input
stringlengths 1
130k
⌀ |
---|
የዚህ ህግ ዓላማ ሰርቢያ ቦስኒያና ሌሎች ሃገራትን የተረጋጉና አስተማማኝ ከሚባሉ ሃገራት ዝርዝር ውስጥ ማስገባት ነው ። |
ይህ ከተደረገም ከነዚህ ሃገራት የሚመጡ የተገን ጥያቄ ማመልከቻዎችን ወዲያውኑ ውድቅ ለማድረግ ይቻላል ። |
ለስደተኞች መብት ተቆርቃሪው ድርጅት ምክትል ሃላፊ ቤርንት ሜሶቪክ ይህ ትርጉም የለሽ አሰራር ነው ይላሉ ። |
ጀርመን ተገን እንዲሰጣቸው ከሚጠይቁት መካከል የተሻለ እድል ያላቸው ሶሪያውያን ናቸው ። |
በጥብቅ መስፈርት ተመርጠው እስካሁን ጀርመን የገቡት ግን ብቻ ናቸው ። |
ከዚህ በተጨማሪም በሌሎች መንገዶች ጀርመን የገቡ የሶሪያ ስደተኞች ጥገኝነት እንዲሰጣቸው አመልክተዋል ። |
የሶሪያ ስደተኞች ጀርመን ከሚገኙት ተገን ጠያቂዎች ከፍተኛውን ቁጥር ይይዛሉ ። |
የተገን ጠያቂዎቹ ብዛትና ጀርመን ልትቀበል ቃል የገባችው የሶሪያ ስደተኞች ቁጥር የሚመጣጠን አይደለም ። |
ሁሌም ወደነርሱ የምንጠቁማባቸው ሌሎቹ ቁጥሩ ሊታመን የማይችል ስደተኛ ጫንቃቸው ላይ ተጭኗል ። |
ከኛ በኤኮኖሚ እጅግ ደካማ በሆኑ ጎረቤት ሃገራ ከሁለት ሚሊዮን የሚበልጡ ስደተኞች አሉ ። |
እኛ ደግሞ ምን ማድረግ እንችላለን ብለን ራሳችንን መጠየቅ አለብን ። |
አንዳንድ ጀርመናውያን አስተያየት ሰጭዎች ጀርመን ስደተኞች በብዛት ከተቀበለች ጫናው ይከብዳታል ሲሉ ስጋታቸውን ይገልፃሉ ። |
ሪኮቭስኪ ግን ለዚህ መልስ የሚሰጡት እጎአ ከ እስከ በተካሄደው የቦስኒያ ጦርነት ወቅት ጀርመን የተቀበለቻቸውን ስደተኞች ብዛት በማስታወስ ነው ። |
በወቅቱ ጀርመን ግጭት ከተከሰተበት ከዚህ አካባቢ ከ ሺህ በላይ ስደተኞችን ተቀብላለች ። |
ይህ አሃዝ ሪኮቭስኪ እንዳሉት በ ጀርመን ተገን እንድትሰጣቸው ከጠየቁት ስደተኞች በሶስት እጥፍ ይበልጣል ። |
በሌላ በኩል ጀርመን ህጋዊ ሰነድ የሌላቸው ሺህ የሚደርሱ የውጭ ዜጎች የሚገኙባትም ሃገር ናት ። |
ከዛሬ ነገ ወደ ሃገራችን እንባረራለን ከሚል ስጋት ጋር የሚኖሩት እነዚህ ሰዎች በሃገሪቱ ምንም መበት የላቸውም ። |
ማርያ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ስትንቀሳቀስ ጥንቃቄ ተለይቷት አያውቅም ። |
ባቡር ከተሳፈረች ትክክለኛውን ቲኬት ይዛ ነው መንገድ ስታቋርጥ እንኳን መኪና የለም ብላ ቀይ መብራት ጥሳ አታልፍም ። |
በቀን ሰዓት ወለልና መፀዳጃ ቤቶችን በምታጸዳበት የስራ ቦታዋ እረፍት አታውቅም ። |
በቂ ደሞዝ ባታገኝም ሁሌም በሰዓቱ በሥራ ገቦታዋ ላይ የምትገኝ አንድም ቀን አመመኝ ብላ የማታውቅ ታታሪ ሴት ነበረች ። |
ዋናው ባቡር ጣቢያ ስትደርስ እንደ አጋጣሚ ፖሊሶች የሰዎችን ህጋዊነት ለማረጋገጥ መታወቂያ ሲጠይቁ ትደርሳለች ። |
