚህ በኋላ እንዲካሄድ በመስማማት መጠናቀቁን ተገልጿል። የሱዳን የሽግግር መንግሥት ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንት ሌፍተናንት ጀኔራል መሐመድ ሃምዳን ደጋሎ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር ለመወያየት ትናንት አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወሳል። በዚህም መሰረት ምክትል ፕሬዝዳንቱ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ጋር ውይይት ማድረጋቸው ተነግሯል።
news-46107030
https://www.bbc.com/amharic/news-46107030
ሳዑዲ አረቢያ የጀማል ኻሾግጂን ግድያ መረጃ ለማጥፋት ባለሙያዎች ልካለች
ከፍተኛ የቱርክ ባለስልጣን ለቢቢሲ እንደተናገሩት ከሆነ ጀማል ኻሾግጂ ከተገደለ በኋላ ሳዑዲ አረቢያ የኬሚካል እና የቶክሲኮሎጂ ባለሙያዎችን ኢስታንቡል ወደሚገኘው ቆንጽላዋ ልካለች።
የዋሽንግተን ፖስቱ አምደኛ እንደወጣ የቀረው ጥቅምት 2 ነበር ሳዑዲ፤ ጋዜጠኛ ጀማል ባሳለፍነው ወር በሳዑዲ ቆንጽላ ውስጥ መገደሉን ብታምንም ስለ አሟሟቱ እርስ በእርስ የሚጣረሱ መረጃዎችን ስትሰጥ ነበር። • የጋዜጠኛው አስክሬን 'በአሲድ እንዲሟሟ ተደርጓል' • “የኻሾግጂን ሬሳ ለማን እንደሰጣችሁት ንገሩን” የቱርክ መርማሪዎች ኻሾግጂ ታንቆ እንደተገደለ እንዲሁም አስክሬኑ በኬሚካል እንዲቀልጥና እንዲተን መደረጉን ያምናሉ። ከሁለት ቀናት በፊት ሁለት የጀማል ኻሾግጂ ልጆች ከሲኤንኤን ጋር በነበራቸው ቆይታ የአባታቸው አስክሬን እንዲሰጣቸው ተማጽነዋል። ''አሁን የምንሻው አባታችንን በመዲና ከተማ አል-ባቂ መቃብር ስፍራ ቤተሰቦቹ በተቀበሩበት ስፍራ ግብዓተ መሬቱን መፈጸም ነው'' በማለት ሳላህ ኻሾግጂ ተናግሯል። ''በጉዳዩ ላይ ከሳዑዲ ባለስልጣናት ጋር መክረናል። ጥያቄያችንን ይቀበላሉ ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ'' ብሏል። • ልዑሉ የኻሾግጂን ገዳዮች ለፍርድ እንደሚያቀርቡ ዛቱ ኻሾግጂ ከአንድ ወር ገደማ በፊት ቱርክ በሚገኘው የሳዑዲ ቆንጽላ ውስጥ ጋብቻ ለመፈጸም የሚረዳውን ሰነድ ለማግኘት በሄደበት ወቅት ነበር የተገደለው። ቱርክ ተፈጽሟል የምትለው ምንድነው? የቱርክ ባለስልጣናት፤ ጀማል ኻሾግጂ በሳዑዲ አረቢያ ቆንጽላ ጽህፈት ቤት ውስጥ ከተገደለ በኋላ የሳዑዲ ባለስልጣናት የኬሚካል ባለሙያ የሆነ አብዱላዚዝ አለጃኖቢ እና የቶክሲኮሎጂ ባለሙያ የሆነ ካሊድ ያይሃ አል-ዛሀረን የተባሉ ግለሰቦችን በመላክ ከግድያው ጋር የተያያዙ መረጃዎች እንዲያጠፉ አድርጋለች ይላሉ። አንድ የቱርክ ጋዜጣ፤ ሁለቱ ግለሰቦች ጀማል ኻሾግጂ ከተገደለ ከአስር ቀናት በኋላ ወደ ቱርክ እንደሄዱና ለአምስት ቀናት ተልዕኳቸውን ለመፈጸም እንደቆዩ፤ ከዚያም ለሶስት ቀናት በቱርክ ቆይታ አድርገው ወደ ሳዑዲ እንደተመለሱ አስነብቧል። የሳዑዲ ምላሽ ጀማል ኻሾግጂ ከተሰወረ በኋላ በሳዑዲ መንግሥት ሲሰጥ የነበረው ምላሽ የሚጣረስ ሆኖ ቆይቷል። በወቅቱ የቱርክ ባለስልጣናት በሳዑዲ ሰዎች ስለመገደሉ የድምጽ ማስረጃ አለን ያሉ ቢሆንም ሳዑዲ ግን በተደጋጋሚ ጀማል ወደ ቆንጽላው ከገባ ከደቂቃዎች በኋላ ቆንጽላውን ለቆ ወጥቷል ስትል ቆይታለች። ሳዑዲ ጀማል ከተሰወረ ከቀናት በኋላ ደግሞ መገደሉን አምናለች። ሳዑዲ መገደሉን ከማመኗ በፊት፤ የሃገሪቱ ጠቅላይ አቃቢ ሕግ በቆንጽላው ውስጥ በነበሩ ሰዎች እና በጀማል መካከል በተፈጠረ ጸብ ምክንያት ሊሞት ችሏል ብላ ነበር። ጀማል ኻሾግጂ ማን ነበር? ጀማል ኻሾግጂ በሳዑዲ ዝነኛ ጋዜጠኛ ነበር። የሶቪየት ሕብረት የአፍጋኒስታን ወረራን በዝርዝር ዘግቧል። እንደ ኦሳማ ቢን ላደን ላሉ ግለሰቦች ቃለ መጠይቅ አድርጓል። ለበርካታ አሰርት ዓመታት ለሳዑዲ ንጉሳውያን ቤተሰብ የቅርብ ሰው የነበረ ሲሆን፤ የሳዑዲ መንግሥት የመገናኛ ብዙሃን አማካሪ ሆኖም ሰርቷል። ባለፈው ዓመት ግን ከሳዑዲ መንግሥት ጋር በተፈጠረ አለመግባባት ሃገር ጥሎ ወደ አሜሪካ ተሰደደ። አሜሪካ ሳለ የዋሽንግተን ፖስት አምደኛ ነበር። በጽሑፎቹ የሳዑዲ አረቢያውን ልዑል አልጋ ወራሽ ሞሐመድ ቢን ሰልማን ይተች ነበር። ይህ ከሳዑዲ መንግሥት ጋር ከፍተኛ ቅራኔ ውስጥ እንዳስገባው በርካቶች ይናገራሉ።
news-42114607
https://www.bbc.com/amharic/news-42114607
አስገራሚው የደቡብ ኮሪያ ፈተና
ደቡብ ኮሪያውን በከፍተኛ የትምህርት ተቋም መግቢያ ፈተና ወቅት የሚደረጉ አስገራሚ ጉዳዮችን ቢቢሲ ኮሪያ ይፋ አድርጓል።
በየዓመቱ በፈተናው ቀን ደቡብ ኮሪያዊያን ጉዞአቸውን ያዘገያሉ፤ የንግድ ገበያውና ሌሎች የንግድ እንቅስቃሴዎች ዘግይተው የሚጀመሩ ሲሆን አውሮፕላኖች ደግሞ መነሳትም ሆነ ማረፍ አይፈቀድላቸውም። ተማሪዎቹ ፈተና ላይ በመሆናቸው መላው ሃገሪቱ እንቅስቃሴዋ ለተወሰነ ጊዜ ይገታል። ቀኑ የከፍተኛ ትምህርት ተቋም መግቢያ ፈተና የሆነው የኮሌጅ 'ስኮላስቲክ ኤብሊቲ ቴስት' የሚሰጥበት ነው። ዘንድሮው ፈተና ባለፈው ዓመት እንዲሰጥ ዕቅድ ተይዞ የነበረ ቢሆንም ሃገሪቱን የደቡብ-ምስራቅ የድንበር አካባቢዎችና የፖሃንግ ከተማን በመታው መሬት መንቀጥቀጥ ምክንያት እንዲራዘም ተደርጓል። የፈተናው ቀን በተፈጥሮአዊ ምክንያት እንዲቀየር ሲደረግ ዘንድሮው መጀመሪያው ነው። እንደአሁኑ ዓይነት ችግር በማያጋጥምበትም ወቅት ቢሆን ፈተናው የተሳካ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የኮሪያ መንግሥት ብዙ ሥራዎችን ያከናውናሉ። ፈተናው እጅግ ከባድ ከሆኑ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተናዎች አንዱ ነው። በረራዎች አይፈቀዱም በፈተናው ወቅት ከሚከለከሉ ጉዳዮች ቀዳሚው ከአደጋ ጊዜ ውጭ ያሉ አውሮፕላኖች መነሳትም ሆነ ማረፍ አይፈቀድላቸውም። የበረራ ዕገዳው ተግባራዊ የሚደረገው የእንግሊዝኛ የማዳመጥ ክህሎት ፈተና በሚሰጥበት ጊዜ ሲሆን ለ35 ደቂቃዎች ይቆያል። በመላው ሃገሪቱ በሚሰጠው ፈተና ላይ ተማሪዎች የእንግሊዘኛ ድምፅም ያለምንም ችግር እንዲሰሙ ለማገዝ የተደረገ ነው። ፈታኞች በአንድ ቦታ ይቆያሉ በየዓመቱ ፈተናው ያወጡና ያስተካከሉ እና በተለያዩ ሥራ ደረጃ ላይ የሚገኙ የፈተና ድርጅቱ ሠራተኞች በማይታወቅ ቦታ እንዲቆዩ ይደረጋል። ይህ ደግሞ ስለፈተናው ምንም ዓይነት መረጃ እንዳይወጣ ያደርጋል። እንዲቆዩበት በሚዘጋጅላቸው ቦታም ቢሆን ከማንም ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት እንዳይኖራቸው ይደረጋል። ከቤተሰብ ውስጥ ሰው ሲሞት ወይም ሌላ ተመሳሳይ አጣዳፊ ችግር ካልተከሰተባቸው በስተቀር ከሚዘጋጅላቸው ቦታ እንዲወጡ አይፈቀድላቸውም። በችግር ወቅት እንዲወጡ ሲደረግም የሚንቀሳቀሱበት ቦታ የተገደበ ሲሆን በደህንነት ሰዎችም ክትትል ይደረግባቸዋል። በዘንድሮው ዓመት ከህዳር 4 ጀምሮ ከሰባት መቶ በላይ የፈተና ድርጅት ባልደረባ ሠራተኞች በተጋጀላቸው ቦታ እንዲቆዩ ተደርጓል። ይህ ማለት ከወር በላይ ከተቀረው ዓለም ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት የላቸውም ማለት ነው። አስቸኳይ ጊዜ አገልግሎቶች መረጃ ሾልኮ ከወጣ ወይንም ደግሞ ተማሪው መፈተኛ ክፍሎች ከተዘጉ በኋላ ከመጣ፤ ፈተናውን ደግሞ እንዲወስድ ወይም በሌላ ቀን እንዲፈተን አይፈቀድለትም። የኮሪያ ብሔራዊ ፖሊስ ድርጅት የዘንድሮውን ፈተና ሁኔታ እንዲከታተሉ 18018 የፖሊስ አባላትን በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች አሰማርቷል። የእሳት አደጋ ክፍሉ ደግሞ አደጋ መከላከያ መኪናዎችን ከማሰማራት በተጨማሪ ለተማሪዎች ደህንነትና ትራንስፖርት አገልግሎት ለመስተት የአደጋ ጊዜ መኪናዎችን አሰማርቷል። ከመደበኛው ጊዜ በቁጥር የሚልቁ ታክሲዎች ለስራ የሚሰማሩ ሲሆን የመንግሥትና የግል መኪናዎች ብዙ ሰዎች ትራንስፖርት በሚጠቀሙባቸው አካባቢዎች ለተማሪዎቹ በተጠባባቂነት ይሰማራሉ። ባንኮችና የግል ድርጅቶች ዕረፍት ያገኛሉ በተማሪዎቹ ትራንስፖርት እንቅስቃሴ ላይ ችግር ላለመፍጠር በሚል የኮሪያ ምርት ገበያ ስራውን የሚጀምረው ከመደበኛ ሰዓቱ በአንድ ሰዓት ዘግየት ብሎ ነው። ብዙ የግል ተቋማትም ስራ የሚጀምሩበትን ሰዓት ያዘገያሉ። ፈተናው ውስብስብ እና ጠንካራ ከመሆኑም በላይ ተፈታኞች ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግባት አለመግባታቸውን የሚወስን ነው። ፈተናው "ቀሪውን ህይወት የሚወስን" ተብሎ በብዙዎች የሚገመት ሲሆን መንግስትም ተማሪዎች በፈተናው ቀን ጥሩ ሁኔታ እንዲመቻችላቸው ጥረት ያደርጋሉ።
news-55264261
https://www.bbc.com/amharic/news-55264261
ኮሮናቫይረስ፡አሜሪካ ሶስት ሚሊዮን ዜጎቿን በሳምንት ለመከተብ አቅዳለች
አሜሪካ የፋይዘር/ባዮንቴክ የኮሮናቫይረስ ክትባት ለአስቸኳይ ጊዜ አገልግሎት እንዲውል ፍቃድ መስጠቷን ተከትሎ ከነገ ጀምሮ ክትባት እንደሚጀመር ተገልጿል።
የመጀመሪያው የተባለው ለ3 ሚሊዮን ዜጎቿ የሚሆን ክትባቶችም በመላው የአሜሪካ ግዛቶች እየተከፋፈለ እንደሆነ ስርጭቱን በበላይነት የሚቆጣጠሩት የአሜሪካ ጦር ጀነራል ጉስታፍ ፔርና አስታውቀዋል። የኮሮናቫይረስ በሽታን በመከላከል 95 በመቶ ድረስ አስተማማኝ መሆኑ የተገለፀው ክትባት ደህንነቱንም በተመለከተ የምግብና መድኃኒት አስተዳደርም (ኤፍዲኤ) ማረጋገጫ ሰጥቷል። በኮሮናቫይረስ ክፉኛ እየተጠቃችው ባለው አሜሪካ በትናንትናው ዕለት ብቻ 3 ሺህ 309 ዜጎቿን አጥታለች። አኃዙን ሪፖርት ያደረገው የጆንስ ሆፕኪንስ ዩኒቨርስቲ ድረገፅ የበለጠ እንደሚያስረዳው በአለም ላይ ከፍተኛ በቀን የተመዘገበ ሞትም አድርጎታል። በአሜሪካ ከህዳር ወር ጀምሮ የኮሮናቫይረስ ሞቶች እየጨመሩም እንደሆነ መረጃዎች ይጠቁማሉ። የፋይዘር/ባዮንቴክ የኮሮናቫይረስ ክትባትን ለአስቸኳይ ጊዜ መጠቀም ፍቃድ እንዲያገኝ በከፍተኛ ሁኔታ በትራምፕ አስተዳደር ጫና የተደረገበት የምግብና መድኃኒት አስተዳደርም ውሳኔውን የወረርሽኙ "አዲስ ምዕራፍ" ብለውታል። ይኸው ተመሳሳይ ክትባት በዩኬ መሰጠት የተጀመረ ሲሆን አሜሪካም ፍቃድ መስጠቷን ተከትሎ በነበረ ጋዜጣዊ መግለጫ ጀነራል ጉስታፍ ፔርና በቀጣዩ 24 ሰዓታት ወደተለያዩ ግዛቶች መላክ ይጀመራል ብለዋል። "በመጪው ሰኞ በተለያዩ ግዛቶች የሚገኙ 145 ቦታዎች ክትባቱ እንደሚደርሳቸው ጠብቁ፣ በቀጣዩ ቀን ማክሰኞ በ425 ቦታዎች እንዲሁም የመጨረሻው በ66 ቦታዎች ረቡዕ ይከፋፈላል" በማለትም የመጀመሪያው ምዕራፍ ክትባት ፕሮግራም አስረድተዋል። በዚህም የመጀመሪያው ምዕራፍ ሶስት ሚሊዮን አሜሪካውያንን ለመከተብ ዕቅድ ተይዟል። ጀነራል ጉስታፍ ለጋዜጠኞች አክለውም እንደተናገሩት የኮሮናቫይረስን ለመግታት የሚያስፈልገው መጠንም ደህንነቱ በተጠበቀ መልኩ እንደሚጓጓዝ "መቶ በመቶ እርግጠኛ ነኝ" ብለዋል። በመጀመሪያው ሳምንት ለሁሉም አሜሪካዊ ማዳረስ ባይቻልም " ሁሉም አሜሪካዊ ክትባቱን እስኪያገኝ አናንቀላፋም" በማለትም አክለዋል። የፋይዘር ክትባት በዩኬ ፣ ካናዳ፣ባህሬንና ሳዑዲ አረቢያ ፈቃድ አግኝቷል። ልክ እንደነዚህ አገራት የአሜሪካ ባለስልጣናትም ቢሆን ለክትባቱ ቅድሚያ የሚሰጡት ለጤና ባለሙያዎችና በእንክክብካቤ ማዕከላትም ላሉ ነው ተብሏል። ተጋላጭ ማህበረሰብ ከተባሉት ውጭ ያሉ አሜሪካውያን ክትባቱ ይደርሳቸዋል ተብሎ የሚጠበቀው ጥር ወር ላይ ሳይሆን በአጠቃላይ በተትረፈረፈ መልኩም በሚያዝያ ወር አቅርቦት እንደሚኖርም ይጠበቃል።
news-54406746
https://www.bbc.com/amharic/news-54406746
እግር ኳስ ፡ ለጡረታ እየተዘጋጁ ያሉት የ80 ዓመቱ እግር ኳስ ተጫዋች
ለእግር ኳስ ጥልቅ ፍቅር ያላቸው የ80 አመቱ የእድሜ ባለፀጋ እግር ኳስ ተጫዋች ከሰሞኑ የመጨረሻ ጨዋታዬን አደርጋለሁ ብለዋል።
በአውስትራሊያ ነዋሪነታቸውን ያደረጉት እንግሊዛዊው ፒተር ዌብስተር ለጡረታም መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል። በባለፉት ጥቂት አመታት አቅማቸው ደክሞ ከዚህ ቀደም በነበራቸው የሰውነት አቋም ባለመሆናቸውም ከሚወዱት የእግር ኳስ ጨዋታ ለመገለልም ምክንያት ሆኗቸዋል። "ለባለፉት ጥቂት አመታት በእንደዚሁ አይነት ሁኔታ የነበርኩት። የምለብሰውንም ማልያ እያባከንኩ መሰለኝ" በማለትም ለቢቢሲ ተናግረዋል። ፒተር ዌብስተር የተወለዱት በጎሮጎሳውያኑ አቆጣጠር 1948 በእንግሊዟ ፕሬስተን ነው። በህፃንነታቸው ራግቢና እግርኳስ ይጫወቱ የነበረ ሲሆን በተለይም ከአስራ አምስት አመታቸው በኋላ ዝንባሌያቸው ወደ እግር ኳስ ሆነ። በፕሮፌሽናል ተጫዋችነትም በዌልስ ለሚገኙ ክለቦች በሃያዎቹና በሰላሳዎቹ እድሜያቸው ተጫውተዋል። በ1981ም ከባለቤታቸውና ከሶስት ልጃቸው ጋር ወደ አውስትራሊያ የሄዱ ሲሆን እዚያም ባለው የእግር ኳስ ደረጃ ከፍተኛ መሆን አድናቆትን እንደፈጠረባቸውም ከሰሞኑ ከቢቢሲ ጋር ባደረጉት ቆይታ ተናግረዋል። ለአስርት አመታትም በአውስትራሊያ ፊግትሪ የእግር ኳስ ክለብም ተጫውተዋል። የመጨረሻ ጨዋታቸውንም በያዝነው ሳምንት አርብ እለት እንዳደረጉም ተዘግቧል። በክለቡም ሆነ በአካባቢው ከፍተኛ ዝናን ያተረፉት ፒተር በሳቸውም ስም ውድድር ተሰይሞላቸዋል- ፒተር ዌብስተር ካፕ የሚባል። "እንዲህ አይነት ውድድሮች በስም የሚሰየሙት አንድ ሰው ገንዘብ ከከፈለ ወይም ከሞተ ነው። እኔ አልሞትኩምም አልከፈልኩም፤ እስቲ በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ እሞክራለሁ" ብለዋል። ለረዥም አመታት በእግር ኳስ ተጫዋችነታቸው ለመቆየት ሚስጥሩ ሳያቋርጡ መጫወታቸውና ከፍተኛ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ማድረጋቸው ነው። ለአመታትም ሩጫ፣ ሳይክል መንዳትን ያዘወትሩ የነበረ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት ግን ከእድሜ ጋር ተያይዞ የልጅ ልጃቸውን ውሻ ይዘው ለመራመድ ይወጣሉ። ምንም እንኳን እግር ኳስ ከመጫወት ራሳቸውን ቢያገሉም የልጅ ልጆቻቸው እግር ኳስ ሲጫወቱም እመለከታለሁ ብለዋል። ከዚህ ቀደም ራሳቸው ጨዋታ ስለነበራቸው የነሱን ጨዋታ መመልከት አልቻሉም ነበር። ባለቤታቸውም በቤት ስራዎች እንዲያግዙዋቸው ጡረታ የሚወጡበትን ቀን በጉጉት እየጠበቀች እንደሆነም ተናግረዋል። የፊግ ትሪ የእግር ኳስ ክለብ ፕሬዚዳንት ማይክ ዶድ የእድሜ ባለፀጋው እግር ኳስ ተጫዋች አስተዋፅኦ "ከቃላት በላይ ነው" በማለትም አሞግሰዋቸዋል።
news-57101750
https://www.bbc.com/amharic/news-57101750
ምርጫ 2013፡ ስድስተኛውን አገራዊ ምርጫ በተያዘለት ቀን ለማካሄድ እንደማይቻል ምርጫ ቦርድ አስታወቀ
ስድስተኛውን አገር አቀፍ ምርጫ በተያዘለት ቀን ማካሄድ እንደማይቻል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዛሬው ዕለት ግንቦት 7፣ 2013 ዓ.ም ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ምክክር እያደረገ ባለበት ወቅት እንዳለው አገር አቀፉን ምርጫ በተያዘለት ቀን ማካሄድ እንደማይቻል አስታውቋል። በዛሬው ዕለት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በስድስተኛው አገር አቀፍ ምርጫ ዙሪያ መክሯል። በምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ስድስተኛው አገር አቀፍ ምርጫ ግንቦት 28 እና ሰኔ 5 ቀን 2013 ዓ.ም ለማካሄድ እቅድ ተይዞ ነበር። ይሁንና የምርጫ ካርድ ምዝገባው እና ሌሎች ስራዎች በተያዘላቸው ቀናት ባለመጠናቀቃቸው የተነሳ ምርጫው በተያዘለት ቀን መካሄድ እንደማይችል አስታውቋል። ምርጫ ቦርድ አክሎም በአዲሱ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት አዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ከቀሪው የአገሪቱ ክፍል ጋር በተመሳሳይ ቀን ተወካዮቻቸውን ይመርጣሉ ብሏል። በመሆኑም ድምጽ መስጫው በሁለት ወይንም በሶስት ሳምንታት እንዲራዘም ቦርዱ ለፖለቲካ ፓርቲዎች ጥያቄ አቅርቧል። ከፖለቲካ ፓርቲዎች የሚገኘውን ሃሳብ ግምት ውስጥ በማስገባት በቅርቡ ውሳኔ ላይ እንደሚደረስና ይፋ እንደሚደረግም ምርጫ ቦርድ አስታውቋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተጨማሪ በዛሬው ምክክር ላይ እንዳስታወቀው እስከ ግንቦት 4 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስ 36 ሚሊዮን 245 ሺህ 444 ሰዎች የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውን ገልጿል። የምርጫ ካርድ ከወሰዱት መካከል 16.6 ሚሊዮኑ ሴቶች ሲሆኑ ፤ 19.5 ሚሊዮኑ ደግሞ ወንዶች ናቸው፡፡ ምርጫ ቦርድ ከዚህ በፊት 50 ሚሊዬን ዜጎች ካርድ ሊወስዱ እንደሚችሉ ግምቱን አስታውቆ ነበር። እንደ ምርጫ ቦርድ መረጃ ከሆነ ጋምቤላ፣ አዲስ አበባ፣ ሶማሌ እና አፋር ክልሎች ከተገመተው በላይ የመራጮች ካርድ ከተወሰደባቸው መካከል ናቸው። በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል በአንጻራዊነት ዝቅተኛ የመራጮች ምዝገባ መከናወኑን የምርጫ ቦርድ መረጃ ያሳያል።
news-47335304
https://www.bbc.com/amharic/news-47335304
በምዕራብ ኦሮሚያ የእርቅ ኮሚቴ አባላት ታፍነው ተወሰዱ
የኦሮሞ ነጻነት ግንባር እና በመንግሥትን መካከል የተደረሰውን ስምምነት ተከትሎ የግንባሩን ወታደሮች ለመቀበል ወደ ቄለም ወለጋ አቅንተው የነበሩ ከሦስት ያላነሱ የአስታራቂ ኮሚቴ አባላት ታፍነው መወሰዳቸው ተሰምቷል።
በቄለም ወለጋ ታፍነው ተወስደዋል የተባሉት የእርቅ ኮሚቴ አባላት መካከል ከቀኝ ወደ ግራ የሚታዩት ሁለቱ ግለሰቦች ይገኙበታል የእርቅ ኮሚቴው ሰብሳቢ የሆኑት አባ ገዳ በየነ ሰንበቶ ለቢቢሲ እንዳረጋገጡት የኮሚቴው አባላት የሆኑ ሁለት አባ ገዳዎች እና አንዲት ሴት በቄለም ወለጋ አንፊሎ ተብሎ ከሚጠራ ስፍራ ታፍነው እንደተወሰዱ ተናግረዋል። አባ ገዳ በየነ ሰንበቶ ''ለማግባባት ወጣ እንዳሉ ነው ታፍነው የተወሰዱት፤ ክፉ ነገር እንደማይገጥማቸው እርግጠኛ ነኝ። ይህንም ችግር በቅርቡ እንፈታዋለን'' ሲሉ ለቢቢሲ ገልጸዋል። • "ከ[እኛ] የተለየን ጦር 5 በመቶ እንኳ አይሆንም" መሮ የኦነግ ጦር አዛዥ ''ብዙ ፈተናዎች እንደሚኖሩን እየወቅን ነው እርቅ ወደማውረዱ የገባነው። እርቅ ለማምጣት ነው እየሰራን ያለነው። ሰላምም ይሰፍናል። የሚያጋጥሙን ችግሮች ወደ ኋላ አያሰቀሩንም'' ሲሉም ጥረታቸውን በዚህ ምክንያት እንደማያቋርጡም ተናግረዋል። ከዚሁ ጉዳይ ጋር በተያያዘ አነጋግረነው የነበረው የኮሚቴው ፀሃፊ ጀዋር መሃመድም የእርቅ ኮሚቴ አባላት ችግር እየገጠማቸው እንደሆነ ተናግሯል። ''የገጠመ ችግር አለ። በተለያዩ ስፍራዎች የሚገኙ ከኮሚቴው አባላት ጋር ውይይት ከተደረገ በኋላ ለህዝቡ መግለጫ እንሰጣለን'' ሲል ጀዋር ገልጿል። ጀዋር ሃሙስ ምሽት ላይ በፌስቡክ ገጹ ላይ ታፍነው ተወስደዋል ያላቸውን አራት ሰዎች ከስም ዝርዝራቸው ጋር አውጥቷል። ታፍነዋል ተወስደዋል የተባሉት ሰዎች የት እንዳሉ ምንም አይነት መረጃ እንደሌላቸው ተናግሯል። • በምዕራብ ኦሮሚያ በታጠቁ ኃይሎች የተገደሉ ሰዎች ቁጥር 41 መድረሱ ተገለፀ በተመሳሳይ መልኩ በምዕራብ ወለጋ መነ ሲቡ ወረዳ የቴክኒክ አባላቱ ድብደባ እንደተፈጸመባቸው ከነዋሪዎች ሰምተናል። ተፈጸሟል ስለተባለው ድብደባ ግን ከቴክኒክ ኮሚቴው አባላት ማረጋገጥ አልተቻለም። የእርቅ ኮሚቴ አባላቱን ማን አፈናቸው? የቴክኒክ ኮሚቴ ሊቀመንበር የሆኑት አባ ገዳ በየነ ሰንበቶም ሆኑ የኮሚቴው ፀሃፊ ጀዋር መሃመድ የእርቅ ኮሚቴውን አባላት ያፈነው ኃይል ይህ ነው በማለት በስም ከመጥቀስ ተቆጥበዋል። ጀዋር የአባላቱን መታፈን ይፍ ባደረገበት ጽሁፍ ''እየደረሰብን ያለውን ስቃይ ሁሉ በሆዳችን ይዘን እየሄድን ነው። አሁን ግን የህይወት ጉዳይ ስለሆነ መናገር አለብን። አባ ገዳዎች፣ እናቶች እና የሃገር ሽማግሌዎች ለሃገር ሰላም እና እርቅ ለማውረድ ነው የሚደክሙት እንጂ ምንም በደል አልፈጸሙም። በአስቸኳይ እንዲለቀቁን እንጠይቃለን'' ሲል በፌድቡክ ገጹ ላይ አስፍሯል። ከዚህ ቀደምም በምዕራብ ኦሮሚያ የደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት የነበሩት ዶ/ር ደለሳ ቡልቻ ለሁለት ቀናት ታፍነው ከቆዩ በኋላ መለቀቃቸው ይታወሳል። ዶ/ር ደለሳ የገጠማቸውንና ማን እንዳፈናቸው ለመናገር ፍቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል። በምዕራብ ኦሮሚያ የሚገኙ ባንኮች በተዘረፉበት ወቅትም የባንክ ሰራተኞችም ታፍነው ተወስደው እንደነበረ ይታወሳል።
48850570
https://www.bbc.com/amharic/48850570
በሊቢያ በስደተኞች መጠለያ ጣቢያ ላይ በደረሰ የአየር ጥቃት ቢያንስ 40 ሰዎች መሞታቸው ተነገረ
በሊቢያ የስደተኞች ማቆያ ላይ በደረሰ የአየር ጥቃት በትንሹ 40 ሰዎች መሞታቸውን ባለስልጣናት ተናገሩ።
ጥቃቱ የደረሰው በትሪፖሊ ምስራቃዊ ክፍል በሚገኝ ታጆራ በሚባል ስፍራ ሲሆን 80 ሰዎች በፍንዳታው መቁሰላቸው ተገልጿል። ከሞቱት መካከል አብዛኞቹ አፍሪካውያን ስደተኞች ናቸው ተብሏል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሊቢያ ወደ አውሮጳ መሻገር ለሚፈልጉ ስደተኞች መነሻ ሆና እያገለገለች ነው። • የአውሮፕላን ጎማ ሥር ተደብቆ እንግሊዝ መግባት ያሰበው ግለሰብ ወድቆ ሞተ ሊቢያ ለረዥም ጊዜ ሲያስተዳድሯት የነበሩት ሙአመር ጋዳፊ እ.ኤ.አ በ2011 ከስልጣን ከወረዱ በኋላ በግጭት እየታመሰች ሲሆን የተለያዩ የጦር አበጋዞች በሚቆጣጠሯቸው ስፍራዎችም ተከፋፍላ ትገኛለች። የድንገተኛ ጊዜ አገልግሎት ቃል አቀባይ የሆነው ኦሳማ አሊ ለፈረንሳዩ የዜና ወኪል እንደተናገረው ከሆነ የአየር ጥቃቱ የስደተኞች መቆያውን ሲመታ 120 ስደተኞች በውስጡ ነበሩ። አክሎም የሟቾች ቁጥር ሊጨምር ይችላል ያለ ሲሆን አሁን ያለውን መረጃ በቅድመ ዳሰሳ ያገኘነው ሲል ገልጿል። በተባበሩት መንግሥታት የሚደገፈው መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትር የሆኑት ፋዬዝ አል ሴራ ራሱን የሊቢያ ብሔራዊ ጦር ብሎ የሚጠራውን አማጺ ኃይል ለጥቃቱ ተጠያቂ አድርገዋል። ጥቃቱ ማክሰኞ እለት የደረሰ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመግለጫቸው "ቀድሞ የታሰበበት" እና ማቆያውን "ኢላማ ያደረገ" ነው በማለት ያወገዙ ሲሆን ድርጊቱ "ከባድ ወንጀል" ሲሉ ገልጸውታል። • አምስት ሰዎች ደቡብ ወሎ ውስጥ በደቦ ጥቃት ተገደሉ አማፂ ቡድኑ በኻሊፋ ሐፍታር የሚመራ ሲሆን ጥቃቱ በደረሰበት አካባቢ በተባበሩት መንግሥታት የሚደገፈውን መንግሥት በመዋጋት ይታወቃል። ሰኞ እለት ጠንከር ያለ የአየር ጥቃት እንደሚያደርግ ገልጾ የነበረ ሲሆን በኢላማውም የተመረጡ ያላቸውን ስፍራዎች እንደሚያጠቃ አሳውቆ ነበር። የተባበሩት መንግሥታት ስደተኞች ድርጅት በስደተኞች ማቆያ ላይ የደረሰውን የአየር ጥቃት "እጅጉን አሳሳቢ" ሲል ገልጾታል። ዶክተር ቢን አታኢ ጥቃቱ በደረሰበት የስደተኞች ማቆያ የተገኙ ሲሆን "እዚህም እዚያም ሰው ይታያል" ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረው "መጠለያው ወድሟል፤ ሰዎች ያለቅሳሉ፤ የስነልቦና ቀውስ አለ፣ ሰቅጣች ነው" ሲሉ ሁኔታውን ገልፀውታል። • ኢትዮጵያ ከገባችበት የፖለቲካ ቅርቃር እንዴት ትውጣ? በሺዎች የሚቆጠሩ በሊቢያ ተሻግረው አውሮጳ ለመድረስ የሚያስቡ ስደተኞች የሚቆዩት መንግሥት በሚቆጣጠራቸው የስደተኛ ማቆያዎች ሲሆን አብዛኞቹ እነዚህ መጠለያዎች የሚገኙት ከአማፂያን ጋር ጦርነት በሚደረግባቸው ስፍራዎች ነው። በሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች የእነዚህ መጠለያ ጣቢያዎች አያያዝ ትችት ይቀርብበታል። የአውሮጳ ህብረት ከሊቢያ ድንበር ጠባቂዎች ጋር በመተባበር የስደተኞች ጀልባን በቁጥጥር ስር ለማዋል እየሰራ ይገኛል። ነገር ግን ሰዎችን በድብቅ የሚያሻግሩ ቡድኖች የሀገሪቱን አለመረጋጋት እና ያለውን ቀውስ ተጠቅመው አውሮጳ ለመግባት የሚጓጉ ስተኞችን በነፍስ ወከፍ በርካታ ሺህ ዶላር ያስከፍሏቸዋል። • "ከፍተኛ ችግር ውስጥ ገብተናል. . . ግን እናሸንፋለን"
