input
stringlengths 1
130k
⌀ |
---|
በኤኮኖሚው ረገድ በፋርስ ባህረ ሰላጤ በጋራ የሚያካሂዷቸው የነዳጅ ዘይት ሥራዎች እና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን አይወዱትም። |
ቀጠር ከሙስሊም ወንድማማቾች ማህበር ጋር ረዥም ጊዜ የዘለቀ ቅርብ ግንኙነት አላት። |
ቡድኑ በጎርጎሮሳዊው ቱ የግብጽ ምርጫ ብዙ ድምጽ ሲያገኝ ቀጠር ከካይሮ ጋር ፖለቲካዊ ግንኙነትዋን ለማጠናከር ሞክራ ነበር። |
የሳውዲ መንግሥት የሙስሊም ወንድማማቾች ማህበር ለአረብ ባህረ ሰላጤ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ስርዓት አደጋ አድርጎ ነው የሚያየው። |
በዚህ የተነሳም ቀጠር አሁን የተጠየቀችውን ሁሉ ማሟላት አስቸጋሪ ነው የሚሆንባት ይላሉ ዞንስ። |
ወይም ደግሞ ከአረብ ወንድሞቿ ጋር ጋር እንደ እስካሁኑ ጥሩውን ግንኙነት አጠናክራ ልትቀጥልም ትፈልግ ይሆናል። |
ከጥቂት ቀናት በፊት የቀጠር አምባሳደር በርሊን ውስጥ ቀጠሮች እና ሳውዲዎች በመሠረቱ አንድ ቤተሰብ ናቸው ብለው ነበር። |
በዚህ ውዝግብ ውስጥ የሚካፈሉት ወገኖች ገጽታቸውን ሳያበላሹ ከዚህ ውዝግብ የሚላቀቁበትን መንገድ ነው የሚፈልጉት። |
በዛም ሆነ በዚህ ግን ቀጠር የተጠየቀችውን ታሟላላቸው ብዮ አላስብም። |
ውይይቱ ወደ ሚካሄድበት ስፍራ ሄደው ለመግባት የጠየቁ ወጣቶችም እርሱ እንደሚለ በልዩ ፖሊስ ተደብድበው ጉዳት ደርሶባቸዋል የታሰሩም አሉ ። |
በውይይቱ ላይ ከህብረተሰቡ ለተነሱ ልዩ ልዩ ጥያቄዎች ጠቅላይ ሚኒስትሩ መልስ ሰጥተዋል። |
የትኛውንም ወረዳ እንደማይወክሉ የተናገሩት እኚሁ ነዋሪ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለህብረተሰቡ ጥያቄዎች የሰጡት መልስ ከሞላ ጎደል ጥሩ ነው ብለዋል። |
ሆኖም ጥያቄ የማቅረብ እድል አለማግኘታቸውን ተናግረው በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ አጥጋቢ መልሶች እንዳላገኙ መነሳት ነበረባቸው ያሏቸው ጥያቄዎችም እንዳልተነሱ ተናግረዋል። |
ወደ ውይይቱ አዳራሽ መግባት ተከለከልኩ የሚል ሌላው ወጣት ደግሞ የአፋር ወጣቶች ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተገኙበት ውይይት ላይ ለመካፈል ቢፈልጉም አለመጋበዛቸውን ይገልጻል። |
ውይይቱ ወደ ሚካሄድበት ስፍራ ሄደው ለመግባት የጠየቁ ወጣቶችም እርሱ እንደሚለው በልዩ ፖሊስ ተደብድበው ጉዳት ደርሶባቸዋል የታሰሩም አሉ። |
ከተጎዱት መካከል ሴቶች እና በእድሜ የገፉም እንደሚገኙበት ወጣቱ ተናግሯል። |
በርሱ አባባል ወጣቶቹ ስብሰባው እንዳይገቡ የተከለከሉት በክልሉ ያለውን ችግር ያጋልጣሉ በሚል ስጋት ሳይሆን አይቀርም። |
ዶቼቬለ ጉዳዩ የሚመለከታቸውን የክልሉን ባለሥልጣናት ለማነጋገር ያደረገው ሙከራ አልተሳካም። |
አቶ ብሩክ መኮንን በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኢትዮጵያ ልዑክ ቃል አቀባይ ናቸው። |
