id
stringlengths
8
14
url
stringlengths
36
42
title
stringlengths
8
90
summary
stringlengths
6
505
text
stringlengths
133
19.2k
news-42335130
https://www.bbc.com/amharic/news-42335130
በደቡብ ሱዳን በተከሰተ ግጭት 170 ሰዎች ተገደሉ
በደቡብ ሱዳን ምዕራባዊ ክፍል በሁለት ጎሳዎች መካከል የተከሰተ ግጭት የ170 ሰዎችን ሕይወት ሲቀጥፍ ከ200 በላይ ሰዎች ደግሞ ጉዳት እንደደረሰባቸው የሃገሪቱ የፓርላማ አባል የሆኑት ደሩዋይ ማቦር ቴኒ አስታውቀዋል።
እርግጥ በአከባቢው ግጭት የተለመደ ቢሆንም ባለፈው ሳምንት የተከሰተው ግጭት ግን እጅግ የከፋ ነው ሲል የቢቢሲው ፈርዲናንድ ኦሞንዲ ከናይሮቢ ይናገራል። የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር በሃገሪቱ ለሶስት ወራት የሚቆይ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ይፋ ማድረጋቸውም ይታወሳል። አዋጁ በዋነኛነት ሶስት የሃገሪቱን ክልሎች የሚያካልል ሲሆን የሃገሪቱ ጦር በእነዚህ ቦታዎች ሙሉ ትጥቁን ታጥቆ እንዲንቀሳቀስ ታዟል። የታጠቁ ሰዎች መሣሪያቸውን በሰላም የማያስረክቡ ከሆነ የሃገሪቱ ጦር አስፈላጊውን እርምጃ የመውሰድ መብት እንዳለውም ነው ሳልቫ ኪር በአዋጁ ያስታወቁት። በታህሳስ ወር መባቻ ላይ ተጋጭተው የነበሩት የዲንካ ማሕበረሰብ ጎሳዎች በርካታ መሣሪያ የታጠቁ ወጣቶች እንደሚገኙባቸው ይነገራል። "ከ170 በላይ ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል። 342 አካባቢ ቤቶች ደግሞ ተቃጥለዋል፤ በዚህ ምክንያት 1800 የሚሆኑ ሰዎች ቤት ንብረታቸውን ጥለው ተፈናቅለዋል" በማለት ቴኒ ሁኔታውን ያስረዳሉ። የሳልቫ ኪር ቃል-አቀባይ የሆኑ ሰው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እየተፈጠረ ላለው የእርስ በርስ ግጭት መፍትሄ ሊያመጣ እንደሚችል ተስፋ እንዳላቸው ይናገራሉ። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በሃገሪቱ እየተከሰተ ያለውን የእርስ በርስ ግጭት የሚያጣራ ቡድን በላከ ሰሞን ነው መሰል ግጭት ተከስቶ የበርካታ ሰው ሕይወት ያጠፋው። በደቡብ ሱዳን እየተከሰተ ያለውን ግጭት የአፍሪካ ሕብረትን ጨምሮ ሌሎች ውጫዊ አካላት ለመፍታት እያደረጉ ያለው ግጭት እስካሁን ምንም ዓይነት መፍትሄ ማምጣት አልቻለም።
news-52709939
https://www.bbc.com/amharic/news-52709939
የሌሴቶ ጠቅላይ ሚንስት ቶማስ ታባኔ ከሥልጣን ለቀቁ
ቶማስ ታባኔ ከጠቅላይ ሚኒስትርነታቸው እንደሚወርዱ አሳወቁ። የቀድሞ ሚስታቸውን በመግደል የተጠረጠሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለረዥም ወራት የቆየ ሕዝባዊ ተቃውሞ ካስተናገዱ በኋላ ነው ይህ ውሳኔያቸው የተሰማው።
የ80 ዓመቱ ቶማስ ታባኔ ረዥም ዓመታት ስልጣናቸው ላይ ከቆዩ አፍሪካ መሪዎች መካከል አንዱ ናቸው ከመቼ ጀምሮ ከሥልጣናቸውን እንደሚያስረክቡ ባይናገሩም ፓርቲያቸው ግን ከማከሰኞ ጀምሮ አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ቃለ መሃላ ይፈጽማል ብሏል። ከ80 ዓመቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር በመኖር ላይ የምትገኘው አዲሷ ሚስታቸው ከግድያው ጋር በተያያዘ ተከስሰው ፍርድ ቤት የቀረቡት በየካቲት ወር ነበር። ሁለቱም ግን በግድያው እጃችን የለበትም ሲሉ አስተባብለዋል። • የሌሴቶ ቀዳማዊት እመቤት የባሏን የቀድሞ ሚስት በመግደል ተያዘች • የሌሴቶው ጠቅላይ ሚኒስትር በሚስታቸው ግድያ ተከሰሱ የቶማስ ታባኔ የቀድሞ ባለቤት ሊፖሌሎ ታባኔ በሽጉጥ የተገደሉት ከሦስት ዓመታት በፊት ነበር። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፖለቲካዊ ባልሆነና ከቤት ውስጥ ግድያ ጋር በተያያዘ ፍርድ ቤት መቅረባቸው በስልጣን ላይ ያሉ የመጀመሪያው አፍሪካዊ ያደርጋቸዋል። ሁኔታው በደቡብ አፍሪካ ተከባ የምትገኘውን ትንሿን ሌሴቶ ያስደነገጠ ሆኗል። • "ዕፀ ፋርስ በመሸጥ ልጆቼን አሳድጋለሁ" የሌሴቶዋ አምራች ከዚህ ቀደም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከግድያው ጋር በተያያዘ በፖሊስ መጠየቃቸውን ተከትሎ በመቶዎች የሚቆጠሩ የተቃዋሚ ደጋፊዎች በመዲናዋ ማሴሩ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስልጣን እንዲለቁ በሰልፍ ጠይቀው ነበር። የተቃዋሚዎች ግፊት በመጨመሩም በወቅቱ ስልጣን እንደሚለቁ ቢያሳውቁም መቼ ሊሆን እንደሚችል አልተናገሩም ነበር። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባለቤታቸውም ሆነ እሳቸው የተወነጀሉበትን ወንጀል ከማንሳት ተቆጥበው በጡረታ ራሴን አገልላሁ ነበር ያሉት። የጠቅላይ ሚኒስትሩ የቀድሞ ባለቤት ሊፖሌሎ ታቤን በሌሴቶ መዲና ማሴሮ በሚገኘው ቤታቸው ጥይት ተተኩሶባቸው የተገደሉት ከሦስት ዓመት በፊት ነበር። በወቅቱም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለበዓለ ሲመታቸው ሁለት ቀናት ሲቀራቸው ነበር ግድያው የተፈጸመው ተብሏል፤ መረር ያለ የፍች ሂደትም ላይ ነበሩ። በወቅቱም ከአሁኗ ባለቤታቸው ጋር አብረው ይኖሩ ነበር ተብሏል። ነገር ግን ሊፖሌሎ በወቅቱ ቀዳማዊት እመቤት ማን ተብሎ ይጠራ የሚለውንም ጉዳይ ወደ ፍርድ ቤት ወስደውት፤ የቀዳማዊ እመቤት ለሳቸው ይገባል በሚል ተወስኗላቸው ነበር። ነገር ግን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለበዓለ ሲመታቸው ሁለት ቀን ሲቀራቸው በመገደላቸው ምክንያት የአሁኗ ባለቤታቸው በክብረ በዓሉ ላይ ተገኝተዋል። ከሁለት ወራት በኋላም ከአሁኗ ባለቤታቸው ጋር በሮማውያን ካቶሊክ ስነ ስርአት መስረት ጋብቻቸውን ፈፀሙ። ቀዳማዊቷ እመቤት ማሳየህ ታባኔ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የቀድሞ ባለቤት ክስ ተመስርቶባቸው በ2ሺ ብር ዋስ ወጥተዋል። ከዚህም በተጨማሪ ቀዳማዊቷ እመቤት የቤተሰቡ ቅርብ የሆነውን ታቶ ሲቦላን በመግደል ሙከራም ክስ ተመስርቶባቸዋል። ታቶ ሲቦላ በወቅቱ የቀድሞዋ ቀዳማዊት እመቤት ሲገደሉ የአይን እማኝ ነበርም ተብሏል።
news-51788725
https://www.bbc.com/amharic/news-51788725
ማርች 8፡ የዓለም የሴቶች ቀንን ማንና የት ጀመረው?
ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን በተመለከተ ከመገናኛ ብዙኃን አለያም ከወዳጅ ሰምተው ይሆናል። ፅንሰ ሐሳቡ ምን ይሆን? መቼ ይከበራል? በዓል ወይስ የተቃውሞ ቀን?
በተመሳሳይስ ዓለማቀፍ የወንዶች ቀንስ ይኖር ይሆን ? ዓለም አቀፋ የሴቶች ቀን በየዓመቱ መጋቢት ስምንት መከበር ከጀመረ ዘመናትን አስቆጥሯል፤ ለተጨማሪ መረጃዎች አብረውን ይዝለቁ፦ ታሪካዊ ዳራ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን የአመፅ እንቅስቃሴን መነሻ በማድረግ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዘንድ እውቅናን ለማግኘት የበቃ በዓል ነው:: ወቅቱ እንደ አውሮፓውያኑ 1908 ነበር በኒውዮርክ ከተማ ነዋሪ የሆኑ 15,000 ሴቶች የተሻሻለ የሥራ ሰዓትና የደመወዝ ክፍያን እንዲሁም የመምረጥ መብታቸው እንዲከበር አደባባይ የወጡት። ከአንድ ዓመት በኋላም የአሜሪካ ማኅበራዊ ፓርቲ ዕለቱን የሴቶች ብሔራዊ ቀን በማለት አውጆታል። ክላራ ዚክተን በተባለች ሴት አማካኝነት ደግሞ በዓሉ ዓለማቀፋዊ ቅርፅን እንዲይዝ በ1910 ላይ በዴንማርክ ዋና ከተማ ኮፐንሀገን በተካሔደው ዓለማቀፋዊ የሠራተኛ ሴቶች ኮንፍረስ ላይ ሐሳቡ ቀረበ። ከአስራ ሰባት ሀገራት የተውጣጡ መቶ ተሳታፊ ሴቶች ሀሳቡን በጄ አሉት። ይህንንም ተከትሎ ኦስትርያ ዴንማርክ ጀርመንና ስዊዘርላንድ በዓሉን በ1911 በማክበር ፈር ቀዳጅ ሆኑ። ባለፈው የፈረንጆች 2011 ይሄው በዓል ለመቶኛ ጊዜ የተከበረ ሲሆን በዚህ ዓመት ሲታሰብ ደግሞ ለ109ኛ ጊዜ ነው ማለት ይሆናል። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሴቶች ቀንን በ 1975 በይፋ ሲያከብር በዓሉ ዓለማቀፋዊ ይዘት ሊኖረው ችሏል። ከዚሁ ጋር ተያይዞም በ1996 ተ.መ.ድ "ያለፈውን በማሰብ የወደፊቱን እናቅድ " የሚል መሪ ቃል ይዞ ተከብሯል። በዚህ ዓመት ደግሞ " እኩልነት የሰፈነባት ዓለም ሁሉን ማድረግ ትችላለች " በሚል የሚከበር ሲሆን ለፆታዊ እኩልነት ህዝቦች በጋራ ተሳስበው እንዲሰሩ የሚያሳስብ ነው። ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ሴቶች በማኅበረሰቡ ዘንድ ተቀባይነትን ለማግኘት የተጓዙትን ጉዞም ያስታውሳል። መቼ ይከበራል? ዛሬ ላይ በዓሉ መጋቢት በባጀ በ8ኛው ቀን ይከበራል። ይሁን እንጂ ክላራ በተባለቺው ሴት አማካኝነት ሐሳቡ ሲጠነሰስ የተቀመጠለት ቋሚ ቀን አልነበረም። የሩሲያ ሴቶች በ1917 "ዳቦና ሰላም " በማለት ያነሱት የተቃውሞ እንቅስቃሴ የበለጠ ቅርፅ እንዲይዝ አድርጎታል። ይሄው ለአራት ቀናት የዘለቀው አመፅ በጁላዊያኑ የዘመን አቆጣጠር ዕሑድ የካቲት 23 የሩሲያውን ቄሳር የሴቶችን የመምረጥ መብት እንዲፈቅድ ያስገደደ ሲሆን በመንግሥት አስተዳደር ደግሞ እውቅና እንዲሰጥ ሆኗል ይህ እንግዲህ በጎርጎሳውያኑ የዘመን አቆጣጠር መጋቢት 8 መሆኑ ነው። ዓለማቀፍ የወንዶች ቀን በ 1990ዎቹ እውቅናን ካገኘበት ዕለት ጀምሮ በየዓመቱ ህዳር 19 ይከበራል፤ ምንም እንኳን እስካሁን ድረስ በተመድ እውቅናን ያላገኘ ቢሆንም ታላቋን ብሪታኒያ ጨምሮ ከ60 አገሮች በላይ የሚያከብሩት ሲሆን አላማውም "የጎልማሶችና የህፃናት ወንዶች ጤንነት" ላይ በማተኮር ፃታዊ ተግባቦትን ለማሻሻል ፆታዊ እኩልነትን ለማስፈንና አርአያ ለሚሆኑ ወንዶች እውቅና መስጠት" ላይ ያተኮረ ነው። "ጎልማሶችና ህፃናት ወንዶች ላይ ተፅእኖ መፍጠር" የ2019 ዓለም አቀፍ የወንዶች ቀን መሪ ቃል ነበር። የሴቶች ቀን ዓለም አቀፍዊ አከባበር እንግዲህ የሴቶች ቀን በብዙ አገሮች ማለት ይቻላል ብሔራዊ በዓል ሲሆን በተለይ በሩሲያ ከዕለቱ ሦስት አራት ቀን ቀደም ብሎ የአበባው ገበያ ይደራል። በቻይና ደግሞ በመንግሥት አስተዳደር በመፈቀዱ አብዛኛው ሴቶች የግማሽ ቀን ዕረፍት የሚሰጣቸው ቢሆንም በአንፃሩ ደግሞ ይህንን የማያከብሩ ቀጣሪዎችም ቁጥራቸው ቀላል አይደለም። ወደ ጣሊያን ስንመጣ ደግሞ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን አስመልክቶ ሴቶች ምሞሳ የተሰኘውን በቢጫና ሮዝ ቀለማት ያሸበረቀ አበባ በገፀ በረከትነት ያገኛሉ። ምክንያቱ በውል ባይታወቅም ይሔው ልማድ ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በሮማ እንደተጀመረ ይታመናል። በአሜሪካ ደግሞ መጋቢት ወር የሴቶች ታሪካዊ ወር ነው፤ የፕሬዝዳንቱ ቢሮም ለሴቶች ስኬትና ድል በየዓመቱ እውቅና ይሰጣል። የዘንድሮው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን "እያንዳንዳችን ለእኩልነት" የሚለውን መሪ ቃል ከፊት በማድረግ ይከበራል። የአብሮነት ህብርን እሳቤ በመመርኮዝ የተመረጠ ነው የበዓሉ ዘመቻም " ሁላችንም ባለ አሻራዎች ነን" ይላል። የእያንዳንዳችን የተናጥል እንቅስቃሴ ባህሪና ሥነ ልቦና በማኅበረሰቡ ዘንድ የሚኖረው ተፅእኖ ቀላል አይደለም። በዚህ ህብረ ቀለምም ለውጥ ማምጣት እንችላለን፤ በአብሮነት ህብርም ፆታዊ እኩልነት እንዲሰፍን መረዳዳት እንችላለን " በማለት ያትታል። ባለፉት ጥቂት ዓመታት ይሔው ዓለም አቀፋዊ በዓል ታላቅ የሚባል እምርታ ላይ ደርሷል። ለአብነት በጥቅምት ወር 2017 #እኔም [#metoo] በማለት የሴቶችን ፆታዊ ጥቃትና ትንኮሳ ለመቃወምና ለማውገዝ ሚሊዮኖች በማህበራዊ መገናኛ ገፆች ድምፃቸውን አሰምተዋል። ይሔው #እኔም እንቅስቃሴ በ2018 አድጎ አለማቀፍዊ ቅርፅ በመያዝ እንደ ህንድ ፈረንሳይና ደቡብ ኮሪያ ያሉ ሀገራት ይህንንኑ ዘመቻ ለለውጥ ተቀላቅለዋል። በአሜሪካ በሚደረገው የኘሬዝዳንቱ ሥልጣን ዘመን አጋማሽ ምርጫ ላይ የሴቶች ቁጥር ብልጫ የታየበት ነው። በሰሜን አየርላንድም የፅንስ ማቋረጥ ኢህጋዊነት ሲሻር የሱዳን ሴቶች እንዴት መልበስና መንቀሳቀስ እንዳለባቸው የሚደነግገው ህግ ምሊቀየር ችሏል።
44144425
https://www.bbc.com/amharic/44144425
ለአፍሪካውያን ስደተኛ ልጆች አደገኛ የሆነው መጠለያ
በደቡብ ቴል አቪቭ በሚገኘው አንድ አነስተኛ ቤት ውስጥ አንዲት ሴት ተቀምጣ ሌላዋ ደግሞ ሴት ምግብ ታዘጋጃለች። 20 የሚሆኑ ህጻናት በቤቱ አንድ ጥግ ላይ ተቀምጠዋል።
የእስራኤል ባለስልጣናት በሺዎች የሚቆጠሩ አፍሪካዊያን ከሃገራቸው እንዲወጡ ይፈልጋሉ አዲስ ሰው ሲያዩ "ሻሎም" ብለው በሂብሩ ሰላምታ ይሰጣሉ። ሰው እንደሚናፍቃቸው ከሰላምታ አሰጣጣቸው መረዳት ይቻላል። ከሴቶቹ አንዷ ህጻናቱን መቆጣጠር ከባድ መሆኑን ትናገራለች። በአካባቢው ይህን የመሰሉ 90 መኖሪያዎች አሉ። ቤቶቹ የአፍሪካውያን ስደተኞች ልጆች ማቆያ ናቸው። የህጻናት ማቆያዎቹ ህጋዊ ፍቃድ የላቸውም። እስራኤል ውስጥ ወደ 37,000 ሺህ የሚጠጉ አፍሪካውያን ስደተኞች አሉ። በአሁኑ ወቅት እነዚህ ስደተኞች ወዴት እንደሚሄዱ ግራ ተጋብተዋል። የእስራኤል መንግስት ወደ ሀገራቸው ሊመልሳቸው ይፈልጋል። በቅርቡ ይህ የመንግስት ውሳኔ በፍርድ ቤት መቀልበሱ ይታወሳል። በሺዎች የሚቆጠሩ ስደተኞች ልጆቻቸውን የሚያስቀምጡት በእነዚህ ቤቶች ውስጥ ነው። ቤቶቹ ለህጻናት ምቹ ባይሆኑም ስደተኞቹ አማራጭ የላቸውም። ልጆቹ በማቆያ ውስጥ ተገቢውን እንክብካቤ አያገኙም። እንደ አውሮፓውያኑ በ2015 በጠባቂዎች ቸልተኛነት አምስት ህጻናት ሞቷዋል። ኤሊፍሌት የተራድኦ ድርጅት የምትሰራው ሶፊያ የስደተኞች ልጆች አማራጭ እንደሌላቸው ትናገራለች። "መንግስት ወደ ሀገራችን ሊመልሰን ይችላል ብለው የፈሩ ወላጆች ገንዘብ ለማጠራቀም ብዙ ስለሚሰሩ ልጆቻቸውን በርካሽ ማቆያ ውስጥ ያስቀምጣሉ።"ትላለች። እንደ አውሮፓውያኑ ከ 2006 እስከ 2016 በእግር ጉዞ ቴል አቪቭ የገቡ ኤርትራውያንና ሱዳናውያን በርካታ ናቸው። ከስደተኞቹ ወደ 15 ሺህ የሚጠጉት ጥገኝነት ቢጠይቁም ፍቃድ የተሰጠው ለአስራ ሁለቱ ብቻ ነው። በርካታ አፍሪካዊያን የሚገኙበት በደቡባዊ ቴልአቪቭ የሚገኘው የሃቲግቫ ገበያ እስራኤል ለስደተኞቹ 3,500 ዶላርና የአውሮፕላን ትኬት ሰጥታ ወደ ሀገራቸው የመመለስ እቅዷን ያሳወቀችው ከወራት በፊት ነበር። ከሀገሪቱ ያልወጡ ስደተኞች ለእስርና እንግልት ተዳራገዋል። "እስራኤል ለህጋዊ ስደተኞች መጠለያ ትሆናለች። ህገ ወጦችን ግን አትቀበልም። ህገ ወጥ ስደተኞች ላይ እርምጃ እንወስዳለን።" ሲሉ ፕሬዘዳንት ቤንጃሚን ናታኒያሁ ተናግረው ነበር። ልጆቻውን በማቆያዎቹ ትተው የሚሄዱ ቤተሰቦች ዘወትር ጭንቀት ላይ ናቸው። ከእነዚህ የስድስት ወር ልጇን በማቆያው አስቀምጣ ወደ ስራ የምትሄደው ኤርትራዊት ትጠቀሳለች። "ልጄን ለማሳደግ ቀኑን ሙሉ ሳጸዳ ነው የምውለው።" በማለት ከህጻናት ማቆያው ውጪ አማራጭ እንደሌላት ትናገራለች። ሶፍያ እንደምትለው የህጻናት ማቆያዎቹ በህጻናቱ እድገትም ተጽእኖ አላቸው። "ልጆቹ ከጭንቀት ባሻገር ትምህርት በፍጥነት ያለመረዳት ችግርም ይገጥማቸዋል።" ትላለች። አብዛኞቹ ስደተኞች በሚኖሩበት የቴል አቪቭ ክፍል የሚኖሩ እስራኤላውያን ስለ ስደተኞቹ ደንታ የላቸውም፥። የጠቅላይ ሚኒስትሩን ውሳኔ የሚደግፉም ብዙ ናቸው። በሌላ በኩል አፍሪካውያኑ እየደረሰባቸው ካለው እንግልት ጀርባ ዘረኝነት አለ የሚሉም አሉ። የ 31 አመቱ ነጋዴ ዛየን ስደተኞቹን በግድ ወደየሀገራቸው መመለስ አግባብ አይደለም ብሎ ያምናል። ከሱ ጋር ተመሳሳይ ሀሳብ ያላቸው 2,500 እስራኤላውያን በቴል አቪቭ ሮቢን አደባባይ ሰላማዊ ሰልፍ ወጥተው ነበር። ሚክላት እስራኤል የተባለ ለስደተኞች ድጋፍ የሚሰጥ ተቋም ያቋቋሙት ራባይ ሱዛን ሲልቨርማን "የሒብሩ ሀይማኖት እንግዶችን እንድንቀበል ያዛል።" ይላሉ። ኤርትራውያንና ሱዳናውያን ስደተኞች የመንግስትን ውሳኔ በፍርድ ቤት አስለውጠዋል። የተባበሩት መንግስታት በበኩሉ ከስደተኞቹ መሀከል በሺዎች የሚቆጠሩትን ወደ ምዕራባውያኑ ሀገራት የመውሰድ ሀሳብ አቅርቧል። በድርድሩ የእስራኤል መንግስት ለተቀሩት ስደተኞች መጠለያ እንድትሰጥ ጠይቋል። "የፍርድ ቤቱ ውሳኔና የአልም አቀፉ ማህበረሰብ ጥያቄ ቢኖርም ህገ ወጦችን ለማስወጣት ሌሎች አማራጮች እንጠቀማለን።" ይላሉ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር። ስደተኞቹ አሁንም ግራ መጋባት ውስጥ ናቸው። ልጆቻቸውን በህገ ወጥ ማቆያዎች የሚያስቀምጡት ቤተሰቦችም እንዲሁ።
news-56249352
https://www.bbc.com/amharic/news-56249352
በኢትዮጵያ በስድስት ወራት 1 ሺህ 849 ሰዎች በትራፊክ አደጋ መሞታቸው ተገለፀ
በኢትዮጵያ በስድስት ወራት ውስጥ 20 ሺህ 672 የመንገድ ትራፊክ አደጋዎች ማጋጠማቸውን የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።
የኮሚሽኑ ወንጀል ኢንተለጀንስ ዳይሬክቶሬት የወንጀልና ትራፊክ መረጃ ትምበያ በዛሬው ዕለት በፌስ ቡክ ገጹ እንዳሰፈረው ከሐምሌ 1 ቀን 2012 እስከ ታኅሣስ 30/2013 ዓ.ም ድረስ በደረሰው አደጋ 1 ሺህ 849 ሰዎች ሞተዋል ብሏል። መረጃው የትምበያውን ተወካይ ዲቪዥን ኃላፊ ኢንስፔክተር መስፍን አይተነውን ዋቢ አድርጎ እንዳሰፈረው ከሞቱት ሰዎች ባሻገር 2 ሺህ 646 ሰዎች ከባድ የአካል ጉዳት፣ 2 ሺህ 565 ዜጎች ደግሞ ቀላል የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል ብሏል። ከዚህም በተጨማሪ 495 ሚሊዮን 240 ሺህ 473 የሚገመት ንብረት መውደሙንም ኢንስፔክተሩ መግለፃቸው ሰፍሯል። በትግራይ ክልል በተከሰተው ግጭት ምክንያት የትራፊክ አደጋ መረጃ እንዳልደረሳቸው ኢንስፔክተር መስፍን አብራርተው ከዚያ ውጭ ያሉ ክልሎችን መሰረት አድርጎ የተጠናቀረ መሆኑን ተናግረዋል። በስድስት ወር በአገሪቱ ከተመዘገቡት የትራፊክ አደጋዎች ውስጥ፣ በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ 15 ሺህ 844 የትራፊክ አደጋ የደረሰ ሲሆን ከዚህም ጋር ተያይዞ 192 ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል። በ846 ሰዎች ላይ ከባድና በ512 ቀላል ጉዳት መድረሱንም ከመረጃው መረዳት ተችሏል። ለእነዚህ አደጋዎች ምክንያት ብለው ኢንስፔክተር መስፍን በዋነኝነት የጠቀሷቸው የአሽከርካሪዎች ሥነ ምግባር ጉድለት፣ ቸልተኝነትና ብቃት ማነስ፤ የተሽከርካሪዎች የቴክኒክ ጉድለት፣ ወቅቱን የጠበቀ የቦሎ እድሳት አለማድረግ፣ የመንገድ ግንባታ ችግርና የእግረኞች የመንገድ አጠቃቀም ችግር ናቸው። "በሰዎች ህይወት፣በአካል እና በንብረት ላይ የሚደርሰውን የትራፊክ አደጋን መከላከልና መቀነስ እንዲቻል ሁሉም አሽከርካሪዎችና ግረኞች የትራፊክ ህግን አክብሮ በመንቀሳቀስ የሚጠበቅባቸውን አስተዋጽኦ ማድረግ አለባቸው" በማለት ኢንስፔክተሩ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