news-52831176
https://www.bbc.com/amharic/news-52831176
መንግሥት ከምዕራብ ኦሮሚያ ለሚሰማው እሮሮ ተጠያቂው "ሸኔ ነው" አለ
በምዕራብ ኦሮሚያ በሚገኙ አራት ዞኖች በተለይም በምዕራብ ወለጋ እና ቄለም ወለጋ ዞኖች ውስጥ 'በመንግሥት ጸጥታ አስከባሪ ኃይሎች ግድያዎች እየተፈጸሙ ነው' የሚሉ ተደጋጋሚ እሮሮዎች ከነዋሪዎች ይሰማል።
በመንግሥት ጸጥታ አስከባሪ ኃይሎች ተገደለች ተባለችው አምሳሉ ጉደታ ከእነዚህ መካከል በምዕራብ ወለጋ ዞን ላሎ አሰቢ ወረዳ ኬሌዬ ቢርቢር በምትሰኝ ቀበሌ ውስጥ ተገደሉ የተባሉት የአራት ልጆች እናት ይገኙበታል። ወ/ሮ አምሳሉ ጉደታ የአራት ልጆች እናት ሲሆኑ ሐሙስ ግንቦት 13 2012 በእርሻ ሥራቸው ላይ ሳሉ በመንግሥት ጸጥታ አስከባሪ ኃይሎች በጥይት ተመትተው መገደላቸውን ባለቤታቸው አቶ ሚረቴ ኢማና ይናገራሉ። "ጥላብኝ የሄደችው ህጻናት 'እናታችን መቼ ነው የምትመጣው' እያሉ ይጨቀጭቁኛል" ይላሉ አቶ ሚረቴ ኢማና። በተመሳሳይ መልኩ በምዕራብ ወለጋ ዞን የገንጂ ወረዳ ነዋሪ የነበረው ወጣት ለሊሳ ተፈሪ ከሁለት ሳምንት በፊት በአካባቢው ተሰማርቶ በሚገኘው የመንግሥት ኃይል በቁጥጥር ሥር ከዋለ ከሁለት ቀናት በኋላ ሞቶ መገኘቱን ቤተሰቦቻቸውን አነጋግረን መዘገባችን ይታወሳል። የወጣቱ እናት ወ/ሮ ጫልቱ ሁንዴሳ ልጃቸው ታስሯል ወደተባለበት ስንቅ ይዘው ሄደው "የልጄ አስክሬን በሸራ ተጠቅልሎ ሜዳ ላይ ተጥሎ አገኘሁ። የልጄን ሞት እዚያው ተረዳሁ" በማለት ለቢቢሲ ተናግረው ነበር። በአከባቢው 'የሸኔ አባላት ጋር ግንኙነት አላቸው ወይም ደጋፊ ናቸው" የሚባሉ ሰዎች ለእስር እየተዳረጉም እንደሆነ የአካባቢው ነዋሪዎች ይናገራሉ። በጉዳዮ ዙሪያ ምላሽ እና ማብራሪያ ለማግኘት የአካባቢውን ባለስልጣናት ለማነጋገር ያደረግነው ሙከራ አጥጋቢ ምላሽ ሳያገኝ መቅረቱን በቀደመ ዘገባችን ተጠቁሟል። 'መነሻው ሸኔ ነው' ቢቢሲ የኦሮሚያ ክልል የአስተዳደር እና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊን በስልክ አግኝቶ ማነጋገር ችሎ ነበር። የቢሮ ኃላፊ አቶ ጅብሪል ሞሐመድ በመንግሥት የጸጥታ አስከባሪዎች ላይ የሚቀርበው አቤቱታ ሐሰት ነው። ይህ ክስ መሠረተ ቢስ ነው ይላሉ። "ጸረ-ሰላም ኃይሎች ራሳቸው ገድለው መንግሥት ላይ ማሳበባቸው የተለመደ ነው" ያሉት አቶ ጅብሪል፤ "እኛ ሰላማዊ ዜጋ ገድለን አናውቅም፤ የጸጥታ መዋቅሩም ሰላማዊ ሰው አይገድልም። ለሚሞቱ ሰዎች መነሻውም መጨረሻውም ሸኔ ነው" ይላሉ። የአስተዳደር እና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊው ለግድያዎቹ ሸኔን ተጠያቂ የሚያደርጉበትን ምክንያት ሲያስረዱ፤ "የመጀመሪያው መንግሥት እና ህዝብ የሰጣቸውን ሰላማዊ ትግል 'አንቀበልም' በማለት የደህንነት ችግር ፈጥረዋል። ሁለተኛው ደግሞ ህዝብ ወደ ሚኖርበት ገብተው፣ ህዝብ መካከል ሆነው ወደ ጸጥታ አስከባሪዎች ይተኩሳሉ" ብለዋል። በዚህም ምክንያት ንጹሃን ዜጎች እየተጎዱ መሆኑን ጨመረው ያስረዳሉ። አቶ ጅብሪል ለግድያዎቹ ሸኔ ተጠያቂ ስለመሆኑ የሚያቀርቡት ሌላኛው መከራከሪያ፤ በዚህ ሁኔታ ንጹሃን ዜጎች ሲጎዱ የመንግሥት ኃይል ሰው ገደለ ብለው በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ይለጥፋሉ፤ አባላቶቻቸው ሲገደሉም 'ንጽህ ዜጋ በመንግሥት ኃይል ተገደለ' ይላሉ"። አቶ ጅብሪል በመንግሥት ኃይሎች እና በታጣቂዎች መካከል በሚደረጉ የተኩስ ልውውጦች ንጹሃን ዜጎች እየተጎዱ እንደሆነ ያረጋገጣሉ። "ከዚህ ቀደም እኔ በነበርኩበት ቦታ ተኩስ ከፍተው፤ የሸኔ ኃይል እየተንቀሳቀስ እያየን፤ ህጻናት፣ ሴቶች እና አዛውንቶች መካከል በመግባታቸው መምታት እየቻልን፤ ተኩስ እንዲቆም አስደርጊያለሁ" ይላሉ አቶ ጅብሪል። ባለቤታቸው የተገደለችባቸው አቶ ሚረቴ ከአራት ልጆቻቸው ጋር የአራት ልጆች እናት እንዴት ተገደሉ? አቶ ሚረቴ እንደሚሉት ባለቤታቸው የበቆሎ ማሳ ውስጥ እያለች በተተኮሰባቸው ጥይት ተመተው ህይወታቸው አልፏል። "የአንድ ዓመት ህጻን የእናቷ አስክሬን አጠገብ ቁጭ ብላ እንዳለች ነው የባለቤቴን አስክሬን ያነሳሁት" በማለት በሃዘን ተውጠው ይናገራሉ። ባለቤታቸው በጥይት ተመትታ ስትገደል በአካባቢው የነበሩ ሰዎች ተመልክተዋል ይላሉ አቶ ሚረቴ። አቶ ሚረቴ እንደሚሉት ከሆነ ከባለቤታቸው ግድያ አንድ ሳምንት በፊት፤ እርሳቸውም በመንግሥት ጸጥታ አስከባሪ ኃይሎች ድብደባ ተፈጽሞባዋል። • 119 ቤተ እስራኤላውያን ከኢትዮጵያ ወደ እስራኤል አቀኑ • ዶናልድ ትራምፕ ፌስቡክን ሊዘጉት ይሆን? "ከአንድ ሳምንት በፊት ደግሞ 'ሸኔ ያለበትን ቦታ ታውቃለህ' ብለው እጄን ወደኋላ አስረው በድብደባ ሰባብረውኝ በቤት ውስጥ አስቀርተውኛል" ይላሉ። በደረሰባቸው ድብዳበ ከቤት ወጥቶ ሥራ መስራት አዳግቷቸው እንደነበረ እና ቤተሰቡ በሙሉ በባለቤታቸው ትከሻ ላይ ወድቆ እንደነበረ ይናገራሉ። "ትናንት በጉልበቴ ሰርቼ ቤተሰቤን አስተዳድር ነበር። አሁን ተሰብሬ ቤት ተቀምጬ ባለሁበት ወቅት የምትረዳኝን የልጆቼን እናት ነጠቁኝ" ይላሉ።ከዚህ ቀደም በአካባቢው በመንግሥት እና ታጣቂዎች መካከል ግጭት ይከሰት እንደነበረ አስታውቀው፤ ባለቤታቸው በተገደለችበት ወቅት ግን በአካባቢያቸው ምንም አይነት ግጭት እንዳልነበረ ተናግረዋል። "እሷ ለመግደል ታስቦ ነው የተተኮሰባት" ይላሉ። በባለቤታቸው ግድያ ተጠርጥሮ የተያዘም ሆነ የባለቤታቸውን ግድያ ለመመርመር የመጣ የመንግሥት አካል እንደሌለ አቶ ሚረቴ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
news-57067385
https://www.bbc.com/amharic/news-57067385
ኮሮናቫይረስ፡በደርዘን የሚቆጠሩ አስከሬኖች በህንድ ወንዝ ዳርቻ ላይ ተገኙ
በሰሜናዊ ህንድ በጋንጀስ ወንዝ ዳርቻ ቢያንስ የ 40 ሰዎች አስከሬን በውሃ ተገፍቶ መገኘቱን ባለስልጣናት ገለጹ፡፡
አስከሬኖቹ በቢሃር እና በኡታር ፕራዴሽ ግዛቶች ድንበር አቅራቢያ መገኘታቸውን ቢቢሲ አረጋግጧል፡፡ አስከሬኖቹ እንዴት እንደመጡ ግልፅ ባይሆንም የአከባቢው የመገናኛ ብዙሃን የኮቪድ-19 ሰለባዎች ሊሆኑ ይችላሉ ብለዋል፡፡ አንዳንድ የመገናኛ ብዙሃን ደግሞ እስከ 100 የሚደርሱ አስከሬኖች መገኘታቸውን ጠቅሰው አስከሬኖቹ በወንዙ ውስጥ ለብዙ ቀናት እንደቆዩ ምልክቶች ተገኝተዋል ብለዋል፡፡ የአከባቢው ባለሥልጣን አሾክ ኩማር የአከባቢውን ነዋሪዎችን ከጠየቁ በኋላ ለቢቢሲ እንደገለጹት "አስከሬኖቹ ከኡታር ፕራዴሽ የመምጣት ዕድል አላቸው" ብለዋል፡፡ አስከሬኖቹ እንደሚቀበሩ ወይም እንደሚቃጠሉ ተናግረዋል፡፡ ባለስልጣናት አስከሬኖቹ ያበጡ እና በከፊል የተቃጠሉ እንደሆኑና ምናልባትም የኮሮናቫይረስ ተጎጂዎችን የማቃጠል ተግባር አካል ሆነው ወደ ወንዙ የደረሱ ሊሆኑ እንደሚችሉ መግለጻቸውን የህንዱ የኤንዲቲቪ የዜና አውታር ዘግቧል፡፡ አንዳንድ የአከባቢው ነዋሪዎች እና ጋዜጠኞች ለቢቢሲ ሂንዲ እንደተናገሩት ለእሳት ማቃጠያ የሚሆን የእንጨት እጥረት እና ከቀብር ሥነ ሥርዓቶች ጋር ተያይዞ እየጨመረ የመጣው ወጪ አንዳንድ ቤተሰቦች በኮሮናቫይረስ ህይወታቸውን ያጡ ዘመዶቻቸውን ወደ ወንዝ እንዲጥሉ እያደረገ ነው፡፡ የአከባቢው ነዋሪ የሆኑት ቻንድራ ሞሃን "የግል ሆስፒታሎች ሰዎችን እየዘረፉ ነው። ብዙ ሰዎች ለካህናት እና በወንዙ ዳርቻ ላይ ለማቃጠል የሚጠየቀውን ገንዘብ አይኖራቸውም። አስከሬኑን በአምቡላንስ ለመውሰድ ብቻ 27 ዶላር ስለሚጠየቅ የመጨረሻው አማራጫቸው አስከሬኑን በወንዙ ውስጥ መጣል ነው" ብለዋል፡፡ ኡታር ፕራዴሽ በሕንድ ውስጥ በጣም ብዙ የህዝብ ቁጥር ያለው ክልል ነው ፡፡ ሁለተኛው የኮቪድ ማዕበል ሕንድን እያመሳት ሲሆን ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ በቫይረሱ ህይወታቸው የሚያልፉ ሰዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ ነው፡፡ አብዛኛዎቹ የአገሪቱ የሬሳ ማቃጠያ ስፍራዎች ሞልተዋል፡፡ አገሪቱ አሁን የዓለም ዋነኛ ወረርሽኝ ማዕከል ሆናለች፡፡ ሕንድ ወረርሽኙ ከተከሰተበት ጊዜ አንስቶ ከ 22.6 ሚሊዮን በላይ ዜጎቿ በኮሮናቫይረስ ሲያዙ 246,116 የሚሆኑት ደግሞ ህይወታቸው ማለፉን የጆንስ ሆፕኪንስ ዩኒቨርሲቲ መረጃ አመልክቷል፡፡ ባለሙያዎቹ ትክክለኛው የሟቾች ቁጥር ከዚህ የበለጠ ሊሆን ይችላል የሚል እምነት አላቸው
news-52917354
https://www.bbc.com/amharic/news-52917354
ጆርጅ ፍሎይድ፡ በጥቁር አሜሪካዊው ሞት ትብብር የተጠረጠሩ ሶስት ፖሊሶች ተከሰሱ
በጥቁር አሜሪካዊው ጆርጅ ፍሎይድ ግድያ ዙሪያ ተባብረዋል ተብለው የተረጠሩ ሦስት ፖሊሶች ክስ ተመስርቶባቸዋል።
ዋና ተጠርጣሪው የጆርጅ ፍሎይድ አንገት ላይ በጉልበቱ ቆሞ የነበረው ዴሪክ ቾቪን የተሰኘ ነጭ ፖሊስ ሲሆን፤ ክስ ተመስርቶበት የነበረው በሦስተኛ ደረጃ ግድያ ነበር። ትላንት የወጡ የፍርድ ቤት መዛግብት እንደሚያሳዩት ግን የሰውየው ክስ ወደ ሁለተኛ ደረጃ የግድያ ወንጀል ከፍ እንዲል ተደርጓል። በስፋት በተሰራጨው ምስል ላይ የሚታዩት የተቀሩት ሦስት ፖሊሶች በግድያ ውስጥ ተባብረዋል በሚል ተከሰዋል። ምንም እንኳ ከጆርጅ ፍሎይድ ሞት በኋላ ተቃውሟችን ለማሰማት የወጡ ሰላማዊ ሰልፈኞች በቢረክቱም በአንዳንድ ቦታዎች ሁኔታው ወደለየት ሥርዓት አልበኝነትና ግጭት ተቀይሮ ነበር። የሦስቱን ፖሊሶች ክስ ያነበቡት የሚኒሶታ ጠቅላይ አቃቤ ሕግ ኪይዝ ኤሊሰን ፖሊሶቹን "ፍትህ ትፈልጋቸዋለች" ሲሉ ተደምጠዋል። የጆርጅ ፍሎይድ ሞት በሚኒያፖሊስ ከተማ ከፈጠረው ተቃውሞ በኋላ ከሥራቸው እንዲታገዱ የተደረጉት ሦስቱ ፖሊሶች ሁለተኛ ደረጃ ግድያን አስተባብረዋል፤ ወንጀሉን ማስቆም አልቻሉም በሚል ተጠርጥረው ፍርድ ቤት እንደሚቀርቡ ይጠበቃል። የሚኒሶታ ሴናተር የሆኑት ኤሚ ክሎቡቻር በትዊተር ገፃቸው ላይ "ወደ ፍትህ ለምናደርገው ጉዞ አንድ ደረጃ የጨመረ" ሲሉ የፖሊሶቹ መከሰስ አግባብ እንደሆነ ፅፈዋል። የፍሎይድ ቤተሰብ ጠበቃ ቤንጃሚን ክራምፕ ባወጡት መግለጫ "ክሱ ፍትህን ለማስከበር ወሳኝ ነው። የጆርጅ ፍሎይድ ሬሳ አፈር ከመቅመሱ በፊት ክሱ በመመስረቱ ደስተኞች ነን" ብለዋል። ነገር ግን ዘግየት ብሎ ሲኤንኤን የተሰኘው የቴሌቪዥን ጣቢያ ላይ ጠበቃው ቀርበው ዋና ተጠርጣሪው በአንደኛ ደረጃ የግድያ ወንጀል መከሰስ ነበረበት ሲሉ ተደምጠዋል። አልፎም በጉዳዩ ላይ ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን አሳውቀው ክሱ ሊቀየር እንደሚችል ፍንጭ ሰጥተዋል። የመብት ተሟጋቹ ቄስ አል ሻርፕተን የፍሎይድ ጉዳይ የፌዴራል ክስ መሆን አለበት ይላሉ። "ይህ ጉዳይ የፌዴራል ክስ ሆኖ ካልታየ ዜጎች ከፖሊስ ጭካኔ ይድናሉ ብሎ ማሰብ ዘበት ነው። ይሄ ሁሉ ድራማ ነው ማለት ነው። መንገድ ላይ የታየው ድራማ ለመሠረታዊ ለውጥ ደጀን ሊሆን ይገባል።" ጠቅላይ አቃቤ ሕጉ ኤሊሰን፤ "ፖሊሶቹ ተከሰሱ ማለት ፍርድ አገኙ ማለት አይደለም" ይላሉ። ''ይህን ፍርድ ማሸነፍ ከባድ ነው። ታሪክ እንደሚያሳየን ገና ብዙ ፈተናዎች እንደሚጠብቁን ነው።'' የሚኒሶታ የፍርድ ቤት ማህደር እንደሚያሳየው ከዚህ በፊት አንድ ፖሊስ ብቻ ነው ያልታጠቀ ዜጋ በመግደሉ ወንጀለኛ ሆኖ የተገኘው። በሚኒሶታ ሕግ መሠረት በአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ግድያ የተጠረጠሩ ሰዎች ወንጀሉን ለመፈፀም መነሳሳታቸውን የሚሳይ መረጃ እንዲቀርብ ግድ ይላል። አንደኛ ደረጃ ነፍስ ማጥፋት የተቃደበት መሆን አለበት ይላል፤ ሁለተኛ ደረጃ ደግሞ የወንጀል ጥማት ሊታይበት ይገባል ሲል የግዛቲቱ ሕግ ያትታል። ሦስተኛ ደረጃ ግድያ ማስረጃ እንዲቀርብ አያዝም። ነገር ግን ተጠርጣሪው አደገኛ የሆነ ወንጀል መፈፀሙ መረጋገእ አለበት። በሁለተኛ ደረጃ ወንጀል የተፈረደበት ሰው እስከ 40 ዓመት እስር ሊቀጣ ይችላል። ይህም ከሦስተኛ ደረጃ ግድያ ወንጀል 15 ዓመት የላቀ ነው። የ46 ዓመቱ ጆርጅ ፍሎይድ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ከዋለ በኋላ አንድ ነጭ ፖሊስ አስተኝቶት በጉልበቱ አንገቱ ላይ ቆሞ የሚያሳይ ተንቀሳቃሽ ምስል መሠራጨቱ አይዘነጋም። ከዚህ በኋላ በርካታ አሜሪካውያን ወደ አደባባይ ወጥተው የጥቁሮች ነብስ ዋጋ አላት በማለት በተለያዩ ከተሞች ውስጥ ከባድ ተቃውሞ ማሰማት ከጀመሩ ሳምንት አልፏቸዋል።
news-45776030
https://www.bbc.com/amharic/news-45776030
ኢትዮጵያዊቷ ሰው አልባ አውሮፕላን
በአሁኑ ሰዓት የሰው አልባ አውሮፕላኖች ለተለያዩ አገልግሎቶች እየተሰሩ ነው። ከእነዚህ መካካል የጤና አገልግሎትን ለመደገፍ የተሰራችው ንስረ ጤና አንዷ ናት።
ከሰው አልባ አውሮፕላን ጀርባ ያለ አእምሮ አቶ ፋሲካ ፍቅሬ የኤሮ ስፔስ ኢንጂነር ነው ያጠኑት፤ ካናዳ ተምረው እዛው ሲሰሩ ቆይተው አሁን ወደ ሀገር ቤት ገብተዋል። ወደ ሀገር ቤት ሲገቡ ግን ባዶ እጃቸውን አልነበረም፤ በሙያቸው ለመስራት ተማሪ እያሉ ጀምሮ ያስቡ የነበረውን የሰው አልባ አውሮፕላንን ሀሳብ ይዘው እንጂ። ሙያቸው አውሮፕላንና የሕዋ ቁሳቁሶችን እንዲሁም ሌሎች በራሪ አካላትን ንድፍ መስራትን ያጠቃልላል። የአውሮፕላን፣ የመንኮራኩር፣ የሳተላይትን ሁሉ ንድፍ ይሰራሉ። የ Twitter ይዘት መጨረሻ, 1 አቶ ፋሲካ ፍቅሬ (በስተቀኝ በኩል) ከጤና ጥበቃ ሚንስትሩ ዶ/ር አሚር አማን እና ከሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ሚንስቴር ተወካይ ጋር። አቶ ፋሲካ ወደ አዲስ አበባ ሲመጡ በሰው አልባ አውሮፕላን ዘርፍ እንቅስቃሴዎችን አላዩም ነበር። "እውቀቱም ተቀባይነቱም ምን ድረስ መሆኑን ለማወቅ ፈታኝ ነበር" ይላሉ ጊዜውን ሲያስታውሱ። አሁን ግን ይላሉ አቶ ፋሲካ "እውቀቱም ያላቸው በዘርፉ ላይ አንቅስቃሴዎችንም የሚያካሄዱ ወገኖች ተበራክተዋል።" • ያልታበሰው የላሊበላ እንባ • መቀመጫቸውን ለማስተለቅ የሚታትሩ ሴቶች እየሞቱ ነው የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ጋር በዚህ ዘርፍ እንደሚሰሩ የሚናገሩት አቶ ፋሲካ እንደውም አሁን የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ የራሱ ኤሮ ስፔስ ቴክኖሎጂን ለማስተማር በጥናት ላይ እንደሆኑ አውቋል፤ እርሱም በሙያው እንዲያግዛቸው ተጠይቆ በቅርቡ እዚሁ ላይ እንደሚሳተፉ ነግረውናል። አሁን በኢትዮጵያ ውስጥ የኤሮ ስፔስ ኢንጂነሪንግ በባለሙያዎች ዘንድ በደንብ እየታወቀ ነው የሚሉት አቶ ፋሲካ በዩኒቨርስቲ ውስጥ ለማስተማር ያለውን ዝግጅትና የተለያዩ ወጣቶች በዘርፉ ላይ ለማሰማራት ያሳዩት ንቁ ተሳትፎ እንደበጎ ጅማሮ ያነሳሉ። • ያለአብራሪ በሚበረው የሰማይ ታክሲ ይጠቀማሉ? • አሽከርካሪ አልባዋ አውቶብስ በመጀመሪያ ቀኗ ተጋጨች ንስረ ጤና ሰው አልባ አውሮፕላን አቶ ፋሲካ ሰው አልባ አውሮፕላን ከወታደራዊ አገልግሎት ውጪ እንዴት ልንጠቀምበት እንችላለን የሚለው ላይ ጥናትና ምርምር ሲሰሩ ነው የቆዩት። ወደ ሃገራቸውም ለመምጣት ሲያስቡ ከኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ አንፃር እንዴት ልንጠቀምበት እንችላለን የሚለውን ሲያወጡ እና ሲያወርዱ ከቆዩ በኋላ ከወዳጆቻቸው ጋር በመሆን በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ የሚሰራ ድርጅት አቋቋሙ። ድርጅታቸው ትርፍን ከማግኘት ባሻገር ማህበራዊ ግልጋሎትን መስጠት የሚል ዓላማን ስለያዘ በመጀመሪያ ሞባይል ጤና የሚል ስራ ላይ ተሰማሩ። በዚህ ስራቸው ለነፍሰጡር እናቶች በተንቀሳቃሽ ስልክ የአጭር መልዕክት ስለራሳቸውና ጨቅላ ህፃናቶቻቸው የጤና መረጃ እንዲደርሳቸው የሚያስችል መተግበሪያ ሰሩ። ይህንን መተግበሪያ ለመስራት ጥናቶች ሲያደርጉ በእርግዝናና በወሊድ ወቅት የእናቶችን ሞት ከሚያስከትሉ ነገሮች መካከል ቀዳሚው የደም መፍሰስ መሆኑን ተገነዘቡ። የደም መፍሰስ ብቻ ሳይሆን በወቅቱ የሚያስፈልገውንም ደም ለማግኘት አለመቻል ለሞቱ መበራከት ሌላኛው ሰበብ እንደሆነ ተረዱ። ይህንን ሀሳባቸውን ከጤና ጥበቃ ሚንስቴር ጋር ሲነጋገሩ በሰው አልባ አውሮፕላን ለእናቶች ጤና የሚያስፈልጉ የህክምና ቁሳቁስ ማድረስ የሚለው ሃሳባቸው ላይ ቢሮው በጎ ምለሽ ሰጣቸው። እነርሱም ይህንን የቢሮውን በጎ ምላሽ በመያዝ ከዚህ ቀደም በንድፍ ደረጃ ወረቀት ላይ ያስቀመጧቸውን የሰው አልባ አውሮፕላንን ለሰብዓዊ ድጋፍ ማዋል የሚያስችል ስራ ማጠናቀቅ ያዙ። ከዚህ በኋላ ቢልና ሚሊንዳ ጌትስ ላይ ሃሳባቸውን አቅርበው በመወዳደር የገንዘብና የሙያ ድጋፍ አገኙ። ሙሉ በሙሉ ኢትዮጵያ ውስጥ የተሰራ ከዚህ በመቀጠል ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች የተነደፈችውና የተሰራችውን ሰው አልባ አውሮፕላን ወደ ማምረት ገቡ። የዚህች ሰው አልባ አውሮፕላን ስያሜ ንስረ ጤና ይሰኛል። ንስረ ጤና ደም ለሚያስፈልጋቸው ነፍሰጡር እና ወላድ እናቶች ደም ለማድረስ ብትሰራም ከዚያ ጋር ግን ተያያዥ የሆኑ ከማዕከል ቦታ መኪና ወደ ማይገባባቸው ስፍራዎች ለማድረስ ተሰርታለች። ይህንን ጉዳይ ከጤና ጥበቃ ሚኒስትሩ ዶ/ር አሚን ጋር ከተነጋገሩ በኋላ ንስረ ጤናን ክትባት ለማድረስ እንድትሆን አድርገውም ሰርተዋታል። ንስረ ጤና 3 ኪግ ጭና በአንድ ጊዜ እስከ 100 ኪሜ ድረስ ከአንድ ሰዓት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ማድረስ የምትችል ናት። ይህች ሰው አልባ አውሮፕላን ገበያው ላይ ካሉ ሌሎች ሰው አልባ አውሮፕላኖች የምትለየው ብዙ የመጫን አቅሟ እና ብዙ ርቀት መሄድ መቻሏ እንደሆነ አቶ ፋሲካ ይናገራል። "ከገበያ ላይ የሚገዙት ቪዲዮ ለመቅረፅ የሚያገለግሉት ሰው አልባ አውሮፕላኖች ሀይለኛ ንፋስን የመቋቋም አቅም የላቸውም። ንስረ ጤና ግን እስከ 50 ኪሎ ሜትር ድረስ ፍጥነት ያለው ንፋስ የመቋቋም አቅም አላት" ብለዋል። ሌላው ገበያ ላይ ያሉትና ተሻሽለው የተሰሩትም ቢሆኑ ዋጋቸው የሚቀመስ እንዳልሆነ አቶ ፋሲካ ጨምረው አስረድተዋል። እነርሱ የሰሩት ሰው አልባ አውሮፕላን የኢትዮጵያን አየር ሁኔታንና መልከአ ምድር አቀማመጥ ያገናዘበ እንደሆነ የሚናገሩት አቶ ፋሲካ ከመስራታቸው በፊት ከአፋር እስከ ቱሩሚ ከዛም እስከ ሞያሌ ድረስ ጥናት አድርገው ወደ ተግባር መግባታችን ይናገራሉ። ንስረ ጤና ኢትዮጵያ ውስጥ ተነድፋ ኢትዮጵያ ውስጥ የተሰራች መሆኗን የሚናገሩት አቶ ፋሲካ የ3ዲ ማተሚያ ከውጭ በማስመጣት የአካል ክፍሎቹን እዚሁ ተነድፎ እዚሁ እንደተመረተ ተናግረዋል። የንስረ ጤናን ሞተር እነርሱ ንድፉን ሰርተው ማስመረታቸውን የተናገሩት አቶ ፋሲካ በአሁኑ ሰአት በኢትዮጵያ ውስጥ ሰው አልባ አውሮፕላን ማብረር ስለማይፈቀድ፤ በሳይንስና ቴክኖሎጂ በኩል ለማብረር የሚያስችላቸውን ልዩ ፈቃድ እንዲሰጣቸው መጠየቃቸውን ተናግረዋል። ፈቃዱን የሚያገኙ ከሆነ ንስረ ጤናን ለሙከራ በዚህ የጥቅምት ወር ጤና ጥበቃ ሚኒስትር በመረጣቸው ስድስት የክልል ከተሞች ላይ ያበራሉ።
news-46719270
https://www.bbc.com/amharic/news-46719270
ግብጽ ከሽብር ጥቃት ጋር በተያያዘ 40 ታጣቂዎችን ገደለች
የግብጽ ፖሊስ ባለፈው አርብ ከደረሰው የቦምብ ጥቃት ጋር በተያያዘ 40 ታጣቂዎችን እንደገለ የሃገር ውስጥ ሚኒስትር መስሪያ ቤቱ አሰታወቀ።
አርባዎቹ ታጣቂዎች ቅዳሜ ዕለት የተገደሉት ጊዛ በተባለ ቦታና በሰሜናዊ ሲናይ ሲሆን፤ በአብያተ ክርስቲያናትና ጎብኚዎች ላይ ሌላ ጥቃት ለማድረስ ዝግጅት ሲያደርጉ ነበር ብሏል ሚኒስትር መስሪያ ቤቱ ባወጣው መግለጫ። ጊዛ ውስጥ ባለፈው አርብ በጎብኚዎች ማጓጓዣ አውቶቡስ ላይ በተሰነዘረው የቦምብ ጥቃት አራት ሰዎች ህይወታቸው ሲያልፍ፤ አስራ አንድ ሰዎች ደግሞ ጉዳት ደርሶባቸዋል። • ድምፅ ፈታዮቹ መረዋዎች • የኮንጎ ምርጫ መጓተት ህዝቡን አስቆጥቷል • በግብጽ መስጊድ በደረሰ ፍንዳታ ቢያንስ 235 ሰዎች ሞቱ አስራ አራት የቬትናም ዜግነት ያላቸው ጎብኚዎችንና አንድ ግብጻዊ አስጎብኚን ይዞ ሲጓ የነበረው አውቶቡስ ላይ ለደረሰው ጥቃት እስካሁን ሃላፊነቱን የወሰደ ቡድን የለም። ግብጽ ውስጥ ጎብኚዎች ላይ ጥቃት የሚሰነዝሩ ታጣቂዎች ግን በርካታ እንደሆኑ ይነገራል። በጊዛ ከተማ ፖሊስ በወሰደው እርምጃ 30 ታጣቂዎችን የደመሰሰ ሲሆን፤ በሰሜናዊ ሲናይ ግዛት ዋና ከተማ ኤል አሪሽ በተደረገ ሌላ ወታደራዊ ዘመቻ ደግሞ ተጨማሪ 10 ታጣቂዎች መገደላቸውን መግለጫው ያትታል። ከዚህ በተጨማሪ ቦምብ ለመስራት የሚያገለግሉ መሳሪያዎችንም ፖሊስ በቁጥጥር ስር እንዳዋለ ተገልጿል። የጎብኚዎች ቁጥር እጅግ ከፍተኛ በሆነበት በዚህ ሰዓት ግብጽ የጥበቃ ስራዋን ከሌላ ጊዜው በተለየ ጠበቅ ያደረገች ሲሆን፤ የክርስትና ሃይማኖት ተከታዮችና ቤተ አምሎኮዎቻቸው እንዲጠበቁ እየተደረገ ነው። • የትራምፕ አማካሪ፡ የግንቡ ውጥን ውድቅ ከተደረገ ሰነባብቷል • በምዕራብ ኦሮሚያ የኦነግ ጦር አዛዥ ስለወቅታዊው ሁኔታ ምን ይላል? ጥቃት የተሰነዘረበት አውቶቡስ ከታሰበለት የጉዞ መስመር ውጪ ሄዶ እንደነበር የሃገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ቢናገሩም፤ አሽከርካሪው ግን ምንም የማውቀው ነገር የለም ብሏል።
news-55147190
https://www.bbc.com/amharic/news-55147190
የኤችአይቪ ኤድስ ስርጭት በአዲስ አበባ እና በጋምቤላ ከፍተኛ መሆኑ ተገለጸ
በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የኤችአይቪ ኤድስ ስርጭት በአዲስ አበባ እና በጋምቤላ ውስጥ ከሌሎች አካባቢዎች በተሌ ከፍተኛ መሆኑ ተገለጸ።
