input
stringlengths 1
130k
⌀ |
---|
እንደ ጥናቱ ከሆነ በ ሀገራት ለበሽታው የመጋለጥ አደጋ የተደቀነበት ህዝብ ቢሊዮን ይሆናል። |
ከዓለም ህዝብ ግማሽ ያህሉን ሊያጠቃ ይችላል የሚባልለት ይህ በሽታ ዴንጊ ፌቨር ይባላል። |
በጎንደር ዩኒቨርስቲ በሜዲካል ማይክሮ ባዮሎጂ ትምህርት ክፍል መምህር የሆኑት አቶ ጌታቸው ፈረደ ስለበሽታው ምንነት ያስረዳሉ። |
ትኩሳት በዋናነት ሆኖ ማንቀጥቀጥ የመገጣጠሚያ ቦታዎች ህመም ማቅለሽለሽ ይኖራል ። |
እነዚህ ደግሞ በወባም በሌሎችም በሽታዎች የሚታዩትን ነው እርሱም የሚያሳየው እና ብዙም በምልክት መለየት ከባድ ነው አይቻልም። |
ከሦስት ዓመት በፊት በተደረገ ጥናት ይህ ቁጥር በሦስት እጥፍ ጨምሮ ተገኝቷል። |
የዓለም ጤና ድርጅትን የመሳሰሉ ተቋማትን እያሳሳባቸው ያለው የቁጥሩ እንዲህ በፍጥነት መመደንግ ብቻ ሳይሆን ከዚህ ቀደም በሽታው ወዳልታየባቸው ሀገራት መስፋፋቱ ነው። |
ከዓመታት በፊት በሽታው አይደለም በኢትዮጵያ በአፍሪካ ደረጃም ይሄን ያህል የሚወራለት አልነበረም። |
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን በሽታው በአህጉሪቱ እዚህም እዚያም ይታይ ይዟል። |
የዛሬ ሁለት ዓመት በቡርኪናፋሶ በተቀሰቀሰ የዴንጊ ወረርሽኝ ከአንድ ሺህ የሚልቁ ሰዎች በበሽታው ተጠቅተዋል ተብሏል። |
በኢትዮጵያም በተመሳሳይ ወቅት በድሬዳዋ እና ሶማሌ ክልል ወረርሽኞች መከሰታቸውን የናሙና ምርመራ ውጤቶች አመላክተዋል። |
እኔ እንዳየሁት ወረርሽኝ ተነስቶ በጣም ከፍተኛ ትኩሳት ያለባቸው በሽተኞችን ሪፖርት ተደረጉ። |
ሪፖርት ሲደረግ እዚያ ከድሬዳዋ ላይ ምክንያታቸው ያልታወቁ ግን ብዙ በሽተኞች ታመዋል። |
ወባን ጨምሮ ታይፎይድ የሎው ፊቨር አይነት ብዙ በሽታዎችን መርምረዋል። |
ያ ነው እንግዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ሪፖርት የተደረገው ሲሉ የጥናቱን ውጤት ያስታውሳሉ። |
የጎንደር ዩኒቨርስቲው መምህር በሌሎች በሽታዎችን ላይ ከባልደረቦቻቸው ጋር ጥናቶች ባደረጉባቸው የመተማ እና ሁመራ አካባቢዎችም ተመሳሳዩን አስተውለዋል። |
ወባም ከሌለ ከዚህ በፊት ካደረግነው ጥናት እዚያ አካባቢ በብዛት የሚገኙት እንደ ካላዛርም ከሌላቸው ከዚህ ተነስተን ምን ሊሆን ይችላል |
የእነ አቶ ጌታቸው ጥናት ውጤት እንደሚያመለክተው በመተማ ከተመረመሩት ናሙናዎች መካከል አርባ በመቶው የዴንጊ ፊቨር ተገኝቶባቸዋል። |