news-56755319
https://www.bbc.com/amharic/news-56755319
ምርጫ 2013፡ ግማሽ ያህል የምርጫ ጣቢያዎች አልተከፈቱም፣ በአፋርና በሶማሌ ምዝገባ አልተጀመረም
ሊካሄድ ሰባት ሳምንት ብቻ በቀረው ስድስተኛው አገራዊና ክልላዊ ምርጫ ላይ የመራጮች ምዝገባ ይካሄድባቸዋል ከተባሉት የምርጫ ጣቢያዎች ወደ ግማሽ የሚጠጉት አለመከፈታቸውን የምርጫ ቦርድ ገለጸ።
ምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ የመራጮች ምዝገባ ከተጀመረ ከሦስት ሳምንት በላይ ሲሆነው በተለያዩ ክልሎች ውስጥ ተከፍተው ድምጽ ሰጪዎችን ይመዘግባሉ ተብለው ከታቀዱት 50 ሺህ ያህል የምርጫ ጣቢያዎች ውስጥ በአሁኑ ጊዜ ምዝገባ እያካሄዱ ያሉት 25 ሺህ 151ዱ ሲሆኑ ከ24 ሺህ በላይ የሚሆኑት ግን ሥራ አልጀመሩም። ከዚህም ውስጥ የሶማሌና የአፋር ክልሎች ውስጥ የመራጮች ምዝገባ እንዳልተጀመረም ተገልጿል። ይህ የተገለጸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የመራጮች ምዝገባና አጠቃላይ የምርጫ ሥራዎች ሂደትን በተመለከተ በምርጫው ከሚሳተፉ ፓርቲዎች አስካሁን ያለውን ሁኔታ በገለጸበት ወቅት ነው። በግንቦት ወር መጨረሻ ላይ ከትግራይ ክልል ውጪ በመላው የአገሪቱ አካባቢዎች በ674 በሚሆኑ የምርጫ ክልሎች ባሉ 50 ሺህ በሚደርሱ የምርጫ ጣቢያዎች መራጮችን ለመመዝገብ ቢታቀድም ከግማሽ በላይ በሚሆኑት ውስጥ ብቻ ምዝገባው እየተካሄደ መሆኑ ተነግሯል። የመራጮች ምዝገባው እየተካሄደባቸው ባሉት የምርጫ ጣቢያዎችም ምዝገባው በተፈለገው መልኩ እየሄደ ነው ማለት እንደማይቻል ሰብሳቢዋ ተናግረዋል። ለማሳያነትም የአገሪቱ መዲና በሆነችውና ከአምስት ሚሊዮን በላይ ነዋሪ በሚኖርባት በአዲስ አበባ፣ ምዝገባው ከተጀመረ ከሦስት ሳምንታት በኋላ ለመምረጥ የተመዘገበው ሰው ወደ 201 ሺህ የሚጠጋ ብቻ እንደሆነ ተገልጿል። በአዲስ አበባ ከተማ 1 ሺህ 848 የምርጫ ጣቢያዎች ተከፍተው መራጮችን ይመዘግባሉ ተብሎ ቢታቀድም፣ ባለፉት ሳምንታት ውስጥ 186 ጣቢያዎች እንዳልተከፈቱ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አመልክቷል። መጋቢት 16 የተጀመረው የመራጮች ምዝገባ ሊጠናቀቅ 10 ቀናት ያህል የቀሩት ሲሆን በቀሩት ቀናት ውስጥ የሚጠበቀውን ያህል ሰዎች ካልተመዘገቡ በቀጣይ ምን አማራጮች እንዳሉ ገና የተገለጸ ነገር የለም። ምርጫና የፀጥታ ሁኔታ የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ የመራጮች ምዝገባ በሁሉም ጣቢያዎች መካሄድ ያልተቻለው በተለያዩ ችግሮች ምክንያት እንደሆነ ገልጸው፤ ከዚህም ውስጥ በ4126 የምርጫ ጣቢያዎች በጸጥታ ችግር ምክንያት የመራጮች ምዝገባ እየተካሄደ እንዳልሆኑ አመልክተዋል። በዚህም ሳቢያ የመራጮች ምዝገባ ሂደት በተለያዩ አካባቢዎች በተፈለገው ፍጥነት እየተከናወነ እንዳልሆነ ወ/ት ብርቱካን ተናግረው፤ ለዚህም በበርካታ ቦታዎች ላይ ባጋጠሙ የጸጥታና የትራንስፖርት ችግሮች የተነሳ ለምዝገባው የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶችን ማድረስ ባለመቻሉ የምርጫ ጣቢያዎችን መክፈት አልተቻለም ብለዋል። በዚህም መሠረት በጸጥታ ችግር ምክንያት የመራጮች ምዝገባ እየተካሄደባቸው ካልሆኑት ስፍራዎች መካከል በኦሮሚያ ክልል አራት ዞኖች ሲኖሩ እነሱም ምዕራብ ወለጋ፣ ምሥራቅ ወለጋ፣ ሆሮጉድሩ እና ቄለም ወለጋ፤ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ፣ የኦሮሞ ብሔረሰብ ልዩ ዞን፣ አርጎባና ዋግ ኽምራ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በመተከል እና በካማሺ እንዲሁም ደቡብ ክልል ጉራፈርዳ፣ ሱርማና ዘልማም እንደሆኑ ሰብሳቢዋ ገልጸዋል። ከእነዚህ ውስጥም የመራጮች ምዝገባ ተጀምረው እንዲቋረጡ የተደረገባቸው ሲኖሩ በተጨማሪም በአንዳንድ ስፍራዎች መልሰው እንዲጀመሩ የተደረጉ እንዳሉ ተመልክተዋል። ከጸጥታ ችግር ጋር በተያያዘ የመራጮች ምዝገባ ማድረግ ካልተቻለባቸው ስፍራዎች ባሻገር በትራንስፖርት ችግር አስፈላጊ ቁሳቁሶችን ባልደረሱባቸው አካባቢዎች አስፈላጊውን ጥረት በማድረግ የምርጫ ጣቢያዎቹ እንዲከፈቱ እንደሚደረግ ሰብሳቢዋ ተናግረዋል። ነገር ግን ቦርዱ በቀጣይነት በሚያደርገው ውይይት የመራጮች ምዝገባ ቀናትን እና ተያያዥ ጉዳዮችን አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት እንደሚመክርና በአጠቃላይ የምርጫ ጣቢያዎችን መክፈት እንዲሁም ምዝገባን በተመለከተ የሚቀጥሉት ሰባት ቀናት የሚኖረውን ሁኔታ እንደሚያሳወቅ ተገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድም ሕዝቡ በአገራዊው ምክር ቤትና ለክልሎች ምክር ቤቶች ተወካዮቹን ለመምረጥ እንዲችል ቀድሞ እንዲመዘገብ በማኅበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ላይ መልዕክት አስፍረዋል። "ዜጎች የመምረጥ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በመጠቀም ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ይጠበቃል። የአገራችንን የነገ ዴሞክራሲ ለመወሰን፣ ዛሬ የመራጮች ምዝገባ መታወቂያ ካርድ እናውጣ። ካርድ ለማውጣት ነገ አትበሉ፤ ነገ ከዛሬ ይጀምራል" በማለት ጠቅላይ ሚኒስትሩጥሪ አቅርበዋል። ሊካሄድ ሰባት ሳምንታት ያህል በቀሩት አገራዊ ምርጫ ላይ 50 ሚሊዮን የሚሆኑ ሰዎች ድመጻቸውን ይሰጣሉ ተብሎ የሚጠበቅ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት እየተካሄደ ባለው የመራጮች ምዝገባ ላይ በተለያዩ ምክንያቶች በርካታ የምርጫ ጣቢያዎች ሥራ አለመጀመራቸው ተገልጿል። ቀኑ እስካልተራዘመ ድረስ የምርጫ ቦርድ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት መጋቢት 16 የመራጮች ምዝገባ በተጀመረባቸው የምርጫ ጣቢያዎች ምዝገባው በመጪው ሳምንት አርብ ሚያዚያ 15/2013 ዓ.ም የሚጠናቀቅ ይሆናል። ምርጫ 2013 ባለፈው ዓመት ሊካሄድ ታቅዶ የነበረው አገራዊና ክልላዊ ምርጫ በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ስጋት ምክንያት ወደዚህ ዓመት ከተሸጋገረ በኋላ፤ በመጪው ግንቦት ማብቂያና በሠኔ ወር መጀመሪያ ላይ ለማካሄድ የጊዜ ሰሌዳ ወጥቶለት የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስፈላጊውን ዝግጅት እያካሄደ መሆኑ ይታወቃል። ባለው ወቅታዊ ሁኔታ ምክንያት ከትግራይ ክልል በስተቀር በሌሎቹ የአገሪቱ ክፍሎች ይካሄዳል በተባለው በዚህ ምርጫ 50 ሚሊዮን መራጮች ማለትም ከአገሪቱ ሕዝብ ወደ ግማሽ የሚጠጋው ድምጽ በመስጠት ይሳተፋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ምርጫ ቦርድ ገልጿል። በምርጫው ከሚሳተፉት 47 የፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል በርካታ ቁጥር ያላቸውን ዕጩዎች በማቅረብ በኩል ገዢው ፓርቲ ብልጽግና 2432 ዕጩዎችን በማስመዝገብ ቀዳሚው መሆኑ በመግለጫው ላይ ተመልክቷል። ከዚህ አንጻር ከብልጽግና በመከተል ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን ዕጩዎች በማስመዝገብ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) 1385 ዕጩዎችን እንዲሁም እናት ፓርቲ ደግሞ 573 ዕጩዎችን አስመዝግበዋል። ሦስቱን ፓርቲዎች ጨምሮ በምርጫው ለመወዳደር በፓርቲና በግል ለመወዳደር ከስምንት ሺህ ሁለት መቶ በላይ ዕጩዎች መመዝገባቸውን ምርጫ ቦርድ አስታውቋል።
news-55451433
https://www.bbc.com/amharic/news-55451433
የጣት አሻራ አልባው ቤተሰብ
አፑ ሳርከር 22 ዓመቱ ነው። ባንግላዲሽ በሚገኘው ናቶሬ ግዛት ከቤተሰቡ ጋር ይኖራል።
የሰው ልጆች አንዳቸው ከሌላቸው የሚለዩበት የጣት አሻራ በእነአፑ ቤተሰብ ውስጥ አይታወቅም። አፑና ቤተሰቡ ከአብዛኞቻችን ይለያሉ። አሻራ የላቸውም። የሰው ልጆች አንዳቸው ከሌላቸው የሚለዩበት የጣት አሻራ በእነአፑ ቤተሰብ ውስጥ አይታወቅም። አፑ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በሕክምና ባለሙያዎች ተባባሪነት ይሠራ ነበር። አባቱና አያቱ አርሶ አደሮች ናቸው። ቤተሰቡ ውስጥ ያሉት ወንዶች የጣት አሻራን የሚያጠፋ የዘረ መል መዋቅር ነው ያላቸው። ይህ በመላው ዓለም በጣም ጥቂት ሰዎች ላይ ብቻ የሚከሰት ነው። የአፑ አያት ያለ ጣት አሻራ መወለዳቸው ብዙም አይገርማቸውም ነበር። የእለት ከእለት ሕይወታቸውን ከማከናወንም አላገዳቸውም። በዚህ ዘመን ግን ነገሮች ተለውጠዋል። የጣት አሻራ መታወቂያ ለማውጣት እና ለሌሎችም ክንውኖች ቁልፍ ግብአት ነው። የአንድ ማኅበረሰብ ነዋሪዎችን በአስተዳደራዊ መዋቅር ለመመዝገብ እጅግ አስፈላጊ ከሆነው የግል መረጃ አንዱ አሻራ ነው። የጣት አሻራ በዓለም ላይ በስፋት ከተመዘገቡ የግል መረጃዎች ቀዳሚነቱን ይዟል። የጣት አሻራ ምዝገባ በምርጫ ድምጽ ለመስጠት፣ በአውሮፕላን ለመጓጓዝ፣ ተንቀሳቃሽ ስልክ ለመክፈት ወዘተ. . . ይውላል። "አሻራ ስለሌለኝ መንጃ ፍቃድ ማግኘት አልቻልኩም" እአአ በ2008 ባንግላዲሽ የብሔራዊ መታወቂያ ሥርዓት ዘረጋች። መታወቂያ ለማውጣት አሻራ መስጠት ግዴታ ነበር። የቀበሌ ሠራተኞች የአፑ አባት አማል ጣት ላይ አሻራ ሲያጡ ግራ ገባቸው። አማራጭ ስላልነበራቸው መታወቂያው ላይ 'አሻራ አልባ' ብለው ጻፉበት። 2010 ላይ ደግሞ ፓስፖርትና መንጃ ፍቃድ ለማውጣት አሻራ ያስፈልጋል የሚል መርህ ወጣ። አማል ከሕክምና ባለሙያዎች የተሰጣቸውን አሻራ አልባለታቸውን የሚያረጋግጥ ሰነድ ይዘው መንጃ ፍቃድ ለማውጣት ሄዱ። ብዙ ጊዜ መመላለስ ነበረባቸው። "ክፍያ ፈጽሜ፣ ፈተና ወስጄ ባልፍም አሻራ ስለሌለኝ መንጃ ፍቃድ ማግኘት አልቻልኩም" ይላሉ። ሞተር ሳይክል መንዳት የሚመርጡት የጣት አሻራ የሚጠይቃቸው ስለሌለ ነው። መኪና ሲነዱ መንጃ ፍቃድ ለማውጣት የከፈሉበትን ደረሰኝ ይዘው ነው። ትራፊክ ሲያስቆማቸው ሁኔታውን ለማስረዳት ቢጣጣሩም፤ የሚረዷቸው ፖሊሶች ጥቂት ናቸው። ከዚህ ቀደም ከአንድም ሁለቴ የትራፊክ ፖሊስ ገንዘብ ቀጥቷቸዋል። "በጣም የሚሰለቸኝ ሁኔታዬን ለእያንዳንዱ ሰው ደጋግሞ ማስረዳት ነው" 2016 ላይ ባንግላዲሽ ውስጥ ሲም ካርድ ለማውጣት አሻራ መስጠት ግዴታ ሆነ። ይህ ሕግ ለአማል ልጅ አፑ መሰናክል ነበር። "የጣት አሻራ የሚሰጥበት መተግበሪያ ላይ መዳፌን ሳስቀምጥ ምንም አያነብም" ሲል አፑ ያስታውሳል። እሱና ሌሎቹም የቤተሰቡ ወንድ አባላት አሻራ ስለሌላቸው ሲም ካርድ ማውጣት አልቻሉም። እናም የሁሉም ሲም ካርድ የተመዘገበው በእናትየው ስም ነው። እንደነሱው ሁሉ የጣት አሻራ የሌላቸው ሰዎች በእንግሊዘኛው Adermatoglyphia የሚባል የዘረ መል መዋቅር አላቸው። ችግሩን የደረሰበት ስዊዛዊው የቆዳ ሀኪም ፕ/ር ፒተር ሊቲን ነው። አንዲት ወጣት አሜሪካ መግባት እንዳልቻለች ስትገልጽለት ነበር ምርምር የጀመረው። ይህቺ ሴትና ሌሎች ስምንት ቤተሰቦቿ አሻራ የላቸውም። ጣቶቻቸው ባለ መስመር ሳይሆን ልሙጥ ናቸው። እጃቸው ውስጥ ያሉ ላብ አመንጪ ህዋሳትም ጥቂት ናቸው። ሰባት አሻራ ያላቸው እና ዘጠኝ አሻራ አልባ የቤተሰቡ አባላት ላይ የዘረ መል ምርመራ ከተደረገ በኋላ ነበር ውጤቱ የተገኘው። ፕ/ር ፒተር ለቢቢሲ እንደተናገረው፤ እስካሁን የጣት አሻራ አልባ ተብለው የተመዘገቡ ቤተሰቦች በጣም ውስን ናቸው። የጣት አሻራ የሌላቸው ሰዎች ተያያዥ ህመም እንደሌላቸው ያስረዳሉ። ፕሮፌሰሩ ይህንን የቆዳ ሁኔታ "ጉዞ አሰናካዩ ህመም" ሲሉ ይጠሩታል። አንድ ሰው አሻራ ከሌለው በአውሮፕላን ከቦታ ቦታ ለመጓጓዝ እንደሚቸገር ከግምት በማስገባት ነው ስሙን ያወጡለት። ህመሙ በአንድ ቤተሰብ ውስጥ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሊሸጋገር ይችላል። የእነአፑ ቤተሰብ ቆዳቸው ይደርቃል። ብዙም አያልባቸውም። ፕ/ር ፒተር የቤተሰቡ ቆዳ ላይ ምርምር መሥራት እንደሚፈልጉ ተናግረዋል። የአፑ አባት በእሳቸው ዘመን ያለ ጣት አሻራ መኖር ብዙም እንደማይከብድ በማስታወስ፤ ለልጆቻቸው ይሰጋሉ። እያንዳንዱ እንቅስቃሴ ከአሻራ ጋር እየተሳሰረ በመጣበት በዚህ ዘመን የወንድ ልጆቻቸው እጣ ፈንታ ምን እንደሚሆን አሳስቧቸዋል። አማል እና አፑ የሕክምና ማስረጃ አሳይተው በቅርቡ ልዩ ብሔራዊ መታወቂያ ተሰጥቷቸዋል። መታወቂያው በጣት አሻራ ምትክ ፊት የሚያነብ ነው። "በጣም የሚሰለቸኝ ሁኔታዬን ለእያንዳንዱ ሰው ደጋግሞ ማስረዳት ነው። ሌላ አማራጭ ካላገኘሁ ጉዳዩን ፍርድ ቤት እወስደዋለሁ" ይላል አፑ። በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ፓስፖርት አውጥቶ ከባንግላዲሽ ውጪ የሚጓዝበትን ይናፍቃል።
news-44653477
https://www.bbc.com/amharic/news-44653477
የአውሮፓ ኀብረት በስደተኞች ጉዳይ ከስምምነት ደረሰ
የአውሮፓ ኅብረት ከእልህ አስጨራሽ ድርድርና ውይይት በኋላ በስደተኞች ጉዳይ ከስምምነት ደርሷል።
በቤልጅየም ብራስልስ የተሰበሰቡት የአውሮፓ መሪዎች 10 ሰዓታት የፈጀ ውይይት ካደረጉ በኋላ ነው ስምምነት ላይ የደረሱት። ጣሊያን ወደ አገሯ ባሕር አቋርጠው የሚገቡ ስደተኞችን በመቀበል ረገድ ሌሎች የኀብረቱ አባላት የማያግዟት ከሆነ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብቷን ተጠቅማ ውሳኔውን እንደምትቀለብስ ማስፈራሪያ ስታቀርብ ነበር። በኢትዮጵያ ስላሉ ስደተኞች አንዳንድ ነጥቦች አሁን አዲሱ ስምምነት የስደተኛ መቀበያ ማዕከላት በሁሉም የኅብረቱ አገራት እንዲቋቋም የሚያበረታታ ነው። አገራቱ ማዕከላቱን ለማቋቋም አስገዳጅ ግዴታ ውስጥ ባይገቡም በፍቃደኝነት ላይ ተመሥርተው ግን ይህንኑ እንዲያደርጉ ስምምነቱ ያበረታታል። እነዚህ ወደፊት የሚቋቋሙት የስደተኛ ማዕከላት ማን ወደ አገሩ መመለስ እንዳለበትና የትኛው ስደተኛ ከለላ ማግኘት እንዳለበት ይወስናሉ፤ የማጣራት ሥራውንም ያሳልጣሉ ተብሏል። የአውሮፓ ካውንስል ፕሬዚዳንት አገራቱ በመጨረሻ ከብዙ ውጣ ውረድ በኋላ ከስምምነት መድረሳቸውን ያሳወቁት ከሰዓታት በፊት በትዊተር ገጻቸው ነው። የ28 አገራት የኅብረቱ መሪዎች የስደተኛ ማዕከላትን ከማቋቁም ስምምነት ባሻገር ቱርክ፣ ሞሮኮና ሌሎች የሰሜን አፍሪካ አገራት ድንበሮቻቸውን እንዲቆጣጠሩ የሚያግዝ የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ የኅብረቱ አገራት ከስምምነት ደርሰዋል። ጣሊያንና ግሪክ ሌሎች አገሮች የስደተኞችን ጉዳይ በተመለከተ እገዛ እስካላደረጉ ድረስ ምንም ዓይነት ስምምነት ላለመፈረም ሲዝቱ ነበር። ስደተኞች ለምጣኔ ሃብት አስተዋፅኦ እያበረከቱ ነው የሰሀራ በረሐን በክራች ያቋረጡት ስደተኞች የጀርመኗ መራሂተ መንግስት አንጌላ ሜርከል ከስብሰባው ቀደም ብሎ የስደተኞች ጉዳይ የኅብረቱን ሕልውና የሚወስን ሊሆን እንደሚችል ጠቁመው ነበር። የፖለቲካ ተንታኞች አውሮፓ ኅብረት የስደተኞች ጉዳይ ቀውስ ውስጥ ሊከተው እንደሚችልም ሲተነብዩ ሰንብተዋል። ሜርክል ወደ ስብሰባው ከመሄዳቸው በፊት ጀርመን ምንም ዓይነት ተጨማሪ ስደተኞችን እንዳይቀበሉ ግፊት ሲደረግባቸው ቆይቷል። በኀብረቱ አገራት የተመዘገቡ ስደተኞች እያሉ ጀርመን አዳዲስ ስደተኞችን ተቀብሎ የማስተናገዷን ሐሳብ በርካታ የኅብረቱ አገራት ሲቃወሙት ሰንብተዋል። የጀርመን ጣምራ መንግሥትን ከመሠረቱት ውስጥ አንዱ ሲኤስዩ ሜርከል በስደተኞች ላይ መጨከን ካልቻሉ ጥምረቱን እንደሚያፈርስ ሲዝት ነበር። ፓርቲው ከጥምረቱ ከወጣ ደግሞ የሜርክል መንግሥት የምክር ቤቱን ብዙኃን መቀመጫን ስለሚያጣ አገሪቱን ለመምራት ይቸገራል። የሕገወጥ ስደተኞች ወደ አውሮፓ ጉዞ አሁን አሁን እየቀነሰ መምጣቱ ተነግሯል። በ2015 ወደ አውሮፓ የሚገቡ ሕገወጥ ስደተኞች የኅብረቱን አገራት መጠኑ ከፍ ያለ ፖለቲካዊ ቀውስ ውስጥ ጥሏቸው ቆይቷል። ከዚያ ወዲህ ግን ወደ ኅብረቱ አገራት የሚገቡ ከለላ ፈላጊዎች ቁጥራቸው በ96 በመቶ እየቀነሰ መምጣቱ ይነገራል። በዚህ ወር ጣሊያን ለስደተኞች ድጋፍ የሚሰጠውንና የሚታደገውን የጀርመን ግብረሰናይ መርከብ ወደ አገሯ እንዳይጠጋ ከከለከለች በኋላ በአገራት መካከል ከረር ያለ አለመግባባት ተከስቶ ነበር። በመጨረሻም ስደተኞችን የሚታደገው መርከብ በማልታ መልህቁን እንዲጥል ዲፕሎማሳዊ ስምምነት ተደርሷል። ኖርዌይም የተወሰኑ ስደተኞችን ለመቀበል ተስማምታለች።
news-53349861
https://www.bbc.com/amharic/news-53349861
የሜላንያ ትራምፕ ሃውልት በትውልድ አገሯ ስሎቫንያ ተቃጠለ
ከእንጨት የተሰራው የአሜሪካዊት ቀዳማዊት እመቤት ሜላንያ ትራምፕ ሃውልት በትውልድ አገሯ ስሎቫንያ ከሰሞኑ ተቃጥሏል።
የሃውልቱ ቀራፂ ብራድ ዶውኒይ እንዳለው ሃውልቱን ያቃጠሉት ሰዎች አሜሪካ የነፃነት ቀኔ ነው ብላ የምታከብረውን ክብረ በዓልም ለመቃወም ነው ብሏል። በበርሊን መቀመጫውን ያደረገው ይህ አርቲስት የሃውልቱን ቀሪ አካልም በነገታው ሙሉ በሙሉ እንዲወገድ አድርጓል። ሃውልቱንም ያቃጠሉ ግለሰቦችንም ፖሊስ እየፈለገና ምርመራ መክፈቱንም ሮይተርስ ዘግቧል። በሃውልቱ መቃጠል ዙሪያ ዋይት ሃውስ አስተያየት ከመስጠት ተቆጥቧል። ሃውልቱ በትውልድ ቦታዋ በስሎቫንያ ማዕከል ሰቭኒካ ይገኝ የነበረ ሲሆን ከዛፍ ግንድም ተቀርፆ ነበር የተሰራው። ሃውልቱ የአሜሪካ ቀዳማዊት እመቤት ሰማያዊ ኮት ለብሳ እጆቿን ወደላይ (ወደ ሰማይ) ዘርግታም የሚያሳይ ነው። በባለፈው አመትም ሲተከል ውዝግቦችን አስከትሎ ነበር። ቀራፂው ለሮይተርስ እንደተናገረው ሃውልቱን ያቃጠሉት ሰዎች "ለምን እና እነማን እንደሆኑ ማወቅ እፈልጋለሁ" ብሏል። ሃውልቱ በአሜሪካ ውስጥ ያለውን ፖለቲካዊ ሁኔታ በተለይም ስደተኞች ጋር የተያያዘ ፖሊሲን አስመልክቶ ውይይት ይከፍታል የሚል ሃሳብ እንደነበረውም ተናግሯል። የዩጎዝላቪያ አካል በነበረችው ስሎቫንያ የተወለደችው ሜላንያ ወደ አሜሪካ የተሰደደችውም ከሁለት አስርት አመታት ነበር። ቀዳማዊት እመቤቷ የፋሽን ሞዴል ነበረች። ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት መሆናቸውንም ተከትሎ የቀዳማዊት እመቤቷ ትውልድ ቦታ የበርካታ ቱሪስቶች መናኸሪያም ሆና ነበር። በባለፈው አመትም በስሎቫኒያ መዲና ልጁብልጃና የዶናልድ ትራምፕም ከእንጨት የተሰራ ሃውልትም ቆሞ ነበር። እንደ ሜላንያ የትራምፕ ሃውልትም በርካታ ውዝግቦችን የያስነሳ ሲሆን፤ ስምንት ሜትር እርዝማኔ ያለው ይህ ሃውልትም በእሳት የወደመው ከወራት በፊት ነው።
news-45911130
https://www.bbc.com/amharic/news-45911130
መስመር ያልያዘው የኢትዮ-ኤርትራ የንግድ ግንኙነት ወዴት ያመራል?