ባለፉት ሁለት አመታት በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በኩል የተጠኑ ጥናቶች አሉ። |
የእነዚህ ጥናቶች አፈጻጸምን በሚመለከት ነው የዚህ ስብሰባ ዋና ትኩረት። |
በአፈጻጸም ሒደቱስ መታየት ያለባቸው ጉዳዮች ምንድናቸው የሚለው ላይ ነው ይኸ ስብሰባ በዋናነት የሚያጠነጥነው። |
ከትልልቆቹ ጥቆማዎች አንዱ ትኩረቱ ከሰላም ማስከበር ወደ ሰላም የማስፈን ተልዕኮ መሻገር አለበት የሚለው ነው። |
የሰላም ማስፈን ተልዕኮ ስራ ግጭት የመከላከል እንቅስቃሴዎች የሰላም ግንባታ የድኅረ ግጭት መልሶ ማቋቋም እና የልማት ሥራን ያካትታል። |
አንዱ ፈታኝ ነገር ሰላሙን ዘላቂ ለማድረግ ምንም ሥራ ሳይሰራ ወታደሮቹ እንዲወጡ መደረጉ ነው። |
በቀውስ በተመቱ አገሮች በመንግሥታዊ አስተዳደር ውስጥ የሕግ የበላይነትን እና ሌሎች አገልግሎቶችን መልሶ ማስፈን ሌላው ችላ የተባለ ነገር ነው። |
ግጭት የነበረባቸውን አካባቢዎች ስንመለከት መላ የጸጥታ ጥበቃ እና የፍትኅ ሥርዓቶቹ ፈርሰዋል። |
ሪያና ፓኔራስ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ግጭት ባቀወሳቸው አካባቢዎች በወታደራዊ ጣልቃ ገብነት ብቻ ተወስኖ ቆይቷል ሲሉ ይተቻሉ። |
በ ገፆች የተቀነበበው ግምገማ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ የፖለቲካ ሒደትን የመደገፍ ሰፊ ሚና አንድ አካል ሊሆን ይገባል የሚል ጥቆማ ሰጥቷል። |
የተባበሩት መንግሥታት በሰላም ማስከበር ተልዕኮዎቹ መስክ ተኮር እና ሰዎችን ማዕከል ሊያደርግ ይገባል ሲልም አትቷል። |
አቶ ብሩክ መኮንን የተሰሩት ጥናቶች የተባበሩት መንግሥታት ተልዕኮዎች ከሰላም ማስከበር የዘለለ ሚና እንዲኖራቸው የታቀዱ ናቸው ሲሉ ይናገራሉ። |
ሽብር እና ድንበር ተሻጋሪ የተደራጀ ወንጀል በሰላም ማስፈን ተልዕኮ ላይ መሰረታዊ ለውጥ አምጥተዋል። |
የባለሙያዎቹ ጥቆማ እነዚህን ለመቀልበስ ሰላም ማስከበር በቀጥታ ጥቅም ላይ ሊውል አይገባም የሚል ኃሳብ አቅርቧል። |
ነገር ግን ተፅዕኖ እስካለው ድረስ አንድ ተልዕኮ ቸል ሊለው ይገባል ብዬ አላምንም። |
በዚያ የአፍሪቃ ኅብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ሰላም አስከባሪ አለ። |
የተደራጀ ወንጀል ተቃዋሚዎችን እና አል ሸባብን ወደ ወደ ፊት እየገፋቸው ነው። |
መንግሥት ይኸን ለመፍታት ደካማ በመሆኑ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ መፍትሔ ካልፈለገለት ማን ሊፈታው ነው |
ከዚህ በተጨማሪ ግጭት ከተከሰተ በኋላ ከመታገል ይልቅ ከመከሰቱ በፊት እንዴት መከላከል ይቻላል የሚለው ኹነኛ መፍትሔ ይሻል። |
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰላም ማስከበር ተልዕኮን ለማሻሻል ጠንካራ ፖለቲካዊ ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግ ሪያና ፓኔራስ ተናግረዋል። |