ዓለም አቀፉ የኤችአይቪ ኤድስ ቀን ኢትዮጵያ ውስጥ 'ኤችአይቪን ለመግታት ዓለም አቀፋዊ ትብብር የጋራ ኃላፊነት' በሚል መሪ ቃል ተከብሯል። የፌደራል የኤችአይቪ ኤድስ የመከላከያና መቆጣጠሪያ ጽህፈት ቤት የሕዝብ ግንኙነትና ኮምንኬሽን ዳይሬክተር አቶ ዳንኤል በትረ ለቢቢሲ እንደተናገሩት፤ በአገሪቱ ከፍተኛ የቫይረሱ ስርጭት የተመዘገበው በሁለቱ አካባቢዎች መሆኑን አመልክተዋል። እንዲሁም በሶማሌ ክልል፣ ደቡብ ክልል፣ ኦሮሚያ ክልል እና ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ውስጥ ደግሞ የቫይረሱ የስርጭት መጠን በአንጻራዊነት ዝቅተኛ እንደሆነ ተገልጿል። አቶ ዳንኤል ጨምረው እንዳሉት፤ በአሁን ወቅት በኢትዮጵያ ውስጥ ከ669 ሺህ በላይ ሰዎች ቫይረሱ በደማቸው ውስጥ የሚገኝ ሲሆን፤ የቫይረሱ አገር አቀፍ የስርጭት መጠን ደግሞ 0.93 በመቶ ነው። የኤችአይቪ/ኤድስ የስርጭት ሁኔታ ከክልል ክልል የተለያየ እንደሆነው ሁሉ ልዩነቱ በከተሞችና በገጠር አካባቢዎች ይስተዋላል። በዚህም መሠረት በከተሞች አካባቢ የበሽታው ስርጭት ከፍተኛ ነው። አቶ ዳንኤል እንዳሉት የበሽታው ስርጭት መጠን በከተማና በገጠር ሲነጻጸር፤ በከተማ 3 ከመቶ ሲሆን በገጠር ደግሞ 0.4 በመቶ ነው። የስርጭት መጠኑ ከአንዱ ክልል በሌላው እንዲሁም በየማኅበረሰቡ እንደሚለያይ የገለጹት አቶ ዳንኤል፤ "በወሲብ ንግድ ላይ የተሰማሩ፣ የረዥም ርቀት አሽከርካሪዎች እና ተንቀሳቃሽ ሠራተኞች አካባቢ የስርጭት መጠኑ ከፍተኛ ነው" ብለዋል። በኢትዮጵያ የኤችአይቪ ስርጭት ከዓመት ዓመት የመቀነስ አዝማሚያ ቢኖረውም በተለያየ አካባቢ የተለያየ የስርጭት መጠንና ሁኔታ እንዳለውም ጠቁመዋል። የአዲስ አበባ እና የጋምቤላ ሁኔታ ስርጭቱ ከፍተኛ ከሆነባቸው ከተሞች አንዷ አዲስ አበባ ናት። ለዚህም ምክንያት ተብለው ከተቀመጡት አንዱ ከተማዋ ብዙ ሰዎችን ከውጪ አገር እና ከክልል ከተሞችም የምታስተናግድ መሆኗ ነው። ሌላው ምክንያት ደግሞ አዲስ አበባ የንግድ ልውውጥ ማዕከልነቷ ነው ሲሉ አቶ ዳንኤል ተናግረዋል። "በአዲስ አበባ አጋላጭ የሆኑ ምክንያቶች በርካታ ናቸው። ጋምቤላ ግን ትልቁን ተጽዕኖ የሚፈጥረው ባህሉ ነው። የተለያዩ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች አሉ" ሲሉ ዳይሬክተሩ አብራርተዋል። ከጊዜ ወደ ጊዜ ለበሽታው የሚሰጠው ትኩረት እየቀነሰ መምጣቱ ይነገራል። ኤችአይቪ ኤድስን በመከላከል ረገድ የሚሠራው ሥራ ከዓመት ዓመት ማሽቆልቆሉም ተያይዞ ይጠቀሳል። አቶ ዳንኤል እንደሚሉት፤ ባለፉት ዓመታት በቫይረሱ ምክንያት የሚመዘገበው የሞት መጠንና አዲስ በቫይረሱ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር መቀነሱ መዘናጋት ፈጥሯል። በአገር አቀፍ ደረጃ እአአ በ1991 የቫይረሱ የስርጭት መጠን 1.97%፣ በ1997 ደግሞ 3.16% ደርሶ ነበር። ይህም ከፍተኛ የሚባል ነበር። ከዚያ በኋላ የስርጭት መጠኑ እየቀነሰ መጥቶ በ2010 ላይ 1.38 በመቶ አሁን ደግሞ 0.93% ደርሷል። ይህንን ቁጥር በማጣቀስ "የስርጭቱ መጠን ከዓመት ዓመት እየቀነሰ መምጣቱ አንዱ አዘናጊ ምክንያት ነው" ብለዋል። ሁለተኛው ምክንያት ቫይረሱን ለመከላከል ከተለያዩ የውጪ አገሮች የሚመጣው ድጋፍ መቀነሱ ነው። ድጋፉ ሲቀንስ መከላከልን በተመለከተ የሚሠሩ የሚዲያ ቅስቀሳና ሌሎችም ንቅናቄዎች ቀንሰዋል።"በተጨማሪም የአመራር ቁርጠኝነት ይጠይቃል። አመራሩ እንደ አጀንዳ ካልያዘው ለውጥ ማምጣት አይቻል" ሲሉም ዳይሬክተሩ አክለዋል። ኤችአይቪ ኤድስ እና ኮቪድ-19 ኮቪድ-19 በዓለም አቀፍ ደረጃ ካስከተለው ማኅበራዊ፣ የምጣኔ ሀብታዊና መሰል ቀውሶች ውስጥ ጤናም ተጠቃሽ ነው። አብላጫው ትኩረት ለወረርሽኙ መሰጠቱ ሌሎች ህመሞች እንዲዘነጉ፣ ህሙማንም አገልግሎት ለማግኘት እንዲቸገሩ ምክንያት ሆኗል። በኢትዮጵያ በኮሮናቫይረስ ከሚሞቱ ሰዎች መካከል የኤድስ በሸውታን የሚያስከትለው ቫይረስ በደማቸው የነበረ ሰዎች ይገኙበታል። ነሐሴ አካባቢ በኮሮናቫይረስ ከሞቱ ሰዎች መካከል 28 በመቶ በደማቸው ቫይረሱ የነበረባቸው እንደሆኑና አሁን ላይ ግን አጠቃላይ ሪፖርት እንዳልተሰራ አቶ ዳንኤል ተናግረዋል። "በአብዛኛው መገለልና መድልዎን በመፍራት መድኃኒታቸውን ራቅ ካለ ቦታ የሚወስዱ ቫይረሱ ያለባቸው ዜጎች በኮቪድ-19 ሳቢያ ትራንስፖርት ሲቋረጥ መድኃኒት ማግኘት አልቻሉም" ሲሉም ምክንያቱን አስረድተዋል። በሌላ በኩል የጤና ተቋሟት ሙሉ አቅማቸውን ኮቪድ-19ኝን ወደ መከላከል በማዞራቸው ለኤችአይቪ ኤድስ የሚሰጠው ትኩረት ተቀዛቅዟል። ዓለም አቀፉ የኤችአይቪ ኤድስ ቀን ኢትዮጵያ ውስጥ 'ኤችአይቪን ለመግታት ዓለም አቀፋዊ ትብብር የጋራ ኃላፊነት' በሚል መሪ ቃል ትናነት ተከብሯል።
news-55715930
https://www.bbc.com/amharic/news-55715930
ቻይና፡ የአሊባባ ኩባንያ መስራች ጃክ ማ ከወራት በኋላ ታዩ
የአሊባባ ኩባንያ መስራች ቻይናዊው ባለፀጋ ጃክ ማ ለወራት ከህዝብ እይታ ተሰውረው ከሰሞኑ ብቅ ብለዋል።
የቻይና ባለስልጣናት የቢሊየነሩ የንግድ አሰራር ላይ ከፍተኛ የሆነ ቁጥጥርና ጫና ማሳደራቸውን ተከትሎ ባለሃብቱ ደብዛቸው ጠፍቶ ነበር። ለወራት ያህልም ያልታዩት ባለፀጋ የት ናቸው የሚለውም ጉዳይ ለበርካታ ጥርጣሬዎችም በር ከፍቶ ነበር። በተለይም መንግሥት የባለሃብቱን የቢዝነስ አሰራር እየፈተሸና ጠበቅ ያለ ምርመራ በከፈተበት ወቅት መሆኑ ደግሞ ወሬዎችን አቀጣጥሏል። ቢሊየነሩ ቻይና የሚገኙ 100 የገጠር መምህራን ጋር በቪዲዮ ስብሰባ በማካሄድ "አለሁ" ማለታቸውን የአገሪቱ ሚዲያ ዘግቧል። ዜናውን መጀመሪያ ሪፖርት ያደረገው ቲናሙ የተባለው የዜና ወኪል እንዳስነበበው እነዚህ መምህራን የጃክ ማ በርካታ እርዳታ ድርጅት ጅማሬዎች አካል መሆናቸውን ነው። አመታዊ የሆነው ስብሰባም ሳንያ በሚባል ሪዞርት ይካሄድ የነበረ ሲሆን በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት በበይነ መረብ ሊካሄድ ግድ ብሎታል። "በወረርሽኙ ምክንያት ሳንያ መሰብሰብ አልቻልንም" በማለት ጃክ ማ ተናግረዋል። አክለውም " ወረርሽኙ ሲገታ እንደ ቀድሞው ዝግጅታችንን ሳንያ እናደርገዋለን" ብለዋል በቪዲዮውም ላይ ግራጫ ቀለም በተቀባ ቤት ሰማያዊ ሙሉ ልብስ ለብሰው የነበረ ሲሆን፤ ካሜራውን ፊት ለፊት እየተመለከቱ ነበር ተብሏል። ከቪዲዮውም ሆነ ቲናሙ ካወጣው ዜና ጃክ ማ የት እንዳሉ ማወቅ አልተቻለም። የቁጥጥር ጫናው ባለፈው ወር የቻይና ማዕከላዊ ባንክ የጃክ ማ አንት ግሩፕ የተባለ ኩባንያቸው አሰራር ላይ ከፍተኛ ፍተሻ እንዲደረግ አዘዘ። ጃክ ማ በቻይና ትልቁ ክፍያ ፈፃሚው ድርጅት የሆነው አንት ግሩፕ መስራችና ባለ ከፍተኛ ድርሻም ናቸው። ከዚህም በተጨማሪ የቻይና የገበያ ስርአት አስተዳዳሪም እንዲሁ አሊ ባባ ገበያውን በበላይነትና በዋነኝነት የተቆጣጠረበትን አካሄድ ላይም ምርመራ ከፍቷል። የጃክ ማ መጥፋት በህዝቡ ዘንድ መነጋገሪያ የሆነው ዳኛ ከሆኑበት 'አፍሪካ ቢዝነስ ሂሮስ' ተብሎ ከሚጠራው የቴሌቪዥን ፕሮግራም በመጥፋታቸው ነው። ምንም እንኳን ኩባንያው አሊባባ በስራ መደራረብ ነው የጠፉት ቢልም በርካታ የቻይና ሚዲያዎች በበኩላቸው ጥቅምት ወር ላይ በተካሄደ ዝግጅት ላይ የቻይናን የባንክ ስርአት በይፋ መተቸታቸውን ተከትሎ ደብዛቸው እንደጠፋ ዘግበዋል።
news-53422736
https://www.bbc.com/amharic/news-53422736
የአቶ ጃዋር ጠበቆች አቤቱታና የዕለቱ የችሎት ውሎ
ከድምጻዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ በኋላ ከተከሰተው አለመረጋጋት ጋር በተያያዘ ከሁለት ሳምንት በፊት በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋሉት የአቶ ጃዋር መሐመድን ጉዳይ የተመለከተው ፍርድ ቤት ተጨማሪ የ14 ቀናት የምርመራ ጊዜ ለፖሊስ ፈቀደ።
አቶ ጃዋር በፖሊስ ቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት የቀረቡ ሲሆን ፖሊስ የጀመረውን ምርመራ ለማጠናቀቅ ተጨማሪ ቀናት እንዲሰጠው ፍርድ ቤቱን ጠይቋል። በፖሊስ ከቀረቡት ክሶች መካከል ለአንድ ፖሊስ ህይወት መጥፋት ምክንያት በመሆንና በኦኤምኤን ቴሌቪዥን ላይ በቀረቡ ጥሪዎች አማካይነት ለሰው ህይወት መጥፋትና ለንብረት መውደም መንስኤ በመሆን ክስ የተመሰረተባቸው ሲሆን ተጨማሪ ምርመራ ለማድረግ የሁለት ሳምንት ጊዜ እንዲሰጠው በመጠየቁ ነው ተጨማሪ ቀናት የተፈቀዱለት። ይህንንም ተከትሎ የጃዋር ጠበቃ ደንበኛቸው በዋስ ከእሰር ቤት ውጪ ሆኖ ጉዳዩን መከታተል እንዲችል እንዲፈቀድለት ጠይቀው የነበረ ቢሆንም ፍርድ ቤቱ ፖሊስ ያቀረበውን የተጨማሪ የ14 ቀናት የምርመራ ጊዜ ጥያቄ ተቀብሎታል። በዚህ ጊዜ የተከሳሽ ጠበቆች ደንበኛቸው ምግብ ከቤተሰቡ የሚቀርብለት ቢሆንም ግንኙነታቸው በርቀት በመሆኑ ባለበት ከርቀት አይቶ የመለየት ችግር ቤተሰቦቹን በቅርበት እንዲያገኝ እንዳልተፈቀደለት ለችሎቱ አቤት ብለዋል። ፖሊስም ይህንን በተመለከተ በሰጠው ምላሽ ታሳሪዎችና ጠያቂዎች መካከል መቀራረብ እንዳይኖር የተደረገው የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ስርጭትን ለመቆጣጠር በወጣው ደንብ መሰረት መሆኑን ጠቅሶ ምላሽ ሰጥቷል። በተጨማሪም አቶ ጃዋር ታስረው የሚገኙበት ክፍል በቂ ብርሃን የሌለው መሆኑና መጸዳጃ ቤት የመጠቀም ችግርን በማንሳት አቤቱታ ያቀረቡ ሲሆን በተጨማሪም ደንበኛቸው ጥፋተኝነታቸው ገና ባልተረጋገጠበት ሁኔታ በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ምስላቸው እየቀረበ ዘገባዎች እንደሚቀርቡና ፍርድ ቤቱም ይህንን እንዲያስቆም ጠይቀዋል። ፍርድ ቤቱም ፖሊስ ለእስረኞች መጸዳጃ ቤትን በተመለከተና በማረፊያ ክፍሎች ውስጥ ያለውን ብርሃን በተመለከተ አስፈላጊውን ማስተካከያ እንዲያደርግ ያዘዘ ሲሆን፤ በመገናኛ ብዙሃን ላይ ስለቀረበው አቤቱታም ጠበቆች ያሏቸውን ተቋማት በስም ለይተው እንዲያቀርቡ አዟል። በዚህም መሰረት ፖሊስ ለምርመራ የጠየቀውን የ14 ቀናት ጊዜ ፈቅዶ ጉዳዩን ለመመልከት ሐምሌ 22/2012 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቶ ችሎቱ አብቅቷል። በተጨማሪም ፖሊስ በአቶ በቀለ ገርባ ላይ የሚያደርገውን ምርመራ ለመቀጠል በተመሳሳይ ተጨማሪ ቀናትን ከፍርድ ቤት ተሰጥቶታል። የጃዋር ጠበቃ ከችሎት በፊት ከአቶ ጃዋር መሐመድ ጠበቆች አንዱ የሆኑት አቶ ቱሊ ባይሳ ከችሎቱ ቀደም ብሎ ለቢቢሲ እንደተናገሩት አቶ ጃዋርን ባለፈው ማክሰኞ አግኝተዋቸው እንደነበር ገልፀው፤ ታስረው የሚገኙት ምድር ቤት ውስጥ መሆኑን ማረጋገጣቸውን ተናግረዋል። በማረፊያ ክፍሉ ውስጥም አነስተኛ ተፈጥሯዊ ብርሃን እያገኙ እንደሆነና ብርሃኑም በትንሽ መስኮት በኩል የሚገባ ብቻ መሆኑን እንደነገሯቸው ለቢቢሲ አረጋግጠዋል። ነገር ግን አቶ ጀዋርና አቶ በቀለ ጨለማ ቤት ውስጥ ታስረዋል ስለመባሉ ሲያብራሩም የኤሌትሪክ መብራት በክፍሉ ውስጥ መኖሩንና ችግሩ የተፈጥሮ ብርሃን አለማግኘታቸው መሆኑን ገልፀዋል። የጃዋር ቤተሰብ ምግብ ሲያደርሱላቸው የቤተሰባቸውን አባላት መለየት አለመቻላቸውን ከቤተሰቡ አባል ማረጋገጣቸውን አቶ ቱሊ ተናግረዋል። "ጃዋርን በምን ምክንያት መለየት እንዳልቻለ ጠይቄው፤ ከቤተሰቡ አባል ጋር የሚገናኙት ከርቀት ቆመው እንደሆነና ድምጻችንን ከፍ አድርገን ነው ጮኸን የምንነጋገረው፤ በዚያ ላይ ደግሞ ከክፍሌ የፀሐይ ብርሃን ወዳለበት ስወጣ አይኔ አጥርቶ ማየት አልቻለም ነበር ብሎኛል" ሲሉ ጠበቃው ገልጸዋል። አቶ ጃዋር መሀመድ እና አቶ በቀለ ገርባ በአንድ ክፍል ውስጥ የሚገኙ ሲሆን አቶ ሀምዛ ቦረና አቶ ሸምሰዲን ጠሃ በሌላ ክፍል በጋራ ታስረው እንደሚገኙ አቶ ቱሊ ለቢቢሲ ተናግረዋል። አቶ ሸምሰዲን ጠሃ አቶ ጃዋር በቁጥጥር ስር በዋለ በማግስቱ ቦሌ ሚካኤል ከሚገኘው የጓደኛቸው ቤት በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን በወቅቱ በፀጥታ ኃይሎች ድብደባ እንደተፈፀመባቸው አቶ ቱሊ አረጋግጠዋል። የሕክምና እርዳታ ለማግኘት በተደጋጋሚ ቢጠይቅም እንዳልተፈቀደለት እነደነገራቸው አቶ ቱሊ ለቢቢሲ ገልፀዋል። አቶ ቱሊ ሸምሰዲንን ሲያገኙት አካሉ ላይ የደረሰበትን ጉዳት እንዳሳያቸው ተናግረው ደረቱ፣ ጎኑ ላይና እግሩ ላይ ጉዳት ደርሶ መመልከታቸውን ተናግረዋል። የጃዋር ጠባቂዎች የጤና ሁኔታ የጃዋር የግል ጠባቂዎች ሦስተኛ ፖሊስ ጣቢያ ተብሎ በሚታወቀው እስር ቤት ውስጥ እንደሚገኙ አቶ ቱሊ አረጋግጠዋል። በእስር ቤቱ ውስጥ በኮሮናቫይረስ መያዙ የተጠረጠረ ሰው መገኘቱን ተከትሎ ምርመራ ተደርጎላቸው ውጤት እየጠበቁ እንደሆነ ከጠባቂዎቹ አስተባባሪ መስማታቸውን አቶ ቱሊ ለቢቢሲ ተናግረዋል። ነገር ግን እስካሁ ግን በቫይረሱ የተያዘ ሰው ስለመኖር የተረጋገጠ እንደሌለ ጠበቃ ቱሊ ባይሳ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
news-46837357
https://www.bbc.com/amharic/news-46837357
የኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ ሰማኒያ ሚሊዮን ብር እንዴት ተዘረፈ?
ከጥቂት ሳምንታት በፊት የኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ ንብረት የሆነ ገንዘብ ከአንድ ቅርንጫፍ ወደ ሌላው ሲዘዋወር እንደተዘረፈ ተሰምቷል።
ታህሳስ 19፣ 2011 ዓ. ም. በምዕራብ ሐረርጌ ዞን ዋና ከተማ ጭሮ ውስጥ የሚገኘው የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ 80 ሚሊዮን ብር ወጭ ያደርጋል። ገንዘቡን ወደ ደብረ ዘይት ቅርንጫፉ ለማዘዋወርም ጉዞ ይጀምራል። ሆኖም ገንዘቡን የጫነው መኪና የታሰበበት ሳይደርስ መኤሶ ወረዳ አሰቦት አካባቢ መሳሪያ በያዙ ሰዎች ተከበበ። • "የመከላከያ ሰራዊትን እንቅስቃሴ የሚያግድ ስራ አንቀበልም" ዶ/ር ደብረፅዮን ከዚያስ? የምዕራብ ሐረርጌ ዞን ፖሊስ መምሪያ ሐላፊ ኮማንደር ጋዲሳ ንጉሳ በዚህ ጉዳይ ላይ የሚከተለውን ብለዋል " የተወሰኑ ኃይሎች ሽጉጥ የያዙ እንዲሁም ባዶ እጃቸውን የነበሩ ግለሰቦች መኪናውን መንገድ ላይ አስቆሙት። ሾፌሩን አስፈራርተው በማስወረድ አሰቦት ወደምትባል አካባቢ መኪናዋን ወሰዷት" ከተዘረፈው 80 ሚሊዮን ብር ውስጥ በሽምግልና፣ በድርድርና በፍተሻ ማስመለስ የቻሉት ገንዘብ እንዳለም ይናገራሉ። ይህን ያህል ገንዘብ አስመልሰናል ለማለት ሰነድ ባያጠናቅሩም "እጅ ከፍንጅ የተያዘ ገንዘብ የለም። አብዛኛው ብር የተመለሰው በጥቆማ ነው። በርካታ መኪና ይዘው ሲሄዱ በፍተሻ የተያዙ አሉ" ብለዋል። • "ጫትን ማገድ ፈፅሞ የሚቻል አይደለም" ዶ/ር ዘሪሁን መሃመድ ለመሆኑ አንድ ባንክ ከአንድ ቅርንጫፍ ወደ ሌላ ቅርንጫፍ ገንዘብ ሲያዘዋውር የሚደረግለት የጥበቃ ኃይል ወደየት ሄዶ ነው ዝርፊያው ሊፈፀም የቻለው? በሚል ቢቢሲ ኮማንደሩን ጠይቋል። "በወቅቱ አብረው የነበሩት ፖሊሶች ከአቅማቸው በላይ ስለሆነ መያዝ አልቻሉም። ወደ ሌላ እርምጃ ከተገባ በነሱም ደህንነት ላይ አደጋ ስለሚመጣ በልመናና በድርድር ገንዘቡን መውሰድ እንዲያቆሙ ለማድረግ ተሞክሯል። ማስፈራራትና ወደ ሰማይም ተተኩሷል።" ዘራፊዎቹ በቁጥር ብዙ እንደነበሩ የሚናገሩት ኮማንደሩ፤ ዘራፊዎቹ ገንዘቡን ከዘረፉበት ቦታ ወደ ከተማ ይዘው ከሄዱ በኋላ ለመከፋፈል ሲሞክሩ የከተማው ከንቲባ "የሕዝብ ንብረት ነው" ብለው በድርድር ለማስቆም ቢሞክሩም እንዳልተሳካላቸው ይገልጻሉ። ፎርቹን ጋዜጣ፤ ብሩ ወደ አዲስ አበባ መጓጓዝ ላይ እንደነበር ጠቅሶ 100 ግለሰቦች በዝርፊያው ተጠርጥረው ተይዘዋል ሲል ዘግቧል። • እናትና ልጇቿ ለወር አበባ በተገለለ ጎጆ ህይወታቸው አለፈ ከዘረፋው ጀርባ ያሉ ሰዎችን ማንነት ለማወቅ ምርመራ እየተደረገ መሆኑን ኮማንደሩ ቢናገሩም፤ "ዘራፊዎቹ ከሩቅ የመጡ አይደሉም" የሚል ጥቆማ ሰጥተዋል። ከዚህ ቀደም የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ ከድሬዳዋ ቅርንጫፍ 80 ሚሊዮን ብር ጭኖ በመኢሶ ወረዳ ሲተላለፍ ነበር። ያኔ ገንዘቡን ይዞ ይጓዝ የነበረው መኪና አሽከርካሪ አህያ ገጭቶ በአካባቢው ፖሊስ ተይዟል። በወቅቱ የተገኘው ገንዘብና አጓጓዡ የያዘው ሰነድ ላይ የሰፈረው የገንዘብ መጠን መካከል ልዩነት ተፈጥሮ እንደነበር ይታወሳል። ገንዘቡን መጫን የነበረበት መኪና ሰሌዳ ቁጥርና በፖሊስ የተያዘው መኪና ታርጋ ቁጥርም የተለያየ ነው ተብሎ ነበር። ለመሆኑ የዚህ ገንዘብ ጉዳይ ከምን ደረሰ? ኮማንደር ጋዲሳ ምላሽ አላቸው። "አምሳ ሚሊዮኑን የሚያሳይ ሰነድ በገንዘብ ያዡ እጅ አልነበረም። ይህም ከኔትወርክ ችግር ጋር የተያያዘ ነው። መንገድ ላይ በኢሜይል እንልክላችኋለን የሚል ነገር ነበር" ገንዘቡ ከወጣበት ቅርንጫፍ ጀምሮ ስለነበረው ሂደት ምርመራ ተእየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል። መጀመሪያ ገንዘቡን ይጭናል ተብሎ የነበረው መኪና ሰሌዳው ቁጥር ሌላ ሲሆን፤ ይህም በአጋጣሚ ገንዘቡን ይጭናል ተብሎ የታሰበው ሾፌር በህመም ላይ ስለነበር ነው ብለዋል። • ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከስድሳ በላይ የኢትዮጵያ አምባሳደሮችን ያገኛሉ "ስለ ሹፌር ለውጥ የሚገልጽ ደብዳቤ ሳይቀየርብ ሌላ መኪና በመተካቱ ነው" ሲሉ የድሬዳዋ ስራ አስኪያጅ እንደነገሯቸው ኮማንደሩ ገልፀዋል። "ገንዘቡ ህጋዊ መሆኑን ነው የምናውቀው። አሁን ምርመራ ላይ ነው። በቅርብ ይፈታል የሚል እምነት አለኝ" ብለዋል። መኪና ውስጥ የተገኘው ገንዘብ ጉዳይ እስኪጣራ ድረስ ገንዘቡ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አዳማ ቅርንጫፍ ውስጥ እንዲቆይ መወሰኑንም ኮማንደር ጋዲሳ ገልፀዋል።
56051980
https://www.bbc.com/amharic/56051980
ኮሮናቫይረስ ፡ ክትባቱ ሴቶች እንዳይወልዱ ያደርጋል መባሉን ሳይንቲስቶች አጣጣሉ
ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የኮሮናቫይረስ ክትባት ሴቶች እንዳይወልዱ ያደርጋል በሚል የሚሰራጨው አሉባልታ መሠረተ ቢስ እንደሆነ ባለሙያዎች ገለጹ።
የፋይዘር ክትባት የሴቶች የሥነ ተዋልዶ ጤና ቀውስ ያስከትላል መባሉ "ምክንያታዊ አይደለም" ሲሉ በለንደን ኪንግስ ኮሌጅ የሚሠሩት ፕ/ር ሉሲ ቻፔል ተናግረዋል። ክትባቱ ሰውነት በሽታውን የመከላከል አቅም እንዲያዳብር የሚረዳ ነው። ሰዎች በቫይረሱ እንዲያዙ ወይም ዘረ መላቸው እንዲለወጥ አያደርግም። ፕ/ር ኒኮላ ስቶንሀውስ የተባሉ የቫይረስ ተመራማሪ፤ ክትባቱ የተሠራበት መዋቅር የሥነ ተዋልዶ ጤና ላይ ተጽዕኖ የሚያሳድርበት መንገድ የለም ይላሉ። ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ እየተሰራጨ ያለው አሉባልታ የሚያጣቅሰው ከዚህ ቀደም በዩናይትድ ኪንግደም መንግሥት የወጣ መግለጫን ነው። መግለጫው እንደሚለው፤ የፋይዘር ክትባትና የመውለድ አቅም ስላላቸው ትስስር መረጃ የለም። ሆኖም ግን ይህ መግለጫ ማሻሻያ ተደርጎበት ክትባቱ የሥነ ተዋልዶ ጤና ላይ ጉዳት እንደማያደርስ የሚገልጽ ጽሑፍ ወጥቷል። ሳይንቲስቶች ስለ አንድ ነገር ሲገልጹ "መረጃ የለም" ካሉ፤ ይህ የሚጠቁመው በጉዳዩ ላይ ገና ጥናት አልተሠራም እንጂ ድምዳሜ ላይ ተደርሷል ማለት አይደለም። ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የተሰራጨው አሉባልታ የኮሮናቫይረስ ክትባት የእንግዴ (ፕላሴንታ) ፕሮቲን አለው ይላል። ይህም ፕላሴንታ ላይ ጉዳት ያደርሳል የሚል ወሬ ነው የተናፈሰው። ሳይንቲስቶች እንደሚሉት ይህ ወሬ ሐሰት ነው። ክትባቱ ከፕላሴንታ ጋር የሚመሳለል ፕሮቲን ቢጠቀምም ይህ ሰውነትን ግራ የሚያጋባ አይደለም። ክትባት የሚሠራው ቫይረስን ለይቶ ለማጥቃት ነው። በነፍሰ ጡር ሴቶች ሕክምና ላይ የሚያተኩሩት ፕሮፌሰሯ እንዳሉት፤ የኮሮናቫይረስ ክትባት በሴቶች ሥነ ተዋልዶ ላይ ጉዳት አያስከትልም። በእንግሊዝ የሕክምና ባለሙያው ጆናታን ቫንቲም "ሴቶች እንዳይወልዱ ስለሚያደርግ ክትባት ሰምቼ አላውቅም። የተሳሳተ ወሬ ነው" ሲሉ ለቢቢሲ አስረድተዋል። በሌላ በኩል ነፍሰ ጡር ሴቶች በክትባት ሙከራው ወቅት አልተካተቱም። ባለሙያዎች በክትባቱና በነፍሰ ጡር ሴቶች መካከል ስላለው ትስስር ግልጽ መረጃ ባይሰጡም፤ በከፍተኛ ሁኔታ ለቫይረሱ ተጋላጭ የሆኑ ነፍሰ ጡር ሴቶች ብቻ ክትባቱን እንዲወስዱ ይመክራሉ።
news-55883437
https://www.bbc.com/amharic/news-55883437
የ110 ዓመቷ የዕድሜ ባለጸጋ የዘፈኑት ሙዚቃ በቲክቶክ ገነነ
የ110 ዓመቷ የዕድሜ ባለጸጋ በአንድ ምሽት የቲክቶክ የዓለም ኮከብ ሆኑ፡፡
እማማ አሚ ሐውኪንስ በቲክቶክ ዝነኛ ያደረጋቸው በአንደኛው የዓለም ጦርነት ወቅት ይዘመር የነበረን መዝሙር ለልደታቸው በመዝፈናቸው ነው፡፡ "It's A Long Way to Tipperary" የተሰኘውን መዝሙር እማማ አሚ ሲዘምሩት በቪዲዮ የቀረጻቸው የልጅ ልጅ ልጃቸው ነበር፡፡ በወቅቱ እማማ አሚ 110ኛ ዓመታቸውን እያከበሩ ነበር፡፡ የልጅ ልጅ ልጃቸው ሳቻ የ14 ዓመት ታዳጊ ሲሆን ይህን የእማማ አሚን ቪዲዮ ባጋራ በሰዓታት ውስጥ 100 ሺህ ተመልካች አግኝቷል፡፡ እማማ አማ የሞንማውዝ አካባቢ ተወላጅ ሲሆኑ በእርሳቸው እድሜ ሳሉ በመላው ብሪታኒያ እየዞሩ ይዘምሩ ነበር፡፡ ነገር ግን እናታቸው መዝፈን እንዲያቁሙ አድርገዋቸዋል፡፡ ምክንያቱም በዚያ ወቅት ሴት ልጅ መዝፈን የሚያስከብራት ተግባር አልነበረም፡፡ የሳቻ እናት ሐና ፍሪማን የልጃቸው ሳቻ ቪዲዮ በመላው ዓለም መወደድ በሰው ልጆች መልካምነት ላይ እምነት እንዲኖረን የሚያደርግ ነው ብለዋል፡፡ እማማ አማ በመጀመሪያው የዓለም ጦርነት ወቅት ዕድሜያቸው 7 የነበረ ሲሆን በዚያ ዘመን ዝነኛ የነበረውን ሙዚቃ ነበር በልደታቸው ያዜሙት፡፡ እማማ አማ አሁን የሚኖሩት ከሦስት ባለቤታቸው ጋር ሲሆን በዚህ ወረርሽኝ ወቅት ትልቋ ሴት አያታቸው ጋር አብሮ መኖር ምንኛ ደስ የሚል እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ እሷ መስህባችን ናት፤ ክብ ሰርተን ከሷ ጋር ነው ጊዜያችንን የምናሳልፈው ይላሉ፡፡ የቲክቶክ መተግበሪያ የተጀመረው በ2016 ሲሆን አሁን በዓለም ላይ አንድ ቢሊዮን ተጠቃሚዎች አሉት፡፡ ቲክቶክ እጥር ምጥን ያሉ አጫጭር ቪዲዮዎችን የሚያጋሩበት መተግበርያ ነው፡፡ የሳቻ እናት ወ/ሮ ፍሪማን ነገሩን ለቀልድ ብለው ልጃቸውን እስኪ ቅድመ አያትህን ቅረጻቸው እንዳሉትና ይህ ይሆናል ብለው እንዳልጠበቁ ተናግረዋል፡፡
news-47634989
https://www.bbc.com/amharic/news-47634989
በነጆው ጥቃት ከተገደሉት አንዱ የማዕድን ኩባንያው ባለቤት ነበር
ትናንት በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን ነጆ ወረዳ ሁምነ ዋቀዮ በተባለ ቀበሌ ታጣቂዎች በፈጸሙት ጥቃት የአምስት ሰዎች መገደላቸውን የኦሮሚያ ክልል የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ አስታውቆ ነበር።