የኤርትራ ነፃነቷን ካወጀች በኋላ የሁለቱን ሃገራት የንግድ ግንኙነት ምን መልክ ሊኖረው እንደሚገባ በውል ውይይት ተደርጎበት መልክ እንዲይዝ አልተደረገም።
የንግድ ልውውጡ መንገድ ላይ ጭምር ይካሄዳል ሁለቱም ራሳቸውን የቻሉ ሃገራት ከሆኑ ከዓመታት በኋላም የሚኖራቸው የገንዘብ ልውውጥ በምን መልኩ መካሄድ እንደለበት ምንም ዓይነት ስምምነት ላይ አልተደረሰም ነበር። በወቅቱ የሁለቱ ሃገራት ምጣኔ ኃብታዊና የንግድ ግንኙነት በተጠናና ግልጽ በሆነ መንገድ አለመመራቱ ደግሞ ለደም አፋሳሹ ግጭት አንድ መንስኤ መሆኑን በርካታ ጉዳዩ በቅርበት የተከታተሉ ምሁራን ይገልፃሉ። በዚሁም ሳቢያ በተቀሰቀሰው ጦርነት በአስር ሺዎች የሚቆጠር ህይወት ሲጠፋ ሃገራቱ ከ20 ዓመታት በላይ በፍጥጫ ውስጥ ቆይተዋል። • ኢትዮጵያዊያን በህጋዊ መንገድ ለሥራ መሄድ የሚችሉባቸው ሃገራት የትኞቹ ናቸው? • በሥራ ቃለ መጠይቅ ወቅት ልንላቸው የማይገቡ 7 ነጥቦች ዛሬስ ሃገራቱ ሰላም አውርደው ድንበራቸውን ክፍት ካደረጉ በኋላ ጠባሳውን ለማሻርና ይበልጥኑም ግንኙነታቸውን ለማደስ በያሚደርጉት ጥረት ውስጥ የምጣኔ ሃብት ግንኙነቱ እንዴት እየተከናወነ ነው? ድንበሩ በይፋ መከፈቱን ከታወጀበት ደቂቃ ጀምሮ በድንበር አካባቢ ከሚኖረው ህዝብ አልፎ የንግድ ግንኙነት በርካቶችን እየሳበ ነው። ነገር ግን ይህ ንግድ በምን መልኩ ነው እየተካሄደ ነው ያለው የሚለው ጥያቄ አሁን ማነጋገር ጀምሯል። ማን ምን ይፈልጋል ኤርትራዊው ገብረመስቀል መኪናውን መቐለ ከተማ መሃል መንገድ ላይ አቁሞ የተለያዩ ጫማዎች ይሸጣል። ጫማዎቹ ከዱባይ የመጡ መሆናቸውንና በምትኩም እሱና መሰሎቹ ደግሞ ጤፍ፣ ብሎኬትና ጣውላ ይዘው ወደ ኤርትራ እንደሚመለሱ ለቢቢሲ ተናግሯል። ገብረመስቀል እንደሚለው ድንበር ተከፍቶ የንግድ ልውውጡ እነደተጀመረ የዋጋ ጭማሪ ታይቶ እንደነበርና በአሁኑ ሰዓት ግን እየተረጋጋ እንደሆነ ምሳሌዎችን ጠቅሶ ይናገራል። "ለምሳሌ አንደኛ ደረጃ ጤፍ እስከ 3300 ናቕፋ ይሸጥ እንደነበር አስታውሶ በአሁኑ ሰዓት ግን 2500 በመሸጥ ላይ ይገኛል። 33 ናቕፋ ይሸጥ የነበረው አንድ ብሎኬት በአሁኑ ሰዓት 25 ናቕፋ ሆኗል፤ ስለዚህ ዋጋው እየቀነሰና እየተረጋጋ ነው'' ብሏል። አቶ ሳምሶን አብርሃ በበኩሉ ከኤርትራ የታሸገ የወተት ዱቄት፣ የተለያዩ የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች፣ በጎች፣ ጫማዎችና አልባሳት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ፤ በአንፃሩ ደግሞ ጤፍ፣ ፍርኖ ዱቄት፣ ብስኩት፣ ስሚንቶና ሌሎች የግንባታ ቁሶችኘን ወደ ኤርትራ በመጓጓዝ ላይ እንደሚገኙ ያስረዳል። • «ዶ/ር ዐብይ ተገዳዳሪያቸውን ስልታዊ በሆነ መልኩ እያገለሉ ነው» ዶ/ር ደሣለኝ ጫኔ • ሞባይል ስልክዎ ላይ መከራን አይጫኑ አቶ ፋሲል መንገሻ የተባሉ ሌላው ኤርትራዊ ደግሞ "የድንበሩ መከፈት ሁለቱንም ህዝቦች አስደስቷል፤ ይህም ሁለቱም ህዝቦች እንደ ልባቸው እንዲገበያዩ አስችሏል። ድንበሩ እንደማይዘጋና የንግድ ግንኙነቱ በምን መልኩ እንደሚቀጥል በቂ ማብራሪያ መሰጠት አለበት" ብሏል። የገንዘብ ምንዛሬ ድንበሩ እንደተከፈተና የንግድ ልውውጡ እንደተጀመረ ዛላምበሳ ከተማ ውስጥ ብርና ናቕፋ እኩል አንድ ለአንድ ይመነዘር እንደነበር በወቅቱ በንግድ ልውውጡ ተሳታፊ የነበሩ ሰዎች ይናገራሉ። በአሁን ግን በተለያዩ የትግራይ ከተሞች የተለያየ የምንዛሬ መጠን እንዳለ ለማረጋገጥ የጠየቅናቸው ነዋሪዎች አረጋግጠውልናል። ለምሳሌም በዓዲግራት ከተማ አንድ መቶ ናቕፋ በአንድ መቶ ሰማንያ ብር ይመነዘራል። ከዓዲግራት ወደ አስመራ በሚወስደው መንገድ ላይ በምትገኘው ቀርሰበር በተባለችው አነስተኛ ከተማ ደግሞ አንድ መቶ ናቕፋ በአንድ መቶ ስድሳ ብር፣ መቐለ ከተማ ውስጥ አንድ መቶ ናቕፋ ሁለት መቶ ብር መድረሱን ቢቢሲ ያነጋገራቸው ሰዎች ገልፀዋል። ነዳጅ ለመቅዳት የተሰለፉ መኪኖች የነዳጅ እጥረትና ወረፋ ድንበሩ ከተከፈተ በኋላ ባለመኪኖች ወደ ሁለቱም ሃገሮች ለመንቀሳቀስ ግማሽ ቀን ብቻ ነው የሚፈጅባቸው። አሁን ላይ አዲስ አበባን ጨምሮ ኢአር የሚል የሰሌዳ ቁጥር መለያ ያላቸው መኪኖች በተለያዩ የትግራይ ከተሞች ማየት የተለመደ ሆኗል። በተለይም ከኤርትራ የሚመጡ የመኪና ባለቤቶች በነዳጅ እጥረት ምክንያት አብዛኛዎቹ መኪኖቻቸው ቆመው እንደነበረ ይናገራሉ። ይህም ድሮም እጥረት ተለይቶት የማያውቀውን የነዳጅ ገበያ አጨናንቆታል ይላሉ ነዋሪዎች። • "የመከላከያ ሚኒስቴርን በተሻለ መልኩ መምራት ይቻላል" ኢንጂነር አይሻ መሀመድ • ዛሚ ሬዲዮ ሊዘጋ ይሆን? በጣም ብዙ ሰዎች ነዳጅ ለመሙላት ሦስት ቀናትን ወረፋ ላይ እንደሚያሳልፉ ለቢቢሲ ተናግረዋል። በተለይ ባለ ባጃጆች ክፉኛ ተማረዋል። በዚህም ሰርተው የቤትና የባጃጅ ኪራይ ለመክፈል እንደተቸገሩም ይናገራሉ። ድንበሩ እንደተከፈተ በጣም ብዙ ሰዎች በበርሜልና በጀሪካን ነዳጅ ሞልተው በመኪና በመጫን ወደ ኤርትራ ሲያጓጉዙ እንደነበር አንዳንዶች ያስታውሳሉ። ይህ ደግሞ በነበረው እጥረት ተጨማሪ ጫና መፍጠሩን ያመለክታሉ። ከምጣኔ ኃብት አንፃር እንዴት ይታያል? ቢቢሲ ያነጋገራቸው የምጣኔ ኃብት ምሁር ዶ/ር ተስፋማርያም መሓሪ "አሁን ላይ እየታየ ያለው ግኑኝነት ጊዜያዊ ነው፤ መደበኛም አይደለም። ቢሆንም የንግድ ግንኙነቱ ሕጋዊ አሰራር ካልተከተለ አለመስማማትን ይፈጥራል" ሲሉ ያላቸውን ስጋት ይናገራሉ። ዶ/ር ተስፋማርያም የቀደመው ጦርነት መነሻን አሁኑ ካለው ሁኔታ ጋር ያመሳስሉታል። "በወቅቱ ሁለቱ ሃገራት አዲስ የገንዘብ ኖቶችን ማሳተማቸው፣ የገንዘብ ምንዛሬ መጠንና የሚገበያዩበት ገንዘብ ለግጭቱ መንስኤ እንደነበረ መታወቅ አለበት" ሲሉ እምነታቸውን ይገልፃሉ። ስለዚህ ከዚህ በኋላ ተመሳሳይ አለመግባባትና ግጭት እንዳይፈጠር ከወዲሁ ሕጋዊና መደበኛ አሰራር ላይ አጽንኦት ተሰጥቶ መስራት ይኖርበታል ሲሉ ይመክራሉ ዶ/ር ተስፋማሪያም።
54263199
https://www.bbc.com/amharic/54263199
ዶ/ር ቴድሮስ እና ዘ ዊኬንድ በታይም መጽሔት የዓመቱ ተጽእኖ ፈጣሪ ዝርዝር ውስጥ ተካተቱ
የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክትር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም እና ታዋቂው ዘፋኝ 'ዘ ዊኬንድ' በታይም መጽሔት የዓመቱ የዓለማችን 100 ተጽእኖ ፈጣሪ ሰዎች ዝርዝር ውስጥ ተካተቱ።
ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ከኮሮናቫይረስ የዓለምን ሕዝብ ለመታደግ ከፊት መስመር ሆኖ ትግል የሚያደርገውን የዓለም ጤና ድርጅትን የሚመሩት ኢትዮጵያዊው ዶ/ር ቴድሮስ እና ከትውልደ ኢትዮጵያዊያን ቤተሰብ የተገኘው ካናዳዊው ዘፋኝ አቤል ተስፋዬ በመድረክ መጠሪያው 'ዘዊኬንድ' በዝርዝሩ ውስጥ ይገኛሉ። እውቁ ታይም መጽሔት በየዓመቱ በተለያዩ ዘርፎች የዓመቱ ተጽእኖ ፈጣሪ ናቸው የሚላቸውን የ100 ሰዎች ስም ዝርዝርን ይዞ ይወጣል። በዚህ ዝርዝር ውስጥ የአገራት እና የድርጅት መሪዎች፣ ሥራ ፈጣሪዎች፣ የእንቅስቃሴ መሪዎች፣ አርቲስቶች እና ስፖርተኞች እንዲሁም ጸሐፊዎች ይካተቱበታል። የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም በታይም መጽሔት የ2020 ተጽእኖ ፈጣሪ ዝርዝር ውስጥ የተካተቱት ሰዎች በእኩልነት የጤና አገልግሎት እንዲያገኙ ባበረከቱት አመራር ነው። "አስቸጋሪ ወቅቶች ማንነታችን ቁልጭ አድርገው ያሳያሉ። ኮቪድ-19 ለዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ወሳኝ ከስተት ነው። ልምድ ያካበቱት ተመራማሪው እና የሕብረተሰብ ጤና መሪው ዶ/ር ቴድሮስ ለኮቪድ-19 የበለጠ ተጋላጭ የሆኑ ሰዎችን ካልጠበቅን ሁላችንም ለበሽታው ተጋላጭ እንደሆንን ያውቃሉ" ሲሉ ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖምን ለታይም የዓመቱ ተጽእኖ ፈጣሪ ዝርዝር ውስጥ እንዲከታቱ ያጩት ናይጄሪያዊቷ ጎዚ ኦኮንጆ-ኢዌላ ጽፈዋል። ዓመቱ ለዶ/ር ቴድሮስ የፈተናና የስጋት ባቻ ሳይሆን ከፍተኛ እውቅናን የተጎናፈፉበት ነው። ከእነዚህም መካከል ትናንት የ2020 "ብሪጅ ሜከር አዋርድ" ሽልማታቸውን ከፈረንሳይ መቀበላቸው ይታወሳል። በዝርዝሩ ውስጥ ከተካተቱት የአገራት መሪዎች መካከል የጀርመኗ መረሂተ መንግሥት አንጌላ መርክል፣ የብራዚሉ ፕሬዝደንት ጄይል ቦልሶናሮ፣ የሕንዱ ጠቅላይ ሚንስትር ናሬንድራ ሞዲ፣ የዲሞክራት የፕሬዝደንት እጩ ጆ ባይደን፣ የአሜሪካ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ናንሲ ፔሎሲ፣ የፓሪስ ከተማ ከንቲባ አን ሂዳልጎ፣ በአሜሪካ የዩናትድ አረብ ኤሜሬትስ አምባሳደር የሱፍ አል ኦታይባ ተጠቃሽ ናቸው። ዘ ዊኬንድ ከ15 በላይ እውቅ የጥበብ ሰዎች የተዘረዙ ሲሆን ከትውልደ ኢትዮጵያዊያን ቤተሰብ የተገኘው 'ዘ ዊኬንድ' አቤል ተስፋዬ ከዝርዝሩ አናት ላይ ተቀምጧል። ጥቁር አሜሪካውያኑ ተዋናያኖች ገብርኤላ ዩኒየን እና ቴይለር ፔሪ በዝርዝሩ ውስጥ ተካተዋል። ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ ባለፈው የፈረንጆች ዓመት [2019] የታይም መጽሔት 100 ተጽእኖ ፈጣሪዎች ዝርዝር ውስጥ ተካተው እንደነበረ ይታወሳል። ከፍተኛ ተከፋይዋ ሴት ስፖርተኛ የሆነችው ጃፓናዊቷ የሜዳ ቴኒስ ተጫዋቿ ናኦሚ ኦሳካ የታይም የዓመቱ ተጽእኖ ፈጣሪ ሰዎች ዝርዝር ውስጥ መካተት ችላለች። ካረቢያን ውስጥ በምትገኘው ሄይቲ ከተወለዱት አባቷ እና ከጃፓናዊት እናቷ የተገኘችው ናኦሚ በቅርቡ የዩኤስ ኦፕን የሜዳ ቴኒስ ውድድርን ማሸነፏ ይታወሳል። የፎርሙላ ዋነ (Formula 1) ተወዳዳሪ የሆነው እንግሊዛዊው ሉዊስ ሃሚልተን በዝርዝሩ ውስጥ ተካቷል። ሉዊስ ሃሚልተን 'የብላክ ላይቭስ ማተር' እንቅስቃሴን በፎርሙላ ዋን ወድድሮች እና በማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ አጉልቶ በማውጣት እንቅስቃሴው በርካቶች ጋር እንዲደርስ ምክንያት ሆኗል። የመብት ተሟጋቹ ናታን ሎው የዓመቱ ተጽአኖ ፈጣሪ ግለበሶች ዝርዝር ውስጥ ተካቷል። የዴሞክራሲ መብቶች አቀንቃኙ ናታን ምንም እንኳ በስደት ከሆንግ ኮንግ እርቆ ቢገኝም፤ የቤይጂንግ መንግሥት የሆንግ ኮንግን የራስ ገዝ ነጻነት እምኖ እንዲቀበል ጥረት ያደርጋል።
news-48557960
https://www.bbc.com/amharic/news-48557960
በዱባይ በደረሰ የመኪና አደጋ 17 ሰዎች ሞቱ
በዱባይ 31 ሰዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ አውቶቡስ ከመንገድ ምልክት ጋር በመጋጨቱ በደረሰ አደጋ የ17 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ በርካቶች ለጉዳት ተዳርገዋል። ሟቾቹ የተለያየ አገራት ዜጎች እንደሆኑም ታውቋል።
መለያ ቁጥሩ በኦማን የተመዘገበው ተሽከርካሪው አደጋ ሲደርስበት 31 ሰዎችን አሳፍሮ በሸክ መሐመድ ዛይድ ጎዳና ላይ እየተጓዘ እንደነበር ፖሊስ አስታውቋል። ከሟቾቹ መካከልም ስምንቱ የሕንድ ዜጎች መሆናቸውን የሕንድ ባለሥልጣናት አረጋግጠናል ብለዋል። • እግር ኳስ ተጫዋቹ ወንድወሰን ዮሐንስ እንዴት ተገደለ? • የሞተር ብስክሌቶች እና ሕገወጥነት በአዲስ አበባ በዱባይ የሚገኘው የሕንድ ኤምባሲ የሟቾቹን ሕንዳውያን ስም ዝርዝር ይፋ ያደረገ ሲሆን ለቤተሰቦቻቸውም አሳውቀዋል፤ ሌሎች ጉዳት የደረሰባቸው ሕንዳውያንም ህክምና እየተደረገላቸው ነው ብለዋል። የ50 ዓመቱ የአውቶብሱ አሽከርካሪ ቀላል ጉዳት ያጋጠመው ሲሆን ሕክምና እየተደረገለት ይገኛል። የዱባይ ፖሊስ በይፋዊ የትዊተር ገፁ ላይ በተፈጠረው አደጋ ማዘኑንና ለተጎጅ ቤተሰቦችም መፅናናትን እንደሚመኝ አስፍሯል። የፖሊስ ኃላፊው ማጅ አብዱላህ ካሊፋ አል ማሪ "አንዳንድ ጊዜ ተራ ስህተት አሊያም ግድ የለሽነት እንዲህ ዓይነት አስከፊ አደጋዎችን ያስከትላሉ" ብለዋል። • የአክሱም ሙስሊሞች ጥይቄ መቼ ምላሽ ያገኝ ይሆን? የአደጋው ምክንያት እየተጣራ ሲሆን ስለ አደጋው ዝርዝር ሁኔታ የተባለ ነገር የለም። ይሁን እንጂ አሽከርካሪው የመንገድ ምልክትን በመጣሱ በድንገት መንገድ ለመቀየር ሲል አደጋው እንዳጋጠመው የአገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። የኦማን የአውቶቡስ አምራች ምዋሳላት " በአደጋው የተሰማቸውን ሃዘን የገለፁ ሲሆን ከሙስካት ዱባይ የሚሰጡትን አገልግሎት ለጊዜው ማቋረጣቸውን አስታውቀዋል።
48836228
https://www.bbc.com/amharic/48836228
የሆንግ ኮንጓ መሪ የተቃዋሚዎችን ድርጊት አወገዙ
የሆንግ ኮንጓ መሪ ካሪ ላም የትላንቱን የተቃዋሚዎች ድርጊት አውግዘዋል።
ትላንት ተቃዋሚዎች የሆንግ ኮንግን ሕግ አውጪ ምክር ቤት ጥሰው ገብተው እንዳልነበረ ማድረጋቸው ይታወሳል። ትላንት የመብት ተሟጋቾች በአደባባይ እያደረጉ የነበረው ተቃውሞ ተሳታፊ የነበሩ ግለሰቦች ከተቃውሞው ወጥተው ወደ ሕግ አውጪ ምክር ቤት በማምራት ለሰዓታት እቃ ሰባብረዋል። መሪዋ ተግባሩን "የሚያሳዝንና ብዙዎች ያስደነገጠ" ብለውታል። • ተቃውሞ በቻይና፡ መንግሥት 'የውጭ ኃይሎችን' እየወቀሰ ነው ትላንት ሆንግ ኮንግ ከእንግሊዝ አገዛዝ ነጻ ከወጣች በኋላ በቻይን ሥር የወደቀችበትን 22ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ሰላማዊ ተቃውሞ እየተደረገ ነበር። እለቱ በየዓመቱ የሚታሰበው ስለዴሞክራሲ መስፈን በሚያወሳ ሰልፍ ሲሆን፤ ዘንድሮ ግን በሆንግ ኮነግ የነበረውን የሳምንታት ጠንካራ ተቃውሞ ተከትሎ መጥቷል። ሆንግ ኮንግ ውስጥ ወንጀል የሰሩ ሰዎች ለቻይና ተላልፈው ይሰጡ የሚል ረቂቅ ሕግ መቅረቡን ተከትሎ ሆንግ ኮንግ በተቃውሞ እየተናጠች ትገኛለች። ትላንት ቀትር ላይ ይደርግ የነበረው ተቃውሞ አካል የነበሩ ጥቂት ሰልፈኞች ተነጥለው ወደ ምክር ቤት አቅንተው ጥቃት ሰንዝረዋል። • የሆንግ ኮንግ የሕዝብ እንደራሴዎች ተቧቀሱ የምክር ቤቱን የመስታወት ወለል ሰባብረው ወደ ውስጥ በመዝለቅ፤ የሆንግ ኮንግን ሰንደቅ አላማ አንስተው፤ ግድግዳው ላይ በደማቅ ቀለም መልዕክት አስፍረዋል። የተለያዩ ቁሳቁሶችንም ሰባብረዋል። ይህን ተከትሎ መሪዋ ጋዜጣዊ መግለጫ ሲሰጡ "ተግባሩን ሁላችንም ማውገዝ አለብን። ማህበረሰቡ ወደ ቀደመ ሰላሙ በቅርብ ይመለሳል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ" ብለዋል። • ሳይንቲስቱ መንትዮች ኤች አይ ቪ እንዳይዛቸው ዘረ መላቸውን አስተካከለ "መሪዋ ለተቃዋሚዎች ጥያቄ ምላሽ ባለመስጠታቸው ተቃዋሚዎች የወሰዱት እርምጃ ነው" በሚል የቀረበባቸውን የሰላ ትችት አጣጥለዋል። የተቃዋሚዎች ጥያቄ ወንጀለኞች ለቻይና ተላልፈው የሚሰጡበትን ረቂቅ ሕግ ማስቀረት ብቻ ሳይሆን፣ የመብት ተሟጋቾችን ከእስር ማስፈታትና በፖሊስ ጥቃት የደረሰባቸው ሰዎችን ጉዳይ መመርመርንም ያካትታል። መሪዋ በበኩላቸው "መንግሥት ለጥያቄዎቹ ምላሽ አልሰጠም መባሉ ትክክል አይደለም። ረቂቅ ሕጉ ሕግ አውጪ ምክር ቤቱ በ2020 ሲከስም አብሮ ይከስማል። ለተጠየቀው ጥያቄ ቀና መልስ ተሰጥቷል" ብለዋል። በተቃዋሚዎቹ ላይ እርምጃ እንደሚወሰድም ገልጸዋል። • ባህር አቋራጩ የቻይና ድልድይ ተከፈተ ተቃዋሚዎች ረቂቅ ሕጉን አጥብቀው መቃወማቸው መንግሥት ይቅርታ እንዲጠይቅ እንዲሁም ረቂቅ አዋጁን እንዲተወውም አስገድዷል። ነገር ግን ረቂቁ ሙሉ በሙሉ እስኪነሳ ተቃውሞው ይቀጥላል። ተቃዋሚዎች መሪዋ ከስልጣናቸው እንዲነሱም ግፊት ማድረጋቸወንም ገፍተውበታል።
50245032
https://www.bbc.com/amharic/50245032
የአማራ ክልል ረዳት ፖሊስ ኮሚሽነር ሰይድ አህመድ በዋስትና ተለቀቁ
የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር ረዳት ኮሚሽነር ሰይድ አህመድ በዋስትና መለቀቃቸውን የክልሉ መገናኛ ብዙኃን ዘግቧል።
ከሰኔ 15ቱ ግድያ ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው የታሰሩት ረዳት ኮሚሽነሩ በዋስትና እንዲለቀቁ መወሰኑን ቢቢሲ ከባለቤታቸው ወ/ሮ ሰሚራ አህመድ ማረጋገጥ ችሏል። • ኢትዮጵያና ግብፅ በአሜሪካ ለውይይት እንጂ ለድርድር አይገናኙም ተባለ • ትዊተር የትኛውንም የፖለቲካ ይዘት ያለው ማስታወቂያ ሊያግድ ነው የአማራ ክልል ፖሊስ ከፍተኛ አመራሮች ለሳምንታት በክልሉ ሥራ አመራር ተቋም ውስጥ ስልጠናና ግምገማ ካካሄዱ በኋላ ረዳት ኮሚሽነሩ መታሰራቸውን በወቅቱ ቢቢሲ ከቅርብ ምንጮች አረጋግጦ ነበር። ረዳት ኮሚሽነሩ የታሰሩት ባለፈው ዓመት ሰኔ 15 ባህርዳር ውስጥ ከተከሰተው የከፍተኛ አመራሮች ግድያ ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው እንደነበር ዘግበን ነበር። ከሰኔ 15ቱ ግድያ ጋር ተያይዞ በጥርጥሬ ተይዘው የነበሩት የአማራ ክልል የደህንነትና ፀጥታ ሃላፊዎች ብርጋዴር ጀነራል ተፈራ ማሞና ኮሎኔል አለበል አማረ ከጥቂት ቀናት በፊት በዋስ መለቀቃቸው ይታወሳል። በተመሳሳይ ከ15ቱ ግድያ ጋር ተያይዞ በሽብር ተጠርጥረው ለአራት ወራት እስር ላይ የነበሩት የባልደራስ አባላት እንዲሁም የብርጋዴር ጀነራል አሳምነው ፅጌ ባለቤት ከትናንት በስቲያ በዋስ መለቀቃቸውም ይታወቃል።
news-46503845
https://www.bbc.com/amharic/news-46503845
በሱዳን ሄሊኮፕተር ተከስክሶ አራት ባለሥልጣናትን ገደለ
በምስራቃዊ ሱዳን ሄሊኮፕተር ተከስክሶ የከተማዋን አስተዳዳሪና ሌሎች አራት ባለሥልጣናት እንደተገደሉ ተዘግቧል።