ዘጠኝ አጥኚዎች የተሳተፉበት ይህ ጥናት በግንቦት ዓ ም በሳይንስ መጽሔቶች ጆርናሎች ላይ ታትሟል። |
አጥኚዎቹ ጥናቱን በሚያካሂዱበት ወቅት ካስተዋሉት ነገር አንዱ ዴንጊ ፊቨር በበሽታነት እንኳ ያለመታወቁ እውነታ ነው። |
አካባቢው ላይ ቃለ መጠየቅ ስናደርግ ዴንጊ ምናምን ስንል ሙያተኞቹ ጭምር ምንድነው ይሄ በሽታ ሲሉ ነበር። |
እና ሙሉ ለሙሉ እንደዚህ አይነት የለም ተብሎ ነበር የሚታወቀው ሲሉ በአካባቢው የተመለከቱትን ያጋራሉ። |
የእስያ እና የደቡብ አሜሪካ በሽታ ይባል የነበረው ዴንጊ ፊቨር በአፍሪካ ሊያውም በኢትዮጵያ እንዴት ሊገኝ ቻለ |
በሚል የተጠየቁት አቶ ጌታቸው ምክንያቱን በትክክል ለማወቅ ተጨማሪ ዝርዝር ጥናቶች ያስፈልጋል የሚል ምላሽ ይሰጣሉ። |
በሽታው በጎረቤት ሀገራት ጭምር እንደታየ የሚናገሩት ጥናት አድራጊው ምክንያቶች ሊሆኑ ይችላሉ ያሏቸውን ያስቀምጣሉ። |
በአሁኑ ጊዜ ከአየር ንብረት ለውጥ እና ከከተሞች መስፋፋት ጋር ተያይዞ እንደ ወባ ትንኝ አይነት የበሽታ አምጪ ተዋህሲያን በቀላሉ እንዲራቡ ያደርጋል። |
ለምሳሌ በአሁኑ ጊዜ ያው በኢትዮጵያ ውስጥ ከተሞቹ እየተስፋፉ ነው። |
ከእነኚህ መስፋፋት ጋር ተያያዞ በቀላሉ እርጥበት ውሃ የመሳሰሉ ለወባ ትንኞች መራቢያ ምቹ ነገሮች ይፈጥራል። |
እነኚህ ዴንጊ ፊቨር የሚባለው በሽታ አምጪ ተዋህሲያን በቀላሉ እንዲራቡ የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎችን ይፈጥራል። |
እና በዚያ በተባሉት ቦታዎች ላይም የአየር ንብረቱም ቆላማ ነው። |
ለወደፊቱ ደግሞ ምንድነው ምክንያቱ የሚለውን ደግሞ ቀጥለን የምናጠናው ይሆናል ይላሉ። |
በዴንጊ ፊቨር ላይ የሚደረገው ቀጣዩ ጥናት አሁን በመካሄድ ላይ እንደሆነ አቶ ጌታቸው ይናገራሉ። |
በዚህ ዓመት መጨረሻ ላይ ይጠናቀቃል ተብሎ የሚጠበቀው ይህ ጥናት ከዚህ ቀደም ከተደረገው ዘርዘር እና ሰፋ ያለ እንደሚሆን ይገልጻሉ። |
ጥናቱ ከአራቱ የበሽታው አይነቶች የትኞቹ በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ለማወቅ እንደሚረዳ እና በሽታውን ለመከላከል ወደፊት ለሚደረገው ጥረት አንድ መነሻ ሊሆን እንደሚችል ያስረዳሉ። |
እስከ ሞት ሊያደርስ ለሚችለው ዴንጊ ፊቨር ፍቱን መድኃኒት እስካሁን ባይገኝም ተመራማሪዎች ግን የመከላከያ ክትባት መስራታቸውን አስታውቀዋል። |
ክትባቱን ያመረተው ዓለም አቀፍ ኩባንያ መድኃኒቱ ተጠቃሚዎች ዘንድ እንዲደርስ ለገበያ ያወጣው የዛሬ ሁለት ዓመት ግድም ነው። |
