input
stringlengths 1
130k
⌀ |
---|
ዛሬ በድጋሚ በተዋቀረው ካቢኔ ውስጥ በተለያየ ዘርፍ የዶክተርነት ማዕረግ ያላቸው ሚኒስትሮች እንደተካተቱ የተገለጸ ሲሆን ሁለት ፕሮፌሰሮችም ቦታ አግኝተዋል፡፡ |
የሰማያዊ ፓርቲው አቶ ይልቃል የቀደመው ካቢኔ ሲጸድቅ ማስተርስ ያላቸው እና የተማሩ እየተባለ የትምህርት እና የትምህርት ልምዳቸው ሲነገር እንደነበር ያስታውሳሉ፡፡ |
የኢህአዴግ አብዮታዊ ዲሞክራሲ እና ጥፍንግ ያለ የማዕከላዊነት አመለካከት እስካልተለወጠ ድረስ የግለሰብ መቀየር ምንም ዓይነት ለውጥ አያመጣም ይላሉ፡፡ |
ሁለቱም የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች ኢትዮጵያ ያለችበት ወቅታዊ ችግር የሚፈታው በሚኒስትሮች መለዋወጥ ሳይሆን ኢህአዴግ መሰረታዊ እና የፖሊሲ ለውጥ ሲያደርግ ነው ይላሉ፡፡ |
ሳይንስ እና ኅብረተሰብ የህዋ ሳይንስ በኢትዮጵያ የሕዋ ሳይንስ እየረቀቀና እየመጠቀ እንደሄደ ብዙዎች ያምናሉ። |
ኢትዮጵያ በጠፈር ሳይንስ ከአፍሪካ ስድስተኛ ሀገር ሆናለች ወደ ህዋ የምትመጥቀዉ ሳተላይት የምንኖርበትን አካባቢ የምድር ገፅታን የሚያመለክቱ መረጃዎችን ወደ ምድር ትልካለች። |
የከፋ ዞን ጥብቅ የተፈጥሮ ደን በተፈጥሯዊ መስህብነት በዩኔስኮ ተመዝግቧል ራድዮ ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። |
ኢትዮጵያ የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የአምቦ ጉብኝት አዲሱ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ ር አብይ አህመድ አምቦን ዛሬ ጎበኙ። |
የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የአምቦ ጉብኝት አዲሱ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ዛሬ የረፋድ ውሏቸውን በአምቦ ከተማ አድርገዋል፡፡ |
ከአዲስ አበባ በስተ ምዕራብ ኪሎ ሜትር የምትርቀው የአምቦ ከተማ ነዋሪዎች የጠቅላይ ሚኒስትሩን ንግግር ለማድመጥ ማልደው ወደ አምቦ ዩኒቨርስቲ ስቴድየም ተምመዋል፡፡ |
በሀገር ባህል ልብሶች ያጌጡ እና የዶ ር አብይ ምስሎች የታተሙባቸው ካኔቴራዎችን ለብሰው ወደ ዝግጅቱ ቦታ ሲሄዱ የታዩም ነበሩ፡፡ |
ለጠቅላይ ሚኒስትሩ አቀባበል ለማድረግ በተሸሞነሞኑ ፈረሶቻቸው ሆነው ወደ አደባባይ የወጡ በርካታ ፈረሰኞች እንደነበሩ የከተማይቱ ነዋሪዎች ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል፡፡ |
ከፈረሰኞቹ ውስጥ በአምቦ ዙሪያ ካሉ አካባቢዎች ጭምር የመጡ እንደሚገኙበት ገልጸዋል፡፡ |
ለዶይቼ ቬለ አስተያየታቸውን የሰጡ አንድ የከተማይቱ ነዋሪ ህዝቡ በብዛት የወጣው ለጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ተጨማሪ የቤት ስራ ለመስጠት ነው ብለዋል፡፡ |
አምቦ እና አካባቢዋ ከሶስት አመታት በላይ ጠንካራ ተቃውሞ ከታዩባቸው የኦሮሚያ ከተሞች ቀዳሚዎቹ ናቸው፡፡ |