ሄሊኮፕተሩ አልቃድሪፍ የሚባል ቦታ ላይ ለማረፍ ትግል ቢያደርግም አንድ የመገናኛ ግምብ መትታ በእሳት መያያዟን ኤኤፍፒ ያናገራቸው የአይን እማኞች ገልፀዋል። እስካሁንም ሄሊኮፕተሩ የተከሰከሰበትን ምክንያት ከሱዳን ባለሥልጣናት በኩል የተገለፀ የለም። የሀገሪቱ ሚዲያ እንደዘገበው በአደጋው የቆሰሉ ሰዎች ሆስፒታል እንደተወሰዱ ገልፆ ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ተቆጥቧል። •ሶሪያውያን ስደተኞች በአዲስ አበባ ጎዳናዎች •አፍሪካ የተሰጣትን ጨለምተኛ እይታ ለመቀየር ያለመው አዲስ ፎቶ ፌስት •በርካቶችን ግራ ያጋባው ፎቶ ከሟቾቹም መካከል የአልቃድሪፍ አስተዳዳሪ የሆኑት ሚርጋኒ ሳልህ፣ የካቢኔቱ ኃላፊ፣ የከተማው የፖሊስ ኃላፊና የግብርና ሚኒስትሩ እንደሚገኙበት ሪፖርቱ ጨምሮ ገልጿል። የሱዳን የወታደራዊ የጦር አውሮፕላኖች ብዙዎቹ ከቀድሞዋ ሶቭየት ህብረት የተገዙ ናቸው። በጥቅምት ወርም በመዲናዋ ካርቱም በሚገኘው አየር መንገድ ሁለት አውሮፕላኖች ተጋጭተው ስምንት ሰዎች ተጎድተዋል። በተጨማሪም በመስከረም ወር በመዲናዋ ካርቱም በምትገኘው ኦምዱርማን ከተማ የጦር ጀት ተከስክሶ የሁለት ፓይለቶች ህይወት ጠፍቷል።
news-52995324
https://www.bbc.com/amharic/news-52995324
ከቀብር በኋላ በደረሰ የምርመራ ውጤት ሰበብ 53 ሰዎች በሰሜን ሸዋ ወደ ለይቶ ማቆያ ገቡ
ጉዳዩ የሚጀምረው አዲስ አበባ ነው። ትውልዳቸው በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን እንሳሮ ወረዳ የሆኑ የአዲስ አበባ ነዋሪ በሥራ ቦታ በገጠማቸው አደጋ ለህክምና ወደ ሆስፒታል ይወሰዳሉ።
በሆስፒታሉ ከሚደረግላቸው ህክምና በተጨማሪ የኮሮናቫይረስ ምርመራ ይደረግላቸዋል። ነገር ግን የግለሰቡ የምርመራ ውጤት ሳይታወቅ ህይወታቸው ያልፋል። ዘመድ አዝማድ እና ወዳጆች አስከሬኑን ግንቦት 29/2012 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ወደ ትውልድ ቀዬአቸው እንሳሮ በመውሰድ በዚያው ዕለት ካራምባ ቀበሌ ጥቁር ዱር ሚካኤል የቀብር ሥነ ሥርዓቱ ይፈጸማል። በቀጣዩ ቀን ከግለሰቡ የተወሰደው ናሙና ቫይረሱ እንዳለባቸው የሚገልጽ መሆኑን የወረዳው ጤና ጥቃ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሲስተር በቀለች ሞገስ ለቢቢሲ ገልጸዋል። በሽታው ወደ ሌሎች የማኅበረሰብ አባላት እንዳይዛመት የወረዳው የኮሮናቫይረስ መከላከልና መቆጣጠር ኮሚቴ የቀብር ሥነ ሥርዓት ወደ ተፈፀመበት ካራምባ ቀበሌ በመሄድ የቅርብ ንክኪ አላቸው የተባሉትን ሰዎችን በመለየት ጊዜያዊ ማቆያ እንዲገቡ ተደርጓልም ብለዋል። እንደ ሲስተር በቀለች ከሆነ ከግለሰቡ ጋር ንክኪ ያላቸውን ሰዎች ወደለይቶ ማቆያ ከማስገባት በተጨማሪ በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ ተሳታፊ የነበሩ ሰዎች ራሳቸውን ለይተው እስከ 14 ቀናት ድረስ እንቅስቃሴ እንዳያደርጉ በጎጥ ደረጃ እንደተነገረም ገልጸዋል። ውጤቱ እሑዱ 10 ሰዓት አካባቢ የደረሳቸው መሆኑን ያስታወቁት የሰሜን ሸዋ ዞን ጤና መምሪያ ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ ጸዳለ ሰሙንጉሥ 53 ሰዎችን በመለየት ምሽቱን ወደ ለይቶ ማቆያ እንዲገቡ ማድረጋቸውን ለቢቢሲ ተናግረዋል። ከእነዚህ ውስጥ የቅርብ ንክኪ ይኖራቸዋል የሚባሉ 20 ሰዎች ተለይተው ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በተዘጋጀው ለይቶ ማቆያ በመውሰድ ወረዳውን ለማገዝ እንደተሞከረም ምክትል ኃላፊዋ ገልጸዋል። ከዚህ ጎን ለጎንም ንክኪ አላቸው የተባሉ ሰዎችን ናሙና መወሰዱን እና ውጤታቸው እየተጠበቀ መሆኑንም አስረድተዋል። እስካሁን ወደለይቶ ማቆያ ከገቡት መካከል ምልክት የታየባቸው ሰዎች እንደሌሉም ጨምረው ተናግረዋል። የኮሮናቫይረስ ናሙና ውጤት በፍጥነት ካለመታወቁ ጋር በተያያዘ ናሙና የሰጡ ሰዎች በአንድ ቦታ ካልተቀመጡ ቫይረሱ ካለባቸው በሚሄዱበት ቦታ ሁሉ ሊያስተላልፉ ስለሚችሉ የመከላከል ሥራውን ያከብዱታል ብለዋል። ከዚህ ቀደምም አዲስ አበባ ውስጥ ቫይረሱ ካለባቸው ሰዎች ጋር ንክኪ የነበራቸው እና ናመና የሰጡ ሁለት ግለሰቦች ውጤት ሳይነገራቸው በፊት ወደ ዞኑ ካቀኑ በኋላ ቫይረሱ እንዳለባቸው መነገሩንም ያስታውሳሉ። "በአዲስ አበባ ያለው የስርጭት መጠን እና ጫናው ይህን ክፍተት ፈጥሮ ሊሆን ይችላል" የሚሉት ወይዘሮ ጸዳለ "ቢቻል የሚመረመረውን ማቆየት፤ አስከሬን ምርመራም ናሙና ወስዶ ወዲያው ከሚመለስ እንዲቆይ ቢደረግ" እንዲህ አይነቱን ክስተት ሊያስቀር እንደሚችል ገልጸዋል። በተለይ ደግሞ አስከሬን ለቤተስብ ከመሰጠቱና ከቀብር በፊት ውጤቱ ቢደርስ የቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ለማድረግ ዕድል ስለሚሰጥ አመልክተው፤ በዚህ በኩል ሊኖር የሚችለውን የስታውን ስርጭት ለመግታት የላብራቶሪ ውጤት በቶሎ መታወቅ አስፈላጊ ነው ብለዋል። ኅብረተሰቡም የኮሮናቫይረስ ምርመራ ካደረገ በኋላ ኃላፊነት በተሞላበት መንገድ ውጤቱ እስኪታወቅ ከሰዎች ጋር ያለውን ንክኪ በማስወገድ እራስን ለይቶ ማቆየት እንደሚያስፈልግ የጤና መምሪያው ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ ጸዳለ ሰሙንጉሥ ተናግረዋል።
news-49990487
https://www.bbc.com/amharic/news-49990487
የወላጆች ራስ ምታት እየሆነ የመጣው የልጆች የጌም ሱስ
ለወላጆች ልጆቻቸው በተንቀሳቃሽ ስልክም ሆነ በበይነ መረብ የተለያዩ ጌሞች ላይ ተጠምደው እንደማየት የሚያሳስባቸው ነገር የለም።
ግን ይህ ታሪኩን የምናጋራችሁ አባት ከአቅሜ በላይ ሆኖ የቁም ቅዠት ሆኖብኛል ይላል። ስቲቭ ይባላል፤ የሚወደው ልጁ ከተራ ጌም ተጫዋችነት አልፎ አሳሳቢ የሚባል ደረጃ ላይ የደረሰ ሱሰኛ ሆኗል። ከዚህም ባለፈ መቆጣጠር የማይችለው የቁማር ሱስ ውስጥ ተዘፍቋል። "ልጄ በጌሞች እንዲህ ይሆናል ወይም መጨረሻው የቁማር ሱስ ይሆናል ብዬ በፍጹም ገምቼ አላውቅም።'' • የስፖርት ውርርድ አዲሱ የወጣቶች ሱስ ይሆን? የስቲቭ ልጅ በሃያዎቹ መጀመሪያው ውስጥ የሚገኝ ወጣት ነው። በልጃቸው ምክንያት ስቲቭና ባለቤቱ ለሦስት ዓመታት ተሰቃይተዋል። ''እኛ ያየነውን መከራ ማንም ቤተሰብ ማየት የለበትም። ልጃችን የቁማር ሱሰኛ መሆኑን ስናውቅ ምን ማድረግ እንዳለብን ግራ ገብቶን ነበር።'' የስቲቭ ልጅ ለትምህርቱ የሚሰጠውን ሳምንታዊ ወጪውን በደቂቃዎች ውስጥ የሚያጠፋ ሲሆን ከአቅሙ በላይ ሲሆንበትም ቤተሰቦቹን አማክሯቸው ነበር። እነሱም በዚሁ የሚገላገሉ መስሏቸው ማንኛውም ቤተሰብ እንደሚያደርገው ሙሉ እዳውን ከፈሉለት። ነገር ግን ብዙ ነገሮች ተከትለው መጥተዋል። ከአንድ ከዓመት በኋላ ስቲቭ ልጃቸው ከእራሱ አልፎ የሰዎችን ገንዘብ እያስያዘ መቆመር መቀጠሉን ሲሰማ በጣም ነበር ያዘነው። የሚያስይዘው ገንዘብ ደግሞ እጅጉን የተጋነነና ትልቅ እዳ ውስጥ የዘፈቀው ነበር። ''በበይነ መረብ ካርታ ነበር የሚጫወተው። እጅግ አስፈሪ ሁኔታ ነበር።'' • እንወራረድ፡- የጦፈው የውርርድ ንግድ በአዲስ አበባ ስቲቭና ባለቤቱ ልጃቸው ከፍተኛ ችግር ውስጥ እንዳለ የተረዱት በዚህ ወቅት ነው። ምን ማድረግ እንዳለባቸውም ሆነ ማንን ማማከር እንዳለባቸው ምንም ዓይነት እውቀቱ አልነበራቸውም። ''የቁማርተኛው ቤተሰቦች መባልን በመፍራትና ልጃችን ገንዘብ የተበደራቸውን ጎረቤቶች ዓይን ላለማየት እራሳችንን ከማህበራዊ እንቅስቃሴዎች እስከ ማገድ ሁሉ ደርሰን ነበር።'' ''ተስፋ ቆርጠን ፊታችንን ወዴት ማዞር እንደምንችል ግራ ገብቶን ነበር። ለራሳችን ጥያቄዎች መልስ ለማግኘት ለብዙ ወራት ምርምሮችን ስንሰራም ነበር'' ይላል ስቲቭ። በሠሩት ጥናት መሠረትም የልጃቸው ሱስ የጀመረው ገና የ12 ወይም የ13 ዓመት ታዳጊ እያለ እንደሆነ ደርሰውበታል። መጀመሪያ አካባቢ የሚያዘወትራቸው ጨዋታዎችም እግር ኳስና የመኪና ውድድር የመሳሰሉትን ነበር። በወቅቱ መኝታ ቤቱ ውስጥ ሆኖ ለሰዓታት ጌሞቹን የሚጫወት ሲሆን ጓደኞቹም ተመሳሳይ ነገር ያደርጉ ስለነበር፤ ብዙም አሳስቦን አያውቅም ይላል ስቲቭ ወደ ኋላ መለስ ብሎ ሲያስታውስ። "ጨዋታዎቹ ምን ዓይነት እንደሆኑና ምን ዓይነት ቴክኖሎጂ እንደሚጠቀሙ ምንም የማውቀው ነገር አልበረም" የሚለው ስቲቭ ከመጀመሪያው ጀምሮ ተከታትዬው ቢሆን ኖሮ ይሄ ሁሉ ላይፈጠር ይችል ነበር ብሎ ያስባል። ''ለረጅም ሰዓታት እግር ኳስ በመጫወት የተጀመረው ሱስ ቀስ በቀስ ወደ ቁማር ሱስ ተቀይሯል።'' በቅርቡ የተሠራ አንድ ጥናት እንደሚጠቁመው 55 ሺህ የሚሆኑ እድሜያቸው ከ11 እስከ 16 የሚደርሱ የእንግሊዝ ታዳጊዎች አሳሳቢ የሚባል የቁማር ሱሰኞች ሲሆኑ ቤተሰቦቻቸው ስለሱሳቸው ብዙም አያውቁም። • በዩቲዩብ 22 ሚሊዮን ዶላር የሚያገኘው የሰባት ዓመቱ ህፃን ከሦስት ዓመታት ትግል በኋላ ስቲቭ የአስተማሪነት ሥራውን ትቶ ልጆች የቁማር ሱስ ውስጥ እንዳይገቡ የሚያስተምርና ቤተሰቦችን የሚደግፍ የበጎ አድራጎት ድርጅት አቋቁሟል። ''ነገር ግን በጣም የተወሳሰበ ነገር ነው። ቤተሰቦች ልጆቻቸው ለረጅም ሰዓታት ኢንተርኔት ላይ ጊዜያቸውን ሲያሳልፉ ምን እየሠሩ ነው ብለው ሊጠይቁ ይገባል'' ይላል። ልጆች ምን ዓይነት ጌሞችን እንደሚጫወቱ መጠየቅ፤ ቢቻል ደግሞ አብሮ ለመጫወት መሞከር ነገሮችን ለመቆጣጠርና በአጭሩ ለመቅጨት ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖራቸው ስቲቭ ይመክራል። ምንም እንኳን በኢንተርኔት የሚደረጉ ጨዋታዎችን በትምህርት ቤቶች አካባቢ ወይም ከ25 ዓመት በታች ለሆኑ ዜጎች እንዳይተዋወቁ በእንግሊዝ ሕግ የተከለከለ ቢሆንም ብዙም ውጤታማ የሆነ አይመስልም። ታዳጊዎቹ በትምህርት ቤታቸው አልያም በሚያዘወትሯቸው አካባቢዎቹ ጌሞቹ ባይተዋወቁም በተለያዩ አጋጣሚዎች ማስታወቂያዎቹን በኢንተርኔትም ሆነ በሌሎች የመገናኛ ዘዴዎች ያገኟቸዋል። ከዚህ ባለፈም ድርጅቶቹ ማስታወቂያዎቻቸውን በታዋቂ ሰዎችና በትልልቅ ስፖርተኞች ስለሚያሠሩ ታዳጊዎቹ ላይ ተጽእኖ የማሳደር አቅማቸው ከፍተኛ ነው። ስቲቭ እንደሚለው እሱና ቤተሰቡ አሁን በጥሩ ሁኔታ ውስጥ ነው የሚገኙት። በተፈጠረው ነገር ከማዘንና ከመሸማቀቅ ይልቅ በጊዜ ወደ መፍትሄ ማፈላለግ መሄዳችን ጠቅሞናል ይላል።
42248529
https://www.bbc.com/amharic/42248529
ሉሲን የምትቀድም የሰው ዘር ቅሪተ አካል በደቡብ አፍሪካ ተገኘች
ቀደምት የሆነች እና የተሟላች የሰው አፅመ ቅሪት በደቡብ አፍሪካ ተገኘች።
አፅመ ቅሪቱ የተገኘችው በዋሻ ውስጥ ነበር ትክክለኛ እድሜዋ አከራካሪ ቢሆንም የደቡብ አፍሪካ ተመራማሪዎች የ3.7 ሚሊዮን ዓመት እድሜ ባለፀጋ መሆኗን ተናግረዋል። ይህ ማለት ደግሞ ከኢትዮጵያዊቷ ሉሲ ባለትንሽ እግሯ ሰው ከ500,000 ዓመት በፊት ኖራለች። ሉሲ እና ባለትንሽ እግሯ ተመሳሳይ የሰው ዘር- አውስትሮፒቲከስ ቢሆኑም በዝርያ ግን ይለያያሉ። ተመራማሪዎች በአፍሪካ የሰው ዘር መገኛ ከዚህ ቀደም ከሚታሰበው በተለየ ቦታ ተበትነው እንደሚገኙ ያሳያል ሲሉ ተናግረዋል። በተጨማሪም የተለያዩ ዝርያዎች መኖራቸውንም ያመለክታል። አጥኚዎች ረዥም ዓመታት በቁፋሮ፣ በማፅዳት አፅመ ቅሪቱን አንድ ላይ በማስቀመጥ አሳልፈዋል። ባለትንሽ እግሯ በሰሜን ምእራብ ደቡብ አፍሪካ ስትርክፎንቴይን በሚባል ዋሻ በፕሮፌሰር ሮን ክላርክ ነው የተገኘችው። ወጣት ሴት ልትሆን እንደምትችል እና በዋሻው ውስጥ ወድቃ ይሆናል ሲሉ ግምታቸውን አስቀምጠዋል። "ትንሽ ሊሆን ይችላል፤ ነገርግን በጣም ጠቃሚ ነው። ምክንያቱም በአንድ ትንሽ አጥንት ነው የተጀመረው። እናም አመጣጣችንን ለማወቅ ይረዳል" ሲሉ ፕሮፌሰር ክላርክ ተናግረዋል። ከዋሻው ውስጥ አጥንቱን ማውጣት አድካሚ ነበር። በተጨማሪም ቅሪተ አካሎቹ "በቀላሉ ተሰባሪ " "በተፈጥሯዊ በንብርብር አለት መሰል ነገር የተቀበሩ" ነበሩ ሲሉ ያስረዳሉ። "ለቁፋሮው በጣም ትንንሽ እንደ መርፌ ያሉ መሳሪያዎችን ነው የተጠቀምነው። ለዛ ነው ረጅም ጊዜ የወሰደው" በማለት አክለዋል።
news-56186305
https://www.bbc.com/amharic/news-56186305
ኡጋንዳ፡ አሜሪካ በምርጫ ጉዳይ ኡጋንዳን ‹‹የማስተማር›› መብት የላትም
አሜሪካ ለኡጋንዳ ስለምርጫ ‹‹ትምህርት›› ከመስጠት ይልቅ በቅድሚያ የራሷን ምርጫዎች ማስተካል ይገባታል ማለታቸወን ተዘገበ።
የኡጋንዳ ፕሬዘዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ አገሪቱን ላለፉት 34 ዓመታት አስተዳድረዋል የኡጋንዳ መንግሥት ቃል አባይ ኦፍዎኖ ኦፖንዶ፤ የአሜሪካ መንግሥት ስለ ኡጋንዳ ምርጫ አስተያየት ከመስጠቱ በፊት 'የራሱን ምርጫ ቢያስተካከል ይሻላል' ስለማለታቸው ቪዥን የተሰኘው ከመንግስት ጋር ግንኙነት ያለው መገናኛ ብዙሃን ዘግቧል። አሜሪካ በኡጋዳን ከተካሄደው ምርጫ ጋር ተያይዞ በፀጥታ ኃይሎች የተፈፀሙ ‹‹ሕገ ወጥነቶችን›› እና ‹‹በደሎችን›› ተከትሎ በዩጋንዳ ላይ ‹‹የታለሙ አማራጮችን›› እያጤነች እንደሆነ መግለጿን ተክተሎ ነው ቃል አቀባዩ ይህንን ያሉት። ኦፔንዶ በሰጡት አስተያየት መንግሥታቸው ከአሜሪካ መንግሥት በጉዳዩ ላይ በይፋ መልክት እንዳልደረሰው ገልፀው ያንን እየተጠባበቀ ነው ብለዋል። ‹‹እስከዛው ግን የአሜሪካ መንግሥት የራሱን ምርጫ ቢያስተካከል ይሻላል፣ እንደ ፕሬዘዳንት ትራምፕ ከሆነ በህይወት የሌሉ ሰዎችም ምርጫ ላይ ተሳትፈዋል እንዲሁም ጆ ባይደን ስልጣን ላይ የወጡት በተጭበረበረ ምርጫ ነው። ስለዚህ እኛን ለማስተማር የመጨረሻዎቹ ነው መሆን ያለባቸው›› ብለዋል ቃል አቀባዩ። ላለፉት 34 ዓመታት ኡጋንዳን እየመሩ ያሉት ፕሬዘዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ በጥር ወር ተካሂዶ የነበረውን ምርጫ አሸንፊያለሁ ማለታቸው ይታወሳል። የሙሴቬኒ ዋነኛ ተፎካካሪያቸው የነበረው ቦቢ ዋይንም ምርጫው ተጭበርብሯል ሲል ቅሬታውን ቢያሰማም የምርጫውን ውጤት በፍርድ ቤት የመሞገት እቅዳቸውን መተውን ገልጿል። የምርጫው ይፋዊ ውጤት እንደሚያሳየው ከሆነ ሙሴቬኒ 59 በመቶ ድምፅ ያገኙ ሲሆን ቦቢ ዋይን 35 በመቶ የሚሆነውን ድምፅ መሰብሰብ ችሏል።
41350379
https://www.bbc.com/amharic/41350379
በኢትዮጵያ የተፈናቃዮች ቁጥር ማሻቀብ የደቀነው ፈተና
በኦሮሚያና ሶማሌ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች የተቀሰቀሱትን ግጭቶች ተከትሎ ከሚኖሩበት ቀዬ የተፈናቀሉ ከ50 ሺህ በላይ መሆናቸው ባለፈው ሳምንት ተዘግቧል።
ከምሥራቅ ሐረርጌ በግጭት ምክንያት የተፈናቀሉ ከዚህ በተጨማሪም የኦሮሚያ ክልል የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ አዲሱ አረጋ እንደሚሉት ደግሞ በ2009 የበጀት ዓመት ከአምስት የግጭት ዞኖች የተፈናቀሉ የኦሮሞ ተወላጆች ቁጥር ከ416 ሺህ በላይ ነው። ቢቢሲ ያነጋገረው በሶማሌ ክልል ቦምባስ ከተማ በሰው ቤት ተቀጥሮ ይሰራ የነበረው ደንሳ ለአንድ ዓመት ከሰባት ወር ያህል የኖረበትን ስፍራ ጥሎ የሄደው ያለንብረት ባዶ እጁን መሆኑን ይናገራል። ለጥቂት ቀናት በሐረር ስቴዲየም ከቆየ በኋላ የተፈናቃዮቹ ቁጥር መብዛት በሃረማያ ከተማ በሰው ቤት ውስጥ እንዲጠለል እንዳስገደደው ያስረዳል። ደንሳ ቀጣይ ጉዞው ወደ ትውልድ ቀዬው ምዕራብ አርሲ ዞን ነንሰቦ ወረዳ ቢሆንም ምን እንደሚገጥመውም ሆነ ሕይወቱ ከዚህ ወዲያ ምን ዓይነት መልክ እንደሚኖረው አያውቅም። ባለፉት ጥቂት ቀናት ግጭቶች ተግ ማለታቸው ቢሰማም በተቃራኒው የሚወጡ ዘገባዎች ግጭቶች እየተከሰቱ እንደሆነ እያመለከቱ ነው። በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንዲሉ ደንሳን ለመሳሰሉ ተፈናቃዮች ዘላቂ መፍትሄ ማፈላለግ ሌላ የራስ ምታት ነው። የተለያዩ ወገኖች ተፈናቃዮችን የማቋቋምን ተግባር ለማገዝ በማሰብ ገንዘብና ቁሳቁሶችን በማዋጣት በመረባረብ ላይ ይገኛሉ። በግጭትና በድርቅ ተፈናቅለው ለተረጅነት የተጋለጡ ሰዎች ቁጥር አነስተኛ ያለመሆን፤ እንዲሁም ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ስደተኞች ከሳዑዲ አረቢያ ከስደት እየተመለሱ መሆኑ አገሪቱ እየተጋፈጠች ያለችውን ሸክም አመላካች ነው። የድርቅ ተረጅዎች ቁጥር ጨምሯል ለሶስተኛ ተከታታይ ዓመት ያጋጠመው የዝናብ እጥረት 8.5 ሚሊዮን ሰዎችን ለአስቸኳይ ምግብ እርዳታ ጠባቂነት እንዳጋለጠ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ገልጿል። ባለፈው ጥር የተረጅዎቹ ቁጥር 5.6 ሚሊዮን እንደነበር ይታወሳል። በዚህም ከየትኛውም የአገሪቱ አካባቢዎች በባሰ የተጠቃው የሶማሌ ክልል ሲሆን፤ በክልሉ 3.3 ሚሊዮን የሚሆኑ ሰዎች ለከፋ የምግብ እጥረት እንደተዳረጉ የደብልዩ ኤፍ ፒ ሪፖርት ያሳያል። ከባለፈው አመት ጀምሮ በክልሉ የሚገኙ አርብቶ አደሮች ከፍ ያለ ቁጥር ያላቸው የሆኑ ከብቶችን እንዳጡ ይዘገባል። ከዚህ በተጨማሪም እንደ አጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት ያሉ በሽታዎች መከሰታቸው ችግሩን ይበልጥ አሳሳቢ አድርጎታል። ለሁኔታው አሳሳቢነት አጽንዖት ለመስጠት በወርሃ ነሐሴ መገባደጃ ሶስት የተባበሩት መንግስታት ከፍተኛ ባለስልጣናት ወደ አካባቢው ተጉዘው ነበር ። የዓለም ምግብ እና የእርሻ ድርጅት (ፋኦ) የበላይ የሆኑት ጆዜ ግራዚያኖ ዳ ሲልቫ፤ ከዓለም የምግብ ፕሮግራም (ደብልዩ ኤፍ ፒ) ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዴቪድ ቢስሊ እና ከዓለም አቀፉ የእርሻ ልማት ፈንድ ፕሬዚዳንት ጊልበርት ሁንግቦ በአራት ቀናት የኢትዮጵያ ቆይታቸው ወደ ሶማሌ ክልል በማቅናት በድርቁ የተጠቁ አርብቶ አደሮችን አናግረዋል። ሶስቱ ባለስልጣናት ከአየር ንብረት መዛባት ጋር በተያያዘ የሚፈጠር ድርቅን ለመቋቋም በሚያስችሉ ዘላቂ የመፍትሄ ተግባራት ላይ ብዙ መሰራት እንዳለበት ጥሪ አቅርበዋል። "ድርቅ የአስቸኳይ ጊዜ ድጋፍን የሚጠይቅ [አደጋ] መሆን የለበትም" ሲሉ በወቅቱ ሁንግቦ ተናግረዋል። የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ እርዳታ ትብብር ጽህፈት ቤት ሪፖርት እንደሚያሳየው አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል ከተባሉ የድርቅ ተጠቂዎች በተጨማሪ እስከ ያዝነው የፈረንጆች ዓመት መገባደጃ ድረስ 4 ሚሊዮን የሚሆኑ በሴፍቲ ኔት የታቀፉ ተጠቃሚዎች ያልተቋረጠ ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል። ዘንድሮ ኢትዮጵያ እነዚህን ተረጅዎቿን ለመመገብ ከ1.2 ቢሊዮን ዶላር በላይ እገዛ እንደሚያስፈልጋት የተገለፀ ሲሆን የሰብዐዊ እርዳታ ትብብር ጽህፈት ቤቱ እንደሚለው ከዚህ በኋላ ላሉት አራት ወራት 418 ሚሊዮን ዶላር ያስፈልጋል። የተረጅዎች ቁጥር አስደንጋጭ ወደ ሆነ ደረጃ ማደጉም አሳሳቢ እየሆነ ነው። ተፈናቃዮች ያረፉባቸው ድንኳኖች ግጭቶች የአገር ውስጥ ተፈናቃዮችን ቁጥር ይጨምራሉ ከሶማሌ ክልል ጋር በሚዋሰነው የኦሮሚያ ምስራቅ ሐረርጌ ዞን ከሚንቀሳቀስ አንድ ግብረ ሰናይ ድርጅት የተገኘ መረጃ እንደሚያመላክተው በዞኑ ከ116 ሺህ በላይ ሰዎች በድንበር ግጭት ምክንያት ተፈናቅለዋል። ግጭቶቹ ለ66 የጤና እና ለ41 የትምህርት ተቋማት ሥራ መቋረጥ ምክንያት እንደሆኑም መረጃው ያሳያል። መቀመጫውን በጄኔቫ፥ ስዊዘርላንድ ያደረገው የአገር ውስጥ ተፈናቃዮች መቆጣጠሪያ ማዕከል (አይዲኤምሲ) እንደሚለው እ.