ማክሰኞ ዕለት በታጠቂዎቹ ጥቃት የተገደሉት አምስት ሰዎች ሰንራይዝ በሚባል በአካባቢው የማዕድን ማውጣት ሥራ ላይ ለተሰማራ ኩባንያ የሚሰሩ እንደነበር ታውቋል። በጥቃቱ የተገደሉት ሦስት ኢትዮጵያዊያን እና ሁለት የውጪ ሀገራት ዜጎች ሲሆኑ እነሱም የህንድና የጃፓን ዜግነት ያላቸው እንደሆ የአካባቢው ኮማንድ ፖስት አባል የሆኑት አቶ አደም ኢስማኤል ለቢቢሲ አረጋግጠዋል። ከተገደሉት አራቱ ወንዶች ሲሆኑ አንዷ የውጪ ዜጋ ሴት ናት። • ኢትዮጵያዊያን፣ ጃፓናዊትና ህንዳዊ በታጣቂዎች ተገደሉ እነዚህ የጥቃቱ ሰለባዎች ከማዕድን ኩባንያው ጋር ይሰሩ የነበሩ ሲሆን አንደኛው የኩባንያው ባለቤት እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል። አቶ አለማየሁ በቀለ ይህንን የማዕድን ማውጣት ሥራ ለመጀመር ሦስት ዓመታትን የፈጀ ጥናት ማከናወኑንና የምርት ሥራውን ለመጀመር በተቃረበበት ወቅት ከአራት ባልደረቦቹ ጋር በታጣቂዎቹ መገደሉን የቅርብ ጓደኛው አቶ አቦማ አምሳሉ ለቢቢሲ ተናግሯል። አቶ አለማየሁ ከአንድ ወር በፊትም በሥራው አካባቢ በድንጋይ በተፈጸመ ጥቃት በመኪናው ላይ የመሰባበር ጉዳት የደረሰበት ሲሆን፤ ከአካባቢው ወጣቶችና ህብረተሰብ ጋር ለመግባባትና ከሥራው ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ ለመወያየት ዕቅድ እንደነበረው ጓደኛው አቶ አቦማ ያስታውሳል። አቶ አለማየሁ በቀለ ተወልዶ ያደገው ጊምቢ ውስጥ ሲሆን ነዋሪነቱ አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ነበር። እንዲሁም ባለትዳርና የሦስት ልጆች አባት፤ የመጀመሪያ ልጁም ገና አምስት ዓመቱ እንደሆነ አብሮ አደግ ጓደኛው ጨምሮ ገልጿል። • አምስት ነጥቦች ስለጌዲዮ ተፈናቃዮች ከአቶ አለማየሁ ጋር አብረው በጥቃቱ ከተገደሉት አንደኛው የመኪናው ሹፌር ሲሆን ሌሎቹ ግን በማዕድን ሥራው የሚረዱት ባለሙያዎች ነበሩ። ጃፓናዊቷና ሕንዳዊው ሥራውን ለማቀላጠፍ በዕውቀትና በልምዳቸው እንዲያግዙት የቀጠራቸው ባለሙያዎች እንደሆኑም ተገልጿል። ግድያው ከተፈጸመ በኋላ የወጡ መረጃዎች የድርጊቱ ፈጻሚዎች ማንነታቸው እንዳልታወቀ የያመለከቱ ቢሆንም አመሻሽ ላይ የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር በብሔራዊው ቴሌቪዥን ላይ ቀርበው ታጣቂዎቹ "ኦነግ ሸኔ" የተባለው ቡድን አባላት መሆናቸውን ገልጸዋል። ምክትል ኮሚሽነሩ ጀነራል ረታ በላቸው እንደተናገሩት፤ አምስቱን ሰዎች በመግደል መኪናቸውን ያቃጠሉት "በአካባቢው እየተዳከመ የመጣው የሸኔ ቡድን አባላት ናቸው" በማለት የጸጥታ ኃይሉም አስፈላጊውን እርምጃ ይወስዳል ብለዋል። • "በመጨረሻ ላይ ሳትስመኝ መሄዷ ይቆጨኛል" እናት ግድያውንና ምክትል ኮሚሽነሩ የተናገሩትን በተመለከተ ምላሽ እንዲሰጡ የኦነግ ቃል አቀባይ የሆኑትን አቶ ቶሌራ አደባን ቢቢሲ ጠይቆ "የድርጅቱን ወታደሮች በተመለከተ የዕርቅ ኮሚቴው የያዘው ጉዳይ በመሆኑ ሃሳብ መስጠት አንችልም" ብለዋል። ነገር ግን በተፈጸመው ግድያ እጅጉን ማዘናቸውንና አስፈላጊው ማጣራት መደረግ እንዳለበት አቶ ቶሌራ ጨምረው ተናገረዋል። ቀደም ባሉት ጊዜያት በምዕራብ ኦሮሚያ ከሚፈጸሙ ጥቃቶችና የጸጥታ ችግሮች ጋር በተያያዘ የኦነግ ስም በሚነሳበት ጊዜ ድርጅቱ በሚሰጠው ምላሽ ላይ መንግሥት ላይ ክስ ያቀርብ የነበረ ሲሆን አሁን ግን ከዚህ ተቆጥቧል።
news-46589180
https://www.bbc.com/amharic/news-46589180
ከአፋር እስከ ዲሲ፤ በዚህ ሳምንት የሚጠበቁ አምስት አበይት ክስተቶች
ዕለተ ሰኞ ላይ እንገኛለን፤ አዲስ ሳምንት ጀምረናል። ምንም እንኳ ሳምንቱ ይዟቸው የሚመጣቸውን ነገሮች ሁሉ ማወቅ ባንችል ተጠባቂ የሆኑትን ግን መጠርጠሩ አያዳግትም። በያዝነው ሳምንት ይከሰታሉ ተብለው የሚጠቁ አበይት ጉዳዮች የትኞቹ ናቸው? እነሆ አምስቱን።
ቭላድሚር ፑቲን አፋር፤ ሰመራ የአፋር ክልል ምክር ቤት ዛሬ ሊያካሂደው ባቀደው አስቸኳይ ጉባኤ ርዕሰ መስተዳድር እና የምክር ቤት አፈ ጉባኤ እንደሚሾም ይጠበቃል። አፋር ብሔራዊ ዴሞከራሲ ፓርቲ በ7ኛ ድርጅታዊ ጉባኤው ባስተላለፈው ውሳኔ መሰረት ሌሎች የተለያዩ ሹመቶች እንደሚሰጡም ነው የሚጠበቀው። ምክር ቤቱ በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተካሄደ ያለውን ለውጥ ለመተግበር የሚያስችል የአስፈፃሚ አካላትን አደረጃጀት፣ ስልጣንና ተግባር እንደገና ለመወሰን በተዘጋጀ አዋጅ ላይም ውይይት ካደረገ በኋላ ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል። • በሳተላይቶች ዙሪያ ሰባት አስደናቂ እውነታዎች (አዲስ ርዕሰ መስተዳድር ለአፋር ክልል የአፋር ክልል ምክር ቤት ዛሬ ማካሄድ በጀመረው አስቸኳይ ስብሰባ አቶ አወል አርባን ርዕሰ መስተዳድር አድርጎ ሾሟል። አዲሱ ርዕሰ መስተዳድር በቅርቡ ክልሉን ከሚያስተዳድረው የአፋር ብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (አብዴፓ) ሊቀ መንበርነት የተሰናበቱትን አቶ ስዩም አወልን በመተካት ነው መንበሩን የተረከቡት። አዲሱ ርዕሰ መስተዳደር አቶ አወል አርባ በቅርቡ አብዴፓ ባደረገው የአመራር ለውጥ የፕረቲው ምክትል ሊቀ መንበር እንዲሆኑ ተመርጠዋል። የክልሉ ምክር ቤት እያካሄደ ባለው ስብሰባ ከርዕሰ መስተዳደሩ በተጨማሪ አፈ ጉባኤ መምረጥ እንዲሁም አዲስ በተመረጡት ርዕሰ የሚቀርቡ ሹመቶችን ያፀድቃል ተብሏል። ) ቭላድሚር ፑቲን የሩስያው ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን በየዓመቱ ከተመረጡ ሩስያውያውን ጋር የሚያደርጉት ውይይት ሐሙስ ዕለት እንደሚከናወን ይጠበቃል። በቴሌቪዥን መስኮት የሚተላለፈው ይህ ስብሰባ ሰዓታትን የሚፈጅ ሲሆን 4 ሰዓት ከ40 ደቂቃ የፈጀው ትልቁ እንደሆነ ይነገርላቸዋል። «የተወደዱ ፑቲን፤ እንወድዎታለን፤ እናከብርዎታለን» ሲል ነበር አንድ ተሰብሳቢ ባለፈው ዓመት በነበረው ንግግሩን የጀመረው። ዘንድሮም በርካታ ማንቆለጳጰሶች ለፑቲን እንደሚወርድላቸው ይጠበቃል። ስብሰባውን ይበልጥ ተጠባቂ ያደረገው ነገር ግን ፑቲን ከአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር ስማቸው በተደጋጋሚ መነሳቱ ነው። ስለዚህ ጉዳይ ፑቲን ምን ይሉ ይሆን? • ከጦርነት ይልቅ ለብዙዎች ሞት ምክንያት የሆኑት አይጦች የብሪታኒያ እና አውሮፓ ሕብረት ፍቺ ከፊታችን ረቡዕ ጀምሮ ብሪታኒያ እና የአውሮፓ ሕብረት በይፋ ፍቺ ለመፈፀም 100 ቀናት ይቀራቸዋል። በእንግሊዝኛው 'ብሬግዚት' የተሰኘ ስያሜ የተሰጠው ይህ ፍቺ ከመገናኛ ብዙሃን አፍ ጠፍቶ አያውቅም። ፍቺው 100 ቀናት ብቻ ይቅሩት እንጂ ብሪታኒያ ከአውሮፓ ሕብረት በምን ዓይነት ሁኔታ ትለይ የሚለው ጉዳይ አከራካሪነቱ ቀጥሏል። አሁን አሁንማ ብሪታኒያ ተመልሳ ከአውሮፓ ሕብረት ጋር ትዳሯን ልታድስ ይሆን እየተባለ ይወራም ተጀምሯል። የዲሞክራቲክ ኮንጎ ጭንቀት በሕዝብ ብዛት በአፍሪካ አራተኛዋ ሃገር ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ሕዝብ የፊታችን ዕሁድ ወደ ምርጫ ጣብያዎች በማምራት ድምፃቸውን ይሰጣሉ። ምርጫው መካሄድ ካለበት ሁለት ዓመታት ዘግይቶ ነው እየተከናወነ ያለው። ሃገሪቱ እዚህ ደረጃ ለመድረስ ብዙ መከራ አይታለች፤ ግጭቶች እዚያም እዚህም ተከስተዋል፤ በርካቶችም ተፈናቅለዋል። የዛሬ ሁለት ዓመት ምርጫው ሊከናወን አካባቢ በነበረው ውጥረት ምክንያት ፕሬዝደንት ጆሴፍ ካቢላ ጊዜው በሁለት ዓመት እንዲራዘም ጠይቀው ነበር። ተቺዎች ግን የስልጣን ዕድሜያቸውን ለማራዘም አስበው እንጂ ሲሉ ወቅሰዋቸው ነበር። ሃገሪቱ በፈረንጆቹ 1960 ከቤልጅየም ቅኝ ግዛት ነፃ ከወጣች ጀምሮ ሰላማዊ ምርጫ አከናውና አታውቅም፤ አሁንም በሃገሪቱ የተወሰኑ ክፍሎች ግጭቶች እየተስተዋሉ ነው። • ከኢትዮጵያና ከሌሎች የአፍሪካ ሃገራት ስለተዘረፉ ቅርሶች ምን እናውቃለን? አሜሪካ ጨለማ ውስጥ የአሜሪካ ሕግ መወሰኛ ምክር ቤት በመንግሥት መሥሪያ ቤቶች በጀት ጉዳይ ካልተስማሙ ዕለተ አርብ የአሜሪካ መንግሥት ድቅድቅ ጨለማ ውስጥ ይገባል። ይህ ማለት ማንኛውም በመንግሥት የተያዘ መሥሪያ ቤት አገልግሎት መስጠት ሊያቆም ይችላል ማለት ነው፤ ከቪዛ መጠየቂያ ቤቶች እስከ ብሔራዊ ፓርኮች ከአገልግሎት ውጭ ሊሆኑ ይችላሉ። ትራምፕ ለድንበር ጥበቃ የሚሆን 5 ቢሊዮን ዶላር (136 ቢሊዮን ብር ገደማ) ይበጀትልኝ ማለታቸው ነው ፖለቲከኞቹን ለዚህ ዓይነቱ አተካራ የዳረጋቸው። ትራምፕ ከዲሞክራቶች ጋር በነበራቸው ስብሰባ ለግንቡ የሚሆን ብር ካልተመደበልኝ «የመንግሥት ሥራን በኩራት እዘጋለሁ» ሲሉ ማወጃቸው አይዘነጋም።
news-57188526
https://www.bbc.com/amharic/news-57188526
በጓቲማላ እስር ቤት ውስጥ በተነሳ ፍልሚያ ታራሚዎች ተቀልተው መሞታቸው ተነገረ
በጓቲማላ ኩዌትላቴናንጎ በተሰኘ ማረሚያ ቤት ውስጥ በተቀናቃኝ ቡድኖች መካከል በተነሳ ፍልሚያ ቢያንስ ሰባት እስረኞች መገደላቸውን የጓቲማላ ፖሊስ ገለጸ።
በማረሚያ ቤቱ ውስጥ በተፈጠሩት ማራ ሳልቫትሩቻ እና የባሪዮ-18 በተሰኙ ቡድኖች የአባላት መካከል በተካሄደ ግጭት ነው ሰባቱ ሰዎች አንገታቸው የተቀላው። ከዋና ከተማው 200 ኪ.ሜ ርቆ የሚገኘው ማረሚያ ቤቱ 500 እስረኞችን ለማኖር የተገነባ ቢሆንም ከ 2000 በላይ ሰዎችን ይዞ ይገኛል። ወደ 500 የሚጠጉ የፖሊስ መኮንኖች በማረሚያ ቤቱ ውስጥ የተነሳውን ቀውስ ለመቆጣጠር እንዲሰማሩ መደረጉን የጓቲማላ ብሔራዊ ፖሊስ ቃል አቀባይ ጆርጅ አጉዬላ ተናግረዋል ። የግጭቱን መነሾ አስመልክቶ አንድ የፖሊስ ምንጭ ለመገናኛ ብዙሃን መረጃ አቀብለዋል። አንድ እስረኛ የተቀናቃኙ ቡድን አባል ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ያዘዘ ሲሆን ይህም ባለቤቱ ላይ ተፈፀመ ላለው ግድያ የበቀል እርምጃ ነው ብለዋል ምንጩ። በባለሁለት እግር ተሸከርካሪ የመጡ ሁለት ሰዎች ግለሰቧን ከሰአታት በፊት ተኩሰው መግደላቸውም ታውቋል። እንደ ምንጩ ከሆነም ከብጥብጡ በስተጀርባ ያለው ታራሚ በግድያ ወንጀል ተፈርዶበት በእስር ላይ ያለ ነው። በጓቲማላ በዓመት ከሚመዘገቡት 3 ሺህ ገደማ ከሚሆኑት የግድያ ወንጀሎች መካከል ግማሽ ያህሉ በወሮበላ ቡደኖች ሚፈፀሙ መሆናቸውን የአገሪቱ ባለስልጣናት ገልፀዋል።
news-52806074
https://www.bbc.com/amharic/news-52806074
ኮሮናቫይረስ፡ “ጀግኖች ሆነን ነበር፤ አሁን ግን ተረሳን"- የጣልያን ሀኪሞች
ጣልያን በኮቪድ-19 ክፉኛ ከተጠቁ አገራት አንዷ ናት። የአገሪቱ የህክምና ባለሙያዎች በበሽታው የተያዙ ሰዎችን ለማከም ያደረጉት ተጋድሎ አስመስግኗቸዋል።
አሁን ግን እነዚህ የአገሪቱ ባለውለታዎች ተዘንግተዋል። ሎምባርዲ በበሽታው ሳቢያ ከመላው ዓለም ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባት ግዛት ናት። የህክምና ባለሙያዎች ሎምባርዲን ሊታደጓት እየሞከሩ ነው። ፓውሎ ሚራንዳ የጽኑ ህሙማን ክፍል ነርስ ነው። “ብስጩ ሆኛለሁ፤ ከሰው ጋርም እጋጫለሁ” ይላል። ከሳምንታት በፊት በጽኑ ህሙማን ክፍል ውስጥ ያለውን ተስፋ አስቆራጭ ሁኔታ የሚያሳዩ ፎቶዎች አንስቶ ነበር። • ዕድሜ ጠገቡ ስታዲየም ሊፈርስ ነው • 'ጨለምተኛው' ፕሮፌሰር "ዓለም ለ10 ዓመታት ትማቅቃለች" አሉ “የደረሰብንን መቼም መዘንጋት አልፈልግም። በቅርቡ ታሪክ ይሆናል። ከጠላት ጋር እየተዋጋን ነበር። አሁን መለስ ብዬ ለማሰብ ጊዜ ሳገኝ አቅጣጫ ቢስነት ይሰማኛል” ሲል ነርሱ ስሜቱን ያጋራል። በጣልያን ሕይወት ወደ ቀደመ ገጽታዋ ቀስ በቀስ እየተመለሰች ነው። አገሪቱ እንቅስቃሴ በመጀመር ደረጃ ሁለት ላይ ትገኛለች። ነርሱ የሚያነሳቸው ፎቶዎች ይህንን ደረጃ ለማሳየት ያለሙ ናቸው። “አደገኛው ጊዜ እየሰከነ ቢሆንም በጨለማ እንደተዋጥን ይሰማናል። ቁስለኞች እንደሆንን ይሰማኛል። ያየነው ነገር በሙላ አብሮን ይኖራል” ይላል። አስፈሪ ቅዠቶች የፓውሎን ስሜት የጽኑ ህሙማን ክፍል ነርስ ሞኒካ ማሪዎቲም ትጋራለች። “ነገሮች ካለፈው ወቅት እየባሱ መጥተዋል። ያኔ በሽታውን እየተዋጋን ነበር። አሁን መለስ ብዬ ስመለከት ግራ እጋባለሁ” ትላለች። በሽታው በከፍተኛ ሁኔታ እየተሰራጨ ቀን ከሌት በሚሠሩበት ወቅት ለማሰብ ጊዜ አልነበራቸውም። አሁን ግን ያለፉት ወራት ሰቆቃ ተደራርቦ እየተሰማቸው ነው። • ማኅበራዊ ርቀትን መጠበቅ የሚያስችሉ ቀላል ተግባራዊ ስልቶች • በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ የተደናቀፈው ጣናን ከእምቦጭ የማጽዳት ሥራ “ያየነው ሁሉ አብሮን ይኖራል። መተኛት አልችልም። በክፉ ቅዠትም እሰቃያለሁ። በየሌሊቱ አስር ጊዜ ልቤ እየመታ፣ ትንፋሽ አጥሮኝ እባንናለሁ” የነርሷ የሥራ ባልደረባ ኤሊሳ ፒዜራ ወረርሽኙ እጅግ አስጊ በነበረበት ወቅት ብርቱ ነበረች። አሁን ግን ዝላለች። ምግብ የማብሰል፣ ቤቷን የማጽዳት ጉልበትም የላትም። ሥራ በሌላት ቀን ተቀምጣ ትውላለች። “ከዚህ ወዲያ በነርስነት መቀጠል የምፈልግ አይመስለኝም” ሌላዋ ነርስ ማርቲና በንዲቲ ቤተሰቦቿንና ጓደኞቿን በበሽታው የምታስይዝ ስለሚመስላት እስካሁን ከማናቸውም ጋር አልተገናኘችም። ከባሌቤቷ ጋርም በተለያየ ክፍል ይኖራሉ። “ከቤት ስወጣ ስለሚጨንቀኝ ተመልሼ እገባለሁ። ከዚህ ወዲያ በነርስነት መቀጠል የምፈልግ አይመስለኝም” ትላለች። ነርሷ፤ “ካለፉት ስድስት ዓመታት በበለጠ ባለፉት ሁለት ወራት ሰው ሲሞት አይቻለሁ” ስትል ያሳለፈችውን ትገልጻለች። አንድ አዲስ ጥናት እንደሚያሳየው፤ በኮቪድ-19 ክፉኛ በተጠቁ አካባቢዎች ይሠሩ የነበሩ 70 በመቶ የሚሆኑ የጣልያን ነርሶች አሁን ላይ ተዳክመዋል። የጥናቱ ጸሐፊ ዶ/ር ሰሪና ባሬሎ “ይህ ወቅት ለዶክተሮችና ለነርሶች ከባድ ነው” ትላለች። የሰው ልጆች አደጋ ውስጥ ሲሆኑ ጭንቀትን መቆጣጠር የሚያስችል ንጥረ ነገር በአካላቸው ይመረታል። ሆኖም ግን ያሳለፍነውን ቆም ብሎ ለማሰብ ጊዜ ስናገኝ ጭንቀት ሊከተል እንደሚችል አጥኚዋ ታስረዳለች። “ጀግኖች ሆነን ነበር፤ አሁን ግን ረሱን” ዶክተሯ ብዙ የህክምና ባለሙያዎች ከአደጋ በኋላ የሚመጣ ጭንቀት ወይም በእንግሊዘኛው post-traumatic stress disorder (PTSD) ይገጥማቸዋል ብላ ትሰጋለች። የበሽታው ምልክት ከወራት ወይም ከዓመታት በኋላም ሊታይ ይችላል። የጤና ባለሙያዎች ከዚህ በኋላ ሥራቸው ላይ ማተኮር ሊከብዳቸውም ይችላል። በመላው ዓለም ዶክተሮችና ነርሶች ለሕይወታቸው ሳይሳሱ ኮሮናቫይረስን በመዋጋታቸው ተሞግሰዋል። ጀግኖችም ተብለዋል። በጣልያን ግን ተቸሯቸው የነበረው ፍቅር እየተሸረሸረ ይመስላል። ሞኒካ እንደምትለው፤ “ሞትን ፈርተው ሳለ ጀግና አድርገውን ነበር። አሁን ግን ረስተውናል። አሁን ምንም ጥቅም እንደሌላቸው ሰዎች እንቆጠራለን”። በቱራን ነርሶች እርስ በራሳቸው ተሳስረው፣ የቆሻሻ መጣያ ፕላስቲክ ለብሰው ተቃውሞ አካሂደው ነበር። ምሳሌያዊ በሆነ መንገድ ለጤና ባለሙያዎች ትኩረት እንዳልተሰጠ ገልጸዋል። በቂ የሀኪሞች መገልገያ ወይም PPE እንዲቀርብላቸውም ጠይቀዋል። • በአዲስ አበባ ኮካና አብነት የሚባሉት ስፍራዎች የኮቪድ-19 ስርጭትን ለመግታት ቁጥጥር እየተደረገ ነው • በጥሬ ገንዘብ ዝውውር ላይ የተጣለው ገደብ ለምን አስፈለገ? የተቃውሞ ሰልፉ ሲካሄድ “መጋቢት ላይ ጀግና ነበርን፤ አሁን ግን ዘንግታችሁናል” ስትል አንድ ነርስ በድምፅ ማጉያ ተናግራለች። ለሥራቸው ተጨማሪ ገንዘብ እንደሚሰጣቸው ተነግሯቸው ነበር። እስካሁን ግን ምንም አላገኙም። ቢያንስ 163 ሀኪሞችና 40 ነርሶች ኮቪድ-19ን ሲዋጉ ሕይወታቸውን አጥተዋል። አራቱ ራሳቸውን ነው ያጠፉት። በርካታ የጤና ባለሙያዎች እንደሚሉት፤ ይህ ሁሉ መስዋዕትነት ቢከፈልም፤ ወረርሽኙ ያልተከሰተ ያህል ችላ ተብለዋል። በአረጋውያን እንክብካቤ መስጫ ትሠራ የነበረችው ዶ/ር ኤሊሳ ናኒኖ “በቁጣ ነድጃለሁ” ትላለች። እንቅስቃሴ ላይ ተጥሎ የነበረው ገደብ ሲላላ፤ ሰዎች አካላዊ ርቀት ሳይጠብቁ፣ ጭምብል ሳያደርጉ ሲበሉና ሲጠጡ አስተውላለች። “የሚያረጉት ነገር እኔንና የሥራ ባልደረቦቼን የሚያዋርድ ነው። የሰውን ሕይወት አደጋ ላይ እየጣላችሁ ነው ብዬ ልጮህባቸው እፈልጋለሁ።” በእርግጥ የጤና ባለሙያዎቹ ከሕዝቡ ያገኙት ድጋፍ ወረርሽኙን ለማለፍ እንዳገዛቸው አይክዱም። “ጀግና ነኝ አልልም። ግን ድጋፉ ጠቃሚ ሰው እንደሆንኩ እንዲሰማኝ አድርጓል” ይላል ነርስ ፓውሎ። ተመራማሪዋ ዶ/ር ሰሪና፤ የህክምና ባለሙያዎችን ከጭንቀት ለመታደግ የሕዝብ ድጋፍ ያስፈልጋል ይላሉ። “ዶክተሮችና ነርሶች ያደረጉልንን መርሳት የለብንም” ሲሉም ሃሳባቸውን ቋጭተዋል።
news-54024260
https://www.bbc.com/amharic/news-54024260
ኮሮናቫይረስ፡ የቀድሞው የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር በርሎስኮኒ ሆስፒታል ገቡ
የጣልያን የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ሲልቪዮ በርሎስኮኒ 83 ዓመታቸው ሲሆን በኮሮናቫይረስ መያዛቸው ከተረጋገጠ በኋላ ሚላን በሚገኝ ሆስፒታል ገብተው እንደነበር ተገለፀ።
በርሎስኮኒ በ1990ዎቹ የጣልያን ፖለቲካ ውስጥ ዋነኛ ተዋናይ ነበሩ የቤርሎስኮኒ ፓርቲ፣ ፎርዛ፣ የጤንነታቸው ሁናቴ የሚያሰጋ አለመሆኑን በመግለጽ "ደህና ናቸው" ብሏል። ቤርሎስኮኒ ከሁለት ልጆቻቸው ጋር በኮሮናቫይረስ መያዛቸው የተረጋገጠው በሳርዲና ከተማ የእረፍት ጊዜቸውን ካሳለፉ በኋላ ነው። ሳርዲና ከጣሊያን ከተሞች ሁሉ ከፍተኛ የኮሮናቫይረስ ስርጭት የሚታይባት ከተማ ናት። ሐሙስ እለት በሚላን አቅራብያ እንዲቆዩ መደረጉ ተገልጿል። " የኮቪድ-19 ሁኔታቸውን ለመከታተል አነስተኛ የጥንቃቄ እርምጃ አስፈላጊ በመሆኑ እንጂ ደህና ናቸው" ያሉት የፎርዛ ኢጣልያ ሴናተር ሊቺያ ሮንዙሊ ናቸው። ሐሙስ ምሽት በርሎስኮኒ በሰሜን ሚላን ከሚገኘው ቤታቸው ወደሳን ራፋዔል ሆስፒታል ተወስደው ለይቶ ማቆያ ክፍል እንዲገቡ ተደርገዋል። ቀደም ብሎ የግል ሐኪማቸው፣ አልቤርቶ ዛንግሪሎ፣ በርሎስኮኒ ምልክት የማይታይባቸው መሆኑን ገልፀው ነበር። የጣልያን መገናኛ ብዙኃን የበርሎስኮኒ አጋር የሆነችው የ30 ኣመቷ ወጣት ማርታ ፋስቺናም በኮቪድ-19 መያዟ በምርመራ መረጋገጡን ዘግበዋል። ወይዘሪት ፋስቺና ፎርዛ ኢታሊያን በመወከል የምክር ቤት አባል ስትሆን ከፍቅር አጋሯ ሲልቪያ በርሎስኮኒ ጋር በለይቶ ማቆያ ትገኛለች። በርሎስኮኒ ለፓርቲያቸው አክቲቪስቶች ሐሙስ ዕለት በስልካቸው ባስተላለፉት መልዕክት " በቻልኩት ሁሉ በቀጣዩ ምርጫ ላይ እሰራለሁ" ካሉ በኋላ በቫይረሱ እንዴት ሊያዙ እንደቻሉ እንደማያውቁ ተናግረዋል። ጣልያን ከዚህ ቀደም ለማካሄድ ቀጠሮ ይዛለት የነበረውና በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ የተነሳ ወደ መስከረም ወር መጨረሻ አካባቢ የተገፋውን ክልላዊ ምርጫ ታካሄዳለች።
news-55434279
https://www.bbc.com/amharic/news-55434279
ትዊተር የዶናልድ ትራምፕን 33 ሚሊዮን የትዊተር ተከታዮች ለጆ ባይደን አላወርሳቸውም አለ
እጅግ ተጽእኖ ፈጣሪ ከሆኑ የማኅበራዊ ትስስር ገጾች አንዱ የሆነው የትዊተር ኩባንያ ዶናልድ ትራምፕ ከቀናት በኋላ ሥልጣን ሲለቁ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት በመሆናቸው ምክንያት ያገኙትን የትዊተር ስምና ተከታዮች ለመጪው ተመራጭ ፕሬዝዳንት አላወርስም ብሏል።
የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ተከታዮች በሙሉ ከገጹ ከተሰረዙ በኋላ ነው ጆ ባይደን ከዜሮ ተከታይ እንዲጀምሩ የሚደረገው ሲል ኩባንያው አስታውቋል። የጆ ባይደን ድጋፍ ሰጪ ቡድን ግን ትዊተር የትራምፕን ተከታዮች በሙሉ ለጆ ባይደን አሳልፎ እንዲሰጥ ከፍተኛ ውትወታና ጫና ሲያደርጉ ነበር። ትዊተር ኩባንያ ይህ የማይናወጽ አቋሜ ነው። የፕሬዝዳንቱን ተከታዮች በሙሉ እደልዛለሁ ሲል የመጨረሻ ውሳኔውን አሳውቋል። በፈረንጆቹ 2016 ትራምፕ ወደ መንበረ ሥልጣኑ ሲመጡ የባራክ ኦባማ 13 ሚሊዮን የትዊተር ተከታዮች በሙሉ ወደ ዶናልድ ትራምፕ እንዲሸጋገሩ ተደርጎ ነበር። አሁን ትዊተር ይህን አሰራሩን ለምን እንደቀየረ ያለው ነገር የለም። በታሪክ ትዊተርን ለመጠቀም የመጀመርያው ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ ቢሆኑም መድረኩን በስፋት 'ለልማትም ሆነ ለጥፋት' የተጠቀሙበት ትራምፕ እንደሆኑ ይነገራል። በእርግጥ የዛሬ 4 ዓመት ትዊተር የባራክ ኦባማን ተከታዮች ወደ ዶናልድ ትራምፕ ያወረሰው ከትራምፕ ቡድን በቀረበለት ጥያቄ ነበር። ስለዚህ ትራምፕ የትዊተር ተከታዮቻቸው 13 ሚሊዮን ሆነው ጀምረው ነው 33 ሚሊዮን ያደረሱት። ጆ ባይደን ግን ከ3 ሳምንት በኋላ ዋይት ሐውስ ሲገቡ የትዊተር ተከታዮቻቸው ብዛት ዜሮ ሆኖ ነው የሚጀምሩት። ትራምፕ ከ4 ዓመታት በፊት የተሰጣቸው የትዊተር ተከታዯች የመውረስ እድል ለባይደንም እንዲሰጥ የጆ ባይደን ቡድን ተመሳሳይ ጥያቄ አቅርቦ አይቻልም ተብሏል። የአሜሪካ ፕሬዝዳንት የትዊተር ስም በእንግሊዝኛ @POTUS ይሰኛል። ትራምፕ ከ4 ዓመታት በፊት የወረሱት ይህንን ስምና ተከታዮች ብቻ ሳይሆን የዋይት ሐውስ ጽሕፈት ቤቱ የሚያንቀሳቅሰውን @WhiteHouse ተከታዮችን ጭምር ነበር። ይህ ግን በ2020 ሊደገም አልቻለም። ትዊተር ባይደን ከዜሮ እንዲጀምር ነግሮናል ብለዋል አንድ የባይደን ረዳት። ትዊተር በበኩሉ ትራምፕን በትዊተር እየተከተሉ ያሉ ሰዎች በሙሉ ባይደንን ይከተሉ ይፈልጉ እንደሆነ ምርጫ ይሰጣቸዋል። ካልሆነ ግን ከትራምፕ ጋር የነበራቸው ታሪክ ወደ ማኀደር ክፍል ይገባል። በቀጥታ ጆ ባይደንን እንዲከተሉ ግን አይደረግም ብሏል። የጆ ባይደን የግል የትዊተር ስም @JoeBiden ሲሆን 21.7 ሚሊዮን ተከታዮች ብቻ ነው ያሉት። ትራምፕ የትዊተር ሰሌዳቸውን በአግባቡ ለግልና ለሥራ በመጠቀም ብዙ ተከታይ ማፍራታቸው ይነገራል። ብዙውን ጊዜ የካቢኔ ሹመⶉችን እንኳን ለማሰናበት ትዊተር ሰሌዳቸውን ሲጠቀሙበት ነበር። በርካታ የዓለም ሚዲያዎችም ትኩስ መረጃ ለማግኘት የትራምፕ የትዊተር ሰሌዳ ሁነኛ ምንጭ ሆኖ ቆይቷል። ዶናልድ ትራምፕ ዋይት ሐውስን ከረገጡ ጀምሮ 50ሺህ ጊዜ በሰሌዳቸው ላይ መረጃን ጽፈው አሰራጭተዋል። ፋክትቤት የተሰኘ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን የሚተነትን ዌብሳይት ይፋ እንዳደረገው ከሆነ ከጥቅምቱ ወር የፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ወዲህ ትራምፕ የትዊተር ተከታዮቻቸው ቀንሰውባቸዋል። በትዊተር ሰሌዳቸው 369ሺህ 849 ተከታዮችን ማጣታቸውን ይፋ አድርጓል፥ ፋክትቤት። በአንጻሩ ተቀናቃኛቸው የነበሩት ጆ ባይደን 2 ሚሊዮን 671 ሺህ 790 አዳዲስ ተከታዮችን አፍርተዋል። ይህ የትራምፕን ተከታዮች ለጆ ባይደን በቀጥታ አላወርስም የሚለው የትዊተር ውሳኔ ይፋ ከመደረጉ በፊት የትዊተር ኩባንያ ሥራ አስፈጻሚ ጃክ ዶርሲ ትራምፕን፥ ባይደንን እና ከማላ ሐሪስን በግሉ መከተል ማቆሙ ተዘግቦ ነበር።
48019531
https://www.bbc.com/amharic/48019531
ታጣፊው የሳምሰንግ ስልክ የ'ስክሪን' መሰበር ወቀሳ ቀረበበት
የሳምሰንግ አዲሱን ታጣፊ ስልክ ቀድመው የሸመቱ ግለሰቦች 'ስክሪኑ' እየተሰበረብን ነው በማለታቸው ምክንያት፤ ኩባንያው የስልኩን ምርቃት ጊዜ አዘግይቶታል።
'ጋላክሲ ፎልድ' የተሰኘ ስያሜ የተሰጠው ይህ ምርት እክል ስላጋጣመው ይቅርታ የጠየቀው ኩባንያው «ትንሽ ጊዜ ስጡኝና ስልኩን ላበጃጀው» ሲል ተደምጧል። • ሳምሰንግ እንደ መጽሐፍ የሚገለጥ ስልክ አመረተ 1980 ዶላር (61 ሺህ ብር ገደማ) ዋጋ የተለጠፈበት 'ጋላክሲ ፎልድ' ምርቃት በቅርቡ መሆኑ አይቀርም ብሏል ኩባንያው። ኩባንያው የችግሩ ምንጭ ሊሆን የሚችለው ስልኩ እንዲታጠፍ የሚረዳው ማጠፊያ ነውና እሱን እናስተካክል ዘንድ ጥቂት ሳምንታት ስጡን ብሏል። • የአዲሱ ሳምሰንግ ጋላክሲ S9 በካሜራ ብቃት ላይ አተኩሯል የደቡብ ኮሪያው ግዙፍ ኩባንያ ሳምሰንግ አዲሱን ምርቱን ሎንዶን፣ ሆንግ ኮንግ እና ሻንጋይ በመሳሰሉ ከተሞች አስመርቃለሁና በጉጉት ጠብቁኝ ብሎ ነበር። አንዳንድ ሸማቾች ስልኩ ላይ ያለው 'ስክሪን ከቨር' ስልኩን ከአደጋ እንዲከላከል የተቀመጠ መስሏቸው የስልኩን 'ስክሪን' መገንጠላቸው ደግሞ ሌላው አነጋጋሪ ጉዳይ ሆኗል። ሁዋዌ ኣነደ ዣዎሚ የተሰኙት የቻይና ስልክ አምራቾችም 'ታጣፊ ስልክ ካልሠራን ሞተን እንገኛለን' ማለታቸው ተሰምቷል። • በሞባይልዎ የኢንተርኔት ወጪ ተማረዋል?