አምባሳደሯ የወጪ ቅነሳውን እንደ ታላቅ ስኬት ቢቆጥሩትም ተንታኞች ግን የሰላም ማስከበር ተልዕኮ መፃኢ ፈተና ጠቋሚ ምልክት አድርገውታል። |
ይሁንና ሐላፊዋ አክለዉ እንዳሉት ወባ አሁንም ከዓለም በርካታ ሕዝብ ከሚገድሉ አምስት በሽታዎች አንዱ ነዉ። |
በዚሕም ሰበብ የዘንድሮዉ የፀረ ወባ ቀን አብይ መርሕ በጣሙን የአፍሪቃ ሕፃናትን የሚፈጀዉን በሽታ ለመከላከል የሚደረገዉ ጥረት እንዲጠናከር የሚጠይቅ ነዉ። |
በኢትዮጵያ ጤና ጥበቃ ሚንስቴር የወባ መከላከያ ዘርፍ አስተባባሪ ወይዘሪት ሕይወት ሰለሞን እንዳስታወቁት የፀረ ወባ ዕለት ኢትዮጵያ ዉስጥም ተከብሮ ነዉ የዋለዉ። |
ከከሟቾቹ ከአምስት መቶ ሥልሳ ሺሕ የሚበልጡት ጨቅላ ሕፃናት ነበሩ። |
የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቬዥንና የኦሮሞ ሚድያ ኔትዎርክ ለነዚህ ተከሳሾች እንደ ልሳን አገልግለዋል ሲል የክስ ዝርዝሩ ይጠቅሳል። |
ዶክተር መረራ ከኅዳር ቀን ዓ ም ጀምሮ እስር ላይ ይገኛሉ። |
ሦስቱም ተጠርጣሪዎች ሕገ መንግሥቱንና ሕገ መንግሥታዊ ስረዓቱን በኃይል እንናስወግዳለን በማለት እንደተንቀሳቀሱ የወንጀል ዝርዝሩ ያመለክታል። |
ዶክተር መረራ በማዕከላዊ እስር ላይ እንደሚገኙ የሚናገሩት ጠበቃቸዉ አቶ ወንድሙ ኢብሳ ደንበኛቸዉ በወንጀል መቅጫ መከሰሳቸዉ ይናገራሉ። |
እሳቸዉ በሚመሩት ድርጅት ላይ የቀረበዉን ዉንጀላም መሰረተ ቢስ ክስ መሆኑን ይናገራሉ። |
ስርዓቱ የኔን ስም ተጠቅሞ ዶክተር መረራን ለመጉዳት ያሰበበት ክስ ነዉ የሚሉት ደግሞ ሦስተኛ ተከሳሽ አቶ ጀዋር መሃመድ ናቸዉ። |
አቶ ጀዋር በአምስተኛ ደረጃ ላይ ክስ የተመሰረተበት የኦሮሞ ሚድያ ኔትዎርክ ሥራ አስኪያጅም ናቸዉ። |
የኢትዮጵያ መንግሥት በተለያዩ ግዜያት ሲወነጅለን ነበር የሚሉት አቶ ጃዋር የሚመሩትን ተቋም ከክሱ ነፃ መሆኑን ይናገራሉ። |
ዶክተር መረራ እስከ ትላንትና ድረስ ክስ ሳይመሰረትባቸዉ ለ ቀናት በእስር እንደቆዩ ጠበቃቸዉ አቶ ወንድሙ ኢብሳ ገልጸዋል። |
ትላንትና የዋስትና መብት እንዲጠበቅላቸዉ ስምንት ሰዓት ላይ ቀጠሮ ነበራቸዉ። |
የኢትዮጵያ የግድግዳ ጡፍ መግቢያ ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። |
ኢትዮጵያ የቤተሰብ የበዓል አከባበር ሦስት ኢድ አልፈጥሮችን በሦስት የተለያዩ እስር ቤቶች አሳልፏል። |
ዘጋቢያችን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር ጋዜጠኛ ኻሊድ ቤት ጎራ ብሎ የበዓል አከባበሩን ተመልክቷል። |
የዜናነህ መኮንን የጤና መቃወስ ዜናነህ መኮንን ከ ዓ ም ጀምሮ ከጋዜጠኝነት በተለይም የኤሌክትሮኒክስ መገናኛ ዘዴዎችን ተለይቶ አያውቅም። |
መጀመሪያ በኢትዮጵያ ራዲዮ ቀጥሎ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን እና በራዲዮ በዝግጅቶች እና በዜና አቅራቢነት ለረጅም ጊዜ ያገለገለ አንጋፋ ጋዜጠኛ ነው። |
ወደ እስራኤል ከተሰደደ በኋላም በተለያዩ የራዲዮ የቴሌቪዥን ጣቢያዎች እና በኢንተርኔት የተለያዩ ዝግጅቶችን በማቅረብ ይታወቃል። |