ኤ.አ 2017 የመጀመሪያ አጋማሽ በኢትዮጵያ 213 ሺህ አዳዲስ የአገር ውስጥ ተፈናቃዮች አሉ። ይህም ከግጭት ጋር በተያያዘ ከሚኖሩበት ወይንም ከሚሰሩበት ቀዬ የለቀቁ የአገር ውስጥ ተፈናቃዮችን ቁጥር ከ588 ሺህ በላይ ያደርሰዋል። በተለይም በ2007 ዓ.ም እና በ2008 ዓ.ም በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የተነሱት ተቃውሞችና ግጭቶች ለተፈናቃዮች ቁጥር መጨመር ምክንያት ሳይሆኑ እንዳልቀረ ይቆጠራል። ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (አይ ኦ ኤም) የወርሃ ሐምሌ ሪፖርት እንደሚያስረዳው ድርጅቱ በ544 የተፈናቃዮች ጣቢያዎች ውስጥ ባደረገው ቅኝት ከ1 ሚሊዮን በላይ የአገር ውስጥ ተፈናቃዮች ሲኖሩ ከዚህ ውስጥ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት በሶማሌ ክልል ይገኛሉ። ድርቅና ግጭት ከቀዬ ለመፈናቀል ዋነኛ ምክንያቶች ናቸው ይላል ሪፖርቱ። ስደተኞች እና ከስደት ተመላሾች ኢትዮጵያ ከጎረቤቶቿ በተለይም ከደቡብ ሱዳን፣ ከኤርትራና ከሶማሊያ ለተፈናቀሉ 800 ሺህ ገደማ ስደተኞች መጠለያ ሰጥታለች። በሌላ በኩል የሳዑዲ አረቢያ መንግሥት ሰነድ አልባ የሆኑ የሌላ አገር ዜጎች አገሪቷን ለቅቀው እንዲወጡ ያስተላለፈውን መመሪያ ተክትሎ በመቶ ሺህዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን ዕጣ ሲያነጋግር ቆይቷል። የኢትዮጵያ መንግስት ዜጎቹን ከባለፀጋዋ ሳዑዲ ለማስወጣትና ወደ አገራቸው ከተመለሱም በኋላ በዘላቂነት ለማቋቋም ጥረት እያደረገ እንደሆነ ይገልፃል። እስካሁንም 70 ሺህ ያህል ዜጎች መመለሳቸው ተዘግቧል። በቅርቡ ሳዑዲ ለሰነድ አልባ ሰራተኞች የሰጠችውን አገሪቱን ለቆ የመውጫ የምህረት ጊዜ ለሶስተኛ ጊዜ ማራዘሟን ተከትሎ ተጨማሪ ሰዎች የሚመለሱ ከሆነ፤ እነርሱን የማቋቋሙ ኃላፊነት በአገሪቷ ጫንቃ ላይ የሚደረብ ሌላ ፈተና ይሆናል።
news-48347821
https://www.bbc.com/amharic/news-48347821
ለልመና ታግቶ የነበረው ታዳጊ ከዓመታት በኋላ ተገኘ
ሳሙኤል አብዱራሂም ይባላል። በደቡብ ናይጄሪያዋ ካኖ ከተማ ውስጥ ከሚገኘው የቤተሰቦቹ ቤት ታግቶ የተወሰደው የሰባት ዓመት ታዳጊ ሳለ ነበር።
ቤተሰቦቹ ሳይክል ለመንዳት ከቤት እንደወጣ ገምተው ነበር። ነገር ግን ሳሙኤል በታጋቾች እጅ ወድቆ ነበር። ታላቅ እህቱ ፊርዳውሲ ኦኬዚ ሳሙኤልን ለማግኘት ያልፈነቀሉት ድንጋይ እንደሌለ ትናገራለች። ወንድሟ ሲታገት እሷ የ21 ዓመት የዩኒቨርስቲ ተማሪ ነበረች። ወደቤተሰቦቿ ስትደውል አዘውትሮ ስልኩን የሚመልሰው ሳሙኤል ድምጹ ሲጠፋባት ነበር የወንድሟን መታገት ያወቀችው። ከአራት ሚስቶቻቸው 17 ልጆች የወለዱት አባታቸው ወንድሟ በጠፋበት ወቅት ቤት ውስጥ የነበረችው ሞግዚት በቁጥጥር ሥር እንድትውል አድርገው ነበር። በጋዜጣ ማስታወቂያ በማውጣት ልጃቸውን ማፈላለግም ጀምረው ነበር። • ከማደጎ ልጅነት ወደ እውቅ ገጣሚና የማንችስተር ዩኒቨርሲቲ ሃላፊነት በስተመጨረሻ የሳሙኤል አባት ተስፋ ቆርጠው ልጃቸው እንደሞተ ቤተሰቡ ማመን እንዳለበት ነገሯቸው። እህቱ ፊርዳውሲ ግን ተስፋዋ አልከሰመም ነበር። ከዩኒቨርስቲ ከተመረቀች በኋላ ሀይማኖቷን ከእስልምና ወደ ክርስትና ቀይራ ቤተክርስቲያን ትሄድ ጀመር። እናቷ የሚሠሩትን ካናቴራ እየሸጠች ራሷን ለማስተዳደር ብላ የካናቴራ መደርደሪያ እያዘጋጀች ሳለ አንድ የሚለምን ሰው "ስለ አላህ" አያለ ምጽዋት ሲጠይቅ ሰማች። የሚለምነው ሰው አይነ ስውር ሲሆን፤ አንድ ልጅ ከፊት ለፊት እየሄደ ሲመራው ተመለከተች። አይነ ስውሩን የሚመራውን ታዳጊ በአንክሮ ስትመለከት ታናሽ ወንድሟ ሳሙኤል መሆኑን ተረዳች። እንዴት ታገተ? ሳሙኤል አሁን 30 ዓመት ሆኖታል። ከቤተሰቦቹ ቤት እንዴት እንደተሰረቀ ባያስታውስም፤ አጋቾቹ ረዥም መንገድ በባቡር እንደወሰዱት ይናገራል። ሌጎስ ውስጥ በርካታ በልመና የሚተዳደሩ አካል ጉዳተኞች የሚኖሩበት አካባቢ ከተወሰደ በኋላ፤ በቀን በ500 ናይራ (140 ብር ገደማ) አይነ ስውር እንዲመራ ተደረገ። • ሴቶች 'ፌሚኒስት' መባልን ለምን ይጠላሉ? ናይጄሪያ ውስጥ የሚለምኑ አይነ ስውሮችን የሚመሩ ታዳጊዎች መመልከት የተለመደ ነው። ሳሙኤልን ለሚለምኑ ሰዎች ያከራዩት ሴት ሌሎች ታዳጊዎችም ያከራዩ እንደነበረም ያስታውሳል። የባርነት ሕይወት በልመና ላይ የተሰማሩ ሰዎች ሳሙኤልን ለሳምንት ወይም ለወር ይከራዩት ነበር። "ባሪያቸው ነበርኩ። የትም የመሄድ መብት አልነበረኝም" ይላል። • የተነጠቀ ልጅነት አልፎ አልፎ ከሚለምኑት ሰዎች ልጆች ጋር ይጫወት ነበር። ሰዎች ምግብ ሳይሰጧቸው ሲቀሩ በየምግብ ቤቱ እየተዘዋወሩ ትራፊ ምግብ ይለቃቅሙ ነበር። ቆሻሻ መጣያ ገንዳ ውስጥ የተጣለ ምግብም ይመገቡ ነበር። ሳሙኤል ጎረቤት ሀገር ቤኒን ድረስ ለልመና ተወስዷል። "አይነ ስውራን የመስማት ችሎቻቸው ከፍተኛ ነው። የሰው ድምጽ ወደሰሙበት ቦታ እንድወስዳቸው ያደረጉ ነበር" ይላል። "ተአምር" እንደ ጎርጎሮሳውያኑ አቆጣጠር 2000 ላይ 'ዊነር ቻፕል' የተባለ ቤተክርስቲያን እርዳታ መስጠት መጀመሩን የሚለምኑ ሰዎች ሰምተው ሳሙኤልን አስከትለው ሄዱ። ቤተክርስቲያኑን የሳሙኤል እህት ፊርዳውሲ ታዘወትረው ነበር። "ሳየው መሬት ላይ ወደቅኩ" ትላለች ቅጽበቱን ስታስታውስ። የቤተክርስቲያኑ አገልጋዮች ሳሙኤልን ሰውነቱን አጥበው ልብስ ቀየሩለት። የሳሙኤል መገኘት "ተአምር ነው" ተባለ። ሳሙኤል ከተገኘ በኋላ ሌሎች ታዳጊዎችንም ከባርበነት ማውጣት እንደነበረባት እህትየው ትናገራለች። "ባደጉ አገሮች እንደዚህ ያሉ ወንጀሎችን ለፖሊስ ሪፓርት ማድረግ ይቻላል። እኛ ሀገር ግን ፖሊሶች ጉቦ ይጠይቃሉ። እኔ ደግሞ በወቅቱ ገንዘብ አልነበረኝም" ስትል ሌሎች ታዳጊዎችን ማዳን አለመቻሏን ታስረዳለች። የ13 ዓመት ወንድሟን መንከባከብ ካሰበችው በላይ ከባድ ነበር። ለልመና የሚመራቸው አይነ ስውራን አጥብቀው ይይዙት የነበረው ቀኝ እጁ ተጣሞ ስለነበር ፊዚዮቴራፒ ተከታትሏል። "ቂም አልይዝም" ሳሙኤል ለስድስት ዓመታት ያለትምህርት በማሳለፉ ማንበብና መጻፍ አይችልም ነበር። እሱን ትምህርት ቤት ማስገባትም ቀላል አልነበረም። እድሜው ከመጀመሪያ ደረጃ ተማሪነት አልፏል በሚል ብዙ ትምህርት ቤቶች አልተቀበሉትም። በስተመጨረሻ ሳሙኤል ቤተክርስቲያን ውስጥ ሲገኝ የተመለከቱ ግለሰብ ሳሙኤልን ትምህርት ቤታቸው ለማስገባት ፈቀዱ። በ17 ዓመቱ የዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና ወሰደ። በጥሩ ውጤት አልፎም ኬሚካል ኢንጅነሪንግ ማጥናት ጀመረ። የአራተኛ ዓመት ተማሪ ሳለ ግን የሌሎች ተማሪዎችን የቤት ሥራ ሲሠራ ተይዞ ከዩኒቨርስቲው ተባረረ። አሁን በግንባታ ሥራ እራሱን ያስተዳድራል። "ገንዘብ ሲኖረኝ ትምህርቴን እቀጥላለሁ" የሚለው ሳሙኤል፤ ኮምፒውተር ሳይንስ የማጥናት ፍላጎት እንዳለው ይገልጻል። ታግቶ የነበረበትን ዓመታት ሲያስብ ትምህርት የቀሰመበት ወቅት እንደነበረ ያምናል። "ሰዎች ምንም ቢያደርጉ ቂም አልይዝም። አንድ የሕይወት አካል እንደሆነ አስባለሁ" ይላል። • "በወንድሜ ለአምስት ዓመታት ተደፍሬአለሁ" የሚለምኑ ሰዎች ሲገጥሙት ገንዘብ ሳይሆን ምግብ ይሰጣል። እሱን ተጠቅመው ይለምኑ የነበሩ አይነ ስውራን ለሱ ገንዘን እንደማይሰጡት ማስታወሱ በልመና ላይ የተሰማሩ ሰዎችን የሚያይበትን መንገድ ቀይሮታል። ሰዎች ታዳጊዎችን ከሚለምኑ ሰዎች ጋር ሲያዩ ገንዘብ ሰጥቶ ከማለፍ ይልቅ "ይህ ልጅ እርዳታዬን ይፈልግ ይሆናል" ብለው ቆም ብለው እንዲያስቡም ይጠይቃል።
50135601
https://www.bbc.com/amharic/50135601
የጆሃንስበርግ ከንቲባ ኸርማን ማሻባ በዘር ምክንያት ከሥልጣናቸው ለቀቁ
በደቡብ አፍሪካ ውስጥ ዋነኛ ተቃዋሚ የሆነውና በታሪክ የነጮች ፓርቲ ብቻ የነበረው ዲሞክራቲክ አሊያንስ ከፍተኛ ኃላፊነት የነበራቸው የጆሃንስበርግ ከንቲባ ከሥልጣናቸው እንዲሁም ከፓርቲያቸው ራሳቸውን አግልለዋል።
ኸርማን ማሻባ ለባለፉት ሶስት አመታት የጆሃንስበርግ ከንቲባ ሆነው አገልግለዋል። በፓርቲው ውስጥ ያለው ስር የሰደደ ችግር ራሳቸውን ከፓርቲ አባልነታቸው እንዲያስወግዱ እንዲሁም ከከንቲባ እንዳስለቀቃቸው አሳውቀዋል። •ደቡብ አፍሪካዊቷ የፓርላማ አባል የዘረኝነት ጥቃት ደረሰባት •የሆሊውዱ ሃኪም ገብረወልድን ያውቁታል? " ሃገሪቱ ውስጥ ባሉት የእኩልነት ጥያቄዎች ውስጥ ዘር ከፍተኛ ቦታ እንዳለው መወያየት ከማይፈልጉ ሰዎች ጋር በጭራሽ አብሬ መስራት አልችልም" በማለት በመልቀቂያቸው በሰጡት መግለጫ አትተዋል። ውሳኔያቸውን ያፋጠነው ጉዳይ ደግሞ ሄለን ዚሌ የተባለች የፓርቲው ነጭ አባል ቅኝ ግዛትን በማሞገስ ከፍተኛ የሆነ ቁጣን ቀስቅሳ የነበረ ቢሆንም በሥልጣን ከፍ መደረጓ ነው። "የሄለን ዚሌ ሹመትም የሚያሳየው ከኔ ተፃራሪ እምነት ያላቸው ሰው ድል እንዳደረጉ ነው" ብለዋል። በፓርቲው ውስጥ የጥቁር ከንቲባ መመረጥ ገዢውን ኤኤንሲ በስልጣን ሊገዳደር ይችል ይሆን የሚሉ መላምቶች እንዲሰጥ አስችሎት ነበር። በራሱ የውስጥ ፖለቲካ እየተበጠበጠ ላለው ገዥው ፓርቲ ኤኤንሲ ይህ የሚያስደስት ዜና ሆኖላቸዋል። ኤኤን ሲ በአሁኑ ወቅት ደካማ ቢሆንም በሃገሪቱ ውስጥ ትልቁ የሚባለው ተቃዋሚ ፓርቲ ምንም ሳይመጣበት በራሱ እየተሸራረፈ መሆኑ ነው። •ለመጀመሪያ ጊዜ ያለእረፍት ከአስራ ዘጠኝ ሰዓታት በላይ በረራ ተደረገ •የጠቅላይ ሚኒስትሩ መፅሐፍ ምን ይዟል? የዲሞክራቲክ አሊያንስ ጥቁር አባላት እንደሚያምኑት ፓርቲው ወደቀድሞው ሙሉ በሙሉ ነጭ የማድረግ አላማው እንደገፋበት አሳይ ነው ማለታቸውን የቢቢሲው ሚልተን ንኮሲ ከጆሃንስበርግ ዘግቧል። "ለደሃ የቆመ" ፖሊሲያቸውም፣ ትችት እንዲሁም ማጣጣል እንዲሁም ትችት እንደቀረበበት ከንቲባው አስረድተው፤ ለደሃ የቆመ ማለትም ለጥቁሮች የቆመ መሆኑን ሚልተን ይናገራል። ኸርማን ማሻበ የጨቋኙ አፓርታይድ ስርዓት ከተገረሰሰ በኋላ ከገዥው ኤኤንሲ ፓርቲ ውጭ የተመረጡ የመጀመሪያው ጥቁር ከንቲባ ናቸው። ሙምሲ ማይማኔ የተባሉት ጥቁር ደቡብ አፍሪካዊ የዲሞክራቲክ አሊያንስ መሪ ተደርገው ሲመረጡ የደቡብ አፍሪካ ኦባማም ተብለው ተሞካሽተው ነበር። ሙምሲ ማይማኔም ቢሆን ለፖለቲካ ህይወታቸው እየታገሉ ያለበት ወቅት ላይ ናቸው። •የዛሬዋን አዲስ አበባ በፎቶ መሰነድ ለምን አስፈለገ? ሰኞ ዕለት በነበረው ጋዜጣዊ መግለጫ ከሥልጣን ከለቀቁት ከንቲባ ጎን በመቆምና እጃቸውን ከፍ አድርገው በመያዝ "ጀግናየ ነህ፣ ጀግናየ ነህ" ብለዋል ። የፓርቲው መሪ ሙምሲ ማይማኔም ዕጣ ፈንታ በሚቀጥለው አመት በሚደረገው የፓርቲው መሪዎች ጉባኤ የሚወሰን ይሆናል። ነገሮች እንዴት በፍጥነት እየሄዱ እንዳሉ በማየት ግን እስከዛ ድረስ ይቆዩ ይሆን ወይ ለሚለው ዋስትና የለም። ሙምሲ ማይማኔ ሄለን ዚሌን ተክተው ነው ወደ ስልጣን የመጡት ምንም እንኳን የሁለቱ አመራሮች ወደ ሥልጣን መምጣት ፓርቲው በጥቁር ደቡብ አፍሪካውያን ዘንድ ያለውን ተቀባይነት ከፍ ያደርገዋል ቢባልም የሄለን ዚሌ ወደ ከፍተኛ አመራር መምጣት ግንቦት ወር ላይ በነበረው ምርጫ እንዲያሽቆለል አድርጎታል።
news-45080727
https://www.bbc.com/amharic/news-45080727
በሶማሌ ክልል በተከሰተው ቀውስ የብዙዎች ህይወት ሲጠፋ አብያተ-ክርስቲያናት መቃጠላቸው ተገለፀ
በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ የመከላከያ ሠራዊት በአካባቢው ተሰማርቷል ተብሎ መነገሩን ተከትሎ ከቅዳሜ ጀምሮ በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች በሰውና በንብረት ላይ ጉዳት ደረሰ።
የክልሉ መስተዳደር በማዕከላዊው መንግሥት መካከል አለ በተባለው አለመግባባት ሳቢያ የሃገር መከላከያ ሠራዊት ወደ ዋና ከተማዋ ጅግጅጋ በመግባቱ ሁከትና ግርግር እንደተቀሰቀሰ ተገልጿል። መከላከያ ሠራዊት የክልሉን የፓርላማ አዳራሽ እንዲሁም ቁልፍ የሚባሉ የመንግሥት መስሪያ ቤቶችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ቅዳሜ ዕለት ተዘግቦ ነበር። • የደቦ ጥቃትና ያስከተለው ስጋት • በድሬዳዋ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አልታወጀም ተባለ ይህንም ተከትሎ በንግድ ተቋማትና መኖሪያ ቤቶች ላይ ዝርፊያ ሲፈፀም፤ የሶማሌ ብሔር ተወላጅ ባልሆኑ የክልሉ ነዋሪ በሆኑ ግለሰቦች ጥቃት ደርሶባቸዋል። በከክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች ያሉ አብያተ-ክርስቲያናት መቃጠላቸውንና ካህናት እንደተገደሉ ከስፍራው የሚወጡ መረጃዎች አመልክተዋል። የዓይን እማኞች በግርግሩ ሳቢያ የሞቱ ሰዎች ቁጥር አስር ቢያደርሱትም አንዳንዶች ግን ቁጥሩ ከዚያ በላይ ሊሆን እንደሚችል ገልፀዋል። የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል መንግሥት የመከላከያ ሠራዊት ጣልቃ መግባቱን "ህገ-ወጥና ህገ-መንግሥቱን" ያልተከተለ ነው በማለት ተቃውሞውን አሰምቷል። የክልሉ ማስታወቂያ ቢሮ ሃላፊ ኢድሪስ እስማኤል አብዲ ለቢቢሲ ሶማሊኛ እንደተናገሩት "ፌዴራሊዝምን መሰረት ያደረገ ህገ-መንግሥት አለን። በህገ-መንግሥቱም መሰረት የፌዴራል መንግሥት ጣልቃ የሚገባው ከክልሉ አቅም በላይ ሲሆንና በክልሉ መስተዳድር ጥያቄ መሰረት ነው። የመከላከያ ሰራዊት ህገ-ወጥ በሆነና ከህገ-መንግሥቱ በሚፃረር መልኩ እኛን ሳንጠይቅ ገብቷል። ለጊዜው መገንጠል አላሰብንም በፌደራል ሥርዓቱም እንተዳደራለን፤ ነገር ግን መገንጠል መጥፎ ሀሳብ አይደለም። ህገ-መንግሥቱም ለዛ ዋስትና ሰጥቶናል" ብለዋል። በተቃራኒው የክልሉን ርዕሰ-መስተዳደርን በመቃወም በድሬዳዋ ከተማ ስብሰባ ላይ የነበሩ ቡድኖች የመከላከያ ሠራዊቱን መግባት ደግፈውታል። • አቶ አብዲ ስለተናገሩት ጉዳይ እንደማያውቅ ኢህአዴግ ገለፀ • መንግሥት ልዩ ፖሊስን እንዲበትን አምነስቲ ጠየቀ ከተቃዋሚዎቹም አንዱ ዶ/ር ኑህ ሼክ አብዲ ጋፎው "ፕሬዚዳንቱ ክልሉ ከእሱ አመራር ውጪ ከሆነ ቀውስ እንደሚፈጥር ሲናገር ቆይቷል። ይህንን በተመለከተ የፌዴራል መንግሥትን ስናስጠነቅቅ ቆይተናል። አሁን ጣልቃ መግባታቸውን እናበረታታለን። የኦሮሞ ብሔር ተወላጆች ክልላችንን ወረውታል የሚባለው ከእውነት የራቀ ነው። ይህ እኛ የጀመርነው አብዮት ነው። የክልሉ አስተዳደርም ድሬዳዋ ላይ በተደረገው ስብሰባ ደስተኛ ስላልሆኑ ነው ይህንን እየፈፀሙ ያሉት" ብለዋል። የሃገር መከላከያ ሠራዊት ቅዳሜ ምሽት ላይ ባወጣው መግለጫ፤ የተከሰተው ብጥብጥ ከክልሉ ዋና ከተማ ባሻገር ወደ ሌሎች የክልሉ ከተሞች መዛመቱን አመልክቶ ይህም "በምንም መልኩ ተቀባይነት የሌለውና በፍጥነት ሊገታ እና ሊታረም የሚገባው ድርጊት ነው" ብሏል። መግለጫው አክሎም የሁከቱን መከሰት ተከትሎ ከሌሎች የጸጥታ ኃይሎች ጋር በመሆን ሁኔታውን ለመቆጣጠርና ህብረተሰቡን ለማረጋጋት ጥረት እንዳደረገ ነገር ግን ብጥብጡ በተፈለገው ፍጥነት ሊቆም እንዳልቻል ገልጿል። በዚህም ሳቢያ የህዝቡን ሰላምና ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥል ሁኔታ በመፈጠሩ ሠራዊቱ ሁከትና ብጥብጡን በዝምታ እንደማይመለከተውና "ሰላም ለማረጋገጥ ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱን ጠብቆ አስፈላጊውን እርምጃ እንደሚወስድ" አስጠንቅቋል። ሁከቱ በተከሰትባቸው አካባቢዎች ያሉ ነዋሪዎች ከፍ ያለ ስጋት ውስጥ መሆናቸውን የተናገሩ ሲሆን የት እንዳሉ ሳይታወቅ የቆዩት የክልሉ ርዕሰ-መሰተዳደር አቶ አብዲ ሞሃመድ ኦማር በክልሉ ቴሌቪዥን ላይ ቀርበው መረጋጋት እንዲፈጠር መልዕክት አስተላልፈዋል።
news-46368421
https://www.bbc.com/amharic/news-46368421
ጆን ማጉፉሊ፦ ታንዛኒያ "አስገዳጅነት የሌለበትን" የቻይናን እርዳታ ትመርጣለች