ማርያ ባለፉት ዓመታት ያለ ህጋዊ ሰነድ ነበርና የምትኖረው ተፈላጊውን ማስረጃ ማቅረብ አልቻለችም ። |
በዚህ አጋጣሚ የተያዘችው የአንዲት ልጅ እናት ማርያ ከልጅዋ ጋር ወደ ሃገርዋ ተጠርዛ ተልካለች ። |
ልጅዋንና ርስዋን በህክምና ይረዱ ቦን የሚገኝ የግብረ ሰናይ ድርጅት ባልደረቦች ጀርመንን ለቃ ከመሄዷ በፊትም ተሰናብታቸዋለች ። |
የድርጅቱ ምክትል ሃላፊ ኡልሪሽ ኮርትማን በጀርመን የማርያን መሰል ህይወት የሚገፉ ስደተኞች ህይወት አስቸጋሪ መሆኑን ያስረዳሉ። |
ግን በድብቅ መኖር ግዴታዋ ነበር ያልተከፈለበት የመጓጓዣ ቲኬት በባቡር ውስጥ ይዞ መገኘት ከሃገር እስከመባበረር የሚያደርስ ትልቅ አደጋ አለው ። |
እናም ዘወትር እያዛለሁ ወይም ተቆጣጣሪዎች ይደርሱብናል በሚል ስጋት ይኖራሉ ። |
ለህክምና አገልግሎት የሚሆን ገንዘብ የላቸውም ጀርመን ውስጥ ያለ ገንዘብ ምንም ማድረግ አይቻልም ። |
ወይዘሮዋ እና ሌሎች ባልደረቦቻቸው ስደተኞቹን ሊረዷቸው ከሚፈልጉ ሃኪሞች ጋር ያገናኟቸዋል ። |
የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸውም ሰዎች የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግ እንፈልጋለን ። |
የዛሬ ዓመታት ሲመሰረት ይህን ያህል እድሜ ይኖረዋል የሚል ግምትም አልነበረም ። |
በግብረ ሰናዩ ድርጅት ስር በልዩ ልዩ የህክምና ዘርፎች አገልግሎት የሚሰጡ ዶክተሮች ታቅፈዋል ። |
እነዚህ ሃኪሞች የጤና ኢንሹራንስ የሌላቸውን ሰነድ አልባ ስደተኞች ያክማሉ ። |
የድርጅቱ ምክትል ሃላፊ ኡልሪሽ ኮርትማን እንደሚሉት አንዳንዴ የስደተኞቹ የጤና ችግር ከባድ ከሆነ መንግስት አስተያየት ሊያደርግላቸው ይችላል ። |
በተግባር እስካሁን እንደታየው ከባድ ህመም ያለባቸው ሰዎች ከሃገር እንዲወጡ አይገደዱም ። |
እነዚህ ስደተኞች በአንድ አጋጣሚ በተቆጣጣሪዎች እጅ ከወደቁ የማርያ እጣ ሊገጥማቸው ይችል ይሆናል ። |
የ መልዕክቶቻችሁን በ ፃፉልን ኤሚላችን ነው በስልክ መልዕክት መተው የምትፈልጉ ደግሞ ቁጥራችን ነው ። |
ዓለም ኢትዮጵያውያን ሐጃጆች በሳዑዲ አረቢያ የኢድ አል አደሐ አረፋ በዓል በነገው ዕለት ይከበራል። |
ጠቅላይ ምኒስትር አብይ አሕመድ ለመላው የእስልምና ዕምነት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። |
ኢትዮጵያውያን ሐጃጆች በሳዑዲ አረቢያ የኢድ አል አደሐ አረፋ በዓል በነገው ዕለት ይከበራል። |
ሳዑዲ አረቢያ የሚገኘው ነብዩ ሲራክ ደግሞ የዕምነት ግዴታቸውን ሊወጡ መንገድ የገቡ ሐጃጆችን አነጋግሯል። |