የዓለም ጤና ድርጅትም በሽታው አዘውትሮ በሚከስትባቸው ሀገራት መድኃኒቱ ጥቅም ላይ መዋል እንደሚችል አዎንታዊ አስተያየቱን ሰጥቷል። |
በ ሀገራት እውቅና እና ፍቃድ የተሰጠው ይህ ክትባት ከዘጠኝ እስከ ዓመት ላሉ ሰዎች የሚሰጥ እንደሆነ ተገልጿል። |
ለመሆኑ ዴንጊ ፊቨር እስከ ሞት ሊያደርስ የሚችለው ምን ሲፈጠር ነው |
የተቃጠሉ መስጊዶች መልሶ ለመገንባት የሚደረገውን ጥረት ግዛሉ ራድዮ ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። |
ራድዮ የሮሒንግያዎች ሥቃይ ዓለም አቀፉ ድርጅት ያነጋገራቸዉ ስደተኞች እንደሚሉት የምያንማር ወታደሮች የሮሒንግያ ሙስሊሞችን በጥይት ይገድላሉ ይደበድባሉ መኖሪያ ቤታቸዉን ያቃጥላሉም። |
እንደሚለዉ በብዙ ሺሕ የሚቆጠሩ ሌሎች ስደተኞች የምያንማርን ድንበር አልፈዉ ባንግላዴሽ ለመግባት እየሞከሩ ነዉ። |
ዓለም አቀፉ ድርጅት ያነጋገራቸዉ ስደተኞች እንደሚሉት የምያንማር ወታደሮች የሮሒንግያ ሙስሊሞችን በጥይት እየመቱ ይገድላሉ ሌሎቹን ይደበድባሉ መኖሪያ ቤታቸዉን ያቃጥላሉም። |
ሊሸከሙት የማይችሉትን ግፍ ሥቃይ እና መከራን የሸሹ ሺሕ ሰዎች እስካሁን ባንግላዴሽ ዉስጥ ከለላ አግኝተዋል። |
የምያንማር መንግሥት አማፂያንን እዋጋለሁ በሚል ሽፋን በሮሒንግያ ሙስሊሞች ላይ የሚፈፅመዉን ግፍ እንዲያቆም የተለያዩ መንግሥታት ቢጠይቁም እስካሁን ድረስ ተቀባይነት አላገኙም። |
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሌሎች ማሕበራትም ሆኑ መንግሥታትም በምያንማር መንግስት ላይ እርምጃ ለመዉሰድ አልቃጡም። |
ተቃውሞ በባሕርዳር ዛሬ በባህር ዳር የክልሉን ገዥ ፓር የሚነቅፍ ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ በባህር ዳር ተካሂዷል፡፡ |
የአማራዴሞክራሲዊ ፓርተ ስለጉዳዩ አስተያየት እንዲሰጥ ሙከራ ቢደረግም ስብሰባ ላይ ናቸው ስለተባለ አልተሳካም። |
ባሕር ዳር በአንድ ሳምንት ውስጥ የተለያዩ ዓላማዎችን ያነገቡ ሶስት ሰላማዊ ሰልፎችን አስተናግዳለች፡፡ |
ተመሳሳይ ይዘት ላቸው ሰልፎች በደብረታቦር በጎንደርና በምስራቅ ጎጃም የተለያዩ የወረዳ ከተሞች መካሄዳቸውን የየዞን የህዝብ ግንኙነት ባለሙያዎች አረጋግጠውልናል። |
በጉዳዩ ዙሪያ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲን አመራሮች የመስተዳድሩን ኃላፊዎች ሀሳብ ለማካትት ያደረግሁት ጥረት ጎንደር ላይ ስብሰባ ናቸው በሚል አልተሳካልኝም። |