የታንዛኒያው ፕሬዝዳንት ጆን ማጉፉሊ ከምዕራባውያን ከሚገኘው እርዳታ ይልቅ አነስተኛ ግዴታ ያለበትን የቻይና እርዳታን እንደሚመርጡ ተናገሩ።
ማጋፉሊ በአጨቃጫቂ ፖሊሲዎቻቸው ምክንያት ምዕራባዊያን ከፍተኛ ጫና እያሳደሩባቸው ነው። በህዳር ወር ዴንማርክ "በተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት ላይ ተቀባይነት የሌለው አስተያየት" ሰጥተዋል በሚል የ9.8 ሚሊየን ዶላር እርዳታን አቋርጣለች። በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ ፈታኝ ከሆነው የምዕራባውያን ተፅዕኖ በተፃራሪው ቻይና ከፍተኛዋ የልማት አጋር ሆናለች። • ". . . ጥፍር መንቀል ሕጋዊ አይደለም ስንለው ብሔሩ ውስጥ ለመደበቅ ይሞክራል" ጠ/ሚ ዐብይ • ''የአንድ ቤተሰብ አባላት ግድያ'' በቤኒሻንጉል ክልሏ ያሶ ከተማ • 418 ኢትዮጵያዊያንን ከየመን ወደ አገር ቤት ማጓጓዝ ተጀመረ በቀጣዮቹ ሶስት አመታትም 60 ቢሊየን ዶላር የሚያወጣ ብድርና እርዳታ በአፍሪካ ላይ ለማፍሰስ ቃል ገብታለች። የዚህ እርዳታና ብድር አብዛኛው ገንዘብ የሚውለው መሰረተ ልማትን ለመገንባት ይሆናል ተብሏል።የሐሙስ ምሽት አጫጭር ዜናዎች "እርዳታቸው የሚያስደስተው ነገር በምንም አይነት ግዴታዎች የታጠረ አይደለም። ሊሰጡ ሲወስኑ ይሰጡናል" ብለዋል ፕሬዝዳንት ማጉፉሊ። ይህንን የተናገሩት ከቻይና መንግስት በተገኘ የ40.6 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ በዳሬ ሰላም በሚገኝ ዩኒቨርስቲ የተገነባውን ቤተ መፃህፍት በመረቁበት ወቅት ነው። በአሁኑ ወቅት የአውሮጳ ህብረት ለምስራቅ አፍሪካ በየአመቱ የ88 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ በማድረግ ትልቁ የልማት አጋር ነው።
news-54869792
https://www.bbc.com/amharic/news-54869792
አርሜኒያ "እጅግ በጣም የሚያም" ያለችውን የሰላም ስምምነት ከአዘርባጃን ጋር ለመፈረም ተገደደች
የአርሜኒያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኒኮል ፓሺንያን በሩሲያ አደራዳሪነት የፈረሙትን የሰላም ስምምነት "እጅግ በጣም የሚያም" ብለውታል።
አርሜኒያና አዘርባጃን ላለፉት ስድስት ሳምንታት ናጎርኖ ካራባህ በተሰኘች ግዛት የይገባኛል ጥያቄ የተነሳ የለየለት ጦርነት ውስጥ ነበሩ። አርሜኒያና አዘርባጃን ላለፉት ስድስት ሳምንታት ናጎርኖ ካራባህ በተሰኘች ግዛት የይገባኛል ጥያቄ የተነሳ የለየለት ጦርነት ውስጥ ነበሩ። በጦርነቱም በሺዎች ተገድለዋል፣ በመቶ ሺዎች ደግሞ ተፈናቅለዋል። የናጎርኖ ካራባህ ራስ ገዝ ግዛት በዓለም አቀፍ ሕግ የአዘርባጃን ክልል ቢሆንም ከ1994 ጀምሮ ግን በአርሜኒያ መንግሥት ድጋፍ የሚደረግለት፣ አርሜኒያዊያን ብሔር ተወላጆች የሚኖሩበት ከአዘርባጃን ቁጥጥር ያፈነገጠ ግዛት ሆኖ ቆይቷል። አዘርባጃን ስትዋጋ የነበረውም ይህንኑ ሕጋዊ ግዛቷን ለማስመለስ ነበር። የሰላም ስምምነቱ ምን ይዟል? ይህ ሩሲያ ያሸማገለችው አዲስ የሰላም ስምምነት በአገሬው አቆጣጠር ከማክሰኞ እኩለ ሌሊት ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል። በዚህ ስምምነት መሰረት አዘርባጃን እስካሁን በጦርነት ድል ያደረገቻቸው የናጎርኖ ካራባህ ቦታዎችን ይዛ ትቆያለች። አርሜኒያ ደግሞ ቀስ በቀስ በሳምንታት ውስጥ ከተቀሩት የግዛቱ አካባቢዎች ለመልቀቅ ተስማምታለች። ይህ ተፈጻሚ እንዲሆን ደግሞ ቭላድሚር ፑቲን 2ሺ የሚሆኑ ወታደሮቻቸውን ወደ አካባበው በሰላም አስከባሪነት ይልካሉ። ሩሲያ ብቻም ሳይሆን ቱርክም ወታደሮቿን በሰላም ማስከበር ወደ ግዛቱ ታስገባለች። ይህ ስምምነት የጦር ምርኮⶉችን መለዋወጥን፣ የተዘጉ ድንበሮችንና የጉዞ እቀባዎች ማንሳትን ይጨምራል። አዘርባጃን የሰላም ስምምነቱ ትልቅ ድል ነው ስትል በአርሜኒያ በኩል ግን "የተሸለው አማራጭ" ተደርጎ ተወስዷል። በአርሜኒያ ዋና ከተማ የረቫን መንግሥታቸው በተሸናፊነት መፈረሙ ያስቆጣቸው ዜጎች የመንግስት ንብረቶችን ሲያወድሙና ተቃውሞ ሲያሰሙ ታይተዋል። አርሜኒያ ወደ ጦርነቱ በታላቅ ጀብዱ ከተቀላቀለች ወዲህ የአዘርባጃንን ጥቃት መከላከል ተስኗት ቆይታለች። ትናንት የራስ ግዝ ግዛቱን ሁለተኛ ትልቅ ከተማ ሹሻን በአዘርባጃኖች ተነጥቃለች። ትናንት አዘርባጃን በስህተት የሩሲያ አውሮፕላንን መትታ ጥላለች። ለድርጊቱ ከፍተኛ ይቅርታ ጠይቃለች። በስህተት ነው የመታሁት፣ ካሳም እከፍላለሁ ብላለች።
news-55277459
https://www.bbc.com/amharic/news-55277459
ኮሮናቫይረስ እስካሁን ባልታየ መጠን የካርቦን ልቀትን ቀነሰ
የኮሮናቫይረስ ስርጭትን ለመግታት የተወሰዱ እርምጃዎች ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ የአየር ብክለት እንዲቀንስ ማገዛቸው ተገለጸ።
ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወዲህ የካርቦንዳይኦክሳይድ ልቀት የቀነሰው ዘንድሮ ነው። የልቀት መጠኑ 7% ቀንሷል። ዝቅተኛ የካርቦንዳይኦክሳይድ ልቀት ያስመዘገቡት ፈረንሳይ እና ዩናይትድ ኪንግደም ናቸው። የወረርሽኙን ሁለተኛ ዙር ስርጭት ተከትሎ የእንቅስቃሴ ገደብ በመጣላቸው ነው የአየር ብክለትን መቀነስ የቻሉት። ከወረርሽኙ ያገገመችው ቻይና ግን በቀጣዩ ዓመት የካርቦንዳይኦክሳይድ ልቀቷ እንደሚጨምር ተገልጿል። “ግሎባል ካርቦን ፕሮጀክት” እንዳለው፤ ዘንድሮ የካርቦን ልቀት ወደ 2.4 ቢሊዮን ቶን ወርዷል። እአአ 2009 ላይ የምጣኔ ሀብት ቀውስ ሲከሰት የካርቦን ልቀት የቀነሰው በግማሽ ብቻ ነበር። በያዝነው ዓመት አሜሪካ እና አውሮፓ 12% ቀንሰዋል። ከፍተኛ መቀነስ የተስተዋለው በፈረንሳይ (15%) በዩናይትድ ኪንግደም (13%) ነው። የዩኬው ፕ/ር ኮርኒ ለኩዌሬ “የሁለቱ አገሮች የካርቦን ልቀት ዋነኛ ምንጭ የመጓጓዣ ዘርፍ ነው። ኢንዱስትሪ እናሌሎች ዘርፎች በሁለተኛ ደረጃ ይገኛሉ” ይላሉ። በመላው ዓለም በወረርሽኙ ሳቢያ የበረራ ቁጥር በእጅጉ ቀንሷል። ይህም ለካርቦን ልቀት መቀነስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው። ከዚህ ዘርፍ የሚመዘገበው የካርቦን ልቀት 40% ሲሆን ይህም ከአምናው ያንሳል። ስለዘንድሮው የካርቦን ልቀት መጠን ጥናት የሠሩት ባለሙያዎች እንደሚሉት፤ ቻይና በዚህ ዓመት የካርቦን ልቀቷን በ1.7% ቀንሳለች። ሆኖም ግን ባለፉት ጥቂት ወራት የወረርሽኙን ስርጭት በተሻለ ሁኔታ መቆጣጠሯ የካርቦን ልቀት ዳግመኛ እንዲጨምር ምክንያት ሆኗል። የጥናቱ ተሳታፊ ጃን አይቨር ኮርስባክን እንዳሉት፤ እአአ በ2020 መጨረሻ ላይ የቻይና የካርቦን ልቀት ከ2019 ጋር ተቀራራቢ ነው። “አንዲያውም አንዳንድ መላ ምቶች እንደሚጠቁሙት የቻይና የካርቦን ልቀት እየጨመረ ሳይመጣ አይቀርም” ብለዋል አጥኚው። የፓሪስ የአየር ንብረት ስምምነት ላይ የተቀመጠው ግብ እንዲሳካ ለቀጣይ 10 ዓመታት፤ በየዓመቱ ሁለት ቢሊዮን ቶን የካርቦን ልቀት መቀነስ እንዳለበት ባለሙያዎች ይናገራሉ። ፕ/ር ፒዬሬ ፍሪድልግስተን እንደሚሉት፤ የዓለም አየር ንብረት በአስተማማኝ ሁኔታ ሊስተካከል የሚችለው የካርቦን ልቀት ዜሮ ሲደርስ ነው።
news-53758759
https://www.bbc.com/amharic/news-53758759
ኢትዮጵያ ፡ መንግሥትንና ህወሓትን የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት እንዲያሸማግሉ ክራይስስ ግሩፕ ሐሳብ አቀረበ
የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትርና የሠላም ኖቤል ተሸላሚው ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታራቂና የሚያቀራርቡ ንግግሮቻቸውን ወደ ተግባር እንዲለውጧቸው ኢንተርናሽናል ክራይስስ ግሩፕ ጠየቀ።
ቡድኑ በተጨማሪም ያለውን ውጥረት ለማርገብ አስፈላጊ ከሆነም የአፍሪካ ሕብረት ወይም የአፍሪካ መሪዎች በማሸማገሉ በኩል ተሳትፎ ሊያደርጉ ይችላሉ ከማለት በተጨማሪ በተለይ የወቅቱ የአፍሪካ ሕብረት ሊቀ መንበር የሆኑት የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ ቁልፍ ሚና ሊጫወቱ ይችላሉ ብሏል። ኢንተርናሽናል ክራይስስ ግሩፕ የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታ፣ በተለይም የትግራይንና የማዕከላዊውን መንግሥት ፍጥጫ ትኩረት ሰጥቶ በገመገመበት ባለ 14 ገጽ ሰነድ እንደጠቀሰው በኦሮሚያ ክልል የሰላም መደፍረስና የፌዴራል መንግሥት ከትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መስተዳደር ጋር የገባበት ፍጥጫ በንግግር ሊፈታ ይገባል ሲል መክሯል። አለበለዚያ ግን ተስፋ የተጣለበት ፖለቲካዊ ሽግግሩ እንቅፋት ሊገጥመው ይችላል ሲል ስጋቱን አንጸባርቋል። በኦሮሚያ ከተሞች በቅርቡ የታዩት ሠላም መደፍረሶች ኢትዮጵያ የጀመረችውን ፖለቲካዊ ሽግግር አደጋ ላይ ሊጥሉ የሚችል አሳሳቢ ቀይ መብራቶች ናቸው ብሏል ድርጅቱ። የትግራይ ክልል ልሂቃን ክልላዊ ራስን የማስተዳደር መብት በክልልላችን ምርጫ ማካሄድ ሙሉ መብት ያጎናጽፈናል የሚል አቋም እንደያዙና የፌዴራል መንግሥት በበኩሉ ሕገ መንግሥቱ ይህን እንደማይፈቅድ በመግለጹ ፍጥጫው መከሰቱን ካብራራ በኋላ ሁለቱም ወገኖች ፖለቲካዊ ጡዘቶችን እንዲያረግቡ ተማጽኗል። ሁለቱም ወገኖች የያዙትን አቋም ያስቀመጠው ኢንተርናሽናል ክራይስስ ግሩፕ ማዕከላዊ መንግሥት በህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ላይ ለማሳደር እየሞከረ እንደሆነ የጠቀሰ ሲሆን ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ በበኩሉ ምርጫ አካሄዳለው ብሎ ዝቷል። ሆኖም እንደ ክራይስስ ግሩፕ ከሆነ ሁለቱም የያዙት አቋም አያዋጣም። የሁለትዮሽ ንግግርንም አያበረታታም። ሁለቱም "የገደል ጫፍ ላይ ናቸው" ያለው ድርጅቱ በብልጽግናና በህወሓት መካከል ያለው መጠላላትና ሽኩቻ በመጨረሻ የአገር ተስፋን የሚያጨልም ነው ብሎታል። ሰነዱ የትግራይ ልሂቃን ከምርጫ ጋር በተያያዘ ካሉ ሁኔታዎች ለማትረፍ የሚያደርጉት ሙከራ አደገኛ ነው ካለ በኋላ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይም የአገር መሪና የሠላም ኖቤል ተሸላሚ እንደመሆናቸው ይበልጥ እርሳቸው የሞራል ልዕልናው ኖሯቸው አስታራቂ መንፈስ ያለው አንደበታቸውን (ንግግሮቻቸውን) ወደ ተግባር እንዲመነዝሩ ጠይቋል። ለተቃዋሚዎችም ሆነ አሁን ከእርሳቸው በተቃራኒ ለቆመው የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ፓርቲ የእርቅ ዕድሎችን እንዲያመቻቹም አሳስቧል። በማዕከላዊው መንግሥትና በህወሓት መካከል ያለውን ፍጥጫና መከራር ለማለዘብ በሰኔ ወር የሽማግሌዎች ቡድን ሙከራ ጀምሮ እንደነበር ያስታወሰው ሰነዱ፤ ሆኖም ሁለቱም ባላቸው ግትር አቋም የተነሳ ሽምግልናውን ከበድ ላለ አካል ማስተላለፍ ሳያስፈልግ አይቅርም ብሏል። ምናልባት ለህወሓትና ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ቅርብ የሆኑ ስመጥር የአፍሪካ መሪዎች በሽምግልናው ላይ ቢገቡ መልካም ይመስላል ሲል ሃሳብ አቅርቧል። ሆኖም ግን የሚመጡት ሸምጋዮች የኢትዮጵያ መንግሥታት ለውጭ ጣልቃ ገብነት ያላትን አሉታዊ አመለካት ከግምት በማስገባት ከአፍሪካ መሪዎች ሸምጋይ የሚሆኑት ርዕሳነ ብሔራት ብልህና ስልተኛ መሆን እንደሚጠበቅባቸው ከወዲሁ አሳስቧል። በዚህ ረገድ የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበርና የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ አዎንታዊ ሚና ሊጫወቱ እንደሚችሉ ተስፋ አድርጓል፤ ኢንተርናሽናል ክራይስስ ግሩፕ። በሽምግልና የሚሳተፉ ተሰሚነት ያላቸው የአገር መሪዎች መጀመርያ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አስተዳደር ወታደራዊ እርምጃ ቀርቶ ምንም አይነት የፋይናንስ ጫና በህወሓት ላይ እንዳያሳድር መምከር ይኖርባቸዋል ብሏል ድርጅቱ። በተመሳሳይ መቀለ ያለውን አመራር ምርጫ የማካሄዱን ሐሳብ እንዲተው ማግባባት ይጠበቅበታል። ሆኖም ድርጅቱ ሁለቱ ወገኖች ጽንፍ በመያዛቸው አስታራቂና አማካይ መንገድ ማግኘት ቀላይ እንደማይሆን ይጠበቃል ብሏል። የትግራይ ክልል ምርጫ የማካሄድ ሙሉ ሥልጣን አለኝ ካለ ሁሉንም የሕግ ሂደቶች አሟጦ መጠቀም ይኖርበታል ይላል። ለምሳሌ ፌዴሬሽን ምክር ቤት የሕገ መንግሥት ትርጉም የመስጠት ስልጣን ስላለው ክልሎች በራሳቸው ምርጫ ማካሄድ አለባቸው ወይስ የለባቸውም በሚለው ጉዳይ ላይ የመጨረሻ ውሳኔ እንዲሰጥ ክልሉ ይግባኝ እንዲልና የሕግ መስመርን ብቻ እንዲከተል መክሯል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ የአራት ክልላዊ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጥምረት የሆነውና ለሦስት አስርት ዓመታት ያህል አገሪቱን ያስተዳደረው ገዢ ፓርቲ ኢህአዴግ ከስሞ አንድ ወጥ አገራዊ ፓርቲ እንዲመሰረት አድርገዋል። ከኢህአዴግ መክሰም በኋላ አዲስ ወደ ተመሰረትው የብልጽግና ፓርቲ መግባት ያልፈለገው በአገሪቱ የፖለቲካ መድረክ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ የነበረው ህወሓት ከማዕከላዊው መንግሥት ጋር አለመግባባት ውስጥ ቆይቷል። በተለይም በዚህ ወር መጨረሻ ላይ ሊካሄድ ታቅዶ የነበረው አገራዊ ምርጫ በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ለሌላ ጊዜ መተላለፉን ህወሓት አምርሮ የተቃወመው ሲሆን በሚያስተዳድረው ክልል ውስጥ የተናጠል ምርጫ አካሂዳለሁ በማለቱ አለመግባባቱ እየተባባሰ ሄዷል።
news-54869791
https://www.bbc.com/amharic/news-54869791
ሕንድ፡ ራሳቸውን ለማጥፋት የሚመጡ ሰዎችን 'አላስሞት' እያለ ያስቸገረው ዋናተኛ
ሺቫ ይባላል፡፡ ወጣት ነው፡፡ በሰሜን ሕንድ ሀይድራባድ ከተማ ይኖራል፡፡ እዚያ አንድ ሐይቅ አለ፡፡ ሑሴን ሳጋር ሐይቅ የሚባል፡፡
ሺቫ ብቻ በሚል መጠሪያ ብቻ የሚታወቀው ወጣት ከ100 በላይ ሰዎችን ሕይወት መታደጉን ይናገራል ብዙ ሰዎች እየገቡ ሰምጠው ይሞቱበታል፡፡ ራሳቸውን ማጥፋት የሚፈልጉ ሰዎች እዚያ ይሄዳሉ፡፡ ራስን ለማጥፋት በጣም የተስማማ ሐይቅ ነው ይሉታል የአካባቢው ሰዎች፡፡ አንደኛ ጥልቅ ነው፤ ሁለተኛ ቆሻሻ ነው፤ ሦስተኛ እባብና በርካታ ገዳይ እንሰሳት ይኖሩበታል፡፡ ራስን ለማጥፋት እንደ ሑሴን ሳጋር ያለ ሐይቅ ከየት ተገኝቶ? ሺቫ ግን አስቸገረ፡፡ ሰዎች በሰላም ሰምጠው እንዳይሞቱ እንቅፋት ሆነባቸው፡፡ ከሞት ጋር ለምን ይተናነቃል? ለዓመታት ሺቫ ፖሊስን ሲያግዝ ነው የኖረው፡፡ ገና 10 ዓመቱ ላይ ሳለ ምን ሆነ መሰላችሁ? የሆኑ ፖሊሶች መጡና ከዚህ ሐይቅ የሞተ ሰው ሬሳ ለሚያወጣ ሰው ገንዘብ እንሸልማለን አሉ፡፡ ሺቫ እዚያ ሰፈር ነበር፡፡ ለፖሊሶቹ "ሰውየውን እኔ አወጠዋለሁ" አላቸው፡፡ ፖሊሶቹ ደንግጠው እርስ በእርስ ተያዩ፡፡ ፖሊስ በዚያ አካባቢ በቂ በጀት ስለሌለው የራሱ ጠላቂ ዋናተኛ እንኳን አልነበረውም፡፡ የፖሊስ መኮንኖቹ መዋኘት እንኳ አይችሉም፡፡ ስለዚህ ነበር ዋናተኛ ያስፈለጋቸው፡፡ ሺቫን ግን አላመኑትም፡፡ ይህ የ10 ዓመት ታዳጊ እንዴት ነው ከዚህ ሐይቅ ሬሳ ተሸክሞ የሚወጣው? "ሬሳ አወጣለሁ ብሎ ሬሳ እንዳይሆን ብቻ" እያሉ ሲከራከሩ ሺቫ ዘሎ ባሕር ውስጥ ገብቷል፡፡ በደቂቃ ውስጥ ሬሳውን ይዞት ወጣ፡፡ 40 ሩጲ ተከፈለው፡፡ በዶላር 0.42 ሳንቲም ቢሆን ነው፡፡ ይህ ከሆነ 20 ዓመት አለፈው፡፡ አሁን ሺቫ 30 ዓመት ደፍኗል፡፡ ሥራውን ግን አልቀየረም፡፡ ሬሳ ያወጣል፡፡ ለምን አላስሞት ይላል? አሁንም ድረስ ሬሳ ጥልቅ ሐይቅ ውስጥ ገብቶ ያወጣል፡፡ ይህ ብቻ አይደለም ግን ሥራው፡፡ ሰዎች ራሳቸውን ሊያጠፉ ሲሉም ያደናቅፋል፡፡ ሺቫ የሚኖረው ከሑሰይን ሳጋር ሐይቅ በቅርብ ርቀት ነው፡፡ ይህ ሐይቅ ሰው ሰራሽ ነው፡፡ ይህ ሐይቅ የሂንዱ አማልክትን ለማጥመቅ እና ጋኔሻ ለሚባለው መንፈሳዊ ክብረ በዓል አገልግሎት ላይ ይውላል፡፡ ይህ ሐይቅ ታዲያ ለማምለኪያነት ብቻ አይደለም የሚውለው፡፡ ሰዎች ራሳቸውንም ለማጥፋት የሚመርጡት ሁነኛ ሐይቅ ነው፡፡ ላለፉት 20 ዓመታት እንዳደረገው ሁሉ ሺቫ አሁንም የሟቾችን ሬሳ ከሐይቁ ያወጣል፡፡ ፖሊስ ዛሬም ድረስ በሱ ተማምኖ ነው ያለው፡፡ በዚህ ሐይቅ ብቻ ሳይሆን በአቅራቢያ ከሚገኙ ሌሎች ሐይቆች በርከት ያሉ ሬሳዎችን ያወጣል፡፡ ሺቫ ሬሳን ብቻ ማውጣት አይደለም ሥራው ብያችኋለው፡፡ እንዲያውም ይበልጥ የሚታወቀው የታቀደን ሞት በማክሸፍ ነው እንጂ ሬሳ በመጎተት አይደለም፡፡ "ኧረ በጣም ብዙ ሰው ነው ያዳንኩት፤ መቁጠር ሁሉ አቁሜያለሁ፤ ለመጨረሻ ጊዜ ትዝ የሚለኝ 114ኛውን ሰው ማዳኔ ነው" ብሏል ለቢቢሲ፡፡ አሁን የሟቾች ቁጥር እየጨመረ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ ነፍስ አዳኝ እጥረት ገጥሞታል፡፡ ከሰሞኑ ሚስቱን ዋና የሚያለማምዳትም ለዚሁ ነው፡፡ እሷ ቢያንስ ሴት ሟቾችን ብታድን፤ ከሞቱም ደግሞ ሬሳቸውን ጎትታ ብታወጣ ቀላል አይደለም፡፡ ኢንስፔክተር ቢ ዳናላክሽሚ የአካባቢው መርማሪ ፖሊስ ናቸው፡፡ እሳቸው ስለ ሺቫ ምስክርነት ሰጥተዋል፡፡ "ሺቫ፣ እኔ ብቻ የማውቀው ከመቶ ሰው በላይ ሰው ራሱን ለማጥፋት ሲል ሕይወቱን አድኗል" ይላሉ፡፡ ራስን ማጥፋት በሕንድ አገር ወንጀል ነው፡፡ ስለዚህ ራሳቸውን ለማጥፋት የሚሞክሩትን ካዳናቸው በኋላ እንዲለቃቸውና እንዲሸሹ ይፈልጋሉ፡፡ በኋላ ግን ፈልገው ያገኙታል፡፡ ይህን ሁሉ ነፍስ የሚያድነው ሺቫ ነፍስ ካወቀበት ዘመን ጀምሮ ወላጆቹን አያውቅም፡፡ ጎዳና ነው ያደገው፡፡ የሆነ ጊዜ ግን አንዲት አሮጊት አስጠጉት፡፡ የሳቸው ልጅ ነው ለመጀመርያ ጊዜ ዋና ያስተማረው፡፡ የሆነ ጊዜ ታዲያ የሆኑ ጓደኞቹ ጋር እየዋኙ ሳለ ይሄ ዋና ያስተማረው "ወንድሜ" የሚለው ልጅ ይሰምጣል። እሱን ለማዳን ጠልቆ የገባው ሌላ ልጅ ግን በዚያው ሞተ፡፡ "አሁን ያ ይጸጽተኛል፤ ሰዎችን የምታደገው ያን ጓደኛችንን ባለማዳኔ ለማካካስ ነው" ይላል፡፡ ሺቫ መሞት ፈልገው ከሞት ድንገት የታደጋቸው ሰዎች በሚሰጡት የኪስ ገንዘብ ነው የሚተዳደረው፡፡ የተመኙትን ሞትን ካስመለጣቸው በኋላ በጣም ይጠሉታል፡፡ ትንሽ ከኖሩ በኋላ ግን ባለውለታቸው ያደርጉታል፡፡ ሺቫ አሁን ትንሽዬ ዝናን እያገኘ መጥቷል፡፡ "የአገሬውን ሰው አላስሞት ያለው ወጣት" በሚል ጋዜጦች ላይ ስሙ ከወጣ በኋላ ቴሉጉ በሚባል የሕንድ ፊልም ላይ እንዲተውን ተደርጓል፡፡ ኮቪድ ደንበኛ አብዝቶለታል ሰሞኑን አንድ ሰውዬ ኮቪድ ያዘኝ ብሎ ደንግጦ ራሱን ለማጥፋት ወደ ሐይቁ መጣ፡፡ ከጓደኛው ጋር ነው የመጣው፡፡ ሆኖም ጓደኛው ይህ ኮቪድ ያዘኝ የሚለው ሰው ራሱን ሊያጠፋ እንደመጣ አላወቀም፡፡ ጥልቁ ሐይቅ ውስጥ ሲገባ ጓደኛውም አብሮት ዘሎ ገባ፡፡ ሺቫ ሦስተኛ ሆኖ ተከተላቸው፡፡ ማዳን የቻለው ግን ለመሞት አቅዶ የነበረውን ጓደኛ ብቻ ነበር፡፡ ባለ ኮቪዱ ሰውዬ ግን እንዳለመው ይቺን ምድር ተሰናበተ፡፡ "ሬሳውን አውጥቼ ሰጠኋቸው፡፡ ነገር ግን ቤተሰቦቹም ኮቪድ ይይዘናል ብለው ሬሳውን ለመውሰድ አልፈለጉም" ይላል ሺቫ፡፡ "ሬሳውን የሚረከበኝ ሳጣ ምን ላድርግ? አቃጠልኩት" ይህ ሰዎች በስፋት እየሞቱበት ያለው ሐይቅ በጣም ቆሻሻና የተበከለ ነው፡፡ በዚህ የተነሳ ሺቫ በርካታ የቆዳ ሕመሞች እንዲሁም ታይፎይድ ይዞታል፡፡ ሆኖም ወዴት ይሂድ፡፡ ለምን ሥራ አትቀይርም ሲባል፣ "እኔ ሰዎችን ከሞት ከማትረፍ በላይ እርካታ የሚሰጥ ሥራ አለ ብዬ አላምንም፤ ከዚህ ኃይቅ ወደየትም ንቅንቅ አልልም" ይላል፡፡