ለዚህም ይመስላል ከተሾሙ ገና ሁለተኛ ሳምንታቸውን እንኳ ያልደፈኑት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ከቀዳሚ የስራ ጉብኝታቸው ስፍራዎች አምቦን ያካተቱት፡፡ |
ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻ ወደ ሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ሲጓዙ እንዳደረጉት ሁሉ በአምቦ ጉዟቸውም ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትን አካትተዋል፡፡ |
በስነ ስርዓቱ ላይ የታደሙት የአምቦ ዩኒቨርስቲ መምህር ኩማ ዴቢሳ ንግግሮቹን በጥሞና ከተከታተሉት አንዱ ናቸው፡፡ |
አቶ ለማ ዛሬ የመጣነው እንደከዚህ ቀደሙ እሳት ለማጥፋት ሳይሆን ተስፋን ለመናገር ነው ማለታቸውን ይጠቅሳሉ፡፡ |
የአቶ ደመቀ ንግግር ቀድሞ ሲያሰሙት ከነበረው የተለየ እንደነበር የሚናገሩት የዩኒቨርስቲው መምህር ከታዳሚው ጥሩ ድጋፍ ማግኘታቸውን ገልጸዋል፡፡ |
በስተመጨረሻ ንግግር ለማድረግ መድረኩን የተረከቡት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ለታዳሚው ሰላምታ ሲያቀርቡ ህዝቡ በሆታ እና በፉጨት አጅቧቸዋል፡፡ |
ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደሌሎቹ ተናጋሪዎች ሁሉ ቄሮ በሚል ስያሜ የሚጠሩትን የኦሮሞ ወጣቶችንም አንስተዋል፡፡ |
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ በንግግራቸው የክልሉን ፕሬዝዳንት እና የምክትላቸውን መልዕክት አስተጋብተዋል፡፡ |
አምቦ ከዚህ በኋላ የቱሪዝም የባህል እና የፖለቲካ ማዕከል ትሆናለች፡፡ |
ለሦስት ቀናት በግብፅ ተካሄደ ዓለም ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። |
በስደት ሊኖሩበት ከተመኙ እስኪደርሱ የብራስልስ መናፈሻ ቤታቸው ሆኗል እግሮቹ በቤልጂግ መዲና ብራስል ጎዳናዎች ላይ ሲመላለሱ አይታክታቸውም አንዳች ግብ አላቸውና። |
ልቡ ግን በብዙ ሺህ ኪሎ ሜትሮች ርቀት ኢትዮጵያ ከእናታቸው ጋር የሚገኙት ሁለት ሕጻናት ልጆቹ ጋር ቀርቷል። |
የተመድ ኛ ዓመት በዓለም ዓቀፉ ማኅበረሰብ ትንታኔ የዓለም መንግስታትን በአንድነት እንደሚያስተሳስር የሚነገርለት የተመድ ዘንድሮ ኛ ዓመቱን ትናንት አከበረ። |
ከ ዱ አባል አገራት አንዷ በሆነችዉ ኢትዮጵያ መዲናም ዛሬ የድርጅቱ ምስረታ ኛ በዓል ታስቦ ዉሏል። |
በዓለም የስደተኞች ቁጥር ማሻቀብ እና በፈረንሳይ የስደተኞች የምግብ ዝግጅት ፌስቲቫልን የተመለከቱ ዘገቦችም አሉን። |
ይድረስ ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መቼም ለጤናዎት እንደምን አሉ ብዬ አልጀምር ነገር የአካል ደህንነትዎን እያየሁት ነው፡፡ |
የመንፈስዎን ደግሞ መገመት ይቻላል ኢትዮጵያን የሚያህል ሀገር ከመቶ ሚሊዮን ህዝብ ጋር መምራት ከባድ እንደሆነ ለመረዳት አይቸግርም፡፡ |
ክቡር ሆይ እርስዎ ወደዚህ መንበር ከመጡ በኋላ ሀገራችን ብዙ ተስፋ የጫሩ ሥራዎች ተከናውነዋል፡፡ |