ይህ መጥፎ ውጤት የ ን የበላይ መራኂተ መንግሥት አንጌላ መርክልንም አላስደነገጠም አይባልም። |
የ ምርጫ ውጤት ለፌደራሉ መንግሥት ምን ዓይነት መልእክት ይሆን የሚያስተላልፈው |
አፍሪቃ ናሚቢያዊው ሽምቅ ተዋጊ ሔንድሪክ ዊትቦይ አብዛናዎቹ የናሚቢያ ገንዘቦች የተዘረጋ ባርኔጣ ራሳቸው ላይ የደፉ የሔንድሪክ ዊትቦይ ፎቶግራፎች አሏቸው። |
ሔንድሪክ ዊትቦይ የጀርመን ቅኝ ገዢዎችን ተፋልመዋል ናሚቢያ በአፍሪቃ ከቅኝ አገዛዝ ነጻ በመውጣት የመጨረሻዋ ሃገር ናት። |
ውይይት የኢትዮጵያ መንግሥት ዉሳኔውን የተቀበለው ከ ዓመት በፊት ነዉ። |
የኤርትራ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ባለፈዉ ረቡዕ ባደረጉት ንግግር የኢትዮጵያ መንግሥት የሁለቱን አገሮች ውዝግብ ለማስወገድ ያሳለፈዉን ዉሳኔ እንደሚደግፍ ፍንጭ ሰጥተዋል። |
ጉዳዩን የሚያጠና የልዑካን ቡድንም ወደ አዲስ አበባ ለመላክ አቅደዋል። |
የሁለቱ ሃገራት መንግሥታት ሰሞኑን ያሳዩት መቀራረብ ዓመታት ያስቆጠረዉን ጦርነትና ውዝግብ ለማስወገድ ይጠቅማል የሚል ተስፋን አሳድሮአል። |
ሌሎች ደግሞ የኢህአዴግ መሪዎች የጋራ አቋም መያዝ እንደተሳናቸው ያመላክታል ይላሉ። |
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ የአልጀርስን ስምምነት በተመለከተ ስለተነሳዉ ተቃዉሞ በያዝነዉ ነው ሳምንት ለም ቤቱ ሰፊ ማብራርያ ሰጥተዋል። |
በማብራርያቸውም የኢትዮጵያ መንግሥት ስምምነቱንና የድንበር ኮሚሽኑን ዉሳኔ የተቀበለው ከ ዓመት በፊት መሆኑን አመልክተዋል። |
ስለዚህ የተቃውሞው ምንጭ የአልጀርሱ ስምምነት ሳይሆን ሌሎች ፖለቲካዊና ምጣኔ ሃብታዊ ጉዳዮች ሊሆኑ ይችላሉ የሚለዉን ግምት ይበልጥ እያጎላዉ መጥቶአል። |
የኢትዮ ኤርትራ አዲስ ግንኙነት የኢህአዴግ ዉሳኔና የህወሓት ተቃዉሞ መወያያ ርዕሳችን ነዉ። |
የሐረር ገበያ ዳግም እሳት ሐረር ከተማ ዉስጥ በሳምንት ልዩነት ባለፈዉ ቅዳሜ ማታም የእሳት አደጋ መድረሱን ኗሪዎቿ ይናገራሉ። |
ኢትዮጵያ ድርቅና የእርዳታ ጥሪ በበርካታ የሀገሪቱ ክፍሎች ዉስጥ የተከሰተዉን ድርቅ በሚመለከት ተደጋጋሚ ዓለም አቀፍ የርዳታ ጥሪዎች ተደርገዋል። |
እስካሁን ለችግር የተጋለጠዉ ሕዝብ ከ ሚሊየን በላይ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን የእርዳታ ድርጅቶች ቁጥሩ ሊጨምር እንደሚችልም ያሳስባሉ። |