news-48822418
https://www.bbc.com/amharic/news-48822418
በኢትዮጵያ የቴሌኮም ዘርፍ ፍላጎቱን ያሳየው የሳፋሪኮም ሥራ አስፈጻሚ አረፉ
በምሥራቅ አፍሪካ ሃገራት ውስጥ ስኬታማውና በኢትዮጵያ ገበያም ለመሳተፍ ፍላጎት ያሳየው ግዙፉ የቴሌኮም ኩባንያ ሳፋሪኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት ቦብ ኮሊሞር ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን ድርጅታቸው አስታደቀ።
ሳፋሪኮም የዋና ሥራ አስፈጻሚውን ዜና እረፍት ይፋ ባደረገበት መግለጫው ላይ እንዳመለከተው፤ ቦብ ኮሊሞር በ61 ዓመት እድሜያቸው በካንሰር ምክንያት ዛሬ ጠዋት ቤታቸው ውስጥ ህይወታቸው ማለፉን ገልጿል። ቦብ ካሊሞር የካሪብያኗ ጉያና ሃገር ተወላጅ ሲሆኑ በዜግነት ደግሞ እንገሊዛዊ ነበሩ። • ሳፋሪኮም የተጠቃሚዎችን መረጃ በማውጣት ተከሰሰ • ኢትዮ-ቴሌኮም፡ አንድ ወደፊት ሁለት ወደኋላ? ከሁለት ዓመት በፊት ጥቅምት ወር ላይ ቦብ ኮሊሞር ወደ ዩናይትድ ኪንግደም ሄደው ላጋጠማቸው የደም ካንሰር አይነት ለወራት ህክምና ሲከታተሉ ቆይተው ከተመለሱ በኋላ ሥራቸውን ማከናወን ቀጥለው እንደነበር ድርጅታቸው በመግለጫው ጠቅሷል። ከዚያም በኋላ ህክምናቸውን ሲከታተሉ እንደቆዩ ነገር ግን የጤና ሁኔታቸው "ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሶ ነበር" ሲል አስታውሷል። ቦብ ኮሊሞር የሳፋሪኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት ከዘጠኝ ዓመት በፊት ሲሆን፤ በቆይታቸውም በሞባይል ስልክ ክፍያን መፈጸምን ጨምሮ ድርጅቱ በአካባቢው ሃገሮች ውስጥ ያለውን የመሪነት ደረጃ ጠብቆ እንዲቆይ ለማድረግ አስችለውታል። የቦብ ኮሊሞር ህልፈትን ተከትሎ በመላው ኬንያ ያሉ ባለስልጣናትና ታዋቂ ሰዎች ሃዘናቸውን እየገለጹ ሲሆን የሃገሪቱ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ግለሰቡ "ባለራዕይና የተለዩ መሪ ነበሩ" ሲሉ ምክትላቸው ዊሊያም ሩቶ ደግሞ "ምሳሌ የሚሆኑ፣ ብልህና ደፋር" ሲሉ በሃዘን መግለጫ መልዕክታቸው ላይ አስፍረዋል። ኢትዮጵያ የቴሌኮም ዘርፉን ለግሉ ዘርፍ ክፍት እንደምታደርግ ካሳወቀችበት ጊዜ ጀምሮ ሳራፊኮም በዘርፉ ለመሳተፍ ፍላጎታቸውን ከገለጹ ቀዳሚ ድርጅቶች መካከል አንዱ ነው።
51131134
https://www.bbc.com/amharic/51131134
እሷ ማናት #11 ቋንቋውን የማይችል እንኳ በትወና ብቃቷ ያጨበጨበላት አርቲስት አበበች አጀማ
አርቲስት አበበች አጀማ ትውልድ እና እድገቷ በገጠራማው የምዕራብ ሸዋ ዞን ነው። በኦሮምኛ ቋንቋ የቴሌቪዥን ድራማ ላይ በመተወን በስፋት ትታወቃለች።
ብልጭ ድርግም በሚሉት የአፋን ኦሮሞ ቲያትሮች ላይ እንደ ኮከብ የሚስሏት በርካቶች ናቸው። ከአንድም ሁለት ቲያትሮች ላይ ዋና ተዋናይ ሆና ሰርታለች። በበዓል ቀናት በሚዘጋጁ የቴሌቪዥን ጭውውቶች ላይም ቋንቋውን የማይችል እንኳ በትወና ብቃቷ ተዝናንቷል። አርቲስት አበበች በምትወደው የጥበብ ዓለም አስርት ዓመታት በላይ ስትኖር ብዙ ውጣ ውረዶችን ማለፏን ታስረዳለች። አበበች የ18 ዓመታት የጥበብ ዓለም ጅማሬዋንና ህይወትን እንዲህ በአንደበቷ ታስቃኘናለች። ተወልጄ ነፍስ ያወቅኩት ገጠር ውስጥ ነው። እኔ በተወለድኩበት ቦታ የሴት ልጅ ጠለፋ በጣም የተለመደ ነበር። ሴት ልጆች ይጠለፉ እና ትምህርታቸውን ከዳር ሳያደርሱ ይዳራሉ። ከዚህ ልትታደገኝ የፈለገችው አክስቴ ወደ አዲስ አበባ መጥተሽ መማር አለብሽ ብላኝ ወደ ከተማ አመጣችኝ። ከዚያም በአዲስ አበባ እስከ 12ኛ ክፍል ድረስ ተማርኩኝ። ከዚያም ከጓደኛዬ ጋር ሆነን ሥራ ፍለጋ ከተማ ውስጥ እየተዘዋወርን የሥራ ማስታወቂያዎችን ማንበብ ተያያዝነው። ከዛ የኦሮሚያ የባህል እና ስፖርት ቢሮ በትያትር እና በስነ-ጽሑፍ መማር የሚፈልግ ይመዝገብ የሚል ማስታወቂያ ተመለከትን። ጓደኛዬ ተመዝግበን ካልተማርን አለችኝ። እኔ ግን ሥራ የማግኘት እንጂ ወደ ትምህርት የመመለስ ፍላጎት አልነበረኝም። በመጨራሻ ግን ተመዝግቤ ከእርሷ ጋር አብሬ መማር ጀመርኩ። እኔ በባህሪዬ በጣም ዓይናፋር ነበረርኩኝና ክፍል ውስጥ እንኳን እቀመጥ የነበረው መጨረሻ መስመር ላይ ነበር። አንድ አቶ ዲማ አበራ የሚባል መምህር ነበረን። ይህ አስተማሪ 'ነይ ወደፊት ውጪና ተናገሪ' ይለኝ ነበር። እኔም ለራሴ 'ለዚህ ሰውዬ ስል ይሄን ትምህርት ማቋረጥ አለብኝ' እያልኩ እናገር ነበር። አሁን ላይ ግን ይህን መምህር ሁሌም ከልቤ አመሰግነዋለሁ። የራስ መተማመን ኖሮኝ ወደፊት ወጥቼ አቅሜን እንድጠቀም ያስቻለኝ እሱ ነው። በተለያዩ ድራማዎች እና ቲያትሮች ላይ የተለያዩ ገጸ ባህሪዎችን ተጫውቻለሁ። አንድ ግዜ ሩህሩህ ሆኜ ሌላ ግዜ ደግሞ ጨካኝ የእንጀራ እናት ሆኜ ተውኛለሁ። የትያትር ሥራ ስጀምር የሚከፈለን 18 ብር ብቻ ነበር። የማገኛትን ይችህን 18 ብር ነበር ለምግብ ሆነ ለሁሉም ወጪዬ መሸፈኛ አደርጋት የነበረው። በዚህ ሙያ ታዋቂ ካደረጉኝ ሥራዎቼ መካከል በፋና ሬዲዮ ለበርካታ ዓመታት የተላለፈው "አባ ጃምቦ" በተሰኘው የሬዲዮ ድራማ ላይ የነበረኝ ተሳትፎ ነው። ይህ ድራማ የጀመርነው ያለምንም ክፍያ ነው። በሬዲዮው ድራማ ላይ ማህበራዊ ጉዳዮች በጥልቅ ስለሚዳሰሱ በብዙዎች ዘንድ በጣም ተወዳጅ አድርጎታል። ደንጋ በሚሰኘው ፕሮግራም ላይም በርካታ ሠራዎችን ሰርቻለሁ። በጣም አስደሳች ጊዜ አሳልፌያለሁ። ለጥበብ ሙያ ከነበረን ፍቅር የተነሳ በቂ ክፍያ እንኳ ሳናገኘ ነበር የምንሰራው። የልምምድ ቦታ አጥተን በቤተ-ክርስቲያን ግቢ ውስጥ ለመለማመድ ሄደን ተባረን እናውቃለን። ዛሬ ላይ ግን የጥበብ ሥራው የተሻለ ደረጃ ላይ ደርሶ፤ ቋንቋ እና ባህላችን አድጎ ስመለከት ከፍተና ኩራት ይሰማኛል። "ሚስጥሬ ትዕግስቴ ነው" በጥብበ ውስጥ ለብዙ ዓመታት እንድኖር ያደረገኝ ነገር ትዕግስቴ ነው። ዓላማ አለኝ፤ ይህም የአፋን ኦሮሞ 'አርት' አድጎ ማየት ነው። አሁን ላይ በጎ ለውጥ አይቻለሁ። ይህም የሆነው ሳልሰላች በምወደው ህዝብ ተስፋ ባለመቁረጤ ነው። አንድ አሁኑ መሠረተ ልማቶች ባልተስፋፉበት ዓመት እየተዘዋወርን በትያትር ህዝቡን የማንቃት ሥራ ስንሰራ ነበር። በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል ግጭት ተከስቶ በነበነረበት ጊዜም ድንበር ድረስ ሄደን ሠራዊቱን በጭውውት ስናዝናና ነበር። ይህን ሁሉ ማድረግ የቻልኩት ለህዝብ በነበረኝ ፍቅፍ ብቻ ነው። የተረፈኝም የህዝብ ፍቅር ነው። ለሙያው እና ለህዝብ ፍቅር እና ክብር ስል ብዙ መስዋትነት ከፍያለሁ። እንደምሳሌ አንድ ሁሉቆ የሚባል ትያትር በራሳችን ወጪ አዘጋጅተን ከስንት ድካም በኋላ ለማስመረቅ አንድ ሳምንት ሲቀረን መንገድ ላይ ወድቄ እግሬ ተሰበረ። ሆስፒታል ተኝቼ የማስበው ስለ ቲያትሩ ነበር። ሃኪሙ መጥቶ 'ይሄ እግር ሊቆረጥ ይችላል' ሲል ስሰማሁ ተነስቼ ጮህኩበት። ከዛ ሌላ ሃኪም ተቀይሮ መጥቶ አከመኝ። ሳይሻለኝ ከሆስፒታል ወጥቼ በሁሉቆ ቲያትር ላይ እያነከስኩ ስተውን ነበር። በተደጋጋሚ ሶስት ግዜ ብወድቅም ቲያትሩን ከመስራት አላገደኝም። የስራ ባልደረባዬ የሆነችው አልማዝ ኃይሌ በአንድ ወቅት እናቷን ሳትቀብር ለህዝብ ክብር ብላ መታ ቲያትር ሰርታለች። እኔም እንደ እርሷ ለህዝብ እና ለሙያው ፍቅር ያለኝ። ለዚህ ሙያ ስል ተርብያለሁ፤ ተጠምቻለሁ፤ ብዙ ውጣ ውረዶችን አልፊያለሁ። አሁን በደረስኩበት ደረጃም ደስተኛ ነኝ። ወደ ሙያው መቀላቀል የሚፈልጉ ወጣቶች በተለይ ደግሞ ሴቶች፤ የማይቻል ነገር የለም። ፍራቻን አስወጥታችሁ በችሎታችሁ ተማመኑ። ከዛ ይሳካል። እሷ ማናት? የሚለው ጥንቅራችን ያሰቡበትን ዓላማ ለማሳካት ብዙ ውጣውረዶችን ያሳለፉ ሴቶችን ታሪክ የምናስቃኝበት ነው።
news-53033475
https://www.bbc.com/amharic/news-53033475
ኮሮናቫይረስ፡ የእንቅስቃሴ ገደብና የታዳጊዎች የአእምሮ ጤና
በርካታ አገራት የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ለመከላከል ብሎም ለመቆጣጠር በማሰብ ይጠቅመናል ያሉትን እርምጃ እየወሰዱ ይገኛሉ። የሰዎች እንቅስቃሴን በመገደብ ንክኪ እንዲቀንሱ ማድረግ ደግሞ የመጀመሪያው ነው።
ታዲያ ሰዎች ወዳጅ ዘመዶቻቸውን እና ቤተሰቦቻቸውን በአካል ማግኘት አስቸጋሪ ሲቀርና ሃሳብ ጭንቀታቸውን አይን አይናቸውን እያዩ ማካፈል ሳይችሉ ሲቀሩ ደግሞ ቀላል የማይባል ሥነ ልቦናዊ ጫና ይደርስባቸዋል። በተለይ ደግሞ በአስራዎቹ እድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙት ታዳጊዎች ላይ ጫናው ይበረታል እተባለ ነው። በእንደዚህ አይነት አስቸጋሪ ወቅት የታዳጊዎች የአንጎል እድገት፣ አጠቃላይ ባህሪ እና የአእምሮ ጤና ሊስተጓጎሉ እንደሚችል የዘርፉ ባለሙያዎች አስጠንቅቀዋል። ምናልባት ቀላል የማይባል ጊዜያቸውን ማኅበራዊ መገናኛ መድረኮች ላይ ተጠምደው ማሳለፋቸው ድብርት ውስጥ እንዳይገቡ የሚያደርጋቸው ሊመስል ይችል ይሆናል፤ ነገር ግን እንዲያውም በርካታ ሰዓታትን ማኅራዊ ሚዲያዎች ላይ አፍጥጦ መዋል ከባድ ሥነ ልቦናዊ ጉዳት ያስከትላል። ለዚህም ይመስላል በርካታ አገራት የእንቅስቀሴ ገደቡን ላላ በማድረግ ትምህርት ቤቶች እንዲከፈቱ ቅድሚያ እየሰጡ የሚገኙት። እንደባለሙያዎቹ ጉርምስና የሚባለው ዕድሜ ከ10 እስከ 24 ዓመት ያሉትን ታዳጊዎች የሚያካትት ሲሆን በዚህ እድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙት ልጆች ለብዙ ነገሮች ተጋላጭ እንደሚሆኑ በተደጋጋሚ ይነገራል። ብዙ ጊዜ ደግሞ እነዚህ ታዳጊዎች በዚህ የእድሜ ክልላቸው ውስጥ ከቤተሰባቸው ጋር ያላቸውን ቅርበት የሚቀንሱበትና ከሚመስሏቸው ጓደኞቻቸው ጋር ከምንጊዜውም በበለጠ የሚቆራኙበት ወቅት ነው። ይህ በተፈጥሮ የሚመጣ ባህሪ ታዳጊዎቹ ወደ ጉልምስና ለሚያደርጉት ጉዞና ለአንጎላቸው እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ የዘርፉ ባለሙያዎች ገልጸዋል። በተጨማሪም ይህ ጊዜ በቀላሉ የአእምሮ በሽታዎች የሚያጋጥሙበት ወቅትም ሊሆን እንደሚችልም ይታወቃል ይላሉ ባለሙያዎቹ። የኮሮረናቫይረስ ወረርሽኝ መከሰት ደግሞ ነገሮችን ይበልጥ ከባድ ያደርጋቸዋል የሚሉት በኬምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ የሥነ ልቦና መምህር የሆኑት ፕሮፌሰር ሳራ ጄን ብላክሞር ናቸው። "የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ከተከሰተበት ጊዜ አንስቶ በመላው ዓለም የሚገኙ ታዳጊዎች ከምን ጊዜውም በበለጠ ጓደኞቻቸውን ማግኘት በሚያስፈልጋቸው ጊዜ ነገሮችን ከባድ ሆኖባቸዋል። ወሳኝ በሚባለው የእድገት ደረጃቸው ላይ ሲደርሱ ጓደኞቻቸውን በአካል ማግኘት አለቻላቸው አጠቃላይ እድገታቸው ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ ይኖረዋል።’’ "ምንም እንኳን የአካላዊ ርቀት ሕጎቹ ጊዜያዊ ቢሆኑም፤ ይህ ከጓደኛ ጋር የመገናኘት ዕድልን ከአንድ ታዳጊ ሕይወት ላይ ለአራትና ለአምስት ወራት ሲወሰድበት እድገት ላይ የሚኖረው ጫና ቀላል አይደለም" ሲሉ ፕሮፌሰር ሳራ ይናገራሉ። ስለዚህም በኮሮናቫይተረስ ወረርሽኝ ምክንያት ልጆች በቤት ውስጥ እንዲቆዩ መደረጋቸው የእራሱ የሆነ ሥነ ልቦናዊ ጫና ይኖረዋል። ቢሆንም ግን ይህ ከማኅበራዊ ግንኙነት የመገለሉ ሁኔታ ለረጅም ጊዜ የሚዘልቅ እንደማይሆን ተስፋ ያደርጋሉ።
news-51640126
https://www.bbc.com/amharic/news-51640126
ኮሮናቫይረስ ከአውሮፓ አገራት አልፎ አፍሪካዊት አገር አልጄሪያ ደረሰ
ከጣሊያን ሳይዛመት አልቀረም የተባለው ኮረናቫይረስ በበርካታ አውሮፓውያን አገራት ሪፖርት እየተደረገ ነው።
ኦስትሪያ፣ ክሮኤሺያ፣ ስዊትዘርላንድ፣ ስፔን፣ ፈረንሳይ እና ጀርመን ኮሮናቫይረስን ሪፖርት ያደረጉ አገራት ሲሆኑ፤ 'ወደ አገራችን የገባው ከጣሊያን በመጡ ሰዎች ነው' ብለዋል። አፍሪካዊቷ አገር አልጄሪያም ከጣሊያን ኮሮናቫይረስ መዛመቱን አሳውቃለች። ኑሮውን በብራዚል ያደረገው ግለሰብም ቫይረሱን ከጣሊያን ወደ መኖሪያ አገሩ በመውሰድ በላቲን አሜሪካ የመጀመሪያው ኮሮናቫይረስ ሊመዘገብ ችሏል። በጣሊያን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 300 የደረሱ ሲሆን 11 ሰዎች በቫይረሱ ሞተዋል። የጣሊያን ጎረቤት አገራት ከጣሊያን ጋር የሚያዋስናቸውን ድንበር ሊዘጉ ይችላሉ የሚል መላ ምት በስፋት ቢነገርም፤ የፈረንሳይ፣ ጀርመን እና የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን ድንበርን ክፍት በማድረግ የቫይረሱን ስርጭት ለመቆጣጠር ጥረት እንደሚያደርግ አሳውቀዋል። በቁጥር ከፍ ያሉ የአውሮፓ አገራት ወደ ጣሊያን ሲጓዙ መውሰድ ስላለባቸው ቅድመ ጥንቃቄዎች ዜጎቻቸውን እያስጠነቀቁ ይገኛሉ። በኮሮናቫይረስ ምክንያት ሊካሄዱ ቀጠሮ ተይዞላቸው የነበሩ የጣሊያን እግር ኳስ ጨዋታዎች በዝግ ስታድየም እንዲካሄዱ ተወስኗል። ከጣሊያን ወደ ብራዚል የተጓዘው የ61 ዓመት አዛውንት ቫይረሱ እንደተገኘበት ተረጋግጧል። የሳኦ ፖሎ ነዋሪ የሆነው ግለሰብ፤ ወደ ብራዚል የተመለሰው ታዋቂው የብራዚል ካርኒቫል ዝግጅት እየተከናወነ በነበረበት ወቅት ነበር። ለካርኒቫል በዓል በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች ወደ ብራዚል እና ሳኦ ፖሎ ይተማሉ በዚህም ቫይረሱ ተሰራጭቶ ከሆነ ሊያስከትል የሚችለው ጉዳት እጅግ ከፍተኛ ሊሆን እንደሚችል ተነግሯል። እስካሁን በአጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 78064 ሲሆን በቻይና ብቻ ወደ 2715 ሰዎች በቫይረሱ ሞተዋል።
news-42785068
https://www.bbc.com/amharic/news-42785068
የአሜሪካ ምክር ቤት አባላት ከስምምነት ላይ ደረሱ
የመንግሥትን ጊዜያዊ በጀት የሚመለከተውን አዋጅ ምክር ቤቱ በማፅደቁ የተዘጉ የመንግሥት ተቋማትም ተከፍተዋል።
አዋጁ እንዳይፀድቅ ሲያደርጉ የነበሩት ዲሞክራቶች በመጨረሻ ከስምምነት ላይ የደረሱት፤ ልጅ እያሉ ወደ አሜሪካ የሄዱ ስደተኞች ጉዳይ በምክር ቤቱ ለውይይት እንደሚቀርብ በሪፐብሊካኖች ቃል ስለተገባላቸው ነው። ሰኞ ማምሻውን አዋጁ ላይ የፈረሙት ፕሬዚዳንት ትራምፕ ግን ዲሞክራቶችን ሳይወቅሱ አላለፉም። በምክር ቤቱ ዘላቂ በጀት ላይ መስማማት ባለመቻሉ ይህ የአገሪቱን በጀት ለማራዘም የተወሰደ አራተኛ ጊዜያዊ እርምጃ ነው። አዋጁ በ81 ለ18 በምክር ቤቱ ድምፅ እንዲሁም 266 ለ150 በተወካዮች ምክር ቤት ድምፅ ፀድቋል። በምክር ቤቱ የሪፐብሊካኖች መሪ ሚች ማኮኔል የስደተኞች ጉዳይን በተመለከተ ድርድር ለማድረግ መስማማታቸውን ተናግረዋል። ነገር ግን ማኮኔልን በመጠራጠር መጀመሪያም ስምምነት ላይ መደረስ አልነበረበትም የሚሉ ዲሞክራቶች ድምፃቸውን አሰምተዋል። በ2020 በምክር ቤቱ የዲሞክራቲክ ፓርቲ እጩ ፕሬዘዳንቶች ይሆናሉ ተብለው የሚጠበቁት ኤልዛቤት ዋረን፣ ኪርስተን ጊሊብራንድ፣ ኮሪ ቡከር፣ በርኒ ሳንደርስና ካማላ ሃሪስ አዋጁን በመቃወም ድምፃቸውን አሰምተዋል። አሁን የመንግሥት ተቋማት ተከፍተዋል ነገር ግን በስደተኞችና በአገሪቱ ዘላቂ የበጀት ጉዳይ የሁለቱ ፓርቲዎች ፍልሚያ የሚቀጥል ይሆናል። ለጊዜው ግን ሁለቱም ወገኖች በተወሰነ መልኩ ድሉ የእኛ ነው እያሉ ይመስላል። የአሜሪካ ምክር ቤት አባላት በበጀት ጉዳይ አልተስማሙም
52307374
https://www.bbc.com/amharic/52307374
ኮሮናቫይረስ ያጠላበት የዛሬው ፀሎተ ሐሙስ እንዴት እየተከበረ ነው?