በኢየሩሳሌም የዶይቸ ቬለ ተባባሪ ዘጋቢ ከሆነበት ጊዜ ጀምሮ የመካከለኛው ምሥራቅን የፖለቲካ ዲፕሎማሲን ውጥንቅጥን በመዘገብ እና በመተንተን ከፍተኛ አስተዋፅኦ አድርጓል። |
ዜናነህ ከጋዜጠኝነቱ በተጨማሪ የሁለት መጽሐፍት እና የግጥሞች ደራሲ ነዉ። |
ነጻነት የተሰኘው የበኩር ስራው በጣሊያን የአምስት ዓመት የወረራ ወቅት የነበረውን ጦርነት የሚያሳይ ታሪካዊ ልቦለድ ነው። |
በሁለተኛ መጽሐፉ ከጣራው ስር ደግሞ የአዲስ አበባን ድብቅ የማህበራዊ ህይወት በልቦለድ ከሽኖ አቅርቧል። |
ጋዜጠኛው ከጎርጎሮሳዊው ጀምሮ የዶይቸ ቬለ የአማርኛው ክፍል የጣቢያ መክፈቻ እና በዝግጅቶች መግቢያነት የሚጠቀምባቸው ማስተዋወቂያዎች አንባቢም ነዉ። |
እውቁ ጋዜጠኛ ከጥቂት ወራት በፊት የገጠመው የኩላሊት ሕመም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ መጥቷል። |
ዜናነህ ሁለቱም ኩላሊቶቹ አገልግሎት መስጠት ማቆማቸውን ሐኪሞቹ የነገሩት ከጥቂት ወራት በፊት ነበር። |
ከኩላሊቶቹ ቢያንስ አንዱ በንቅለ ተከላ ካልተቀየረ የጤንነት ሁኔታው አሁን ካለበትም ሊከፋ እንደሚችልም አስጠንቅቀውታል። |
ስለ ጋዜጠኝነት ህይወቱ ስለ መጽሐፍቶቹ የህዝቡን እርዳታ ስለጠየቀበት የኩላሊት ህመሙ አውግቶናል። |
የኢትዮጵያውያን ውይይት በፓሪሱ የኢትዮጵያ ኤምባሲ በፈረንሳይ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ጋር በተካሄደ ውይይት ጥሪውን ያስተላለፈው ኤምባሲው ዜጎችን ለማገልገል ዝግጁ መሆኑንን አስታውቋል። |
ፈረንሳይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በተለያዩ ዘርፎች ሀገራቸውን ሊያግዙ እንደሚገባ ተጠየቀ። |
ቡድኑ ወደኢትዮጵያ የገባው በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ጋባዥነት ሲሆን በዚህ አጋጣሚም ህክምና አከናውኗል። |
ቡና ፈላጊዉ ዓለም በተለይ በተፈጥሮ መንገድ ለሚያድገዉ የጫካ ቡና የሰጠዉ ትኩረት የኢትዮጵያን ደን ከዉድመት ይታደገዉ ይሆን |
በዓለማችን የጫካ ወይም ወፍ ዘራሽ ቡናን የሚያመርቱ ሃገራት ሶስት ብቻ ናቸዉ። |
ከእነዚህ ሃገራት አንዷ ደግሞ በሀገር በቀል የተፈጥሮ ደን ዉስጥ ይህን ቡናዋን በማብቀል ትታወቃለች። |
ይህችዉም ቡናን በዉድ ዋጋ ለጠጪዎች ማቅረቡን የሚያዉቅበት ዓለም በኩራት ጠቀም ባለ ገንዘብ የሚቸበችበዉ አረቢካ የተሰኘዉ ቡና መገኛ ምድር ኢትዮጵያ ናት። |
በመቶ የሚሆነዉ የተፈጥሮ ደን በእርሻ ሥራ ማስፋፊያ በሰዎች መኖሪያና በሰፈራ እንቅስቃሴዎች እንዳልነበር ሆኗል። |
በአሁኑ ወቅት ካለዉ የደን ሀብት በመቶዉ የሚገኘዉ በኦሮሚያ መስተዳድና አካባቢዉ ነዉ። |
ጄፍሪ ያነጋገራቸዉ የጃፓን ዓለም አቀፍ ትብብር ተቋም አማካሪ እንደሚሉት አማራጭ አጥቶ እንጂ ሕብረተሰቡ የደን ሀብቱን በመንከባከብ ሊያገኝ የሚችለዉን ጥቅም አልዘነጋዉም። |
ቡናዉ በዓለም ገበያ እዉቅና አግኝቶለት ኑሮዉን የሚያሻሽልበት አማራጭ ሲቀርብለት መተባበሩም ይህንኑ አመላካች ነዉ። |
ይህም ገበሬዎቹ ለዓለም ገበያ ለሚያቀርቡት ቡና ጥራት ትልቅ ዋስትና ነዉ። |