ኢትዮጵያ ዉስጥ ከ ዓመታት ወዲህ ታይቶ የማይታወቅ በተባለዉ ድርቅ የተጎዱትን ወገኖች ለመርዳት ከአንድ ቢሊየን ዶላር በላይ እንደሚያስፈልግ ተገልጿል። |
የዓለም አቀፍ ለጋሾች እርዳ መዘግየቱን ያመለከተዉ የኢትዮጵያ መንግሥትም ለጋሾች አስቸኳይ ምላሽ እንዲሰጡ አሳስቧል። |
በርከት ያለ የእህል ምርት ለማፈስ ከጥንት ጀምሮ አርሶ አደሮች የዘር እኽል እየመረጡ በመዝራት አያሌ ዘመናት ጠብቀው ለማቆየት መቻላቸው የሚታበል አይደለም። |
አንድ ርምጃ ሲወሰድ የሚያስከትለው ጉዳት ምን ሊሆን እንደሚችል ታሳቢ አድርጎ መንቀሳቀስ እንደሚገባ ራሳቸው ከታዘቡት አንድ ታሪክ በመነሣት እንዲህ ይላሉ። |
ለዚህ ዝግጅት መነሻ የሆነን ባለፈው ሳምንት እንደጠቀስነው በሜክሲኮ ያህል ከአነዚህም ገሚሱ አነስተኛ የመሬት ይዞታ ያላቸው ባቄላ አምራቾች ያነሱት ጥያቄ ነው። |
በፖላንድ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ብቻ በመጠቀም የሚያመርቱ አርሶ አደሮች ቁጥር ባፋጣኝ በመጨመር ላይ መሆኑ ይነገራል። |
አዉሮጳና ሕገ ወጥ የሰዉ አሻጋሪዎች ራድዮ ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። |
ጀርመን ስደተኞች እና የመራሒተ መንግሥቷ አቋም ቢያንስ የሰው አመለካከት ለሁለት ተከፍሎአል፡፡ |
አሁንም ቢሆን አንዳዶቹ ከፊታችን የተደቀነውን ችግር እንፈታዋለን እንወጠዋለን ብለው የሚያምኑ ናቸው፡፡ |
ከዚያም አልፈው እንዲያውም እነሱ መራሂተ መንግሥትዋን ይህን እሳቸው ያለፈው ዓመት እንወጣዋልን ያሉትን ቃል ፊት ለፊት አሁን ይቃወማሉ ይተቻሉም፡፡ |
በጀርመን አገር ውስጥ ነገሮች እየተቀያየሩን እየተለዋወጡ እንደመጡ እዚያ እና እዚህ የሚታዩ ፍንጮች በቂ ምስክሮች ናቸው፡፡ |
ጊዜው ተቀይሮ ግን አሁን ለድርጅቱ አመቺ የሆነ ሰዓት የመጣ ይመስላል፡፡ |
እንዲያውም አንዳንዶቹ እዚህ እንደሚሉት የመጠጥና የራት ግብዣ አርዕስትም ሁኖ ብዙ ሰው ሳይፈራ ፊት ለፊት የሚነጋገርበት ጉዳይ ሁኖአል፡፡ |
በሌላ አካባቢ በታላቁዋ ብርታኒያ ለየት ያለ ሥዕል እዚያ እናያለን፡፡ |
እርግጥ ኑዋሪው ሕዝብ በመራሂተ መንግስትዋ ላይ ያለው አመለካከት እንደ አለፉት ጊዜያት ሳይሆን አሁን ተቀይሮአል፡፡ |
እንደ አለፉት አመታት ዘነድሮ መራሂተ መንግሥትዋ ወይዘሮ አንጌላ ሜርክል በሕዝቡ ዘንድ ተወዳጅ አይደሉም፡፡ |