የሁለት ሀገራት ምርጫ ታሕሳስ ዘመኑ በሙሉ እንደ ጎርጎሪያዉያን አቆጣጠር ነዉ ጋምቢያዎች የወደፊት ፕሬዝደንታቸዉን መረጡ። |
የምርጫዉ ሒደት ዉጤት አንድነት ተቃርኖዉ ያፍታ ዝግታችን ትኩረት ነዉ። |
መልከዓ ምድራዊ ካርታዋን ትኩር ብሎ ያየ የብሪታንያ እና የፈረንሳይ ቅኝ ገዢዎች ሽኩቻ ዉጤት መሆንዋን ለማወቅ ሌላ ምርምር አይጠይቀዉም። |
ካርታዉን ከባሕሩ ወደ ምድሩ ሲመለከቱ በቀድሞዋ የፈረንሳይ ቅኝ ተገዢ ሴኔጋል ላይ ያረፈ የአንድ እግር ፈለግ ትመስላለች። |
ወይም አካሉን ባሕር ዉስጥ ደብቆ መላሱን ሴኔጋል ላይ የጎለገለ ሰዉ ወይም እንስሳ። |
ሴኔጋል ራስዋን ደረቷ ላይ አስደግፋ እግሯን ባሕሩ ዉስጥ ነክራ የተቀረ አካሏን በሁለት ክንዶችዋ ታቅፋ የምታጥባት ሕፃን ትመስላለች። |
ጋና በቆዳ ስፋትም በሐብትም በሕዝብ ብዛትም ጋምቢያን ከአስር ጊዜ በላይ ታጥፋታለች። |
የቀድሞዋ የወርቅ ጠረፍ ጎልድ ኮስት የ ሚሊዮኖች ሐገር ናት። |
ጋና ቀደም ጋምቢያ ከተል ብለዉ ሁለቱም በ ዎቹ ከቅኝ ገዢያቸዉ ነፃ ወጡ። |
ሥለ ነፃነት ገድል ድል ታሪካቸዉ ሲያወሩ ጋናዎች ክዋሚ ንኩሩማን ይዘክራሉ። |
ጋናዎች በመፈንቅለ መንግሥት በአመፅ ሁከት ሲተራመሱ ጋሚቢያዎች በየአምስት ዓመቱ እንዴ መሪ እና እንደራሴዎቻቸዉን እየመረጡ ቀዝቃዛዉን ጦርነት ዘመን ተሻገሩ። |
በሁሉም ምርጫ የሚያሸንፈዉ ግን ዳዋድ ጃዋራ የሕዝብ ዕድገት ያሉት ፓርቲያቸዉ ነበር። |
የጋምቢያ ሕዝብ በጣሙን ጦር ሐይሉ ብዙ ዘግይቶ ከጋና እና ከብዙዎቹ የአፍሪቃ ሐገራት የተማረዉን ገቢር አደረገ። |
የመጀመሪያዉን መፈንቅለ መንግስት የመሩት መቶ አለቃ ያሕያ አብዱል አዚዝ ጄሙስ ጁንኩንግ ጃሜሕ የትሺቱ ሐገር ሁለተኛ መሪ ሆኑ። |
ምክንያቱም ይሕ ከመላዉ ዓለም በጣም ግልፅና የማይጭበረበር ምርጫ ነዉ። |
ምርጫ እንዲደረግ የወሰነዉም የሚመራችሁን ሰዉ ማንነት የምትወስኑት እናንት የጋምቢያ ሕዝብ በመሆናችሁ ነዉ። |
ተቃዋሚዬ በአንድ ድምፅ እንኳን ቢበልጠኝ ምርጫዉ ነግልፅ እስከሆነ ድረስ ዉጤቱን እቀበላለሁ። |
የምርጡኝ ዘመቻዉ የተፎካካሪዎች አሰላለፍ የድምፅ አሰጣጡ ሒደትም ታዛቢዎች እንደመሰከሩት የጋምቢያም የጋናም ተመሳሳይ ነበር። |
እንደ ምርጫዉ ጊዜ ሁሉ ዉጤቱ ቀደሞ የታወጀዉ ግን ከባንጁል ነበር። |
ከተሰጠዉ ድምፅ ዉን ድምፅ በማግኘት አዳማ ቦሮዉ የጋምቢያ ሪፐብሊክን በፕሬዝደትነት እንዲያገለግሉ መመረጣቸዉን አስታዉቃለሁ። |
ጃሜሕ ቤተ መንግሥት የገቡበትን ስምንተኛ ዓመት ሲያከብሩ ፖለቲካ የማያዉቁት የዕድሜ አቻቸዉ ያሁን ተቀናቃኛቸዉ ወደ ብሪታንያ ተሰደዱ። |
የድሮ የሐገራቸዉ ቅኝ ገዢዎች ያሉ ያደረጓቸዉ ወይም ያደረጉላቸዉ አይታወቅም። |
ድላቸዉ ሲታወጅ ደግሞ ከትራምፕ በላይ አስደናቂ ዉጤት እያሉ አደነቋቸዉ። |