በዚህም በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና አግኝተውበት የ የሰላም ኖቤል ተሸላሚ ሆነዋል፡፡ |
እኔ እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ሽልማቱ መቶ በመቶ ይገባዎታል ብዬ የማምን ዜጋ ነኝ፡፡ |
በእኔ ምልከታ በብዙ ፈተና ውስጥ እያለፉም ቢሆን ብዙ ውጤቶችን በማስመዝገብዎት ትልቅ እውቅና እሰጣለሁ፡፡ |
በሀገራችን የህግ የበላይነት ባለመከበሩ ከዕለት ወደ ዕለት የዜጋው ሰላም ውሎ መግባት ጥያቄ ውስጥ ሲወድቅ ማየት በእጅጉ የሚረብሽ ጉዳይ ነው፡፡ |
በእርግጥ ብዙዎቻችን ነገሮችን የምንመለከተው በተናጠል በመሆኑ መፍትሔው ቀልሎ ቢታየንም ሀገር መምራት የብዙ ዘርፎች ድምር ውጤት ነውና ሊከብድ እንደሚችል መገመት ይቻላል፡፡ |
ለመሆኑ ሰሞኑን የተከሰተው ግጭትና የሰዎች ህልፈት መነሻው ከወዴት ይሆን |
በሚዲያ ዘራፍ ያዙኝ ልቀቁኝ ባይነታቸው በሁሉም የኢትዮጵያ ክልል ውስጥ እንደገባ ወረርሽኝ ከዳር ዳር እየተስተጋባ ይገኛል፡፡ |
ይህ ሁሉ ሲሆን ተው የሚል አካል ባለመኖሩ ይኸው እሳቱ እየፈጀን ይገኛል፡፡ |
ስለዚህ መንግስት የህግ የበላይነትን ማስከበር ባለመቻሉ ሃገር እየታመሰች እንደሆነ አውቆ ለነገ በማሰብ መንቀሳቀስ ዋና ሥራው እንደሆነ ሊታሰብበት ይገባል፡፡ |
የዚህ ችግር መፍትሔ በመራቁ አሁንም መንግስትንና ህዝብን ንቀው የሚንቀሳቀሱ አካላት በአራቱም ማዕዘናት ማየት የተለመደ ነው፡፡ |
በሌሎቹም ዘርፎችም እንዲሁ አዎንታዊነቱንና አሉታዊነቱን እያነሱ ብዙ ማለት ይቻላል፡፡ |
ጉዳዩ የእርስዎን ያላሰለሰ የሰላም ጥረትና ከጠረጴዛ ዙሪያ ውይይት በኋላ የሚደረግ ውሳኔ ይጠብቃል፡፡ |
እነዚህም ቡድኖች የሞቱለትን ዓላማ ዘንግተው በተቃራኒው ጎራ በመቆም ሰውን የሚያህል ክቡር ፍጥረት በድንጋይ ወግረው እስከ መግደል እየደረሱ ነው፡፡ |
ግን አሁን የእርስዎ ዘመን ነውና በሚዲያ ወጥቶ የእንባ አድርቅ ቃላት የሚወረውር አንድ የፌደራል ባለሥልጣን መጥፋቱ ለምን ይሆን አስብሎናል፡፡ |
ሀሳብዎት ገዢ በመሆኑ አለመደገፍ ባንችልም ሃሳብዎትን ለማስፈፀም የሚችሉበትን ሜዳ እያጠበቡት መመልከታችን ያሳስበናል ከዚያም አልፎ ሀገራችን ነችና ያገባናል፡፡ |
ከዕለታት አንድ ቀን አዕዋፋት ተሰብስበው እያደኑ ስለሚይዟቸው ጠላቶቻቸው ይወያያሉ አሉ፡፡ |
በዚህም መሠረት የተለያዩ አዕዋፋት ለምርጫ ቀረቡና በከፍተኛ ድምጽ የተመረጠችው ቆቅ ሆነች፡፡ |
እናንተን እወክል ዘንድ ስለመረጣችሁኝና ዕምነታችሁን ስለጣላችሁብኝ ከልብ የመነጨ ምስጋናዬን አቀርባለሁ፡፡ |
ሆኖም ካለመሳተፍ መሳተፍ የበለጠ ጥቅም ይኖረዋልና እናንተን መስዬ እናንተን አክዬ እና እናንተን ሆኜ ለመቅረብ ዝግጁ ነኝ፡፡ |
ኛው እነሱን አለመናቅና ሊበልጡኝ የሚችሉበት አንዳንድ ጉዳይ እንደሚኖር ማመን ነው፡፡ |
ይኸውም ቆቅ ቆቅ የሚለውን ስሟን ይዛ የትም አትደርስም የሚል ዕምነት ነው ያለኝ፡፡ |
ማን እንበላት ካላችሁም እኔ ዋ ኔ የሚል ስም ቢሰጣት መልካም ነው እላለሁ አለች፡፡ |
እርግብም ቀጥላ አሁን የሚያዋጣን ዛሬ ከባላንጦቻችን መወዳጀት ነው አለች፡፡ |