አብዛኛው የጀርመን ሕዝብ ስደተኞቹን አስታኮ የመጣውን ችግር እንፈተዋለን የሚለውን ነገር ሙሉ በሙሉ አምኖ በልቡ አልተቀበለውም፡፡ |
በውጭ ጉዳይ ፖለቲካ ፖሊሲአቸውም ሆነ በሚያቀርቡት አመለካከታቸው መራሂተ መንግስትዋ እንደ አለፉት ዘመናት ዘንድሮም በአዉሮጳ መሪዎች ዘንድ ትልቅ ድምጽና ተቀባይነት አላቸው፡፡ |
ግን ያም ሁኖ ጀርመኖችም በስደተኞች ላይ ያላቸውና የነበራቸው አመለካከት ደግሞ እንዳለ ተቀይሮአል፡፡ |
በመጀመሪያ ቀናት ይታይ የነበረው የእንግዳ ተቀባይነትና የማስተናገድ መንፈስ ቀስ እያለ እየቀዘቀዘና እየበረደ አሁን ሌላ መልክ ይዞአል፡፡ |
ድንበሩ ቢዘጋ ደግሞ በሺህና በአሥር ሺህ በመቶና በሁለት መቶ ሺህ የሚቆጠሩ ነፍሳቸውን ለማዳን የሚሸሹትን ስደተኞች መርዳት በአልተቻለ ነበር፡፡ |
ትናንሽ ልጆችን የጀርመንኛ ቋንቋ በማስተማር አንዴ የጀመሩትን ሥራ አሁንም ቀጥለውበት ያስተምሩአቸዋል፡፡ |
ብቻቸውን እዚህ የደረሱትን ገና ለአቅመ አዳም ያልደረሱትን ወጣት ልጆች ወስደው እየተንከባከቡአቸው አሁንም ያሳድጉአቸዋል፡፡ |
መሥራት ለሚፈልጉት ሥራ የሙያ ትምህርት ቤት ገብተው ለመማር ለሚፈልጉት ለእነሱም ትምህርት ቤት አብረው ፈልገው እዚያ ይልኩአቸዋል፡፡ |
በሚሊዮን ከሚቆጠሩት አንዱም ስድተኛ መንገድ ላይ ሳያድር ሁሉንም ማስተናገድ በቀላሉ ታይቶ የሚታለፍ ሥራም አይደለም፡፡ |
የሆነው ሆኖ አሁንም ቢሆን ትልቁ ገና ያልተፈታው ችግርም ከፊታችን ተደቅኖ እንደ ቆመም መረሣት የለብንም፡፡ |
እሱም ሕብረተሰቡ የተገን ጠያቂን ስደተኛ ልጆችን ትምህርት ቤት አስገብቶ እነሱን ማስተማር አለበት፡፡ |
ነፍስ ያወቁትን ጎልማሦዎችን እንደዚሁ እነሱን አስተምሮና አሠልጥኖ የሥራ ዓለም ውስጥ ማሰማራትም ይኖርበታል፡፡ |
ይህ ሁሉ ደግሞ ሲሆን ጊዜና ጉልበት ከዚያም በላይ ብዙ ወጪ ገንዘብም የሚጠይቅ ሥራና ኃላፊነት ነው፡፡ |
እዚህ ቀርተው ለመኖር ለሚፈልጉ ስደተኞች የጀርመንን ቋንቋ መማር አላባቸው፡፡ |
ይህ አዲስ ሁኔታ ደግሞ አዲስ ነገር ይዞልን ሊመጣም ይችላል፡፡ |
ቁም ነገሩ ያለው ስደተኞቹን አቅፎና ተቀብሎ እነሱን ከሕብረተሰቡ ጋር በቀላሉ እንዲዋሃዱ መርዳቱ ላይ ነው፡፡ |
ያኔ ነው አብረው እነሱም ጀርመንን በአላቸው ችሎታ ለመገንባት አስተዋጽኦቸውን የሚያበረክቱት፡፡ |
Subsets and Splits
No community queries yet
The top public SQL queries from the community will appear here once available.