የፖለቲካ ተንታኞች ባሮዉን የ ዓመቱን አምባ ገነን ገዢ ያንበረከኩ የማይደፈረዉን የደፈሩ እያሉ አወደሷቸዉ። |
ትንሺቱ ዓመት በአምባገነን የብረት ጡንቻ ስትገዛ የኖረችዉ ጋምቢያ ያስተናገደችዉ ምርጫ በቅርቡ ዩናይትድ ስቴትስ ከተደረገዉ ምርጫም የበለጥ ሽግግር ነዉ የሚመስለዉ። |
የምዕራባዉያንን መርሕ ባደባባይ በማጋለጥ በመዝለፍ መሳደብ የሚበልጥ እና በቅርቡ ዘመን የሚቀድማቸዉ ከነበረ። |
የምዕራባዉያን ጃሜሕን የሚጠሉ ዜጎቻቸዉ ለዉጥ የፈለጉ ምናልባትም የአዳማ ባሮዉን ትኩረት መሳብ የሚሹ ሁሉ እንጂ። |
በፌስታ ፈንጠዝያዉ መሐል ጋምቢያዊዉ አንጋፋ ድምፃዊ ጃሊብ ኩያቴሕ ባንድ ወቅት ሐገሬን ስጠራ አፍሬ ነበር አለ። |
ባንጁል የ ዓመት ገዢዎችዋን አንገት አስደፍታ አሸናፊዎችን ሥታስቦርቅ አክራ የምርጫ ዉጤትዋን አወጀች። |
አሁን በሥልጣን ላይ ያሉትን ፕሬዝደንት ጆን ድራማኒ ማሐማን በከፍተኛ የድምፅ ልዩነት አሸነፉ። |
የአኩፎ አዶ ደጋፊ አድናቂዎች በተገኘዉ ዉጤት መፈንደቅ መቦረቃቸዉ አልቀረም። |
ፍንደቃ ቡረቃዉ ግን እንደ ጋምቢያዎች ተሸናፊዉን በማዉገዝ መዝለፍ መወረፍ ላይ ያተኮረ አልነበረም። |
ስለዚሕ አዲሱ መሪ በጋራ ሆነን እንድንታገል የሚያስተባብረን መሆን አለበት። |
ያም ሆኖ ሁሉም ተመሳሳይ መልዕክት ወይም አቋም አለዉ ማለት አይደለም። |
ጋና ጋምቢያ ናጄሪያ ሆነ ኢትዮጵያ ለመጥፎ ይሁን ለጥሩ የአብዛኛዉን ሕዝብ አስተሳሰብ የሚቀርፁ የሚቀይሱ አቅጣጫ የሚያመለክቱትም አንድም መሪዎቹ ሁለትም አዋቂዎቹ ናቸዉ። |
አሸናፊነታቸዉ በታወጀ በሳልስቱ የ ዓመቱን ገዢ ያስጠነቅቁ ያሳሰቡ ለማዘዝም ይንጠራሩ ገቡ። |
በሥልጣን ላይ ያለዉ መንግሥት የፖለቲካ እስረኞቹን መፍታት አለበት አሉ። |
ይሕን ካደረጋችሁ ሥልጣን ስትለቁ ጥሩ የንግድ ምልክት ትታችሁ ትሔዳላችሁ። |
በስልጣን ላይ ያለዉን መንግስት ባለሥልጣናት ፍርድ ቤት እንደሚያቀርቡ ዛቱ። |
ጋምቢያ በጃሜሕ ዘመን የገባባቻቸዉን ዓለም አቀፍ ዉሎች ዳግም እንደሚያጤኑት አስታወቁ። |
ጃሜሕ አሁንም ሥልጣን ላይ መሆናቸዉን ዘነጉት መሰለኝ አሉ የባንጁል ነዋሪ። |
ጋናዎች ከተሸናፊዎች ጋር ሰላማዊ የሥልጣን ሽግግር ለማድረግ እንደሚመክሩ ሲያስታዉቁ የጋምቢያ ምርጫ ዉጤት የወለፊንድ ባረቀ። |
የ ዓመቱ ገዢ ተቀናቃኛቸዉ በአንዲት ድምፅ ቢበልጣቸዉ እንኳን ዉጤቱን ለመቀበል ቃል የገቡት ጃሜሕ የምርጫዉን ዉጤት ዉድቅ አደረጉት። |
በተመድ የየመን የሰላም መልክተኛ ኢስማኢል ኦልድ ቼክ ረቡዕ ዕለት በሰጡት መግለጫ በየመን ተቀናቃኞች መካከል ያለዉ ልዩነት የሰፋ ነዉ። |
አሳሳቢዉ የየመን ሁኔታ ዳግም ለሰላም ለድርድሩ ለመቀመጥ ተስፋ አይታይም በየመን በአየርና በምድር የሚደረገዉ ጦርነት ተባብሶ ቀጥሎአል። |