news-52491114
https://www.bbc.com/amharic/news-52491114
የናይጄሪያው ፕሬዚዳንት ሙሃማዱ ቡሃሪ ለሞተ ግለሰብ ሹመት ሰጡ
የናይጄሪያው ፕሬዚዳንት ሙሐማዱ ቡሃሪ ለሞተ ሰው ሹመት መስጠታቸው አነጋጋሪ ሆኗል።
ቶቢያስ ቹክዌሜካ ኦክውሩ ከሞቱ ሁለት ወራት ቢያልፋቸውም በቅርቡ የአንድ የመንግሥት መስሪያ ቤት የቦርድ አባል ተደርገው በፕሬዚዳንቱ ተሹመዋል። ፕሬዚዳንት ቡሃሪ ለአገሪቱ ምክር ቤት ከሰሞኑ የ37 እጩ ተሿሚዎችን ዝርዝር የያዘ ደብዳቤ የላኩ ሲሆን፤ የሞቱትም ግለሰብ ስም በዝርዝሩ ውስጥ ተካቷል። የፕሬዚዳንቱ ሚዲያ አማካሪ ላውሬታ ኦኖቺ በበኩሏ ፕሬዚዳንቱ በቦርድ አባልነት ሲሾሟቸው ግለሰቡ በህይወት እንደነበሩ ገልፀው "የትምህርትና የሥራ ማስረጃቸውን አቅርበዋል። ለሹመታቸውም ዝግጁ ሆነው በደስታ ነበር የተቀበሉት" ብላለች ላውሬታ። "በሚያሳዝን ሁኔታ ህይወታቸው ሲያልፍ የምክር ቤቱን የማጣራት ሂደት እየጠበቁ ነበር። የማለፋቸውም ዜና ለፌደራል መንግሥቱ አልተነገረም" ብላለች። ምንም እንኳን አማካሪዋ ይህንን ትበል እንጂ ፕሬዚዳንቱ እንዲህ አይነት ከባድ ስህተት ሲፈፅሙ የመጀመሪያቸው አይደለም። ከዚህ ቀደምም፣ ከሦስት ዓመታት በፊት ከሞቱ ረዥም ጊዜ ያለፋቸውን አምስት ሰዎች ለመንግሥት መስሪያ ቤቶች በቦርድ አባልነት ሾመዋል።
news-47579856
https://www.bbc.com/amharic/news-47579856
ቦይንግ 737-8 ማክስ አውሮፕላኖቹ በሙሉ እስከ ግንቦት እግድ ተጣለባቸው
እሁድ ዕለት በኢትዮጵያ አየር መንገድ የደረሰውን አደጋ ተከትሎ ቦይንግ 737- ማክስ 8ና 9 አውሮፕላኖቹ ቢያንስ እስከ ግንቦት ድረስ እንዲታገዱ የአሜሪካ ፌዴራል አቪየሽን አስተዳደር ውሳኔን አስተላልፏል።
የአሜሪካ ተቆጣጣሪዎች እንዳሳወቁት ሶፍትዌሮቹ ተገጥመው እስኪሞከሩ ድረስ መብረር አይችሉም ተብሏል። •ቦይንግ 737-8 ማክስ አውሮፕላኖቹን በሙሉ አገደ እለተ እሁድ መጋቢት 1 ቀን ከኢትዮጵያ ወደ ኬንያ ሲበር የነበረው ቦይንግ 737-8 ማክስ አውሮፕላን አደጋ ከ35 አገራት ለመጡ 157 ሰዎች ህይወት መቀጠፍ ምክንያት ሆኗል። •"አደጋውን ስሰማ በረራው ጠዋት እንዳልሆነ ራሴን አሳመንኩኝ" የረዳት አብራሪው ጓደኛ ከአምስት ወራት በፊት የኢንዶኔዥያ ንብረት የሆነው ቦይንግ 737-8 ማክስ ተከስክሶ 189 ሰዎች ከሞቱበት አደጋ ቀጥሎ አስከፊው ነው ተብሏል። በዘርፉ ላይ ያሉ አስተያየት ሰጭዎች ከአደጋው ቦታ ላይ የተወሰዱ መረጃዎችንና የሳተላይት ምስሎችን በማጤን በኢትዮጵያ አየር መንገድና ከስድስት ወራት በፊት በኢንዶኔዥያ የደረሰው ግንኙነትና ተመሳሳይነት እንዳለው ነው። •"የሞተው የኔ ያሬድ ነው ብዬ አላሰብኩም" የካፕቴን ያሬድ የ11 አመት ጓደኛ በተጨማሪም የመከስከስ አደጋው በደረሰበት ቦታ ላይ የተገኙት መረጃዎች በላየን አየር መንገድ ከደረሰው ጋር ተመሳሳይ መሆኑን አሳይ ነው ብለዋል። የአሜሪካ ተወካይ ሪክ ላርሰን እንደገለፁት መተግበሪያውን (ሶፍትዌሩን) ለማሻሻል ጥቂት ሳምንታት እንደሚወስድና በአውሮፕላኖቹ ላይ ለመግጠምም ቢያንስ እሰከ መጋቢት ድረስ ይቆያ። •"እናቱ ስታየኝ 'ልጄ ያሬድ ይመጣል' እያለች ታለቅስ ነበር"- በናይሮቢ የካፒቴኑ ጸጉር አስተካካይ እሁድ እለት የተከሰከሰው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ቦይንግ 737-ማክስ 8 የበረራ ቁጥር ET 302 አውሮፕላን መረጃ ሳጥን በፈረንሳይ አገር እንዲመረመር በትናንትናው ዕለት ወደ ፓሪስ መወሰዱን የኢትዮጵያ አየር መንገድ በትዊተር ገጿ አስፍራለች። ሪፖርቶች እንደሚያሳዩት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ጀርመንን የጠየቀችው በጎርጎሳውያኑ 2010 ሊባኖስ ላይ በደረሰው አደጋ የምርምሩን ስራ በሰራችው ፈረንሳይ ኢትዮጵያ ደስተኛ ባለመሆኗ ነው።
55976538
https://www.bbc.com/amharic/55976538
የሚየንማር ዜጎች ሥራ አቁመው ተቃውሞውን ተቀላቀሉ
በሚየንማር በመፈንቅለ መንግሥት ከሥልጣን የተወገዱት አን ሳን ሱ ቺ እንዲለቀቁ የሚጠይቀው አገራዊ ተቃውሞ እንደቀጠለ ነው። ሠራተኞችም የሥራ ማቆም አድማ በመምታት ተቃውሞውን ተቀላቅለዋል።
በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች በመዲናዋ ፒ ታው በሚገኙት ያንጎን እና ማንዳሊ አደባባዮች ተቃውሞ እያካሄዱ ነው። ሚየንማር እንደዚህ ያለ ተቃውሞ ካየች ከአስር ዓመት በላይ ይሆኗታል። ወታደራዊ ሃይሉ የሚየንማርን መሪ በመፈንቅለ መንግሥት አስወግዶ ለአንድ ዓመት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ደንግጓል። መሪዋ፣ ፕሬዘዳንት ዊን ሚንት እንዲሁም ሌሎችም የገዢው ፓርቲ ኤንኤልዲ አባላት የቁም እስር ላይ ይገኛሉ። "አንሠራም" በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች በኔይ ፒ ታው የተቃውሞ ሰልፍ እያካሄዱ ነው። በሌሎች ከተሞችም ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ነዋሪዎች ተቃውሞውን ተቀላቅለዋል። መምህራን፣ ጠበቃዎች፣ የባንክ ሠራተኞችና የመንግሥት ተቀጣሪዎች ከተቃዋሚዎቹ መካከል ይገኙበታል። በሺዎች የሚቆጠሩ መምህራን ያንጎን ከተባለ ከተማ ሱሌ ፓጎንዳ ወደተባለው ማዕከላዊ ሚየንማር አቅንተዋል። ሠራተኞች የተቃውሞው አካል እንዲሆኑ ሥራ እንዲያቆሙም በበይነ መረብ ንቅናቄ እየተደረገ ነው። የ28 ዓመቱ የፋብሪካ ሠራተኛ ሂኒን ታዚን "ዛሬ የሥራ ቀን ነው። እኛ ግን አንሠራም። ደሞዛችን ቢቆረጥም አንሠራም" ሲል ለኤኤፍፒ ተናግሯል። በኔይ ፒይ ታው ፓሊስ ሰልፈኞችን ለመበተን ውሃ እንደተጠቀመና ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች እንዳሉም ተዘግቧል። ተቃዋሚዎች እርስ በእርስ ሲረዳዱና አይናቸውን ሲያሹ አንድ ተንቀሳቃሽ ምስል ያሳያል። በየጎዳናው መፈክር ይዘው ድምጻቸውን የሚያሰሙ ተቃዋሚዎችም ታይተዋል። የሚየንማሩ ኤንኤልዲ ፓርቲ ብሔራዊ ምርጫ አሸንፏል መባሉን ተከትሎ መከላከለያው መፈንቅለ መንግሥት አካሂዷል። ወታደራዊ ሀይሉ ምርጫው ተጭበርብሯል በማለት ተቃዋሚዎችን ደግፏል። ሆኖም ግን የአገሪቱ የምርጫ ኮሚሽን ምርጫው ስለመጭበርበሩ ምንም ማስረጃ የለም ብሏል። መከላከያው የገንዘብ፣ የጤና፣ የአገር ውስጥ እና የውጪ ጉዳይ ሚንስትሮችን አንስቶ ሌሎች ባለሥልጣኖች ሾሟል። ፌስቡክ፣ ትዊተር እና ኢንስታግራም የመሳሰሉትን ወታደራዊ ሀይሉ አግዷል። ከቅዳሜ ጀምሮ እስከዛሬ ድረስ ተቃውሞ እየተካሄደ ይገኛል። ሚየንማር ውስጥ እንዲህ ያለ ተቃውሞ የተካሄደው እአአ በ2007 ነበር። በያኔው የሻፍሮን አብዮት በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ወታደራዊ አገዛዙን ለመቃወም አደባባይ ወጥተው ነበር።
news-56855670
https://www.bbc.com/amharic/news-56855670
በአዲስ አበባ በጅምር ላይ የነበረ ህንጻ ተደርምሶ የሦስት ሰዎች ሕይወት አለፈ
በአዲስ አበባ ከተማ በጅምር ላይ የነበረ ህንጻ ተደርምሶ የሦስት ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተነገረ።
አደጋው የደረሰበት የካዛንችስ አከባቢ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እሳትና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ቡድን መሪ አቶ ጉልላት ጌታነህ ለቢቢሲ እንደገለጹት አደጋው የደረሰው በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 ካዛንቺስ ጁፒተር ሆቴል ፊት ለፊት ነው። እንደ ቡድን መሪው ገለጻ ከሆነ አደጋው ትላንት ሚያዝያ 15 2013 ዓ.ም. ከጠዋቱ 5 ሰዓት አከባቢ ነበር የደረሰው። ለሦስት ሰዎች ሕልፈት ምክንያት የሆነው አደጋው የደረሰው ጅምር ላይ ህንጻ በመደርመሱ መሆኑን ጠቁመው ለጅምር ህጻው መደርመስ ግን እስካሁን መንስኤው አልተለየም ብለዋል። ሕይወታቸው ያለፈው ሦስቱ ግለሰቦች በ23 እና የ24 የእድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ወጣቶች እንደነበሩ አቶ ጉልላት ገልጸዋል። በህንጻው መደርመስ ሕይወታቸው ካለፈው ወጣቶች በተጨማሪ አራት ሰዎች ጉዳት የደረሰ ሲሆን ሦስቱ ቀላል፤ አንደኛው ላይ ግን ከባድ ጉዳት እንደደረሰ አቶ ጉልላት አስረድተዋል። "በሥራው ላይ ተሰማርተው የነበሩ 112 ሠራተኞች ነበሩ" ያሉት አቶ ጉልላት "ከአዲስ አበባ ፖሊስ እና ከፌደራል ፖሊስ ጋር በመተባበር 109 ሰዎችን ማትረፍ ተችሏል" ብለዋል። አደጋውን ለመቆጣጠር 35 የአደጋ ጊዜ ሠራተኞች፤ 3 ከባድና 4 ቀላል ተሽከርካሪዎች እና 3 አምቡላንሶች ተሠማርተዋል። አደጋውን ለመቆጣጠርም 2 ሰዓታት የፈጀ ሥራ መከናወኑን ገልጸዋል። በአደጋው 100 ሺህ ብር የሚገመት ንብረት ጉዳት ሲደርስበት 2 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ንብረት ለማትረፍ መቻሉን አቶ ጉልላት ተናግረዋል። ሰፊ የግንባታ ሥራዎች በሚከናወኑባት አዲስ አበባ ከተማ በጥንቃቄ ጉድለት ምክንያት ከዚህ ቀደ በሰው እና በንብረት ላይ ጉዳት ሲደርስ ተስተውሏል።
news-53728754
https://www.bbc.com/amharic/news-53728754
ኦነግ ፡ “ስለመግለጫው አላውቅም፤ አላማውም ምን እንደሆነ አይገባኝም" አቶ ዳውድ ኢብሳ
የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ሊቀ መንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ ትናንት ሰኞ በድርጅታቸው አመራሮች አዲስ አበባ ውስጥ ስለተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ለቢቢሲ ተናገሩ።
አቶ ዳውድ፤ “ስለ መግለጫው አላውቅም። አጀንዳውም፣ አላማውም ምን እንደሆነ አይገባኝም” ሲሉ እንደግንባሩ ሊቀመንበርነታቸው ምንም እንደማያውቁ ገልጸዋል። በግንባሩ ስም በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መግለጫ የሰጡት ከፍተኛ አመራሮች አቶ አራርሶ ቢቂላ ምክትል ሊቀመንበር፣ አቶ ቶሌራ አደባ ቃል አቀባይ እና አቶ ቀጀላ መርዳሳ በጋራ ሆነው ሲሆን ኦነግን የተመለከቱ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል። አመራሮቹ እንዳሉት ግንባሩ በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ቢወስንም አመራሮቹና አባላትን በማሰር እንዲሁም ስሙን የማጠልሸት ዘመቻ እየተካሄደበት መሆኑን ጠቅሰው በተጨማሪም በመቶዎች የሚቆጠሩ አባላቱ እንደታሰሩበትም አመልክተዋል። ከሁለት ሳምንት በፊት የግንባሩ ሊቀመንበር አቶ ዳውድ ለደኅንነታቸው ሲባል በጸጥታ ኃይሎች ከቤታቸው እንዳይወጡ በተደረገበት ጊዜ ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች በጽህፈት ቤቱ ስብሰባ ማካሄዳቸውን በተመለከተ የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ለቢቢሲ መናገራቸው ይታወሳል። ይህንንም በተመለከተ የኦነግ የሕግና የቁጥጥር ኮሚቴ የማጣራት ሥራ እንዲያከናውን እንደሚደረግ አቶ ዳውድ ኢብሳ ተናግረው ቀደም ያለው ስብሰባ ጉዳይ እስኪጣራ ድረስ መግለጫ መስጠት መከልከሉንና የአሁኑም ጋዜጣዊ ጉባኤ ከዚህ ጋር የተቃረነ መሆኑን ጠቅሰዋል። “የተደረገው ስብሰባ በጣም የተምታታ ስለሆነ የሕግና የቁጥጥር ኮሚቴው እስከሚያጣራ ምንም አይነት መግለጫ እንዳይሰጥ ተብሎ አቁሟል። እነሱም ምን መግለጫ እንደሚሰጥ አናውቅም ብለው መልሰውልኛል። የማምታታት ሥራ እየተሠራ ነው” ሲሉ አቶ ዳውድ ሁኔታውን ገልጸዋል። የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ለሁለት ተከፍሏል በሚል በስፋት እተነገረ ስላለው ጉዳይ በተመለከተም ሊቀ መንበሩ ግንባሩን ለማዳከም “አሁን ባለው የፖለቲካ ሁኔታ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር ኢላማ ውስጥ ነው” ብለዋል። “መንግሥት በራሱ የዴሞክራሲ ሂደት፣ በሰላም መንቀሳቀስ ሲያቅተውና ተፎካካሪ ፓርቲ ሲበረታበት በገንዘብም ይሁን በማስፈራራትም በፖለቲካ ፓርቲዎች ላይ ጣልቃ ይገባል” ሲሉ ሊቀ መንበሩ አስረድተዋል። ከዚህ ቀደምም መሰል ጣልቃ ገብነት በግንባራቸው ላይ ሲሞከር እንደነበረ የተናገሩት አቶ ዳውድ፤ “ይሄ አሁንም የማይደረግበት ምክንያት የለም። ብዙ ገንዘብ ነው የሚረጨው” ሲሉ ጥረቱ በገንዘብ ችምር የሚደገፍ መሆኑን ገልጸዋል። ከሳምንታት በፊት ከቤታቸው እንዳይወጡ የተደረጉትም በዚሁ ምክንያት እንደሆነ ገልጸው ”ስልኬን ያፈኑበትም የዚህ ኦፕሬሽን (ተልዕኮ) አካል ነው” ሲሉ እየደረሰብን ነው ያሉትን ጫና ተናግረዋል። ቀደም ሲል በግንባሩ ጽህፈት ቤት ያለ ሊቀመንበሩ የተካሄደውን ስብሰባ ተከትሎ የሚቃረኑ አስተያየቶች የተሰነዘሩ ሲሆን የስብሰባው ተሳታፊዎች ጉዳዩን አቶ ዳውድ እንደሚያውቁት ቢናገሩም እሳቸው ግን የሚያውቁት ነገር እንዳልነበረ ለቢቢሲ ተናግረዋል። ሰኞ ዕለት በአዲስ አበባው ሒልተን ሆቴል ውስጥ የተሰጠውን መግለጫ በሚመለከተም የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ሊቀመንበር የሚያውቁት ነገር እንደሌለና በተለያዩ መንገዶች ጫና እየገጠማቸው መሆኑን ለቢቢሲ ገልጸዋል። አቶ ዳውድ ኢብሳ ከቤታቸው መውጣት ባልቻሉባቸው ጊዜያት የተካሄደውን የግንባሩን አመራሮች ስብሰባ ተከትሎ አዲስ ሊቀመንበር ስለመመረጡ እና ድርጅቱ ለሁለት ስለመከፈሉ ወሬዎች ሲናፈሱ ቢቆዩም ሁሉም አመራሮች እነዚህ ወሬዎች ሲያስተባብሉ ቆይተዋል። ኦነግ ለኦሮሞ ሕዝብ መብት ከሚታገሉ ድርጅቶች ቀዳሚው ሲሆን በተለያዩ ጊዜያት ከግንባሩ እራሳቸውን የለዩ አባላቱ በኦሮሞ ስም የተለያዩ ድርጅቶችን በማቋቋም ሲንቀሳቀሱ ቆይተዋል። አሁን በአቶ ዳውድ ኢብሳ ሊቀመንበርነት የሚመራው ግንባር ከሌሎች የኢትዮጵያ የፖለቲካ ቡድኖች ጋር በሕገ ወጥነት ተፈርጆ ለበርካታ ዓመታት መቀመጫውን አሥመራ ውስጥ አድርጎ የትጥቅ ትግል ስልትን ሲያራምድ ቆይቷል። በቅርቡ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ለውጥ ከተካሄደ በኋላ ኦነግና ሌሎች የፖለቲካ ቡድኖች ከአገሪቱ የሽብር ዝርዝር ውስጥ እንዲወጡ ተደርጎ ወደ አገር ቤት ተመልሶ በሰላማዊ የፖለቲካ መድረክ በመሳተፍ ላይ ይገኛል።
news-53727586
https://www.bbc.com/amharic/news-53727586
ጃዋር መሐመድ እና በቀለ ገርባ፡ ጉዳያቸውን በሚመለከቱ የዳኛ ገለልተኛነት ላይ ጥያቄ አነሱ
ዛሬ ፍርድ ቤት የቀረቡት አቶ ጃዋር መሐመድና ሌሎች 14 ተጠርጣሪዎች ጉዳያቸውን በሚመለከቱት ዳኛው ገለልተኛነት ላይ ጥያቄ እንዳነሱ ከጠበቆቻቸው አንዱ የሆኑት አቶ ቱሊ ባይሳ ለቢቢሲ ገለጹ።
ጠበቃው እንዳሉት፤ ተጠርጣሪዎቹ “ችሎቱን እየመሩ ያሉት ዳኛ ገለልተኛ፣ ሚዛናዊና ፍትሐዊ ስለመሆናቸው እንጠራጠራለን” ሲሉ ባለ ሰባት ገጽ ማመልከቻ አስገብተዋል። በማመልከቻው ላይ አቶ ጃዋር “ዳኛው የፌዝ ሳቅ ስቀው ነው ያስተናገዱኝ” ማለታቸውን ከአሥሩ ተከላካይ ጠበቆች መካከል አንዱ የሆኑት አቶ ቱሊ አክለዋል። ተጠርጣሪዎቹ ዳኛው እንዲነሱ ጥያቄ ቢያቀርቡም፤ ችሎቱን እየመሩ የሚገኙት ዳኛ ግን ጥያቄያቸውን ውድቅ አድርገውታል። የተጠርጣሪዎቹ ጥያቄ በሌሎች ዳኞች ታይቶ ብይን እስከሚሰጥ ድረስ መዝገቡ ተዘግቶ ተጠርጣሪዎቹ ባሉበት እንዲቆዩ መወሰኑንም ተናግረዋል። ጠበቃው ለቢቢሲ እንዳሉት፤ ተጠርጣሪዎቹ ባስገቡት ማመልከቻ ላይ “ዳኛው ለከሳሽ ወግነው ጉዳዩን እየመሩ ስለሆነ ይነሱልን” ሲሉ ጠይቀዋል። በሕጉ መሠረት፤ እንዲህ አይነት ጥያቄ ሲቀርብ፤ ዳኛው ጥያቄውን ተቀብለው ከችሎት ካልተነሱ ጉዳዩ በሌሎች ዳኞች የሚታይ ይሆናል። አቶ ጃዋር መሐመድ እና አቶ በቀለ ገርባን ጨምሮ 14ቱ ተጠርጣሪዎች ፍርድ ቤት የቀረቡት አቃቤ ሕግ በቀዳሚ ምርመራ ምስክሮችን ለመስማት ለዛሬ ቀጥሮ በመስጠቱ ነበር። ዐቃቤ ሕግ በቀዳሚ ምርመራ ከሚያቀርባቸው 15 ምስክሮች መካከል አምስቱ ማንነታቸው ሳይገለጽ [ከመጋረጃ በስተጀርባ] ቃላቸውን እንደሚሰጡ ባለፈው ሳምንት መገለጹ ይታወሳል። አቶ ቱሊ እንዳሉት፤ ተጠርጣሪዎቹ ችሎቱን የሚመሩት ዳኛ ገለልተኛነት ላይ ጥያቄ ካነሱበት ምክንያት አንዱ “የመሰማት መብታችን ተገድቧል” ብለው ነው። “ተጠርጣሪዎቹ፤ ዳኛው በጠበቆቻችን የሚቀርቡ ማመልከቻዎችን በአግባቡ እየሰሙ አይደለም ብለዋል። ከመጋረጃ በስተጀርባ ሆነው ይመስክሩ የተባሉ ሰዎች ማንነታቸው ሳይገለጽ የሚመሰክሩበት ሁኔታ አለ ወይስ የለም? በሚለው ላይ መከራከሪያ ለማቅረብ ብንጠይቅም ፍርድ ቤቱ አልተቀበለውም” ብለዋል። በሕጉ መሠረት የአገር ደኅንነትን የሚጎዳ ጉዳይ ሲሆን ወይም ምስክሮች ለደኅንነታቸው ሲሰጉ ማንነታቸው ሳይገለጽ ቃላቸውን ለመስጠት ዐቃቤ ሕግን ይጠይቃሉ። ጠበቃው እንደሚሉት፤ ዐቃቤ ሕግ ከመጋረጃ በስተጀርባ ይመስክሩ ያላቸው አምስት ግለሰቦች፤ ማንነታቸው ሳይገለጽ ቃላቸውን መስጠት እንደሚፈልጉ ከዐቃቤ ሕግ ጋር ውል የገቡበትን ሰነድ ለፍርድ ቤት አላቀረበም። “ዐቃቤ ሕግ እነዚህ [ምስክሮች ማንነታቸው ሳይገለጽ ቃል ለመስጠት የጠየቁበት ሰነድ] ባልተሟሉበት ሁኔታ ምስክሮቹ ከመጋረጃ ጀርባ ሆነው ይመስክሩ ማለቱን አልተቀበልንም” ይላሉ አቶ ቱሊ። ጠበቃው እንዳሉት፤ ተጠርጣሪዎቹ ባስገቡት ማመልከቻ ላይ የችሎት ሂደቱን ከመንግሥት መገናኛ ብዙኃን በተጨማሪ የግል የአገር ውስጥና የውጭ ሚዲያዎች እንዲዘግቡ ጥያቄ ቢያቀርቡም፤ ፍርድ ቤቱ ጥያቄያቸውን ውድቅ እንዳደረገው ጽፈዋል።
42973000
https://www.bbc.com/amharic/42973000
ካለሁበት 21፡በእንግሊዝ ሰው ወደየግል ጉዳዩ ነው የሚሯሯጠው
ፍካረ ሃይለ እባላለሁ። በእንግሊዝ አገር ለንደን ከተማ ነው የምኖረው። እዚህ ከተማ ውስጥ ለስምንት አመታት ቆይቻለሁ።
ታሪኬን ላውጋችሁ ከእኔጋ ቆዩ። የተወለድኩት በአስመራ ከተማ ነው። በባህር ሃብት ሚኒስቴርም ተቀጥሬ እሰራ ነበር። በወቅቱ አስመራ ላይ የነበረው አስተዳደር አሁን እንዳለው ዓይነት ኣልነበረም። ለጥበብና ለስእል ከፍተኛ ፍቅር ስለነበረኝ የስነ-ጥበብ ትምህርቴን ለመከታተል ወደ አዲስ አበባ ከ24 ዓመት በፊት መጣሁ። ለሶስት ዓመታት ከተማርኩ በኋላም ትምህርቱን አቋርጨ ከአዲስአበባ ወደ ጣልያን የሚያስገባ ቪዛ ስላገኘሁ የተሻለ ትምህርት ለመከታተል በማሰብ ወደ ጣልያን አመራሁ። ለ12 ዓመታትም ያህል በጣልያን አገር በህትመት ስራዎችና በማስዋብ (ዲኮሬሽን) ሰርቻለሁ። ስደት እንዳሁኑ ፈታኝ አልነበረምና ብዙም ችግር አልገጠመኝም። ከህንፃ አሰራር ጀምሮ ጣልያን ከኤርትራ ጋር የሚያመሳስሏት በርካታ ነገሮች ስላሉ የእንግድነት ስሜት አልተሰማኝም። ራሴንም እንደ ስደተኛ አድርጌም አልቆጠርኩም። ጣልያን አሪፍ አገር ነች፤ተሰባስበንም አንድላይ ጥሩ ጊዜ እናሳልፍ ነበር። ብዙ ሰዎች ኣንዴ ወደ ጣልያን ከገቡ መውጣት አይፈልጉም። እኔ ግን ለተሻለ ህይወት ኑሮየን ወደ ለንደን ቀየርኩኝ። በእንግሊዝና በጣልያን አገራት የስደት ህይወት ተመሳሳይ አይደለም። በጣልያን አገር የማህበራዊ ቁርኝቱ ሰፊ ነው። በእንግሊዝ ግን ሰው ወደ የግል ጉዳዩ ነው የሚሯሯጠው። ትዳር ራሱ በስደት በጣም ከባድ ነው። የሰውን ልጅ መሰረታዊ ሰብአዊ መብቶችን በማክበር ረገድ ግን በጣም የማደንቃት አገር ነች። በዚህ ረገድ ጣልያንና እንግሊዝ አይወዳደሩም ። ጣልያን የስደተኞችን መብት በማክበር ብዙም ርቀት አልሄደችም። በእንግሊዝ ትምህርቴን ለመቀጠል ፍላጎት ቢኖረኝም ስራ ላይ ብቻ ነው ያተኮርኩት። ሆኖም ስእልና ጥበቡን አልተውኩትም። አስመራና ለንደን ለንደን ከተማ ከአስመራ ጋር አይወዳደሩም። ለንደን በቴክኖሎጂ ረገድ በጣም ያደገች ከተማ ነች። ልዩነቱ በጣም ሰፊ ነው። በተለይ ደግሞ በትራንስፖርት ዘርፍ ለንደን ላይ ያለው የትራንስፖርት ስርአት ከባቡር ጀምሮ እስከ አውቶብስ የተቀናጀ ነው። በሚልዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች በሚኖሩባት ለንደን ለሁሉም የሚበቃ ትራንስፖርት ማዘጋጀት ቀላል አይደለም። በጣም ያስቀናል። ይሄስ የትራንስፖርት ስርዓት እኛ አገር ላይ በተዘረጋ ብዬ አስባለሁ። ከምግብ ፓስታና ሽሮ እወዳለሁ ፤ ለማግኘትም አያስቸግርም። ጥበብ እና ተፈጥሮ ተፈጥሮ ለኔ ከፍተኛ የሆነ ደስታን ይሰጠኛል ፤ ለኔ ብዙ ትርጉም ስላለውም የምስላቸው ስእሎችም ከተፈጥሮ ጋር የሚተሳሰሩ ናቸው። የተፈጥሯዊ ውበት ባላቸው ቦታዎች ስሄድ በጣም እመሰጣለሁ። በቦታው በመደመም አላበቃም ለህይወቴ መመርያ ሊሆነኝ የሚችል ብዙ ሃሳብ አመነጫለሁ። ከለንደን መቀየር የምፈልገው ነገር ቢኖር በዚህ ከተማ የሚኖር ህዝባችን እንዲጠነክርና በአንድነት ተባብሮ ባየው ደስ ይለኛል። ካገር ወጥቶ መኖር ቀላል አይደለም። በሰው አገር እየኖሩ አብሮህ ከሚኖሩ የአገርህ ልጆች ጋር በፍቅር እና በመተሳሰብ መኖር የማይቻልበት ሁኔታ አይኖርም። በኤርትራ ያለንን ተስፋ የሚያጨልም ብዙ ሁኔታዎች ቢፈጠሩም ጊዜ የማይቀይረው ስለሌለ ሁሉም ነገር ሲሻሻል ወደ አገሬ የምመለስባት ቀን እናፍቃለሁ። ስደት ላይ ላለ ሰው በተለይ መጀመሪያ አካባቢ ላይ ሁሉም ነገር ከባድ ነው። ገንዘብ ቢኖር ራሱ ያስጨንቃል። እንግዳ በመሆናችን ሰው ራሱ ይሸሸነናል። ረዥሙን ጊዜዬን የማሳልፈው በስራ በህትመት ስራዎችና በማስዋብ (ዲኮሬሽን) ነው። ንቅሳትን መንቀስ፣ የሞባይል እና የኤሌክትሮኒክስ ጥገና፣ ቅርፃ ቅርፅ እና ካፌ ውስጥ በትርፍ ግዜየ የምሰራባቸው ተጨማሪ ሙያዎቼ ናቸው። የዚህ አገር የስደት ህይወት ከሌሎች የአውሮፓ አገራት ለየት ያለ ነው። ችግር ብዙ ነገር ስለ ሚያስተምር የሚያጋጥሙንን ነገሮች በትእግስት ማለፍ አለብን። በዚህ ሰአት ራሴን ወደ ሌላ ቦታ መላክ ብችል በርሬ ወደ አስመራ ከተማ በሄድኩ። ለተመስገን ደበሳይ እንደነገረው። ለኤደን ሃብተሚካኤል እንደነገራት የ'ካለሁበት' ቀጣይ ክፍል ለማግኘት ፦ ካለሁበት 21፡በእንግሊዝ ሰው ወደየግል ጉዳዩ ነው የሚሯሯጠው ካለሁበት 22፡ የተወለድኩባት፣ የቤተሰብ ፍቅርና ህይወት ያሞቃት ቤቴ ትናፍቀኛለች
53917951
https://www.bbc.com/amharic/53917951
ኢትዮጵያ፡ የ2013 የትምህርት ዘመንን ለማስጀመር ምን እየተሰራ ነው?