እንደዘገባዉ ጃፓኖች በፈጣን ባቡሮቻቸዉ ለሚጓዙ መንገደኞች ይህንን ከጅማ ዞን የተፈጥሮ ደን ዉስጥ የበቀለ ቡና ማቅረብ ከጀመሩ አራት ወራት ተቆጥረዋል። |
በዓለም ገበያ እጅግ ተፈላጊ የሆነዉ ወፍ ዘራሹ የጫካ ቡና ህልዉና እንዲቀጥልም የተፈጥሮ ደኑን መጠበቁ አማራጭ እንደሌለዉ ነዉ ግልፅ የሆነዉ። |
ሆኖም ከሽያጩ ያገኙት ከበፊቱ የተሻለ ገቢ ትርጉም ሳይኖረዉ የቀረ አይመስም። |
ምንም እንኳን አንዳንዶቹ አሁንም ያገኙት ገቢ የእነሱን ወገብ በጣሽ ልፋትና የፈሰሰ ላብ እንደማያካክስ በግልፅ ቢናገሩም። |
በዚህ መልኩ እንቅስቃሴዉ ተጠናክሮ የኢትዮጵያ የጫካ ቡና ልዩ ሆኖ በዓለም ገበያ ሲቀርብም ደንን ከመራቆት መታደግ መቻሉም ትልቅ ግምት ይሰጠዋል። |
ማብራሪያ በመስጠት የተባበሩንን የኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ አራርሳ ረጋሳን ከልብ እናመሰግናለን። |
የደመራ በዓል አከባበር በጀርመን እንደ ብዙዎች ግምት በዚህ ክብረ በዓል ከ በላይ ሰዉ ነበር የተገኘዉ። |
በዚህ ዝግጅታችን በፍራንክፈርት እጅግ በርካታ ኢትዮጵያዉያን የተገኙበትን የደመራ በዓል ቃኝተን በአሁኑ ወቅት በአዉሮጳ ብሎም በጀርመን ስላለዉ የስደተኝነት ቀዉስ እናያለን። |
በየዓመቱም የከተማዉ ከንቲባ አልያም ሌሎች ከፍተኛ የጀርመን ባለስልጣናት በክብር እንግድነት ይጋበዙበታል። |
ዘንድሮ የፍራንክፈርቱ ደመራ በዓል ላይ በክብር እንግድነት የተጋበዙት አዲስ ተሾመዉ የኢትዮጵያ ቆንስላ ጀነራል ምህረትዓብ ሙሉጌታም ነበሩ። |
ከቀኑ አስር ተኩል ሲሆን ምዕመናኑ ትልቁን ደመራ ከበዉ ዘማሪዎች ልብሳቸዉን ለብሰዉ ደመራዉ በተደመረበት ሰፊ ሜዳ ላይ ተሰበሰቡ። |
ክብረ በዓሉም በፍራንክፈርት ደብረ ፀሐይ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስትያን አስተዳዳሪ በአባ ኃይለመለኮት ተስፋ ማርያም በይፋ ተጀመረ። |
በፍራንክፈርት ደግሞ በየዓመቱ እንደዚሁ ከ ዓመት ጀምሮ በታላቅ ነዉ የሚከበረዉ። |
በመጀመርያዎቹ ዓመታት የጀርመን ከፍተኛ ባለስልጣናት የፍራንክፈርት ከተማ ምክት ከንቲባ እየመጣ አብሮን አክብሮአል። |
የደመራዉም አከባበር ልክ እንደ ሀገራችን ነዉ ደስ ይላል ሕዝቡም ደስተኛ ነዉ። |
በአባ ኃይለ መለኮት በጀርመን ብሎም በአዉሮጳ የወቅቱ ያለዉን የስደት ቀዉስ በተመለከተ ቤተ ክርስትያኒቱ ምዕመኑ ሁሉ ስለ ችግሩ እንደሚያስብ እንደሚፀልይ ተናግረዋል። |
ሁላችንም አይተናል ሰምተናል በተለይ በመካከለኛዉ ምሥራቅ ያለዉ ችግር በሶርያ በአፍጋኒስታን በኤርትራ እንደዚሁ ከባድ የስደት መከራ ነዉ ያለዉ። |
ጀርመኖችም ሁኔታዉ የሁለተኛዉን ዓለም ጦርነት ያስታዉሳል ነዉ የሚሉት በቤተ ክርስትያናችን እንፀልያለን። |
በአሁኑ ጊዜም ከአዉሮጳ ሀገራት በበለጠ ስደተኞችን የምትቀበለዉ ጀርመን ናት። |
Subsets and Splits
No community queries yet
The top public SQL queries from the community will appear here once available.