እያንዳንዱ ድል አንድ አንድ ጠላት እንደሚወልድ አትርሳ ይላሉ ፀሐፍት፡፡ |
ስለዚህም አሸነፍኩ ብሎ ዘራፍ ማለት ከመሸነፍ አንድ የሚሆንበት ጊዜ አለ፡፡ |
ድልን በማጭበርበር የምንቀዳጅ ከሆነም ዕድሜ ልካችንን እንቅልፍ እንዳይወስደን ያደርገናል፡፡ |
ደራሲና ፀሐፌ ተውኔት ፀጋዬ ገ መድህን በአንደኛው ቴያትሩ እንዳለው አብዮትኮ ኳስ ጨዋታ ነው፡፡ |
አቀበለ ተቀበለ ይዞ ሄደ መታ ፎሪ ወጣ አብዮቱ ከሸፈ ይባላል ወይም ቀጥሎ ደግሞ ይዞ ሄደ |
መቼ እንደምናቀብል መቼ ወደፊት እንደምንሄድ መቼ አብዶ ምሣ እንደምንሠራ ካላወቅን ፖለቲከኛ መሆን አንችልም፡፡ |
የጐጃም ትውልድ በሙሉ ከአባይ እስከ አባይ በሚለው መጽሐፉ ደራሲ ግርማ ጌታኹን እንዲህ ይላል ወለተ አልፋ አመተ አልፍን ወለደች፡፡ |
እርሱ ግን የውርጭ ድደን ጥርሱን ገጥሞት መናገር ቸግሮት ነበርና ከዛፉ አውርደው ፀሐይ ቢአሞቁት ዘመድ ላይ ከጃራ ሹም የመጣሁ ነበርሁ፡፡ |
የዚህ ጊዜ እናትና ልጆች የኔ ባል ይሁን የኔ ባል ይሁን ተባባሉበት፡፡ |
ተያይዘው ከዲማ መነኮሳት ከነአባ ተጠምቀ መድኅንና ከነአባ ዮሐኒ ዘንድ ለፍርድ ሄዱ፡፡ |
እኒያም ሲፈርዱ አንች ባል አግብተሺ ቤት ሠርተሺ እርስዋን ወልደሻል፡፡ |
አንች ብታገኝ አግቢ ብታቂ መንኩሺና ተቀመጪ ብለው ፈረዱ ይባላል፡፡ |
ድፍረትን ከሀፍረት ሳንነጥል የምናይበት ዐይን ይስጠን በተለይ በምርጫ ወቅት፡፡ |
ዘራፍ ማለት አለሁ አለሁ ማለት ያለ እኔ ማን አለ ማለት ካለፈው አለመማር ከመርገምት ሁሉ የከፋ መርገምት ነው፡፡ |
ምንጊዜም ቢሆን የሚባለው ነብር ከጓዳ ሳይወጣ የሚበላው ፍየል ተክለፍልፎ መጣ የሚለውን አገርኛ ግጥም አንርሣ |
ኢትዮጵያ የአስቸኳይ ግዜ አዋጁና የኦሮሚያው ተቃዉሞ ለ ወር የዘለቀው የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ ሊጠናቀቅ ጥቂት ቀናቶች ይቀሩታል። |
የአዋጁን አፈፃፀም በበላይነት የሚከታተለዉ ብሔራዊ ኮማንድ ፖስት መቋቋሙም ይታወቃል። |
አቶ ሲራጅ ለላፉት ወራቶች ሲተገበር የነበረዉ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በአገሪቱ ሠላም እና ፀጥታ መማምጣት ችለዋልም ብለዋል። |
በባቱ ከተማ ብዙ ሱቁች መዘጋታቸዉንና የማህበረሰቡ ብሶት ከግብር ዉጭ እንደሆነም ጠቅሰዋል። |
በዚህ ክልል ዉስጥ ያለዉ ማህበረሰብ ከመንግስት ምንም ነገር እየጠበቀ አይደለም። |
የአስቸኳይ ግዜ አዋጁ ጥሩ ዉጤት አስገኝተዋል የሚሉት ለራሳቸዉ እንጅ ለሕዝቡ አደገኛ አዋጅ ነዉ። |
በኦሮሚያ ያለዉ ሠላምና ፀጥታ በተሻሻለ ሁኔታ ላይ እንደምገኝ አቶ አዲሱ አረጋ ተናግረዋል። |
በተወሰኑ ቦታዎች የተከሰተዉን መጠነኛ ክስተት ወስዶ አዋጁ ይራዘማል አይራዘምም የሚል ድምዳሜ መዉሰድ ግን ያሳስታል ብለዋል። |
ወደ መቐለ ይደረጉ የነበሩ በረራዎች በኮሮና ሳቢያ ቀነሱ በኢትዮጵያ በኮረና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ለበዓልና ዕረፍት ይደረጉ የነበሩ በረራዎች እየተስተጓጎሉ ይገኛሉ፡፡ |