በ2013 የትምህርት ዘመን ተማሪዎች ለኮቪድ-19 እንዳይጋለጡ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።
የትምህርት ሚኒስቴር ኮሙኑኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ሐረግ ማሞ ለቢቢሲ እንደተናገሩት ትምህርት ከመጀመሩ በፊት እንዴት ይጀመር ተብሎ ሲታሰብ ከግምት ውስጥ ከገቡ ጉዳዩች አንዱ ለተማሪዎች የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ማቅረብ፣ የክፍል ውስጥ ጥግግትን ለማስቀረት ትምህርት በፈረቃ ይሁን አይሁን የሚሉት ናቸው። የሚኒስቴሩ የኮሙኑኬሽን ዳይሬክተር ለቢቢሲ እንደገለፁት፣ አንድ ትምህርት ቤት የኮሮናቫይረስን ከመከላከል አንጻር ምን ማድረግ አለበት የሚለውን በተመለከተ ትምህርት ሚኒስቴር ሲያስብ የተማሪዎች በአንድ ክፍል ውስጥ ያላቸው ቁጥር አንዱ ነው። ትምህርት ሚኒስቴር "ትምህርት በፈረቃ ይሁን አይሁን፣ ተማሪዎችን እንዴት አድርገን አራርቀን እናስቀምጥ" የሚሉና የተማሪዎች ጤንነት መጠበቂያ መሳሪያዎችን በተመለከተ ምን መደረግ እንዳለባቸው የት መቀመጥ እንዳለባቸውና ሌሎች ጉዳዮች ላይ ውይይት እየተደረገ መሆኑን ጨምረው ገልፀዋል። ትምህርት ሚኒስቴር መጪው ዓመት የትምህርት ዘመን ሲጀምር ምን መደረግ አለበት የሚለውን ከጤና ሚኒስቴርና ከሰላም ሚኒስቴር ጋር በመሆን እየሰራ መሆኑንም አስታውቀዋል። ከኮሮናቫይረስ መከላከያ መንገዶች አንዱ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ማድረግ በመሆኑ ምን ማድረግ አለብን የሚለውን ትምህርት ሚኒስቴር ከሚመለከታቸው የባለድርሻ አካላት ጋር እየተነጋገረ መሆኑን ኃላፊዋ ገልፀዋል። ትምህርት ከመጀመሩ በፊት ለትምህርት ማህበረሰቡ አጠቃላይ፣ መረጃ እንደሚሰጥ የገለፁት የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተሯ፣ ይህንን ጨምሮ ሌሎች ጉዳዮችን በተመለከተ እንደሚያሳውቁ ገልፀዋል። የትምህርት ሚኒስቴሩ በትናንትናው ዕለት ከአገር ውስጥ መገናኛ ብዙኀን ጋር በነበራቸው ቆይታ ወደ መማር ማስተማር ተግባር በሚገባበት ወቅት ለተማሪዎች ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር እንደሚሠራ ገልጸው፣ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ፣ የእጅ ማፅጃ እና መሰል አቅርቦቶችን ከባላድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለማቅረብ በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ተናግረው ነበር። የሚኒስቴሩ ኮሙኑኬሽን ዳይሬክተር በበኩላቸው ለቢቢሲ እንደገለፁት ይህንን ታሳቢ በማድረግ ውይይት እና ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል። ኃላፊዋ ትምህርት ሚኒስቴር እስካሁን ድረስ የ2013 የትምህርት ዘመን መቼ እንደሚጀመር አለመወሰኑን በመግለጽ ትምህርት የሚጀመርበትን ወቅት ለማሳወቅ "የስርጭቱ መጠንና የመንግሥት ውሳኔ ይወስነዋል" ሲሉ ገልፀዋል። ትምህርት ቤቶች ምዝገባ በሚያካሄዱበት ወቅት የኮሮናቫይረስ ስርጭት እንዳይከሰት ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ማድረግ፣ አካላዊ ርቀትን መጠበቅ እና እጅን በመታጠብ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚኖርባቸው ወ/ሮ ሐረግ ማሞ ጨምረው ገልፀዋል። የተማሪዎች ምዝገባው እስከ መቼ ድረስ ይካሄዳል ለሚለው የቢቢሲ ጥያቄ ኃላፊዋ ሲመልሱ፣ እንደ ትምህርት ቤቶቹ ተጨባጭ ሁናቴ የሚወሰን መሆኑን ገልፀዋል። በትምህርት ቤቶች ውስጥ ከምዝገባ ጀምሮ የኮቪድ-19 በመከላከል ረገድ ኃላፊነቱ የሁሉም ነው ያሉት ወ/ሮ ሐረግ "ተማሪዎች፣ ወላጆች፣ የትምህርት ማህበረሰቡ ኃላፊነት አለበት" በማለት "በተለይ ደግሞ በትልቁ መምህራን ኃላፊነት አለባቸው" ሲሉ ተናግረዋል። እንዲሁም መምህራንን ተማሪዎች እንደ ወላጅ ስለሚመለከቷቸው መምህራን ተማሪዎቻቸውን ከኮሮና ራቸውን እንዲከላከሉ በማድረግ ረገድ " እጥፍ ድርብ ኃላፊነት አለባቸው" ብለዋል። በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች በኮሮና ወረርሽኝ ከተከሰተ ወዲህ በለይቶ ማቆያነት ያገለገሉ እንዲሁም በአገሪቱ ውስጥ በተከሰቱ አለመረጋጋቶች የተለያዩ አገልግሎት የሰጡ ትምህርት ቤቶች ምዝገባ ከመጀመራቸው በፊት በሚገባ መጽዳት እንዳለባቸውና ትምህርት ቤቶችም ይህንን ማረጋገጥ እንዳለባቸው በመግለጽ፣ የምዝገባ ጊዜው ሰፋ የተደረገው ይህንን ታሳቢ በማድረግ መሆንም ለቢቢሲ ጨምረው አስረድተዋል። ከቅድመ መደበኛ ጀምሮ እስከ 12ኛ ክፍል ላሉት ተማሪዎች በ2012 የትምህርት ዘመን በ2ኛ ሴሚስተር ያለፋቸውን ትምህርቶች ማካካሻ ለመስጠት መታሰቡንም ዶክተር ኢንጂነር ጌታሁን መኩሪያ ትናንት ከአገር ውስጥ መገናኛ ብዙኀን ጋር በነበራቸው ቆይታ ወቅት መግለፃቸው ይታወሳል። በኢትዮጵያ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ መከሰቱ ከታወቀ ወዲህ የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት በሚል ከመጋቢት ሰባት 2012 ዓ.ም ጀምሮ ትምህርት ቤቶች መዘጋታቸው ይታወሳል። ትምህርት ሚኒስቴር ከስምንተኛ ክፍል እና የ12 ክፈል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ወሳጆች ውጪ ቀሪዎቹ ተማሪዎች በግማሽ ዓመት ውጤታቸው ወደ ቀጣዩ ክፍል እንዲዛወሩ መወሰኑ ይታወቃል። እስካሁን ድረስ የስምንተኛም ሆነ የ12 ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና መቼ እንደሚካሄድ አልታወቀም።
news-41036952
https://www.bbc.com/amharic/news-41036952
ያለሙዚቃም ውዝዋዜ አለ- መስማት የተሳናቸው ተወዛዋዦች ቡድን በአዲስ አበባ
ሙዚቃና ውዝዋዜን ነጣጥሎ ማሰብ ከባድ ሊሆን ይችላል፤ ምክንያቱም ለብዙዎች የዳንሱን እንቅስቃሴ የሚወስነው ሙዚቃው ነው።
መስማት የተሳናቸው ተወዛዋዦች ቡድን እርሶስ ከሚሰሙት ሙዚቃ ጋር በጥቂቱም ቢሆን እየተወዛወዙ ሳለ ድንገት ሙዚቃው ቢቆም ዳንሱን ይቀጥላሉ? መስማት ለተሳናቸው ሰዎች ግን ሙዚቃው በራሱ ትርጉም አልባ ነው፤ ስለማይሰሙት ምንም ስሜት አይፈጥርባቸውም ። ይልቅስ ውዝዋዜያቸውን የሚወስነው የሙዚቃው ምት ነው። እነዚህ መስማት የተሳናቸው ተወዛዋዞች ያለሙዚቃም እንዳሻቸው መወዛወዝ ይችላሉ የሙዚቃውን ምት እንዴት ይረዱታል ? በአዲስ አበባ ሽሮ ሜዳ አካባቢ የሚገኘው መስማት የተሳናቸው የውዝዋዜና የቲያትር ቡድን አባላት እንደሚሉት የሙዚቃውን ምት የሚረዱበት ሁለት መንገድ አላቸው። ለውዝዋዜ የመጀመሪያ ልምምዳቸውን የሚያደርጉትን ትከሻ ቆጠራን ነው፤ ይህ ሂደት ትካሻቸውን እያወዛወዙ አንድ ሁለት ሶስት እያሉ የትከሻ ምት የሚቆጥሩበት ነው ። ይሕ መስማት የሚችሉት ተወዛዋዦችም የሚጠቀሙበት ሂደት ቢሆንም ለእነርሱ የውዝዋዜ መነሻ ሲሆን እነርሱ ግን በመድረክ ሲጫወቱም የሚጠቀሙበት ስልት ነው። አንድ ምት ሁለት ምት ሶስት ወይም ከዚያ በላይ የሚያስፈልጋቸውን ሙዚቃ ለይተው በቁጥሩ መሰረት ትከሻቸውን እየወዘወዙ እስክስታ ይመታሉ። ''በፊት ዳንሰኞችን ሳይ በጣም እቀና ነበር ፤ እኔ ይህን ለማድረግ አልችልም ብዬ ብዙ ሳዝን ቆየሁ፤ በኋላ ግን ካልሆነም ይቀራል ለምን አልሞክርም ብዬ ሰዎችን ሳማክር 'መስማት ለማይችል ሰው ውዝዋዜ የማይታሰብ ነገር ነው አሉኝ' ይላል በቴሌቪዥን ባያቸው ዳንሶች ወደ ውዝዋዜ የተሳበው ቅዱስ። ''ብዙ ቦታ ሞክርኩ ግን የሁሉም ኃሳብ አንድ አይነት ነበር። ግን በመጨረሻ ተስፋ ሳልቆርጥ ብጠይቅ ስለዚህ ቡድን የሚያውቅ ሰው አገኘሁና ይዞኝ መጣ'' ቅዱስ ቡድኑን ቢቀላቀልም በእርግጥም ውዝዋዜውን እንደሚችል ራሱን ለማሳመን ብዙ ጊዜ ፈጅቶበታል፤ ሂደቱንም ቴክኒኩንም በድንብ እስኪረዳው ድረስ ያለመታከት በቤትም በልምምድ ቦታውም ብዙ ሰርቷል ። ''የሙዚቃውን ስሜት ለመረዳት ማጫወቻውን ወለል ላይ ስናስቀምጠው እግራቸን ላይ ንዝረቱ ይሰማናል። ከታች ተነስቶ በመላ አካሌ ላይ እንዲሰማኝ ሙዚቃው በደንብ መከፈት አለበት፤ ያኔ ንዝረቱ ሌላ አለም ውስጥ ይከተኛል ፤ እወነትም መወዛወዝ እንደምችል ያወቅኩ ጊዜ በራሴ በጣም ኮራሁ፤ አሁንም አላቆምም ገና ብዙ እሰራለሁ'' ብሏል ቅዱስ። ቡድኑን ገና እንደተቀላቀሉ ብዙዎቹ ሂደቱን መረዳት ይከብዳቸዋል፤ የ19 ዓመቷ ስምረትም ለዳንስ ልዩ ፍቅር ቢኖራትም ትክኒኩን ለመረዳት ተቸግራ ነበር። '' መጀመሪያ አካባቢ በጣም ያስቸግረኝ ነበር ፤ ደጋግሜ ድምጹን ከፍ አድርገው ነበር ። በተለይ አማርኛ ሲሆን ምቱን መረዳት ስልላቻልኩ 'ድገሙልኝ ድገሙልኝ ' እል ነበር'" ትላለች ። ከተወዛዋኞቹ ብዙሃኑ የትግርኛ ሙዚቃዎችን ይመርጣሉ፤ ምክኒያቱም የዜማው አጣጣልና የከበሮው ድምጽ የሚፈጥረው ምት ጥርት ያለና ከፍተኛ ንዝረት የሚፈጥር ነው። ለተቀናጀ የዳንስ እንቅስቃሴ (ኬሮግራፊ)መድረክ ላይ እንዴት ይግባባሉ? መስማት የሚችሉ ሰዎች ከቦታ ቦታ ለመንቀሳቀስና ቦታ ለመቀያየር ብዙ ጊዜ የዜማውን ለውጥ እንደምልክት ይጠቀማሉ፤ ለዚህም አስቀድመው በንግግር ይግባባሉ። ''እኛ ደግሞ የምንግባባው በእይታ ነው'' ይላል ቅዱስ " ከፊት ያለው ተወዛዋዥ ከኋላ ያሉትን የመምራት ኃላፊነት ይጣልበታል ምክኒያቱም መጀመሪያ የሚቀይረው እርሱ ነው ከዛ ሌሎቹን እሱን ይከተላሉ ፤ ስለዚህ ከሌሎቹ የሚጠበቀው የሚደረጉ የእንቅስቃሴና የቦታ ለውጦችን በቅድመ ተከተል መያዝ ብቻ ነው ፤ አንዳንዴ ደግሞ የምት ቆጠራው ብዙም በማይወሳሰብበት ሙዚቃ ከስንት ምት በኋላ እንደምንንቀሳቀስ ቀድመን ተነጋግረን የጋራ ውዝዋዜዎችን እንሰራለን" በጉለሌ ክፍለ ከተማ ሽሮ ሜዳ አካባቢ በሚገኘው የወረዳ 3 ወጣቶች ማዕከል ልምምዱን የሚሰራውና በሚያዝያ 2008 የተቋቋመው ይህ ቡድን በ 14 አባላት ውዝዋዜና ቲያትሮችን በተለያዩ መድረኮች ያቀርባል። ሲሳይ ተሰማ የዚህ የውዝዋዜና የቲያትር ቡድን ዋና ስራ አስኪያጅና አሰልጣኝ ነው፤ በሳምንት ሶስት ቀናት ከ 8 እስከ 11 ከ 30 ስልጠና ይሰጣቸዋል። ቡድኑ በሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር፤ መስማት በተሳናቸው ብሄራዊ ማህበር፤ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቱ የልዩ ፍላጎት ትምህርትና፡ መስማት በተሳናቸው ስፖርት ፌዴሬሽን ድጋፍ እንደሚደረግለት ይናገራል። ሆኖም ብዙ እቅዶቹ በገንዘብ እጥረት ምክንያት ከዳር አይደርሱም ባይ ነው። "እኛ ብዙ እያሰብን እቅድ ብናወጣም ለባለሙያ የምንከፍለው ገንዘብ የለንም፤ ግን አሁንም ተስፋ አልቆርጥም መስማት ለተሳናቸው ሰዎች የሚሆን ቲያትር ቤትና የቴሌቪዥን ውድድር የማዘጋጀት ህልም አለኝ። "
news-51031486
https://www.bbc.com/amharic/news-51031486
በምዕራብ ኦሮሚያ የስልክና ኢንተርኔት ከተቋረጠ ቀናቶች ተቆጠሩ
በምዕራብ ኦሮሚያ በሚገኙ በሁለቱ የወለጋ ዞኖች (ምስራቅ ወለጋና ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞኖች) የኢንተርኔት እና የስልክ አገልግሎት መቋረጡን የአካባቢው ነዋሪዎች ለቢቢሲ ተናገሩ።
በአሁኑ ወቅት በአራቱም የወለጋ ዞኖች፤ ቄለም ወለጋ፣ ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ፣ ምዕራብ ወለጋና ምስራቅ ወለጋ የኢንተርኔት አገልግሎት የለም የምዕራብ ኦሮሚያ ዲስትሪክት ባልደረባ የሆኑ ግለሰብ ለቢቢሲ እንዳረጋገጡት የኢንተርኔት አገልግሎቱ ከተቋረጠ አምስት ቀናት ተቆጥረዋል። የነቀምቴ ከተማ ነዋሪ የሆኑና ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ ግለሰብ "ሞባይል ዳታም ሆነ ዋይፋይ መስራት ካቆመ ቆይቷል። እዚህ ካለው ቴሌም ምንም አይነት ምላሽ ማግኘት አልቻልንም" ብለዋል። • "በተስፋ፣ በስጋት፣ በቁጭት መካከል ነው ያለሁት" ጀዋር መሐመድ • ኢትዮቴሌኮም ኢንተርኔት ለምን እንደተቋረጠ መግለፅ እንደማይችል አስታወቀ እኚህ ነዋሪ ጨምረው ለቢቢሲ እንደተናገሩት፤ የኢንተርኔት አገልግሎት በመቋረጡ ለከፍተኛ የትምህርት ዕድል ወደ ውጪ ሃገር መላክ ያለባቸው ማመልከቻ ጊዜ ሊያልፍባቸው ተቃርቧል። የሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ዋና ከተማ የሆነችው ሻምቡ ነዋሪ በበኩላቸው፤ ኢንተርኔት ሙሉ በሙሉ ከተቋረጠ አምስት ቀናት ማለፉን ጠቅሰው የስልክ አገልግሎትም ቢሆን አልፎ አልፎ እንጂ አብዛኛውን ጊዜ እንደማይሰራ ተናግረዋል። ቢቢሲ ስለጉዳዩ ዝርዝር መረጃ ለማግኘት ያደረገው ጥረት በአካባቢው የስልክና ኢንተርኔት አገልግሎት በመቋረጡ ምክንያት ማግኘት አልቻለም። ከኢንተርኔት በተጨማሪ የስልክ አገልግሎት የሌለባቸው ደግሞ ምዕራብ ወለጋና የቄለም ወለጋ ዞኖች ናቸው ምዕራብ ኦሮሚያ በኮማንድ ፖስት ሥር መተዳደር ከጀመረ ወራት አልፈዋል። አካባቢው በኮማንድ ፖስት መተዳደር ከጀመረ ወዲህ የስልክ፣ ኢንተርኔትና የሰዎች እንቅስቃሴ ላይ በተለያዩ አጋጣሚዎች ገደብ እንደሚጣል ነዋሪዎች ይናገራሉ። የስልክና የኢንትርኔት አገልግሎቶች ለምን እንደተቋረጡ ለማወቅ ወደ ኢትዮ ቴሌኮም ምዕራብ ሪጅን ብንደውልም ምላሽ የሚሰጠን በማጣታችን ጥረታችን አልተሳካም። ይሁን እንጂ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው የኢትዮ ቴሌኮም ባልደረባ ለቢቢሲ እንደተናገሩት፤ "የስልክና ኢንተርኔት አገልግሎቱ እንዲቋረጥ የተደረገው በቴሌ ከፍተኛ አመራሮች ትዕዛዝ ነው።" በአሁኑ ወቅት በአራቱም የወለጋ ዞኖች ማለትም፤ ቄለም ወለጋ፣ ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ፣ ምዕራብ ወለጋና ምስራቅ ወለጋ የኢንተርኔት አገልግሎት የለም። • ከ6ሺህ ሰዎች በላይ የሞቱበት የኩፍን ወረርሽኝ ከኢንተርኔት በተጨማሪ የስልክ አገልግሎት የሌለባቸው ደግሞ ምዕራብ ወለጋና የቄለም ወለጋ ዞኖች ናቸው። የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ ወይዘሪት ጨረር አክሊሉን በዞኖቹ ውስጥ የኢንተርኔትና የስልክ አገልግሎት ለምን እንደተቋረጠ ቢጠየቁም አሁን አስተያየት መስጠት እንደማይችሉና በቅርቡ በጉዳዩ ላይ መግለጫ እንደሚሰጡ ተናግረዋል።
news-49393879
https://www.bbc.com/amharic/news-49393879
አፋር ውስጥ የሞተችው እስራኤላዊት የገጠማት ምን ነበር?
አያ ናሚህ አፋር ክልል ውስጥ ወደሚገኘው የምድራችን ሞቃቱና ዝቅተኛው ደናክል አካባቢ ከሄዱት ስድስት እስራኤላዊያን ተማሪዎችና ሁለት ኢትዮጵያዊያን መካከል አንዷ ነበረች።
የ22 ዓመቷ ወጣት ቅዳሜ ዕለት ግዙፉ በረሃ ውስጥ ከቡድኑ ተነጥላ መጥፋቷ ከታወቀ በኋላ በተደረገ ፍለጋ ሞታ ተገኝታለች። አያ ለኢንጂነሪንግ ተማሪዎች በተዘጋጀው የአንድ ወር ስልጠና ላይ ከሌሎች ተማሪዎች ጋር ተሳታፊ ለመሆን ነበር ወደ ኢትዮጵያ የመጣችው። • ከ125 በላይ የተጠፋፉ ኢትዮጵያዊያን ቤተሰቦችን ያገናኘችው አሜሪካዊት ተማሪዎቹ ባለፈው ሳምንት ረቡዕ ስልጠናቸውን ሲጨርሱ ስድስቱ እስራኤላዊያን ከሁለት ኢትዮጵያዊያን ጋር በመሆን ወደ አፋር ክልል በመሄድ የኤርታሌ የእሳተ ገሞራ ሐይቅንና የዳሎል አካባቢን ለመጎብኘት እቅድ አውጥተው ነበር ወደዚያው ያቀኑት። ከቡድኑ ጋር አብረው ከተጓዙት ሁለት ኢትዮጵያዊያን መካከል አንዷ የሆነችው ጽዴና አባዲ ለቢቢሲ አንደተናገረችው፤ ወደ ኤርታሌ በሚያደርጉት ጉዞ ላይ ሐሙስ ምሽት አብረው እንደነበሩና አያም "በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደነበረች" ገልጻለች። "ሁሉም ሰው በጉዞው ተደንቆና ደስተኛ ሆኖ ነበር" ስትል ጽዴና ለቢቢሲ ተናግራለች። ቀጣዩንም ቀን አፍዴራ ሐይቅ ላይ እየዋኙና እየተዝናኑ ማሳለፋቸውን ታስታውሳለች። ቅዳሜ ጠዋትም አያና ጓደኞቿ ወደ ደናክል ዝቅተኛ ቦታ ደርሰው አካባቢውን በደንብ ለመመልከት እንዲችሉ በአቅራቢያው ወዳለ ኮረብታ አቀኑ። • በደቡብ ወሎ እውን የህፃናት ስርቆት አለ? "ከአካባቢው ከሚወጣው ኬሚካልና ካለው ከፍተኛ ሙቀት የተነሳ ድካም ስለተሰማቸው" አያና እሷ ወዳመጣቸው መኪና ሲመለሱ ሌሎቹ ደግሞ ጉዟቸውን እንደቀጠሉ ትናገራለች። ጽዴና እንዳለችው፤ አያ ወደ መኪናቸው ስትመለስ የነበረው ቀድማ ነበር። በኋላ ላይም አያ እንደጠፋችና በተደረገው ፍለጋም መሄድ ከሚገባት በተቃራኒ አቅጣጫ ሞታ እንደተገኘች ተናግራለች። ነገር ግን ሲመለሱ ከነበሩት መካከል የጠፋችው አያ ብቻ እንዳልነበረችም ጽዴና ተናግራለች። "ሌላ ሰው አግኝቼ እሷን በመከተል ወደ መኪናው እስክደርስ ድረስ እኔም ጠፍቼ ነበር" የምትለው ጽዴና "አካባቢው ተመሳሳይ ከመሆኑ የተነሳ አቅጣጫችንን ለማወቅ አስቸጋሪ ነበር" ስትል ለቢቢሲ ተናግራለች። • በባሕር ዳር ለበቀል የተነሳች ሴት በአንድ ኃላፊ ላይ የአሲድ ጥቃት ፈጸመች ጽዴና አክላም ከአከካባቢው የሚወጣው ሽታና ከባድ ሙቀት እንዳሳመማትና "የምትሞት እንደመሰላት" አስታውሳለች። እስራኤላዊቷ መጥፋቷ ከታወቀ በኋላ የአካባቢው ነዋሪዎችና ፖሊስ ለፍለጋ የተሰማሩ ሲሆን፤ አንድ የኢንሹራንስ ኩባንያም በኋላ ላይ በፍለጋው ላይ ተሳታፊ ሆኗል። በፍለጋውም አያ ህይወቷ አልፎ የተገኘች ሲሆን፤ አስክሬኗም ትናንት ዕሁድ በአውሮፕላን ወደ አዲስ አበባ ተወስዷል። ጽዴና እንደምትለው፤ አያ በሁሉም ሰው የምትወደድና ተግባቢ ነበረች። ለእስራኤላዊቷ ሕይወት ማለፍ ምክንያቱ ምን እንደሆነ እስካሁን የታወቀ ነገር የለም።
news-50357373
https://www.bbc.com/amharic/news-50357373
ዚምባብዌ 211 ሀኪሞችን ከሥራ አገደች
ዚምባብዌ ደሞዛችን አንሷል ብለው አድማ የመቱ 211 ሀኪሞችን አገደች።
የአገሪቱ የጤና ጥበቃ ተቋም እንዳለው፤ ሀኪሞቹ መልቀቂያ ሳያስገቡ ለአምስት ቀናትና ከዚያም በላይ ሥራ አልገቡም። ሀኪሞቹ የሥራ ማቆም አድማ የጀመሩት መስከረም ላይ ነበር። በመንግሥት ሆስፒታሎች ከሚሠሩት 1,601 ሀኪሞች 516ቱ እርምጃ እንደሚወሰድባቸውም ተገልጿል። • ዚምባብዌ በሺህ የሚቆጠሩ ነርሶችን አባረረች • "ሀኪሙ ትግሉን አቀጣጠለው እንጂ የሚታገለው ለታካሚው ነው" የዚምባብዌ ሀኪሞች ስብስብ የሆነው 'ዚምባብዌ ሆስፒታል ዶክተርስ አሶሴሽን' ስለ መንግሥት እርምጃ እስካሁን ምንም አላለም። ከዚህ ቀደም ግን መንግሥት ሀኪሞች እያስፈራራ እንደሆነ ለሮይተርስ ገልጸው ነበር። የሥራ ማቆም አድማ አገሪቱ ውስጥ የሚገኙ ዋና ዋና ሆስፒታሎች ላይ ጫና አሳድሯል። በእነዚህ ሆስፒታሎች አገልግሎት እየሰጠ ያለው የድንገተኛ አደጋ ክፍል ብቻ ነው። • "ማህበሩ የማያልፈው ቀይ መስመር የስራ ማቆም አድማ ነው"-ዶ/ር ገመቺስ ማሞ የኢትዮጵያ ህክምና ማህበር ፕሬዚዳንት የዚምባብዌ መንግሥት እንደሚለው ከሆነ ለሀኪሞች ደሞዝ የመጨመር አቅም የለውም። በተቃራኒው ሀኪሞቹ ያሉበትን ሁኔታ "ቀስ በቀስ የመሞት ያህል ነው" ሲሉ ይገልጻሉ። መንግሥት በአፋጣኝ እርምጃ እንዲወስድም በተደጋጋሚ ጠይቀዋል። ዚምባብዌ ከፍተኛ የምጣኔ ኃብት ቀውስ ውስጥ ናት። የዋጋ ንረት የበርካቶችን ሕይወት ፈታኝ አድርጎታል። ሀኪሞች በወር ከ100 ዶላር በታች ይከፈላቸዋል። ዶ/ር ሊንዚ ሮበርትሰን "ደሞዛችን ለአስቤዛና ለቤት ኪራይም አይበቃም" በማለት የአገሪቱን ነባራዊ ሁኔታ ለቢቢሲ ገልጸዋል።
news-54223311
https://www.bbc.com/amharic/news-54223311
ዶናልድ ትራምፕ፡ቲክ ቶክ በአሜሪካ አገልግሎቱን እንዲቀጥል ለማስቻል የቀረበው ስምምነት ምን ይላል?