በሌላ በኩል የየመኑን ጦርነት አልፈዉ ወደ ስዑድ አረብያ የሚገቡት ኢትዮጵያዉያን ቁጥር ጥቂት እዳልሆነ በጅዳ የሚገኘዉ ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ ገልፆልናል። |
በተመድ የየመን የሰላም መልክተኛ ኡልድ ቼክ አህመድ በየመን በአየርም ሆነ በመሪት ለመሪት ዉግያዉ ተጠናክሮ መቀጠሉን ትናንት በሰጡት መግለጫ አዉግዘዋል። |
እንደ ኡልድ ቼክ አህመድ ከሁለቱም የየመን ተቀናቃኝ ኃይሎች በኩል የተኩስ አቁም ስምምነት ለማድረግ ምንም ዓይነት ጥረትም ሆነ ፍንጭ አይታይም። |
ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ እንደገለፀዉም የየመን ሁኔታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ መጥቶአል። |
በየመን የየርስ በርሱን ጦርነት አልፈዉ ወደ ርያድ የሚገቡ የኢትዮጵያዉያን ስደተኞች ቁጥርም ከፍተኛ መሆኑን ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ ገልጾልናል። |
የየመንን ቀዉስ እየተባባሰ ነው ሲሉ የመንግሥታቱ ድርጅት የሰብዓዊ ጉዳዮች ተጠሪ ስቴፈን ብሪይን በሳምንቱ መጀመርያ ላይ አስጠንቅቀዋል። |
በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ደግሞ በዞኑ የተደራጀና የታጠቀ ኃይል ፈፅሞ የለም ባይ ነው። |
ካለፈው ቅዳሜ ጀምሮ በሰሜን ሸዋ ዞን አጣየ አካባቢ በተፈጠረው ግጭት ሰዎች መገደላቸውና መቁሰላቸው ተነግሯል፡፡ |
የሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳደር አጣየን ለማጥቃት የተዘጋጀ እና የተደራጀ ኃይል በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ውስጥ አለ ይላል። |
ካለፈው ቅዳሜ ጀምሮ በሰሜን ሸዋ ዞን አጣየ አካባቢ በተፈጠረው ግጭት ሰዎች መሞታቸውና መቁሰላቸውን አመራሮቹ ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል፡፡ |
አፍሪቃ አሸባብ ላይ ያነጣጠረው የኬንያ በቀል የኬንያ መንግስት የዳዳብ የስደተኞች መጠለያ ጣቢያን ሊዘጋ መሆኑን የጀርመን የዜና ወኪል ዘገበ። |
በጣቢያው የሚገኙ ከ ሺ በላይ የሶማሊያ ስደተኞች የአሸባብ ታጣቂ ቡድን ወደ ማይገኝባቸው የሶማሊያ ግዛቶች እንዲመለሱ ይደረጋል ተብሏል። |
የኬንያ መንግስት ከዚህ ውሳኔ የደረሰው በጋሪሳ ከተፈጸመው ጥቃት በኃላ መሆኑን የዜና ወኪሉ አክሎ ዘግቧል። |
Subsets and Splits
No community queries yet
The top public SQL queries from the community will appear here once available.