ኃላፊው ሙሉ በሙሉ ትምህርት ቤቶች የፈረሱባቸው አካባቢዎች አሉ ብለዋል ራድዮ ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። |
ኢትዮጵያ የተቃዉሞ ሰልፎችና አስተያየት በኢትዮጵያ ከተሞች የተቃዉሞ ሰልፎች መካሄድ ከጀመረ ሰነባበተ። |
በኦሮምያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ከወራት በፊት የተቀሰቀሰዉ ተቃዉሞ እየበረደ ዳግምም እያገረሸ ቀጥሏል። |
ተቃዉሞ ጎንደር ባለፈዉ እሁድ በታላቅ ሕዝባዊ ሰልፍ ብትጥለቀለቅም አጀማመሩም አፈፃጸሙም ሰላማዊ እንደነበር ተነግሮላታል። |
የፊታችን እሁድ ባህር ዳር ከተማ ላይ ሰማያዊ ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ መዘጋጀቱን ያረጋገጡት አቶ አዲሱ በበኩላቸዉ የሰልፉን አላማ ዘርዝረዋል። |
ትራምፕ ስደተኞችን በግንብ ሙስሊሞችን በመግቢያ ፍቃድ ለማገድ ሲዝቱ የፓኪስታኑ ሙስሊም ስደተኛ ልጅ ሳዲቅ ካሕን የለንደን ከንቲባ ሆኑ። |
ለዶናልድ ትራፕ ግን ዉሳኔዉ በዘር ቀለም ሐይማኖት ጥላቻ ከተሞላ መርሐቸዉ ጋር መጣጣሙ አጠራጣሪ ነዉ። |
የመካከለኛዉ ምሥራቅና የምሥራቅ አዉሮጳ ትናንሽ ሐገራት በደቡባዊ አሜሪካዊቱ ትልቅ ሐገር ትልቅ ፖለቲካዊ ቀዉስ ለመደሰት ማዘናቸዉ ፖለቲካዊ ምክንያት የላቸዉም። |
የብራዚል ፖለቲካዊ ቀዉስ መነሻ ዉስጣዊና ዉጪያዊ ምክንያቱማጣቀሻ እድምታዉ መድረሻችን ነዉ። |
ከ ዎቹ ማብቂያ እስከ ዘመኑ በሙሉ እንደ ጎርጎሪያኑ አቆጣጠር ነዉ ድረስ በምጣኔ ሐብት በፍጥነት በማደግ ከዓለም ቻይናን አስቀድማ ትከተል ነበር። |
የተፈጥሮ ሐብቷን ብዛት አይነት ዉበት ሥብጥሩን መዘርዘር ሲበዛ አታካች ነዉ። |
የሐገሬዉ አንጡራ ተወላጅ ጉልበት ለአዉሮጳዉያኑ ሠፋሪዎች ባለመብቃቱ ወይም ባለማርካቱ የሠፋሪዎቹን ፍላጎት ለማሟላት ጥቁር አፍሪቃዉያን በባርነት በገፍ በግፍ የተጋዙትም ያኔ ነበር። |
ይሁንና ፌርናንዶ ኮሎር ከሁለት ዓመት በላይ ሥልጣን ላይ አልቆዩም። |
በሙስና ተጠርጥረዉ የሐገሪቱ ሕግ መምሪያ ምክር ቤት ኮንግረስ እንዲከሰሱ ወሰነባቸዉ። |
ዉሳኔዉን ሕግ መወሰኛዉ ምክር ቤት ሴኔቱ እንደሚያጸድቀዉ ሲያዉቁ ሥልጣናቸዉን በፈቃዳቸዉ ለቀቁ። |
በ ኛ ዓመቱ ዘንድሮ ተራዉ በሉላ ደ ሲልቫ ጠንካራ ድጋፍ ሥልጣን የያዙት የግራ ፖለቲከኛዋ የዲልማ ቫናሮዉሴፍሆነ። |
ፕሬዝደንቷ በሕግ መወሰኛዉ ምክር ቤት ክስ ይመሥረትባቸዉ የሚለዉን ሐሳብ ከምክር ቤቱ አባላት ቱ ደግፈዉታል። |
ሮዉሴፍ የምክር ቤቱን ዉሳኔ ዘመናይ መፈንቅለ መንግሥት በማለት አዉግዘዉታል። |
የተያዘባቸዉን ሥልጣንን አለ አግባብ የመጠቀም ክስ ዉድቅ ለማድረግም እስከ መጨረሻዉ ድረስ እንደሚከራከሩም አስታዉቀዋል። |
ይሁንና ምክር ቤቱ የወሰነዉን እንዳይወስን የሐገሪቱ ሕገ መንግሥታዊ ፍርድ ቤት እንዲያግደዉ የፕሬዝደንቷ ጠበቆች ያቀረቡትን ማመልከቻ ፍርድ ቤቱ ዉድቅ አድርጎታል። |
Subsets and Splits
No community queries yet
The top public SQL queries from the community will appear here once available.