የአሜሪካው ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ባለቤትነቱ የቻይና የሆነው የተንቀሳቃሽ ምስል መጋሪያ መተግበሪያ [አፕሊኬሽን] በአሜሪካ አገልግሎቱን መስጠት እንዲቀጥል የሚፈቅደውን ስምምነት ማፅደቃቸውን አስታወቁ።
ትራምፕ የቻይናው ቲክ ቶክና የአሜሪካ ድርጅቶች ኦራክልና ወልማርት በጋራ ለመስራት እንዲስማሙ መፍቀዳቸውን ለጋዜጠኞች ተናግረዋል። ፕሬዚደንቱ መተግበሪያው የብሔራዊ ደህንነት አደጋ ላይ ይጥላል በማለት ከአሜሪካ እንዲታገድ ትዕዛዝ ሰጥተው ነበር። የአሜሪካ የደህንነት ባለሥልጣናትም የቲክ ቶክ ባለቤት በመተግበሪያው አማካኝነት ከተጠቃሚዎች የሰበሰበው መረጃ ለቻይና መንግሥት ተሰጥቶ ሊሆን ይችላል የሚል ስጋት አላቸው። የቻይና የቴክኖሎጂ ኩባንያውና የቲክ ቶክ ባለቤት ብቴዳንስ ግን፤ በቻይና ገዥው የኮሚኒስት ፓርቲ ቁጥጥር ሥር ነው ያለው ወይም መረጃዎችን አሳልፎ ይሰጣል በሚል የቀበረበበትን ክስ ተቃውሟል። ቅዳሜ እለት ትራምፕ አዲሱ ስምምነት የ100 ሚሊዮን አሜሪካዊያንን መረጃ ደህንነቱ መጠበቁን ያረጋግጣል ሲሉ ተናግረዋል። ደህንነቱም መቶ በመቶ አስተማማኝ ይሆናል ብለዋል ትራምፕ። በሰሜን ካሮላይና የምርጫ ሰልፍ ቀደም ብሎ ዋይት ሃውስን ለቀው ሲወጡ "ስምምነቱን ባርኬዋለሁ" ካሉ በኋላ ስምምነቱን ያፀደቁት በሃሳብ ደረጃ እንደሆነም ጠቁመዋል። ቢቴዳንስ ግን አዲስ በቀረበውና ከቻይና መንግሥት ተጨማሪ ይሁንታ በሚያስፈልገው የቲክ ቶክ ስምምነት ላይ ያለው ነገር የለም ። ፕሬዚደንት ትራምፕ በጋራ የመስራቱን ሃሳብ የደገፉት አስተዳደራቸው በአገሪቷ ያሉ ሕዝቦች ቲክ ቶክን ከየትኛውም 'አፕስቶር' እንዳያወርዱ ከእሁድ ጀምሮ ሊያግድ እንደሚችል ካሳወቀ ከቀናት በኋላ ነው። ሆኖም የአሜሪካው የንግድ መሥሪያ ቤት "በቅርቡ አዎንታዊ ሂደቶች በመታየታቸው" ትዕዛዙን ለማስፈፀም አርብ ዕለት ሰጥቶት የነበረውን የ48 ሰዓታት የጊዜ ገደብ በአንድ ሳምንት ማራዘሙን አስታውቋል። በቲክ ቶክ ላይ የተፈጠረው አለመግባባት የተከሰተው በትራምፕ አስተዳደርና በቻይና መንግሥት መካከል በንግድ፣ በሆንግ ኮንግ ተቃውሞ እና ቤጂንግ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝን የተቆጣጠረችበትን መንገድ ጨምሮ በበርካታ ጉዳዮች ሳቢያ ከፍተኛ ውጥረት ከተከሰተ በኋላ ነው። የቀረበው ረቂቅ ስምምነት ምንድን ነው? የቀረበው ስምምነት 'ዳብድ ቲክ ቶክ ግሎባል' የተባለ አዲስ ኩባንያ እንዲቋቋም እንደሚያመላክት ሮይተርስ የዜና ወኪል ሐሙስ ዕለት በዘገበው አስታውቋል። ይህ ኩባንያ በአብዛኛው አሜሪካዊያን ዳሬክተሮች ይኖሩታልም ተብሏል። ፕሬዚደንቱና የደህንነት ባለሙያም የቦርድ አባል ይሆናሉ ይላል። የአሜሪካ ኩባንያዎቹ ኦራክልና ወልማርትም በኩባንያው ውስጥ ወሳኝ ድርሻ እንደሚኖራቸው የሚጠበቅ ሲሆን የቻይና ኩባንያው ቢቴዳንስም የአሜሪካ ተጠቃሚዎችን መረጃን ለመጠበቅ ተስማምቷል። የቲክ ቶክ መረጃዎችም በኦራክል ቋት የሚከማቹ ሲሆን ይህም የመረጃ ምንጭ ኮዱን የመመርመር መብት ይኖረዋል ተብሏል። ፕሬዚደንት ትራምፕ አዲሱን የቲክ ቶክ ኩባንያ ኦራክልና ወልማርት ሙሉ በሙሉ እንደሚቆጣጠሩት ተናግረዋል። አዲሱ ስምምነት በአገሪቷ ተጨማሪ የሥራ እድል እንደሚፈጥርና ገቢ እንደሚያስገኝም ፕሬዚደንቱ አክለዋል።
44298965
https://www.bbc.com/amharic/44298965
በኢሳትና ኦ ኤም ኤን ላይ የተከፈቱ ክሶች ተቋረጡ
''ሕገ- መንግሥቱና ሕገ- መንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለማስወገድ ሙከራ አድርጋችኃል'' በሚል የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ክስ ከፍቶባቸው የነበሩት አቶ ብርሃኑ ነጋና የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ ስራ አስኪያጅ አቶ ጃዋር መሃመድ ክስ እንዲቋረጥ መደረጉ ተሰምቷል።
ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት፣ የተደራጁ ድንበር ተሻጋሪ ሀገራዊ ጉዳት የሚያስከትሉ ወንጀሎች መከታተያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ወንድማገኝ ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው ክሳቸው እንዲዘጋ የተወሰነላቸው ታዋቂ ግለሰቦች የአርበኞች ግንቦት ሰባት ሊቀመንበር ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ እና የለውጥ አራማጅ እና የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ ስራ አስኪያጅ አቶ ጃዋር መሃመድ ናቸው። ከዚህም በተጨማሪ በተቋም ደረጃ " ግለሰቦቹ የሚያስተላልፉትን ጥሪ በመቀበል፣ የሽብር ቡድን ድጋፍ በማድረግ፣ በዋና ወንጀል ላይ ተካፋይ በመሆን የሽብር ተግባር ወንጀል" ተከሰው የነበሩት የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቭዥን( ኢሳት) እና የአሮሞ ሚዲያ ኔትዎርክ (ኦ ኤም ኤን) ክሳቸው እንዲቋረጥ መወሰኑም ተሰምቷል። ውሳኔው ከተሰማ በኋላ ቢቢሲ ያናገራቸው የኢሳት ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አበበ ገላው ወትሮም በተቋማቸው ላይ የቀረበው ክስ በሀሰት ላይ የተመሰረተ መሆኑነ ጠቅሰው የክስ ማቋረጥ እርምጃውን ግን በአዎንታ እንደሚመለከቱት ገልፀዋል ። «የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቭዥን እና ራዲዮ የኢትዮጵያዊ ህዝብ የነፃነት ልሳን እንጂ የአሸባሪ ድምፅ አይደለም ፣በውስጡ ያሉ ጋዜጠኞችም በመናገራቸውና በመፃፋቸው ምክንያት ለስደት እና ለመከራ የተዳረጉ ጋዜጠኞች ናቸው፣» ያሉት አቶ አበበ አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀገሪቱን 'በመጠኑም' ቢሆን የመቀየር አቅጣጫ ማሳየታቸው በመልካምነት እንደሚወሰድ ጠቅሰዋል። ሆኖም የአሁኑ ርምጃ የቴሌቭዥን እና ራዲዮ ጣቢያቸው የሚታወቅበትን በመንግሥት ላይ የሰላ ትችት ማቅረብን ከመሰሉ የቀደሙ መታወቂያዎቹ እንዲያፈገፍግ እንደማያደርገው አስገንዝበዋል። «የህዝባችን እና የቄሮ ትግሎች በሺ የሚቆጠሩ ሰዎችን እንዳስፈቱ ሁሉ፣ ዛሬ በእኔም ሆነ በኦ ኤም ኤን ላይ የቀረበውን ክስ ለማዘጋት ችለዋል፣» በማለት አድናቆታቸውን ያስቀደሙት የኦ ኤም ኤን ዋና ስራ አስኪያጅ ጃዋር መሃመድ በበኩላቸው' ከሃይል ይልቅ መደራደር ይቻላል!' በሚል ብቅ ያሉ አዲስ አመራሮችን አመስግነዋል። ከአሁኑ እርምጃ በተጨማሪ 'አፋኝ ናቸው' እየተባሉ የሚጠቀሱ የፀረ ሽብር እና የፕሬስ አዋጆችን የመሰሉ ህግጋት በተመሳሳይ በአዲስ ከተተኩ በኢትዮጵያ ውስጥ የመገናኛ ብዙሃን ብዙሃነትን የሚያጠናክር እርምጃ ተደርጎ እንደሚታሰብ አስረድተዋል።
news-52774083
https://www.bbc.com/amharic/news-52774083
የወባ በሽታ በአማራ ክልል 25 ወረዳዎች በወረርሽኝ መልክ መከሰቱን ተነገረ
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ ሃያ አምስት ወረዳዎች ውስጥ የወባ በሽታ በወረርሽኝ መልክ መከሰቱን የክልሉ የኅብረተሰብ ጤና ተቋም ገለጸ።
የወባ ትንኝ የወባ በሽታው ካለፉት ሁለት ዓመታት ከፍ ባለሁኔታ በወረርሽኝ ደረጃ በበርካታ የክልሉ አካባቢዎች መከሰቱን ለቢቢሲ የገለጹት የአማራ ክልል ኅብረተሰብ ጤና ተቋም የወባ ክፍል ባለሙያ አቶ አማረ ደስታ ናቸው። "በዚህ ዓመት ወባ በክልሉ ከአምናውም ሆነ ከካቻምናው በበለጠ ጨምሯል" ያሉት ባለሙያው በተለይ በቋራ መተማ፣ ምሥራቅ ደምቢያ፣ ጎንደር ዙሪያ፣ ጃዊ፣ ባህርዳር ዙሪያ፣ ደብረ ኤልያስ፣ ሸዋ ሮቢት፣ ራያ ቆቦ፣ ቃሉ እና አበርገሌን የመሳሰሉ ወረዳዎች በሽታው በጣም ከጨመረባቸው አካባቢዎች ጥቂቶቹ ናቸው ብለዋል። ለወባ በሽታው መስፋፋት የተለያዩ ምክንያቶች እንዳሉ የተጠቀሰ ሲሆን በተለይ ቀደም ሲል በሽታውን ለመከላከል ይወሰዱ የነበሩ እርምጃዎች መላላታቸውና በሽታውን ለመከላከል ኅብረተሰቡ ያደርጋቸው የነበሩ ጥንቃቄዎች መቆመቀቸው እንደሆነ ተገልጿል። ከእነዚህ መካከልም "ወባ ጠፍቷል በሚል የአጎበር አጠቃቀም ከጊዜ ወደ ጊዜ መቀነስ፣ ለወባ መራቢያ ምቹ የሆኑ አካባቢዎችን አለማጽዳት፣ የአየር ንብረት ለውጥና ከኮቪድ-19 ጋር ተያይዞ የጤና ኬላዎች ትኩረት መቀነስ" ለወባ በሽታ ክስተት መጨመር በምክንያትነት ተጠቅሰዋል። በክልሉ በአሳሳቢ ደረጃ ላይ የሚገኘው የወባ ወረርሽኝን ለመቆጣጠርና ለመከላከል የጤና ጥበቃ ሚንስቴር 260 ሺህ ኪሎ ጸረ ወባ ኬሚካል መላኩን አቶ አማራ ደስታ አስታውቀዋል። ከአማራ ክልል 80 በመቶ የሚሆነው አካባቢ ለወባ መራቢያ ምቹ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን 68 በመቶው ነዋሪም ለበሽታው ተጋላጭ ነው ተብሏል። በክልሉ ከመስከረም እስከ ታኅሳስ ድረስ ወራት የወባ በሽታ በስፋት የሚከሰት ሲሆን ከመጋቢት እስከ ሰኔ ደግሞ በመካከለኛ ደረጃ እንደሚከሰት ታውቋል።
54546137
https://www.bbc.com/amharic/54546137
ሰላም፡ በርግጥ ወጣቶቹ የእርቅ ሃሳባቸው ምንድን ነው?
ዳንኤል ዳባ፣ አብዲሳ ንጉሴ እና ተሰማ ገመዳ ከኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች የተገኙ ወጣቶች ናቸው። እነዚህ ወጣቶች ከየመጡበት አካባቢዎች ያገኙትን ሰላምና እርቅ ሃሳብ በማደራጀት 'እኔም የእርቅ ሃሳብ አለኝ' ሲሉ ተወዳድረው ነበር።
ለመሆኑ የእርቅ ሃሳባቸው ምንድን ነው? ቢሾፍቱ አብዲሳ ንጉሴ የቢሾፍቱ ከተማ ነዋሪ ሲሆን በወሎ ዩኒቨርስቲ አምስተኛ አመት የሕግ ተማሪ ነው። የእርቅና ሰላም ኮሚሽን የሰላም ቀንን በማስመልከት ባዘጋጀው ውድድር ውድድር ላይ "እኔም የእርቅ ሃሳብ አለኝ" በሚል ርዕስ ተወዳድሮ ማሸነፍ ችሏል። የእርቅና ሰላም ኮሚሽን ኣዘጋጀው ይህ ውድድር እኔም የእርቅ ሃሳብ አለኝ በሚል ስም የተዘጋጀ ሲሆን የእርቅ ሃሳብ ያላቸውን ወጣቶች በማወዳደር ሸልሟል። አብዲሳ በቢሾፍቱ አካባቢ ያስተዋለውን የሽምግልና ስርዓት ላይ መሰረት በማድረግ ነበር የእርቅ ሃሳብ አለኝ በማለት የተወዳደረው። "ሽምግልና በኦሮሞ ባሕል ውስጥ ትልቅ ቦታ አለው። በሽምግልና ወንጀል የማሕበረሰብ፣ የቤተሰብ ጉዳይ ሊፈታበት ይችላል። በሽምግልና ሕብረተሰቡ ውስጥ ያሉ ልዩነቶች ሳይሰፉ መፍታት ይቻላል" የሚለው አብዲሳ ሕዝቡ የተለያየ የሆነ የሽምግልና ባሕል እንዳለው በመግለጽ፣ እርሱም ይህንን የማሕበረሰቡን የሽምግልና ባሕል መሰረት በማድረግ የዕርቅ ሃሳቡን ማቅረቡን ገልጾ፣ "አዲስ ነገር ከራሴ አልጨመርኩም" ይላል። በሌላ በኩል ደግሞ እርሱ ያዘጋጀው ጥናታዊ ጽሑፍ ወጣቶች የራሳቸውን ባሕል እንዲማሩ ያግዛልሲል ለቢቢሲ ገልጿል። ወጣቶች በአሁን ሰዓት ባሕላቸውን እየረሱ ነው። ይህ ጥናታዊ ጽሑፍም ወጣቶች የራሳቸውን ባሕል እንዲረዱ እና በሽምግልና ስርዓት ውስጥ እንዲሳተፉ ያግዛቸዋል ሲል ያስረዳል። ወጣቶች የራሳቸውን ባሕል ማወቅ አለባቸው ችግሮች ቢኖሩም በገዳ ስርዓት ውስጥ ታቅፈው ነው መፍታት ያለባቸው በማለት ምክሩን ያስተላልፋል። ወደፊት እዚህ ውድድር ላይ ከተሳተፉ ወጣቶች ጋር በጋራ በመሆን ሕዝባቸውንና አካባቢያቸውን ለመርዳት በጋራ ለመስራት እቅድ እንዳላቸው ይናገራል። አዲስ አበባ ዳንኤል ዳባ አዲስ አበባ ነው ተወልዶ ያደገው። የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ አጥንቷል። ዳንኤል 'እኔም የእርቅ ሐሳብ አለኝ' ለሚለው ውድድር ቤተ እምነቶች እንዴት ሰላም በማምጣት ውስጥ ሊሳተፉ ይችላሉ በሚል ጽሁፉን ማቅረቡን ይናገራል። መጀመሪያ ቤተ እምነቶች ሰላምን በማምጣት ረገድ ምን ሊሰሩ ይችላሉ የሚለውን ሃሳብ በሥራ ቦታው አካባቢ ለመስራት እየተዘጋጀ ባለበት ወቅት ነው 'የእኔም የእርቅ ሃሳብ አለኝ' የሚለው ውድድር መኖሩን የሰማው። ከዚህ በኋላም ይህንኑ ሃሳቡን ሰፋ አድርጎ ለውድድሩ አቀረበ። በኋላ ላይ ግን የቤተ እምነቶች ሰላምን በማስፈን ረገድ የታየባቸው ክፍተት ምንድን ነው? ጥንካሬያቸውስ የሚለውን በዝርዝር በማየት ለመስራት መሞከሩን ያስታውሳል። ዳንኤል በርካታ ኢትዮጵያውያን በቤተ እምነቶች ውስጥ ማደጋቸውን፣ መጽሐፍ ቅዱስ ማንበባቸውን፣ ቅዱስ ቁርዓን መቅራታቸውን በማንሳት ሰላም ለማስፈን በሚደረገው ጥረት ውስጥ ቤተ እምነቶች ቁልፍ ሚና እንደሚኖራቸው ያስረዳል። ይህ ብቻም ሳይሆን ደግሞ በአገር ውስጥ በሚኖር አለመግባባትን ለማስታረቅ ወደፊት የሚመጡ ሰዎች በየእምነት ተቋም ውስጥ ያሉ አባቶች እንደሚሆኑ ማስተዋሉን ያነሳል። እነዚህ ሁለት የማይታለፉ ነጥቦች ለሰላምና እርቅ ወሳኝ መሆናቸውን ዳንኤል ይጠቅሳል። የቤተ እምነቱ ተከታዮች መሪዎቻቸውን ስለሚሰሙ የሰላምና የእርቅ ሀሳብ በእነሱ በኩል መምጣት አለበት የሚለው ዳንኤል አስታራቂም ሆነው ሰባኪ እነዚህ የቤተ እምነት አባቶች ቢሳተፉ መልካም መሆኑን ማስተዋሉን ይናገራል። "ሰላም ከግለሰብ የሚጀምር ነው" የሚለው ዳንኤል ነገውን የሚያስብ ወጣት የራሱን እንዲሁም የሌሎችን ሰላም በሚጠብቅበት ወቅት ሰላሙን ለሌሎች እንደሚያካፍል ይህም ለአገር እንደሚተርፍ ይናገራል። ይህ የሰላም እና የእርቅ ሀሳብ ቀድሞውንም በማህበረሰቡ እና በቤተ እምነቶች ውስጥ ያለ መሆኑን በመግለጽም " እርሱ እንዴት ይጎልብት" የሚለው ላይ ማተኮር መፈለጉን ይናገራል። ስለ ሰላም ወጣቶች እና ሕጻናት ላይ አበክሮ መስራት እንደሚያስፈልግ በመግለጽም የሃይማኖት አባቶችም እነዚህ አካላት ላይ አተኩረው መስራት እንደሚያስፈልጋቸው አስተውሏል። ሰላም ከወጣትነት፣ ከስሜት ከብሔር ከሁሉም ይበልጣል ሲልም ይገልጻል። ኮንሶ ተሰማ ገመዳ የመጀመሪያ ዲግሪውን በኢኮኖሚክስ የትምህርት ዘርፍ ነው ያገኘው። ኮንሶ ተወልዶ ያደገው ተሰማ የእርቅ ሃሳብ ብሎ ካቀረበው መካከል በኮንሶ ማሕበረሰብ ዘንድ ያለ ባህላዊ የእርቅ ሃሳብ መሆኑን ይገልጻል። ባሕላዊ የእርቅ ሀሳብ ውስጥ ተሳትፎ ሲያደርጉ የሚታዩት በእድሜ ከፍ ያሉ፣ አዛውንቶች መሆናቸውን በመግለጽ በእርሱ ግምገማ ወጣቶች በእርቅ ስርዓት ውስጥ ሲሳተፉ አልተመለከተም። በእድሜ በገፉት ሰዎች ዘንድም ወጣቶቹን ከባህል አፈንጋጭ አድርጎ የመመለክት አዝማሚያ አለ የሚለው ተሰማ፣ ወጣቶቹም ኋላ ቀር ስርዓት አድርጎ የመመልከት ዝንባሌ እንዳላቸው አስተውሏል። ይህ የትውልድ ክፍተትን ለመፍታት ወጣቶችን በእርቅ ስርዓቱ ውስጥ ማሳተፍ ቢቻል መልካም መሆኑን፣ ወጣቱንም መሳብ እንደሚቻል ይናገራል። በባሕላዊ እርቁ ላይ የሚወሰኑ ውሳኔዎችም ሰብዓዊ መብትን የሚጥሱ፣ የሃይማኖት ነጻነትን የማያከብሩ ሆነው ያገኘበት ወቅት መኖሩን በመግለጽ የሃይማኖት አባቶችና የአገር ሽማግሌዎች በዚህ ረገድ ስልጠና ቢወስዱ ወጣቶችን የበለጠ ለማሳተፍና ለመማረክ ይችላሉ ሲል ሃሳቡን ለቢቢሲ አጋርቷል። ተሰማ ወጣቶችን በእርቅ እና በሰላም ሂደት ውስጥ ማሳተፍ ግጭቶችን ለመቀነስና ለማስቀረት ሁነኛ መፍትሔ ይሆናል ሲልም ያስረዳል። በግለሰቦች መካከል የሚነሳ ግጭት አድጎና ሰፍቶ የአገር ሰላም እንደሚያደፈርስ እንዲረዱ፣ ግጭቶች የሚያደርሱትን ምጣኔ ሃብታዊና ማሕበራዊ ጫና እንዲመለከቱና እንዲማሩ ማድረግ ወጣቶቹ ለሰላም የሚኖራቸውን ድርሻ ያጎላዋል ይላል። በአገራችን ሰላም እና እርቅ ላይ ወጣቶችንና ሴቶችን ማሳተፍ ወሳኝ መሆኑንም ያነሳል። ሰላም በሚደፈርስበት ወቅት ቀድመው ሲሯሯጡ የሚታዩት ፖለቲከኞች መሆናቸውን ያስተዋለው ተሰማ፣ የአገር ሽማግሌዎች በሰላምና እርቅ ጉዳይ መቼ ነው መሳተፍ ያለባቸው፣ ፖለቲከኞችስ ጣልቃ መግባት ያለባቸው መቼ ነው የሚለው ቢለይ መልካም መሆኑን ይናገራል። በተለያዩ የአገሪቱ ክፍል የሚገኙ ወጣቶች የእርቅ ሃሳባቸውን በማምጣት መወያየትና ጠቃሚውን መማር ቢቻል ለዘላቂ ሰላም አማራጭ መሆኑን ይገልጻል። ለወደፊት ውድድሩን አዘጋጅቶ የነበረው የእርቀ ሰላም ኮሚሽን ጋር ወደ ፊት ለመስራት ሃሳብ እንዳለው ይናገራል። ሰላም
news-45443694
https://www.bbc.com/amharic/news-45443694
ኤች አይ ቪን የሚከላከለው መድሃኒት ተስፋ ሰጪ ነው ተባለ
ዌልስ ውስጥ በሙከራ ደረጃ የሚገኘው የኤች አይ ቪ መከላከያ መድሃኒት ለማግኘት የሚደረገው ምርምር በበሽታው የመያዝ እድልን ለመቀነስ ሊረዳ እንደሚችል እየተገለጸ ነው።
የመድሃኒቱን ውጤታማነት ለመፈተሽ ለበሽታው የመጋለጥ ከፍተኛ እድል አላቸው ለተባሉ 559 የሙከራ ጥናቱ ተሳታፊዎች ከለፈው ዓመት ሐምሌ ወር ጀምሮ መድሃኒቱ መስጠት የተጀመረ ሲሆን፤ ከአንድ ዓመት በኋላ በተደረገላቸው ምርመራ ሁሉም ሰዎች ኤች አይ ቪ አልተገኘባቸውም። ይህም ውጤት እጅግ አስደሳችና በበሽታው ዙሪያ ያሉ መጠራጠሮችን የሚቀንስ ነው ተብሎለታል። • አተት እና ኮሌራ ምን እና ምን ናቸው? • አዲሱ የማዋለጃ ቦርሳ የእናቶችን ህይወት እየታደገ ነው ምርምሩን የሚያካሂዱት የህክምና ባለሙያዎች እንደገለጹት አብዛኛዎቹ የጥናቱ ተሳታፊዎች ላይ ሌሎች በግብረ ሥጋ ግንኙነት የሚተላለፉ በሽታዎች እንደተገኙባቸውና ከኤች አይ ቪ ነጻ መሆናቸው ደግሞ የመድሃኒቱን ውጤታማነት ያሚያሳይ ነው። መድሃኒቱ ''ፕሪ ኤክስፖዠር ፐሮፊላክሲስ'' የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል። በየቀኑ የሚወሰድ ሲሆን በሽታው ከአንድ ሰው ወደ ሌላ የመተላለፍ እድሉን እስከ 86 በመቶ ድረስ ይቀንሳል ተብሏል። • ጎዳና ተዳዳሪዎችን በህክምና መታደግ እስካሁን ድረስ በወሲብ ንግድ የሚተዳደሩና ሌሎች ለኤች አይ ቪ ተጋላጭ ነን ብለው የሚያስቡ በአሜሪካ፣ ካናዳ፣ አውስትራሊያና ፈረንሳይ የሚገኙ ሰዎች መድሃኒቱን መጠቀም ጀምረዋል።
50805233
https://www.bbc.com/amharic/50805233
ደሃ ሃገራት የምግብ እጥረት እንዲሁም ከልክ በላይ ውፍረት እንደሚያስቸግራቸው ተገለፀ
በደሃ ሀገራት የሚገኙ ሰዎች ከልክ በላይ ውፍረትም ሆነ ከፍተኛ የምግብ እጥረት እንደሚያስቸግራቸው አንድ የወጣ ሪፖርት አስታወቀ።
ዘ ላንሴት ላይ የወጣው ይህ ሪፖርት ለዚህ ምክንያት ያለውን ሲያስቀምጥ በፋብሪካ የተቀነባበሩ ምግቦች በብዛት መመገብ እንዲሁም የስፖርታዊ እንቅስቃሴ አለማድረግ መሆኑን አስፍሯል። ሪፖርቱን ይፋ ያደረጉት ባለሙያዎች ይህንንን ከልክ በላይ ውፍረት እንዲሁም ከፍተኛ የምግብ እጥረት "ዘመናዊ አመጋገብ ሥርዓት" በማለት እንዲለውጡ ጠይቀዋል። በዚህ የተጎዱ የተባሉ ሀገራት ከሰሃራ በታች ያሉ የአፍሪካ ሀገራትና የእስያ ሀገራት ናቸው። • ጨው በየዓመቱ 3 ሚሊዮን ሰዎችን ይገድላል • አፍሪካዊያን ተወዳጅ ምግባቸውን መተው ሊኖርባቸው ይሆን? ይህ ሪፖርት በዓለማችን ላይ 2.3 ቢሊየን ህጻናትና አዋቂዎች ከልክ በላይ ውፍረት እንደተጠቁ የተጠቀሰ ሲሆን፣ 150 ሚሊየን ሕጻናት ደግሞ የተገደበ እድገት አላቸው ሲል ያስቀምጣል። ዝቅተኛ እና መካከለኛ ገቢ ያላቸው ሀገራት በእነዚህ በሁለት ጉዳዮች በተመሳሳይ እንደሚጠቁ ያሰፈረው ሪፖርቱ ይህንንም " የምግብ ዕጥረት መንታ መልኮች" ሲል ይገልጻቸዋል። ይህም ማለት 20 በመቶ ሰዎች ከልክ በላይ ወፍራም፣ 30 በመቶ ዕድሜያቸው ከአራት ዓመት በታች የሆኑ ሕጻናት ተገቢ እድገት ያለመኖር፣ እንዲሁም 20 በመቶ ሴቶች ደግሞ ከመጠን በላይ ቀጭን ናቸው ይላል። ማሕበረሰብም ሆነ ቤተሰብ እንዲሁም በየትኛውም የሕይወት መስክ የተሰማሩ ግለሰቦች በዚህ ዓይነት የምግብ ዕጥረት ሊጠቁ እንደሚችሉ ሪፖርቱ ያስቀምጣል። በ1990ዎቹ ይላል ሪፖርቱ ከ123 ሀገራት መካከል 45ቱ በዚህ ችግር ተጠቅተው የነበረ ሲሆን በጎርጎሳውያኑ 2010 አካባቢ ደግሞ ከ126 ሀገራት 48 ተጠቅተዋል። በ2010 በተደረገ ፍተሻ፣ ከ1990ዎቹ ጀምሮ 14 ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ሀገራት በምግብ ዕጥረት መንታ መልኮች [በተመሳሳይ ሰዓት የተገደበ እድገት እንዲሁም ከልክ በላይ ውፍረት ] ተጠቅተዋል ይላል። ሪፖርቱን ያዘጋጁ አካላት እንዳሉት ከሆነ የሃገራት መሪዎች፣ የተባበሩት መንግሥታት እንዲሁም ምሁራን ይህንን ችግር በማስተዋል የበኩላቸውን ማድረግ አለባቸው ያሉ ሲሆን ጣታቸውንም የአመጋገብ ስርዓት መለወጥ ላይ አድርገዋል። የበርካታ ግለሰቦች የአመጋገብ፣ አጠጣጥ እንዲሁም የአካል ብቃት እንቅስቃሴ መለወጥ ለዚህ ሁሉ ምከንያት ነው ያሉት ባለሙያዎቹ፣ በሀገራት በየገበያ አዳራሹ የሚገኙ በቀላሉና በርካሽ የሚገኙ ምግቦች በርካታ ሰዎች ከልክ በላይ እንዲወፍሩ እያደረገ ነው ብለዋል። እንደ ሪፖርቱ ከሆነ በፋብሪካ የተቀነባበሩ ምግቦችን ከልጅነት ጀምሮ መመገብ እድገት ባለበት እንዲቀር የራሱ አስተዋጽኦ አለው ብለዋል። " አዲስ የተመጣጠነ ምግብ እውነታን እየተጋፈጥን ነው" ያሉት በዓለም ጤና ድርጅት የሥነ ምግብ ጤናና ዕድገት ክፍል ዳይሬክተር ዶ/ር ፍራንሲስኮ ብራንካ ናቸው። • ጨቅላ ልጅዎትን ከአቅም በላይ እየመገቡ ይሆን? " ከአሁን በኋላ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን በምግብ እጥረት የተጎዱ ወይንም ከፍተኛ ገቢ ያላቸውን ደግሞ ከልክ በላይ ውፍረት ጋር ማዛመዳችን መቅረት አለበት" ብለዋል። ሁሉም ዓይነት የምግብ ዕጥረት ጉዳት የጋራ መለያ ነው። የምግብ ስርዓታችን ጤናማ፣ በጥንቃቄ የተዘጋጁ፣ በቀላሉ የሚገኙ፣ ርካሽ፣ እና በቂ የሆነ የተመጣጠነ ምግብ ይዘት ያላቸው አይደሉም ሲሉ ወቅሰዋል። ዶ/ር ብራንካ እንዳሉት የምግብ ስርዓታችን ከምርት እስከ ማቀነባበሪያ፣ ከሽያጭ እስከ ስርጭት፣ ከዋጋ ትመና እስከ ገበያ፣ አስተሻሸግና ፍጆታ እንዲሁም አወጋገድ ላይ መለወጥ ይኖርበታል። አክለውም " ፖሊሲዎችና እስካሁን በዚህ ጉዳይ ላይ የፈሰሱ ኃብቶች በሙሉ ዳግመኛ መፈተሽ አለባቸው" ይላሉ ዶ/ር ብራንካ።
news-54128783
https://www.bbc.com/amharic/news-54128783
ፕሬዝደንት ማዱሮ የአሜሪካ ሰላይ ነዳጅ ማውጫ ስፍራ ላይ ያዝን አሉ
የቬንዙዌላው ፕሬዝደንት ኒኮላስ ማዱሮ የአሜሪካ ሰላይ ነዳጅ ማውጫ ስፍራ ላይ በቁጥጥር ሥር አዋልን አሉ።
ፕሬዝደንቱ በቴሌቪዥን መስኮት ቀርበው ለህዝባቸው እንደተናገሩት የአሜሪካ ሰላይ ነው ያሉት ግለሰብ ከጦር መሳሪያ እና ከፍተኛ መጠን ካለው ጥሬ ገንዘብ ጋር የነዳጅ ማውጫ እና ማቀነባባሪያ ስፍራ አቅራቢያ ተይዟል። ማዱሮ በቁጥጥር ሥር የዋለው አሜሪካዊ “የአሜሪካ የጦር አባል እና መቀመጫውን በኢራቅ የሲአይኤ ቢሮ ያደረገ ነው” ብለዋል። አሜሪካ በጉዳዩ ላይ እስካሁን ያለችው ነገር የለም። ፕሬዝደንቱ ጨምረውም በቅርቡ የቬንዙዌላ ባለስልጣናት በነዳጅ ማውጫ ጣቢያዎች ላይ ፍንዳታ ለመፈጸም የተሸረበን ሴራ ማክሸፍ ችለዋል ብለዋል። ከአንድ ወር በፊት የቬንዙዌላ ፍርድ ቤት ሁለት የቀድሞ የአሜሪካ ጦር አባላት ላይ ፕሬዝደንቱን በኃይል ከስልጣን ለማስወገድ ሞክረዋል በሚል ክስ የ20 ዓመት እስር በይኗል። ሁለቱ ፍርደኞች ግንቦት ወር ላይ ከሌሎች 11 ሰዎች ጋር ከጎረቤት አገር ኮሎምቢያ በባህር በኩል ወደ ቬንዙዌላ ተደብቀው ሊገቡ ሲሉ ነበር በቬንዙዌላ ጦር በቁጥጥር ሥር የዋሉት። አሜሪካ ለፕሬዝደንት ኒኮላስ ማዱሮ እውቅና አትሰጥም። ይልቁንም ዋሽንግተን የተቃዋሚ ፓርቲ መሪው ሁሃን ጓይዶን ነው ሕጋዊ የቬንዙዌላ ፕሬዝደንት አደርጋ የምትቆጥረው። በአሜሪካ እና በቬንዙዌላ መካከል ያለው ግንኙነት ከጊዜ ወደጊዜ እየሻከረ መጥቷል። ማዱሮ አሜሪካ በቬንዙዌላ ፖለቲካ ውስጥ እጇን በማስገባት ነዳጅን ጨምሮ የቬንዙዌላን የተፈጥሮ ሃብት ለመበዝበዝ ጥረት እያደረገች ነው ሲሉ ይከሳሉ። አሜሪካ እና ጓይዶ በበኩላቸው ቬንዙዌላ ለተዘፈቀችበት ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ማዱሮን ተጠያቂ ያደርጋሉ።
49699380
https://www.bbc.com/amharic/49699380
የወንድ ልጅ የዘር ፍሬን ሙቀት የለካው ምርምር ተሸለመ
በዘንድሮው የስፑፍ ኖቤል ሽልማት ላይ ካሸነፉ የምርምር ሥራዎች መካከል በግራና በቀኝ የዘር ፍሬዎች መካከል የሙቀት መጠን ልዩነት መኖር አለመኖሩን ለማወቅ የተደረገው ጥናት ይገኝበታል።
ወንድ ልጅ የሱሪውን ዚፕ ከፍቶ ተመራማሪዎቹ በዚህ ጥናታቸው የወንድ ልጅን የቀኝና የግራ ዘር ፍሬ ሙቀት በመለካት ልዩነቱን ለማወቅ ጥረዋል። በአጠቃላይ 22 ወንዶችን ለዚህ የምርምር ሥራ የተጠቀሙ ሲሆን፤ ግለሰቦቹ የፖስታ ቤት ሠራተኞችና የአውቶቡስ አሽከርካሪዎች ናቸው ተብሏል። • “በአፍ መፍቻ ቋንቋ መማርን ዛሬም፣ ነገም፣ ወደፊትም የምከራከርበት ነው” ገነት ዘውዴ [ዶ/ር] • በፈረንጅ "ናይት ክለብ" ጉራግኛ ሲደለቅ • በአንድ የጦር አውድማ ላይ ከወላጅ አባቷ ጋር የተፋለመችው ታጋይ ምርምሩ የተካሄደው እርቃናቸውን እንዲሁም ልብስ ለብሰው በቆሙ የፈረንሳይ ፖስታ ቤት ሠራተኞች ላይ ነው። በዚህ ምርምር፤ የግራ የዘር ፍሬ ከቀኙ ይልቅ እንደሚሞቅ ማረጋገጥ ችለናል ብለዋል ተመራማሪዎቹ። ይህ ግን የሚሆነው ልብስ ከለበሱ ብቻ ነው ይላሉ። ምርምሩ የተደረገው በ11 የፖስታ ቤት ሠራተኞች ላይ ሲሆን፤ ለ90 ደቂቃ ያህል ቆመው የዘር ፍሬያቸው ሙቀት መለካቱንም ለማወቅ ተችሏል። የፖስታ ቤት ሠራተኞቹ የዘር ፍሬ የሙቀት መጠን በየሁለት ደቂቃው የተለካ ሲሆን፤ የግራ የዘር ፍሬ ሙቀት መጠን ከቀኙ ከፍ ብሎ ታይቷል። 11 የአውቶቡስ ሹፌሮች ተቀምጠውም የዘር ፍሬ ሙቀት የተለካ ሲሆን፤ የምርምር ውጤቱ የሕክምና ምርምር ሥራዎች በሚታተምበት መጽሔት ላይ እንደወጣ ተነግሯል። በዚህ ምርምር ማረጋገጥ እንደተቻለው የዘር ፍሬ ሙቀት የወንዶች የመውለድ አቅም ላይ ተጽዕኖ አለው። በምዕራቡ ዓለም የወንዶች የዘር ፈሳሽ ጥራት መቀነስ የታያ ሲሆን፤ ይህንን ለማሻሻል የተደረጉ ጥናቶች በቁጥር አናሳ ናቸው።
55976627
https://www.bbc.com/amharic/55976627
ትግራይ ፡ የዓለም ምግብ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ትግራይ ገቡ
የዓለም ምግብ ድርጅት እና የኢትዮጵያ መንግሥት በትግራይ የሰብዓዊ ድጋፍ ለሚያሻቸው ሰዎች ድጋፍ ለማድረስ ከስምምነት መድረሳቸው ተገለጸ።
የዓለም ምግብ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዴቪድ ቢዝሊይ በተባባሩት መንግሥታት የዓለም ምግብ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዴቪድ ቢዝሊይ የኢትዮጵያ መንግሥት እና እርሳቸው የሚመሩት ድርጅት በመላው ትግራይ የሰብዓዊ ድጋፍ ለማድረስ ከስምምነት መድረሱን አስታውቀዋል። ዴቪድ ቢዝሊይ "በትግራይ ሦስት ሚሊዮን ሕዝብ የእኛን አስቸኳይ እርዳታ ይሻል። የምናባክነው ጊዜ የለም" ሲሉ በትዊተር ገጻቸው ላይ ጽፈዋል። በትግራይ የሚገኙት ዋና ዳይሬክተሩ፤ የዓለም ምግብ ድርጅት 1.3 ሚሊዮን ሕዝብ ለመርዳት 20 ሺህ ቶን ምግብ በመላው ትግራይ እያሰራጨ መሆኑን በተንቀሳቃሽ ምስል አስደግፈው አሳይተዋል። በተያያዘ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ በፕሮጄክት ሲንዲኬት ላይ በጻፉት እና ከሁለት ቀናት በፊት በታተመው ጽሑፋቸው፤ በትግራይ እና በመላው አገሪቱ በሰዎች ላይ የሚደርሱ ስቃዮችን መቀነስ ቅድሚያ የሚሰጡት ጉዳይ መሆኑን ጠቅሰው፤ የተባበሩት መንግሥታት እና ዓለም አቀፍ የረድኤት ድርጅቶች በትግራይ እርዳታ ለሚሹ ዜጎች የሰብዓዊ ድጋፍ ለማድረስ አብረው እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል። ጠቅላይ ሚንሰትሩ በጽሑፋቸው በትግራይ ክልል የሰብዓዊ እርዳታ ለማድረስ እና በክልሉ ሕይወት ወደ ቀደመ ሁኔታ እንዲመለስ አስተዳደራቸው "ቀን እና ለሊት" እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚንስትሩ የሰብዓዊ እርዳታውን በማቅረብ ሥራ ላይ "በሕወሓት ኃይሎች ሆነ ተብሎ እንዲቋረጥ የተደረው የኮሚኒኬሽን ግንኙነት" ለአስተዳደራቸው ፈተና ሆኖ መቆየቱን ገልጸው፤ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በመልሶ ግንባታው ላይ ከፍተኛ ትብብር ሊያደርግ ይችላል ብለዋል። "በትግራይ ያለው ሁኔታ አሳሳቢ ነው" የተባባሩት መንግሥታት በትግራይ ክልል የተከሰተውን ግጭት ተከትሎ 4.5 ሚሊዮን ሕዝብ አስቸኳይ የሰብዓዊ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል ማለቱ ይታወሳል። የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር ፊሊፖ ግራንዲ፤ በትግራይ ያደረጉትን ጉብኝነት ከቀናት በፊት ሲያጠናቅቁ በክልሉ ያለው ሁኔታ እጅግ አሳሳቢ ነው ሲሉ መግለጫ ሰጥተው ነበር። በተመሳሳይ የኖርዌጂያን ሪፊውጂ ካውንስል (ኤንአርሲ) ዋና ጸሀፊ ጃን ኢግላንድ በትግራይ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ሰዎች በበቂ ሁኔታ ድጋፍ እያገኙ አይደለም ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት በበኩሉ በትግራይ ክልል እርዳታ የሚሹ ሰዎች ቁጥር 2.5 ሚሊዮን መሆኑን እና ለእነዚህም ዜጎች አስፈላጊ የሆነ እርዳታ ለማድረስ በቂ ዝግጅት ማድረጉን ሲያስታውቅ ነበር። የብሔራዊ የአደጋ ሥጋት ሥራአመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ምትኩ ካሳ "በትግራይ እርዳታ የሚያስፈልጋቸውሰዎች ቁጥር 4.5 ሚሊዮን ሳይሆን 2.5 ሚሊዮን ነው" ብለዋል። ኮሚሽነሩ፤ 2.5 ሚሊዮን ሕዝብ ለመርዳት መንግሥት በቂ ዝግጅት አድርጓልም ብለዋል።
news-47316931
https://www.bbc.com/amharic/news-47316931
ከድምፃዊ ቤቲ ጂ እና ቸሊና ጀርባ ያለው ወጣት
ከሁለት ዓመታት በፊት ገደማ ነበር ድምፃዊት ብሩክታዊት ጌታሁን (ቤቲ ጂ) 'ማነው ፍፁም' በተሰኘ አልበም ብቅ ያለችው። ቀጥላም 'ወገግታ' ብላ በሰየመችው ሁለተኛ አልበሟ ኢትዮጵያና አፍሪቃን ዋጀች።
ቤቲ ጂ፤ በአምስተኛው የመላው አፍሪቃ የሙዚቃ ሽልማት (አፍሪማ) ላይ በስድስት ዘርፎች ታጭታ ሦስቱን ወደሃገሯ ይዛ ተመለሰች። ታድያ ከቤቲ ጂ ስኬታማ አልበም ጀርባ ብዙ ያልተባለለት አንድ ወጣት አለ። ያምሉ ሞላ 'ወገግታ' አልበምን ሙሉ በሙሉ 'ፕሮዲዩስ' ከማድረግም አልፎ የአልበሙን ሙዚቃዎች ሙሉ ግጥም የፃፈላት እርሱ ነው። • ታዋቂ ኢትዮጵያዊያን አርቲስቶች ለመዋብ ምን ያህል ይከፍላሉ? • የአለማየሁ ተፈራ ፖለቲካዊ ካርቱኖች «አልበሙ የሁለታችንም ሕይወት ነፀብራቅ ነው። አንድ ዘፈን አብረን ፅፈናል። በሳምንት አንዴ ሁለቴ እንገናኝ ነበርና እናወራለን። ከዚያ በአምስት ወር ገደማ አልበሙን አጠናቀቅነው። ድህረ 'ፕሮዳክሽን' የነበረው ሂደት ግን ጊዜ ወስዶብናል።» ቤቲ ጂ እና ያምሉ የለፉበት ሥራ ፍሬ አፍርቶ የአልበሙ ስኬታማነት በአፍሪካ ናኝቷል፤ አልፎም በሥራዎቿ ትልቁን የአፍሪማ ሽልማት ልታገኝ ችላለች። «በጣም ደስ የሚያሰኝ ጊዜ ነበር። ሥራዎቻቸው ቢልቦርድ ላይ የወጡላቸው ታዋቂ ዘፋኞች ነበሩ። ከአንድ ሃገር ብዙ በታጨ በሚለው እኛ ነበርን አንደኛ። ቤቲ በስድስት ዘርፎች፤ እኔ ደግሞ በሁለት ዘርፎች። የዓመቱ ምርጥ አልበም ተብለን ስንሸለም በጣም 'ሰሪል' የሆነ ስሜት ነበር የተሰማን።» ያምሉ ሞላ በሁለት ዘርፎች ቢታጭም ሽልማት ሊያገኝ ግን አልቻለም። ለምን? «እውነት ለመናገር ነገሩ ግርታን ፈጥሮብኛል። ምክንያቱም ብዙ ጊዜ አንድ አልበም ሲያሸንፍ፤ አልበሙን ያቀናበሩ፤ ግጥሙን የፃፉ፤ ዜማ የደረሱ አብረው ይሸለማሉና። አሠራራቸው እንዴት እንደሆነ አላውቅም፤ ግን እኔ የታየኝ ነገር ቤቲ ማሸነፏ እኔ እንዳሸነፍኩ እንደሆነ ነው። እናሸንፋለን ብዬ አስቤ ስላልነበር፤ እጅግ በጣም ደስ የሚል ጊዜ ነበር። እኔ ይህ በመሆኑ ምንም አልከፋኝም። ምክንያቱም ይህ ገና የመጀመሪያ ነው እንጂ የመጨረሻው አይደለም።» ቸሊና 'ሳይ ባይ' በተሰኘው ነጠላ ዜማዋ የምትታወቀው ቼሊና በቅርቡ የመጀመሪያ አልበሟን ለሙዚቃ አድማጩ ማበርከቷ የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው። 14 ሙዚቃዎች የተካተተቡት ይህ አልበም አዲስ ነገር ይዞ መጥቷል ሲሉ በርካቶች እያወደሱት ይገኛሉ። ታድያ ከ14ቱ ሙዚቃዎች 11 ያህሉን ያዘጋጃቸው ያምሉ ነው። • “ከወጡት ስራዎቼ ይልቅ ገና የሚወጡት ናቸው ትልቅ ቦታ ያላቸው” አለማየሁ ገላጋይ «ከቼሊና ጋር ሥራውን የጀመርነው የዛሬ ሁለት ሦስት ዓመት ገደማ ነው። ከዚያ መሀል ተቋርጦ ነበር። እንደገና ደግሞ ተመለስንበት። ብዙዎቹን ጽፌያቸዋለሁ፤ ግጥምና ዜማቸውን። እሷም ጎበዝ ዜማ ሠሪ ናት። አልበሙ ከወጣ ብዙ ጊዜ አልሆነውም። ቢሆንም ደስ የሚል 'ፊድባክ' እየሰማሁ ነው።» አዳዲስ ሥራዎች "ወገኛ ነች" እና "እስከመቼ" በተሰኙ ነጠላ ዜማዎቹ ይታወቃል፤ ጊታሩ ተጫዋቹ ዜመኛ ዘሩባቤል ሞላ። የያምሉ ሞላ ወንድም ነው። በቅርቡ ሙሉ አልበም ሠርተው ለአድማጭ ጆሮ ለማድረስ ተፍ ተፍ እያሉ ነው። ያምሉ፤ «ዘሩባቤል በጣም ጎበዝ ጊታሪስት እንዲሁም ቮካሊስት ነው» ሲል ስለ ወንድሙ ይመሰክራል። ያምሉ፤ ከታዋቂ ሙዚቀኞች ይልቅ ከአዳዲሶቹ ጋር መሥራትን እንደሚመርጥ ይናገራል። «በጣም ታዋቂ ከሆኑ ሰዎች ጋርም እየሠራሁ ነው። ነገር ግን እኔ የሚያስደስተኝ ከአዳዲስ ሙዚቀኞች ጋር ስሠራ ነው። ከዘሩባቤል በተጨማሪ ከሚኪያስ (የሃሴት አኩስቲክ አባል)፤ ጋር አልበም እየሠራን ነው። ፌላ የምትባል አዲስ ልጅ አለች። አርቲስት፣ ራፐር እንዲሁም የግጥምና ዜማ ደራሲ ከሆነው ደስ (ደስ አበጀ) ጋርም እየሠራሁ ነው። ብዙ ጽሑፎችን የጻፈ ነው፤ ለጃኖ ባንድ የመጨረሻ አልበም ሙዚቃዎችን አበርክቷል።» 3-11 ብዙ ጊዜ የሙዚቃ ሰዎች ሥራዎቻቸውን ከቀን ይልቅ ምሽት ላይ መሥራት እንደሚመርጡ ሲናገሩ ይደመጣል። ያምሉ ግን የፈለገ ቢሆን አምሽቼ መሥራት አልመርጥም ይላል። • ተፈራ ነጋሽ፡ "በነገራችን ላይ ሙዚቃ አልተውኩም" «ትልቁ ነገር ምን መሰለህ? ጤና ነው። ጤንነት ያስፈልጋል። ሙዚቀኞች ሌሊት ላይ የሚሠሩበት የራሳቸው ምክንያት ሊኖራቸው ይችላል። እኔ ግን ጠዋት በሰዓቴ ገብቼ ደንገዝገዝ ሲል ነው መውጣት የምፈልገው። አንደኛው ምክንያቴ ደግሞ ከሱስ መራቅ መፈለጌ ነው። ላምሽ ብዬ ጫት መቃምም ሆነ ሌላ ዓይነት አበረታች ነገር መውሰድ አልፈልግም።» ሙዚቃ፣ ፀሎት እንዲሁም በዙሪያው ያሉ ነገሮች ማነቃቂያው እንደሆኑ የሚናገረው ያምሉ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን ትልቅ ምሣሌ አድርጎ ይወስዳል። «እኔ ፖለቲካ አልወድም። ነገር ግን እርሣቸው በዚህ ዕድሜያቸው እንቅልፍ ሳይወስዳቸው ለሃገር ይህን ሁሉ ነገር ካደረጉ እኔም ማድረግ አያቅተኝም ብዬ አስባለሁ። እርሳቸው በ40ዎቹ ዕድሜ ውስጥ ናቸው። እኔ ደግሞ በ30ዎቹ።» ስኬት ሲለካ እውን ያምሉ ስኬትን የሚለካው እንዴት ይሆን? በሽያጭ? በተቀባይነት? ወይስ በሽልማት? «(ፈገግ. . .) ምን መሰለህ? እኔ አነዚህ ነገሮች አይመለከቱኝም። ምን አስባለሁ መሰለህ ሁሌ. . . እኔ የምወደው ሥራ ነው? አብሬው ከምሥራው ሙዚቀኛ ጋር የውስጣችንን ማበርከት ችለናል ወይ? እኛ ወደነዋል ወይ? እኛ ጋር ያለው ስሜት ጤነኛ ነው ወይ? ነው የኔ ጥያቄ። ለመጨረስ ነው የሠራነው? ወይስ የተሰማንን ነገር በሙዚቃ ለማበርከት? ዋናው ነገር ነገ የምፀፀትበት ነገር፤ የኢትዮጵያን ሙዚቃ ተጨምሬ ወደኋላ የምጎትትበት ነገር እንዳይሆን ነው ትልቁ ስጋቴ።»
news-54202817
https://www.bbc.com/amharic/news-54202817
በሕንድ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ያለ እድሜ ጋብቻን ማባባሱ ተገለፀ
ራኒ 13 ዓመቷ ነው። የስምንተኛ ክፍል ተማሪ ናት። ቤተሰቦቿ ሊድሯት ሲሉ ታግላ አስቁማቸዋለች።
ሕንድ ውስጥ እንቅስቃሴ ላይ ገደብ ሲጣል ትምህርት ቤቶች ተዘግተዋል። የቲቢ ታማሚው የራኒ አባት በዚህ ወቅት ነበር ልጃቸውን ለመዳር ያሰቡት። ራኒ ግን ተቃወመቻቸው። “ሴቶችን ለመዳር ምን እንደሚያጣድፋቸው አላውቅም። መማር፣ ሥራ መያዝና ራሳችንን መቻል እንዳለብን አያስቡም።” በሕንድ ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ሴቶች መዳር ወንጀል ነው። ነገር ግን በርካታ ያለ እድሜ ጋብቻ ይፈጸማል። ቁጥሩ ከዓለም አንድ ሦስተኛውም ነው። ዩኒሴፍ እንደሚለው፤ በየዓመቱ ቢያንስ 1.5 ሚሊዮን ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ሴቶች ይዳራሉ። ዘንድሮ ደግሞ ነገሮች ተባብሰዋል። ‘ቻይልድላይን’ የተባለው ድጋፍ ሰጪ እንደገለጸው፤ ከሰኔ እስከ ሐምሌ ልንዳር ነው ብለው ወደ ድርጅቱ የደወሉ ታዳጊዎች ቁጥር 17 በመቶ ጨምሯል። በእንቅስቃሴ ገደቡ ሳቢያ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች ሥራቸውን አጥተዋል። ይህም በኢ-መደበኛ ሥራ የተሰማሩትን ይጨምራል። መንግሥት እንደሚለው ከ10 ሚሊዮን በላይ ስደተኛ ሠራተኞች ወደየቀያቸው ተመልሰዋል። በገጠር የሚኖሩ ወላጆች ሴት ልጆቻቸውን መዳር ብቸኛ አማራጭ እንደሆነም ያስባሉ። አገሪቱ ሰኔ ላይ እንቅስቃሴ ብትጀምርም አሁንም ብዙ ሥራዎችና ትምህርት ቤቶች እንደተዘጉ ነው። ምጣኔ ሀብትቱም እየላሸቀ ይገኛል። ሁኔታው ብዙ ታዳጊዎችን አጣብቂኝ ውስጥ ከቷል። ለታዳጊዎች ከለላ ይሰጡ የነበሩ ትምህርት ቤቶች ተዘግተዋል። ቤተሰቦቻቸው ያለ እድሜያቸው ሊድሯቸው ያሉ ሴቶች ቀድሞ ከለላ የሚያገኙት ከመምህራኖቻቸው ነበር። በአክሽን ኤድ የሚሠሩት ስሚታ ካንጆው “በጣም ድሀ በሆኑ ማኅበረሰቦች ዘንድ ሴቶች እንዲማሩ አይበረታቱም። ሴቶች ትምህርት ካቋረጡ በኋላ በድጋሚ እንዲጀምሩ ቤተሶቻቸውን ለማሳመን ከባድ ነው” ይላሉ። 2011 ላይ የተሠራ ጥናት ከ260 ሚሊዮን የሕንድ ልጆች 10 ሚሊዮኑ የጉልበት ሥራ እንደሚሠሩ ያሳያል የታዳጊዎች ትግል የራኒ ጓደኛ የተዳረችው በዚህ ዓመት ነበር። እሷንም ቤተሰቦቿ ሊድሯት እንደሆነ ስታውቅ ወደ የልጆች አደጋ ጊዜ ክፍል ደወለች። አንድ የተራድኦ ድርጅት ከፖሊሶች ጋር ተጋግዞ ጋብቻውን አስቁሟል። የራኒ አባት ብዙም ሳይቆይ አረፉ። ትምህርት ቤት ሲከፈት ትምህርት መጀመር እንዳለባትም ትናገራለች። “አሁን ቤተሰባችንን ማስተዳደር የኔ ኃላፊነት ነው” ትላለች። ታዳጊ ወንዶች ቤተሰቦቻቸውን ለመደገፍ ፋብሪካ ውስጥ እንዲሠሩ ይገደዳሉ። ሕንድ ውስጥ ልጆችን በጉልበት ሥራ ማሠማራት ሕገ ወጥ ቢሆንም፤ 2011 ላይ የተሠራ ጥናት ከ260 ሚሊዮን የሕንድ ልጆች 10 ሚሊዮኑ የጉልበት ሥራ እንደሚሠሩ ያሳያል። ፓንካጅ ላል የ13 ዓመት ልጃቸውን ለሕገ ወጥ አዘዋዋሪዎች ለመስጠት ተገድደዋል። ምንም ገቢ ሳይኖራቸው አምስት ልጆቻቸውን መመገብ አልቻሉም ነበር። ልጃቸው ከመንደራቸው በ1000 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኝ ፋብሪካ ውስጥ እንዲሠራ ልከዋል። በወር 68 ዶላር ይከፈለዋል። ልጃቸው ፋብሪካ እንዲሠራ መላካቸው ፓንካጅን እጅግ ያሳዝናቸወል። “ልጆቼ ለሁለት ቀናት አልበሉም። ስለዚህ ሕገ ወጥ አዘዋዋሪው እንዲወስደው አደረግኩ። ጠንካራ እጅ ያለው ሰው ነው የምንፈልገው ስላሉኝ እኔ መሄድ አልቻልኩም። እና ልጄ ከመላክ ውጪ አማራጭ አልነበረኝም።” ትራንስፖርት ላይ ገደብ ቢጣልም ሕገ ወጥ አዘዋዋሪዎች ልጆችን ከቦታ ቦታ እያንቀሳቀሱ ነው። ሱርሽ ኩመር የእርዳታ ድርጅት ይመራሉ። ለ25 ዓመታት ታዳጊዎችን ከሕገ ወጥ አዘዋዋሪዎች ሲያስጥሉ የነበሩት ሱርሽ ዝውውሩ በእጥፍ መጨመሩን ይናገራሉ። “ለአዘዋዋሪዎች ያተረፍናቸው ልጆች ከአምና በእጥፍ ጨምሯል። ባለፉት ወራት ሕገ ወጥ አዘዋዋሪዎች ተጠናክረዋል።” መንግሥት ሕገ ወጥ የልጆች ዝውውርን በተመለከተ ጥብቅ ሕግ አውጥቷል። የተለያዩ ግዛቶች ስለ ጉዳዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ እንዲሰጡ፣ ሕጋቸውን እንዲያጠብቁ እንዲሁም በወረርሽኙ ወቅት ለሴቶችና ሕፃናት ማቆያ እንዲያዘጋጁ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል። የመብት ተሟጋቾች እንደሚሉት ከሆነ ግን ሕገ ወጥ አዘዋዋሪዎች ጉቦ እየሰጡ ከእስር ያመልጣሉ። ቤተሰቦች ጉዳዩን ለፖሊስ እንዳያመለክቱ ማስፈራሪያ ሊደርሳቸውም ይችላል። ፓንካጅ እድለኛ ሆነው ልጃቸውን ይዞ ይጓዝ የነበረው አውቶብስ ተይዞ ልጃቸው በማቆያ እንዲገባ ተደርጓል። በቅርቡም ከቤተሰቡ ጋር ይቀላቀላል። “ደካማ ሆኜ ነበር ልጄን የላኩት። ከእንግዲህ በትራፊ ብንኖርም ልጄን ወደ ሥራ አልክም።”
news-53544125
https://www.bbc.com/amharic/news-53544125
"ከዓመት በፊት ከነበሩብን የሠላም ችግሮች በአንጻራዊነት ተላቅቀናል" አቶ ተመስገን ጥሩነህ
የአማራ ክልል ከዓመት በፊት ከነበሩበት የሠላም ችግሮች በአንጻራዊነት መላቀቁን የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ ተመስገን ጥሩነህ ተናገሩ።
ርዕሰ መስተዳድሩ "አፍራሽና ለውጥ አደናቃፊ" ያሏቸው ኃይሎች በአንዳንድ የክልሉ አካባቢዎች የጥፋት አጀንዳ እና የማንነት ጥያቄዎችን በማንሳት አለመረጋጋት ለመፍጠር መሞከራቸውን ገልጸዋል። ጨምረውም ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትና በአንዳንድ ስፍራዎች ችግር በመፍጠር ግጭት እንዲከሰትና በሰው ህይወት እንዲሁም በንብረት ላይ ጉዳት እንዲደርስ አድርገዋል ብለዋል። አቶ ተመስገን ይህን የተናገሩት የአማራ ክልል ምክር ቤት ጉባዔ ዛሬ በባህር ዳር ከተማ በተጀመረበት ጊዜ ሲሆን፣ አቶ ተመስገን የ2012 የአስፈጻሚ አካላት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርትንም አቅርበዋል። ርዕሰ መስተዳደሩ በተለይ በክልሉ የጸጥታ ሁኔታ ላይ እንደተናገሩት አፍራሽ ያሏቸው ኃይሎች "በማኅበራዊ የትስስር መድረኮች ላይ የሚለቀቁ ሐሰተኛ ትርክቶችን በማሰራጨት ክልሉን ወደ ትርምስ ለማስገባት ሁሉን አቀፍ መንገዶችን ሲጠቀሙ ቆይተዋል" ብለዋል። ይህንንም ሲያብራሩ የክልሉን ሰላም ለማደፍረስ ከሚንቀሳቀሱት መካከል በተለይ "የቅማንት ኮሚቴ ነኝ በሚል ጥላቻን ካነገቡ ኃይሎች ጋር በመቀናጀት ትምህርት ቤቶች እንዲዘጉ፣ ትራንስፖርት እንዲቋረጥና በከተሞች ነውጥ እንዲሰፍን ያደረጉት ጥረት በቁጥጥር ስር የማዋል ሥራ ተሠርቷል" ሲሉ ጠቅሰዋል። በክልሉ አንዳንድ ቦታዎች ላይ ሰላም ለማስፈን እርቀ ሰላም እንዲፈጠር መደረጉን የገለጹት አቶ ተመስገን ችግር ሲፈጥሩ የነበሩ ያሏቸው 387 ሰዎች በምህረት እንዲገቡ ተደርጎ አንጻራዊ ሠላምና መረጋጋት ለመፍጠር ተችሏል ብለዋል። "የፋኖን ስም በመጠቀም በሁሉም አካባቢዎች በሚባል ደረጃ የክልሉን ሕዝብ ላይ ችግር በመፍጠር መንግሥት ሕግን ማስከበር የማይችል ለማስመሰል" መሞከሩን አስታውሰው ይህንን ችግር በዘላቂነት በሠላም ለመፍታት ጥረት መደረጉን ገልጸዋል። ከዚህም ጋር በተያያዘ ሕግና ሥርዓት ለማስከበር በተደረገው ጥረት 215 በምህረት ሲገቡ 405 ሠላማዊ በሆነ መንገድ እጅ ሰጥተዋል። ፈቀደኛ ያልነበሩ 686 ሰዎች ደግሞ በኃይል እጅ እንዲሰጡ መደረጉን አመልክተዋል። ርዕሰ መስተዳደሩ ለክልሉ ምክር ቤት እንደተናገሩት "ከመንግሥት መዋቅር ውጪ ሆኖ የተለያዩ አካባቢዎችን ሲያተማርምስ የነበረውን ሕገ ወጥ ኃይል የማፍረስ ሥራም ወርቃማ ነው" ሲሉ ስኬታማነቱን ገልጸውታል። አክለውም የክልሉ ተወላጆችን መፈናቀል፣ የሕይወት መጥፋትና የንብረት ውድመት በተደራጁ ቡድኖችና ግለሰቦች ሲፈጸም የቆየ መሆኑን ጠቅሰው፤ "ከበስተጀርባው የጸረ ለውጥ ኃይሉ እጅ ያለበትና ሁሉንም ክልሎች የቀውስ ቀጠና ለማድረግ የታሰበ ነው" ሲሉ ተናግረዋል። "ለውጥ አደናቃፊው ቡድን" ያሉት ኃይል የክልሉን ሰላም ከማይፈልጉ ኃይሎች ጋር በመሆን አካባቢውን የብጥብጥ ማዕከል ለማድረግ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል ብለዋል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ተመስገን ጥሩነህ። ይህ ኃይል "አሁንም ሕዝብን ለማደናገር ሐሰተኛ መረጃ ሆን ብሎ እየለቀቀ ለዘመናት በአብሮነት የኖረውን የቅማንትና የአማራ ሕዝብ ወደ ግጭት እንዲያመራ እየሠራ ነው" ሲሉ ከስሰዋል። ርዕሰ መስተዳደሩ በተጨማሪ እንደተናገሩት ለዘመናት በክፉም ሆነ በደግ አብረው የኖሩ በሥጋም ሆነ በደም የተጋመዱ "የአማራና የትግራይ ሕዝቦችን ለማጋጨት በአማራ አዋሳኝ የትግራይ ክልል አካባቢዎች የተለያዩ ጠብ አጫሪና የትንኮሳ ተግባራት" እየተከናወኑ እንደሆነ ገልጸዋል። ይህንን "ትኮሳውና ጠብ አጫሪነት ፈር ለማስያዝ የሚመለከታቸው አካላት እንዲገነዘቡና የክልሉ የትኛውንም ራስን የመከላከል ተግባር ሕዝቡ እንዲደግፍ" ጠይቀው ይህን መፈጸም ተቀዳሚ ተግባር እንደሆነ ለምክር ቤቱ አሳውቀዋል። ለሁለት ቀናት በሚቆየው በዚህ የክልሉ ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤው የ2012 ዓ.ም በጀት ሪፖርት ግምገማ፣ የሕግ የበላይነትና በሰላም ማስከበር፣ ኮቪድ-19ን በዘላቂነት መከላከል እና በሌሎችም ክልላዊና አገራዊ ጉዳዮች እንደሚመክር ይጠበቃል።
51313703
https://www.bbc.com/amharic/51313703
በኮሮናቫይረስ ሳይያዙ አይቀሩም ተብለው የተጠረጠሩት ኢትዮጵያውያን ከቫይረሱ ነጻ መሆናቸውን ተነገረ
በኮሮናቫይረስ ሳይያዙ አይቀሩም ተብለው የተጠረጠሩት አራት ኢትዮጵያውያን ከቫይረሱ ነጻ መሆናቸውን መረጋገጡን የጤና ጥበቃ ሚንስቴር አስታወቀ።
ከሁለት ቀናት በፊት በኮሮናቫይረስ ሳይያዙ አይቀሩም ተብለው የተጠረጠሩ አራት ኢትዮጵያውያን ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ መገኘታቸውን የጤና ጥበቃ ሚንስቴር አስታውቆ ነበር። በወቅቱ የጤና ጥበቃ ሚንስቴር ለተጠርጣሪ ህመምተኞቹ የላብራቶሪ ናሙና ተወስዶ ለምረመራ ወደ ደቡብ አፍሪካ መላኩን አስታውቆም ነበር። በዚህም መሠረት ወደ ደቡብ አፍሪካ ለተጨማሪ የላብራቶሪ ምርመራ የተላኩት የአራቱ ተጠርጣሪዎች ውጤት ከኖቭል ኮሮናቫይረስ ነፃ መሆናቸው ተረጋግጧል ተብሏል። ከአራቱ ኢትዮጵያውያን መካከል 3ቱ ቫይረሱ በተከሰተበት ዉሃን ግዛት ተማሪ እንደነበሩ ተገልጿል። በበሽታው የተጠረጠሩት ግለሰቦቹ በለይቶ ማከሚያ ማዕከል ተለይተው ክትትል እንደሚደረግላቸው በወቅቱ ተነግሮ ነበር። በአሁኑ ወቅት በቻይና አንድ ግዛት ውስጥ የተቀሰቀሰው የኮሮናቫይረስ መላ ቻይናን ማዳረሱንና በበሽታው የሞቱ ሰዎች ቁጥርም 170 መድረሱ ተነግሯል።
news-45339555
https://www.bbc.com/amharic/news-45339555
ሽጉጥ ይዘው ለመንቀሳቀስ የተገደዱት ከንቲባ
የዛምቢያዋ ዋና ከተማ ሉሳካ ከንቲባ ማይልስ ሳምፓ በፌስቡክ አድራሻቸው ላይ የለጠፉትን ሽጉጥ ይዘው የሚያሳይ ምስል ለማንሳት ተገደዋል።
''ከዚህ በኋላ ወደ ስራ ስሄድም ሆነ መስክ ስወጣ እንደዚህ ነው እራሴን የምጠብቀው። ትናንት ጥቃት ያደረሳችሁብኝ ሰዎች ማን እንደላካችሁ አውቃለሁ። ምናልባት ጥቃት ቢደርስብኝና ፖሊስ ሊደርስልኝ ባይችል እራሴን ከአደጋ እንደዚህ እከላከላለሁ'' ሲሉ ከምስሉ ግርጌ ላይ አስፍረዋል። ምስሉ ከሰውዬው የፌስቡክ ገጽ ወዲያው የተነሳ ቢሆንም፤ በርካቶች ምስሉን በተንቀሳቃሽ ስልኮቻቸው ለይ በማስቀረት እየተቀባበሉት ነው። • ያለመከሰስ ለማን? እስከምን ድረስ? ከንቲባ ሳምፓ ሽጉጡን ይዘው የተነሱትን ፎቶ በፌስቡክ ገጻቸው ላይ ለማስፈርና ሽጉጥ ይዘው ለመንቀሳቀስ የተገደዱት ከደረሰባቸው ጥቃት ጋር ተያይዞ እንደሆነ ለቢቢሲ ተናግረዋል። ጥቃቱ የደረሰባቸውም በህገወጥ መንገድ መሬት የሚሸጡና የግንባታ ህጎችን የሚጥሱ ሰዎች ላይ በከፈቱት ዘመቻ ምክንያት እንደሆነ ገልጸዋል። ከዚህ ጋር በተያያዘም ወደ አንድ የግንባታ ስፍራ አቅንተው ድርጅቱ ተገቢውን የግንባታ ፈቃድ የሚያሳይ ዶሴ እንዲያስገባ ጠይቀው ሲመለሱ ሃያ ወጣቶች በመኪና ተከታትለዋቸው ዛቻና ማስፈራራት እንዳደረሱባቸው ለቢቢሲ ገልጸዋል። • የደሞዙን 100 እጥፍ በስህተት የተከፈለው ሰው ''ለህይወቴ እየሰጋሁ ስለሆነ ራሴን የመከላከል መብት አለኝ'' ሲሉ ውሳኔያቸው ትክክል እንደነበረ ተናግረዋል። እንደውም ከዚህ በኋላ ወደ ስፖርት ማዘውተሪያዎች ጎራ እንደሚሉና የሰውነት ብቃታቸውን ለመጨመር እንዳሰቡም ጨምረው ተናግረዋል።