ዛሬ ፀሎተ ሐሙስ ነው። ለወትሮው እለቱን ምዕመናን ቤተ ክርስትያን በመሄድ በፀሎት ያሳልፉ ነበር። ዘንድሮ ግን የኮሮናቫይረስ ስርጭትን ለመግታት ሲባል ምዕመናን ቤተ ክርስቲያን እንዳይሄዱና ሥነ ሥርዓቱን ቤት ሆነው በተለያዩ የቴሌቭዥን ጣቢያዎች እንዲከታተሉ ታውጇል።
የ2009 ዓ.ም የስቅለት በዓል በቦሌ መድኃኒዓለም ቤተክርስቲያን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ አገረ ስብከት የካህናት አስተዳደር ኃላፊ መላከ ሕይወት ቆሞስ አባ ወልደየሱስ ሰይፉ ለቢቢሲ እንደተናገሩት፤ መንግሥት እንዲሁም ቅዱስ ሲኖዶሱ ባወጣው መመሪያ መመሰረት ምዕመናን ከቤታቸው ሆነው የፀሎተ ሐሙስ ሥነ ሥርዓትን እንዲከታተሉ ተደርጓል። "በአዲስ አበባ በሁሉም አድባራት መመሪያው ተግባራዊ እንዲሆን ተደርጓል። ኅብረተሰቡ በየቤቱ ተቀምጦ የቀጥታ ስርጭቱን እንዲከታተልም ተደርጓል" ይላሉ። በየቤተክርስቲያኑ ያለውን ሥርዓተ ቅዳሴ፣ ግብረ ሕማማ ንባብ እና አጠቃላይ አገልግሎቱ በተለያዩ የቴሌቭዥን ጣቢያዎች በቀጥታ እየተላለፈ ነው። የቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን አገልግሎት በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት፣ በባላገሩ እንዲሁም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ጣቢያዎች ላይ እየታየ ሲሆን፤ የቦሌ መድኃኔዓለም አገልግሎት በፋና ቴሌቭዥን እየተሰራጩ ይገኛሉ። "አልፎ ተርፎም መብራት በጠፋባቸው አካባቢዎች መብራት እንዲለቀቅም የሚመለከተውን አካል ጠይቀናል" ሲሉ መላከ ሕይወት ቆሞስ አባ ወልደየሱስ ሰይፉ ተናግረዋል። መመሪያውን ለማስፈጸም በየቤተ ክርስቲያኑ የጸጥታ አካላት እንደተገኙ ገልጸውም፤ "ኅብረተሰቡ ለራሱ መሆኑን አውቆ እየተባበረ ነው" ብለዋል። በአዲስ አበባ በአስሩም ክፍለ ከተሞች በቤተ ክርስቲያን የተገኙ ጥቂት ምዕመናን ማኅበራዊ ርቀት ጠብቀው እንዲቆሙ በማድረግ ረገድ በጎ ፍቃደኛ የሰንበት ተማሪዎች እያስተባበሩ እንደሚገኙም አክለዋል። እሳቸው በሚገኙበት ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን የተገኙ ጥቂት ምዕመናን አንዳቸው ከሌላቸው ተገቢውን ርቀት እንደጠበቁም ለቢቢሲ ገልጸዋል። "ዛሬ ዋናው የሥጋ ወ ደሙ ሚስጥር የተፈጸመበት እለት ስለሆነ ሁሉም ቀሲሳን ይቆርቡ ነበር። አሁን ካለው ችግር የተነሳ ግን ቤተ ክርስትያን ያለ ሰው ብቻ እንጂ ማንም ሰው ከውጪ እንዲካፈል አልተደረገም። የበለጠ በበሽታው ተጠቂ እንዳይኮን በሚል ነው ይህ የተደረገው" ይላሉ። በፀሎተ ሐሙስ የሚካሄደው እግር የማጠብ ሥነ ሥርዓት ነው። መላከ ሕይወት ቆሞስ አባ ወልደየሱስ ሰይፉ፤ "በየቤተ ክርስቲያኑ ካሉ ጥቂት አባቶች ውጪ ንክኪ አይኖርም" ብለዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ "ምዕመናን በጉጉት በሚጠባበቁት የማጠቃለያው ሥርዓተ ቅዳሴና ቅዱስ ቁርባን ለመሳተፍ እንዳይከለከሉ" የሚጠይቅ ደብዳቤ ለጠቅላይ ሚንስትሩ እንደጻፉ ቢቢሲ ተረድቷል። ፓትሪያርኩ በደብዳቤያቸው ዛሬ በጸሎተ ሐሙስ እና እሁድ በበዓለ ትንሣኤ ቆራቢዎች የሆኑ ምዕመናን የጤና ጥበቃ ሚንስቴር በሰጠው ምክር መሠረት አስፈላጊውን ጥንቃቄ በማድረግ እንዲቆርቡ ክልከላው እንዲነሳላቸው ጠይቀዋል። ቢቢሲ ፓትሪያርኩ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ለጻፉት ደብዳቤ የተሰጠ ምላሽ እንዳለ ከቤተ ክርስቲያኗ ለማረጋገጥ ጥረት ቢያደርግም ከዕለቱ ሥነ ሥርዓት በኋላ መልስ እንደሚሰጡን ያነጋገርናቸው ኃላፊዎች ነግረውናል።
news-56100772
https://www.bbc.com/amharic/news-56100772
"ከሞት ይልቅ የምፈራው መኖርን ነው"
በ20ዎቹ መጀመሪያ ላይ የሚገኝ ወጣት ለመኖር ሲጓጓ እንጂ ሕይወትን ሲፈራ ማየት የተለመደ አይደለም።
አሌክዞ ፓዝ ስፔናዊው አሌክዞ ፓዝ ግን ሞትን ይመርጣል፤ ሕይወትን ይፈራል። በሕይወት መቆየቱን ሲያስብ ይንዘፈዘፋል፤ በፍርሃት ላብ ያሰምጠዋል። አሌክዞ 8 ዓመቱ ላይ መጥፎ እጣ ገጠመው። 90 በመቶ ሰውነቱ በእሳት ተለበለበ። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ይኸው በስቃይ ውስጥ ለመኖር ተገዷል። ከሞት ይልቅ መኖርን ቢፈራ እንዴት ይፈረድበታል? አሌክሶ ፓዝ ለቢቢሲ ሲናገር፣ "በእያንዳንዱ ቀን ከአልጋዬ እንድነቃና እንድኖር የሚያደርገኝ ብቸኛው ነገር ቁጣ ነው" ይላል። "ቁጣ በሕይወት እንድቆይ አድርጎኛል። ቁስሌ እየጠገግልኝ ያለውም ለዚያ ይመስለኛል" ይላል። የራሱን ታሪክ እንዲህ ይተርካል። "እያዳንዷ ትንፋሽ ለእኔ ስቃይ ናት" ከአባቴ ጋር ነዳጅ የጫነ ቦቴ ውስጥ ነበርን። በአውራ ጎዳና ላይ ቦቴው ከባድ የመኪና አደጋ ደረሰበት። እንቅልፍ እያንገላታኝ ነበር። ስነቃ ሰውነቴ እንደ ጭድ ይነዳል። ከዚህ በኋላ የሆነውን አላውቅም። ተአምር ገደብ የለውምና ተረፍኩ። ምን አለበት ባልተረፍኩ? ምናለ ሞቼ በሆነ። ያልተኖረ ልጅነቴን፣ ያልተኖረውን ጉርምስናዬን በሆስፒታል ኖርኩት። ምን አማራጭ አለኝ? ዕድሜ ዘመኔን ቀዶ ጥገና አደርጋለሁ። ዕድሜ ልኬን ከስቃይ ጋር እኖራለሁ። ቅዠት እና ቁጣ፣ ቁስልና ነበልባል ይቀባበሉኛል። ሰዎች የሚሰበሰቡባቸውን ሥፍራዎች እንደ ጦር ነው የምፈራው። ሰዎች ሲያፈጡብኝ ቁስሌ የመረቀዘ ያህል ይሰማኛል። የሰው ዓይን መርፌ ሆኖብኛል። ደግሞ ተጠራጣሪ ነኝ። ሰዎች ከንፈር ሲመጡልኝ ራሱ ህመም እንጂ ሰላም አይሰማኝም። በቅርቡ ግን ታሪኬን በዘጋቢ ፊልም ለሕዝብ እንዲደርስ ፈቅጃለሁ። ዘ ፋየር ኪድ (The Fire Kid-El Niño de Fuego) ይሰኛል ዘጋቢ ፊልሙ። እውነት ለመናገር ካሜራ ለዓመታት ተደቅኖብኝ ስቃዬን ሲመዘግብ ምቾት ሊሰማኝ አይችልም። ነገር ግን አስቀድሜ ተናግሪያለሁ። ዘጋቢ ፊልሙ ሲጀምር ተመልካቾች ከእኔ ምንም መልካም ነገር እንዳይጠብቁ አስጠንቅቂያለሁ። አንዳች የሚያነቃቃ፣ አንዳች ብርታት የሚሰጥ ንግግር በፍጹም እንዳይጠብቁ አደራ ብያለሁ። ጥሬ የስቃይ ሕይወቴን ማየት ከፈቀዱ ብቻ ነው የእኔን ዘጋቢ ፊልም ሰዎች ማየት ያለባቸው እላለሁ። በሕይወቴ ምንንም ነገር ታግዬ አላሸንፍኩም እኮ፤ ድል ያደረኩ ጀግና አይደለሁም፤ የስቃይ ተምሳሌት ነኝ። የእኔ ብቸኛ ጥንካሬ ከሞት ይልቅ ሕይወትን መፍራቴ ነው፤ ይህ ጥንካሬ ከተባለ ማለቴ ነው። ሰዎች እኔ ብርቱ ሰው እንደሆንኩ ይነግሩኛል። ምኑ ነው ብርቱ ያስባለኝ ስላቸው 90 ከመቶ ሰውነትህ ተቃጥሎ ሕይወት መኖርን ቀጥለሃል ይሉኛል። አያውቁም ሞት ምርጫዬ እንደሆነ፤ አያውቁም ሕይወት ሞት እንደሆነብኝ። ሰውነቴ በእሳት ሲነድ የነበረው ቅጽበት ከአእምሮዬ አልጠፋም። አሁንም እንዳለ ነው። ልረሳው አልቻልኩም፤ ከትዝታ ማኅደሬ አልፋቅ አለኝ። ምናባቴ ላድርግ!? ይህ የአደጋ ክስተት ቀንና ሌሊት ያባንነኛል። እያስጮኸ ያነቃኛል፤ ያስቃዠኛል። ሰላማዊ እንቅልፍ የማገኝባቸው ቅጽበቶች ጥቂት ናቸው። አንዳንድ ቀናት ከእንቅልፌ የምነቃው በእሳት ስለበለብ እየታየኝ፣ በላብ ተዘፍቄ እየጮህኩ ነው። ብዙ ሰዎች ቆዳዬ መለብለቡን ነው የሚመለከቱት። ከቆዳዬ ሥር ያለውን የስሜት ህመም የሚያይልኝ ማንም የለም። ከነዳጅ ጋር ነው አብሬ የነደድኩት። ያ አደጋ እኔነቴን መሉ በሙሉ ነው የቆየረው። ራሴ የለሁም። እኔን እሳት በልቶኛል። አሌክዞ ፓዝ የለም። አሁን ያለው የእኔ ቅሪት ነው። የአሌክዞ ፓዝ ቅሪት። አሌክዞ ፓዝ ከፊልም ዳይሬክትር ኢግናሲዮ አኮንሺያ አንዳንድ ጊዜ የልጅነት ፎቶዬን ሳየው ራሴን ማወቅ ይሳነኛል። እያወራሁ ያለሁት ስለ መልክ አይደለም። እያወራሁ ያለሁት ስለ ስሜት ነው፤ ስለ ተስፋ ማጣት። ከዚህ ዓለም ስለመሰናበት ነው። መኖርን ስለመፍራት ነው። ስሜ አሌክዞ ነው። አሌክዞ ግን አሁን የምታዩት እኔ አይደለሁም ብያችኋለሁ። አሌክዞ ስሜ ነው እንጂ እኔ አይደለሁም። እኔማ በልጅነቴ አለፍኩ። አሁን አጽሜ ነው ያለው አልኳችሁ። ዘጋቢ ፊልሙ ከታየ በኋላ በርካታ ሰዎች የእኔ ታሪክ ለእነርሱ እንደረዳቸው ነግረውኛል። አልዋሻችሁም ያ የተወሰነ መልካም ስሜት እንዲሰማኝ ምክንያት ሆኗል። መጀመሪያ የፊልሙ ርዕስ አላስደሰኝም ነበር። The Fire Kid የሚለው ርዕስ አልወደድኩትም። እኔና እሳትን ለምን ያጣምራል አልኩ። በኋላ ላይ ግን ቅጽል ስሜ ሆነ። አሁን ለመድኩት። ከስቃዩ አንጻር ለስሜ የምጨነቅበት ቅንጦት የለኝም። ሰዎች ድንገት ሲያዩኝ ወደኔ ይጠጉና ሕይወቴን በአንተ ተለወጠ ብለው ያሞግሱኛል። መቼስ ወደደኩም ጠላሁ እንደዛ ሲሉኝ በእኔ ላይ ተጽእኖ ማሳደሩ አይቀርም። ሰዎች እየመጡ ሲያመሰግኑኝ አንዳንድ ጊዜ ራሴን ማታለለል ሁሉ ይቃጣኛል። አይዞን ፓዝ አሁን ሕይወትህ እየተቀየረ ነው እለዋለሁ ራሴን። ሌላው ተስፋዬ ሙዚቃ ነው። ይገርመኛል። ብዙ ሰዎች አይዞህ ሁሉም ነገር መልካም ይሆናል ይሉኛል። ውሸት ነው። ሁሉም ነገር መልካም አይሆንም። ቢያንስ ለእኔ እንደዛ ሆኖልኝ አያውቅም። እንዲያውም ለእኔ እንዳንዱ ደቂቃ ህመም ነው። የሆድ ህመም፣ የጡንቻ ህመም፣ የአጥንት ህመም። ከስቃይ ወደ ስቃይ…፣ ከኡኡታ ወደ ኡኡታ። ጭንቀት ጥበት። ምኑን ነው "ምንም አይደል" [It's OKAY] የሚሉኝ? ነው እንጂ! [It's not Okay!] አሁን ትንሽ ህመም መለስ የሚልልኝ ሙዚቃ ስጫወት ነው። ትንሽ ተስፋ የሚፈነጥቅልኝ ያኔ ነው። ትንሽ ብርሃን በሙዚቃ ውስጥ ትታየኛለች። የቀድሞ የቦክስ ሻምፒዮን፣ እስረኛና በኋላም ራፐር ኢሳክ ሪል (ቻካ) ተምሳሌቴ ነው። እውነት መናገር አለብኝ። ሙዚቀኛ አይደለሁም። በሙዚቃ የትም እንደማልደርስ አውቃለሁ። እኔ ያበቃልኝ ሰው ነኝ። በሕይወት ማሳካት የምፈልገው ምንም ነገር የለም። መኖርን ከሞተ በላይ ለሚፈራ ሰው ምን ተስፋ አለውና። ሆኖም ግድግዳውን በብስጭት በቡጢ ከምነርተው ጥቂት የሙዚቃ ስንኞችን ጽፌ ሳዜም ህመሜ መለስ ይልልኛል። ቁጣዬም ለቅጽበትም ቢሆን ይበርድልኛል። ስቃዬ ግን ቀጣይ ነው። የማያባራ!
52891110
https://www.bbc.com/amharic/52891110
አዶልፍ ሂትለር የተወለደበት ቤት ፖሊስ ጣቢያ ሊሆን ነው
በዓለም የጭካኔ ቁንጮ ተደርጎ የሚታየው አዶልፍ ሂትለር የተወለደው በኦስትሪያዋ የድንበት ከተማ ብራውና ነበር፡፡ የብራውና ነዋሪዎች ስማቸው ከዓለም ጨካኙ ሰው ጋር መነሳቱ ይከነክናቸዋል፡፡
መንግሥትም ቢሆን የሂትለር ቤት ለአክራሪ አፍቃሪዎቹ የጉብኝት መዳረሻ መሆኑ ሲያሳስበው ቆይቷል፡፡ ይህም ሆኑ ሂትለር የተወለደበት ቤት እስከዛሬም ድረስ ባለበት አለ፡፡ የእርሱ የትወልድ ስፍራ ስለመሆኑ የሚያመላክት ግን ምንም ዓይነት ቅርስ የለም፡፡ የርሱ ስም ያለበት ጽሑፍም አይታይም፡፡ ደጁ ላይ ብቻ ‹‹ ፋሺዝም መቼም እንዳይደገም›› የሚል ጽሑፍ ድንጋይ ላይ ታትሟል፡፡ ይህንን መኖርያ ቤት መንግሥት የአስገዳጅ ግዥ በመፈጸም የራሱ ካደረገው ቆይቷል፡፡ ባለፈው ኅዳር ነበር መንግሥት አወዛጋቢ ውሳኔ ላይ የደረሰው፡፡ ቤቱን ወደ ፖሊስ ጣብያነት መቀየር፡፡ አንድ የኦስትሪያ የኪነ ሕንጻ አሰናጅ ቤቱን ወደ ፖሊስ ጣቢያነት የሚቀይረውን ሀሳብ እየነደፈ ይገኛል፡፡ ‹‹ለጨካኙ የናዚ ጌታ የትውልድ ቤት አዲስ ምዕራፍ ይከፈትለታል›› ብለዋል የኦስትሪያ የአገር ውስጥ ጉዳዮች ሚኒስትር ካርል ናሃመር፡፡ ንድፉን ያሸነፈው ማንቴ ማንቴ የሚባለው ድርጅት ከ12 እጩዎች መሀል የተመረጠ ሲሆን በሦስት ዓመታት የማሻሻያ ግንባታውን አጠናቆ በፈረንጆች 2023 መኖርያ ቤቱን ፖሊስ ጣቢያ አድርጎ ለማስረከብ የ5 ሚሊዮን 6 መቶ ሺህ ዶላር ስምምነት ፈጽሟል፡፡ የሂትለር የትውልድ ቤት ወደ ፖሊስ ጣቢያነት ሲቀየር ስለርሱ ታሪክ የሚያወሳ ምንም ዓይነት ቅሪት እንደማይኖር ተነግሯል፡፡ ‹‹ፋሸዝም መቼም አይደገም!›› የሚለው መፈክርም ወደ ኦስትሪያ ዋና ከተማ ቪየና ሙዝየም ይወሰዳል፡፡ አንድ የከተማዋ ነዋሪና የታሪክ ባለሞያ ለቢቢሲ እንደተናገሩት ይህ ‹‹ፋሺዝም መቼም አይደገም›› የሚለው ድንጋይ ጽሑፍ በከተማዋ መቆየት ይኖርበታል ብለዋል፡፡ በዚህ የሂትለር የትውልድ መኖርያ ውስጥ አምባገነኑ ሰው የተወለደው በ1889 ሲሆን ቤተሰቦቹ ግን ከጥቂት ሳምንታት በኃላ አፓርትመንቱን ለቅቀው ወደ ሌላ ሰፈር ሄደዋል፡፡ ሂትለር 3 ዓመት ሲሞላው ደግሞ ጭራሽ ከተማዋን ጥለው ሄደዋል፡፡ ዛሬም ድረስ የናዚ ደጋፊዎች ወደ ሂትለር የትውልድ ቤት እንደሚጓዙ የጠቀሱት የመንግሥት ባለሥልጣናት ይህንን ለማስቀረት አንዱ መንገድ የቤቱን አገልግሎት መቀየር እንደሆነ ተረድተዋል፡፡ ኦስትሪያ በናዚ ጀርመን እንደ አውሮፓዊያን በ1938 የተጠቃለለች ሲሆን የናዚ ቀዳሚ ተጠቂ አገር አድረጋ ራሰዋን ትመለከታለች፡፡ ነገር ግን በዚያን ጊዜ አብዛኛው ሕዝብም ሆነ አስተዳደሩ ወደ ጀርመን መቀላቀሉን ወዶት እንደነበር ይነገራል፡፡ ቤቱን ከ1970ዎቹ ጀምሮ መንግሥት ለግለሰቦች ያከራየው ነበር፡፡ በኋላም የአካል ጉዳቶች የእንክብካቤ ማዕከል ተደርጎ ቆይቷል፡፡ ቤቱ በቅርስነት መቆየት እንጂ መነካት የለበትም በሚሉና የመንግሥትን እርምጃ በሚደግፉ መካከል አሁንም ድረስ የጦፈ ክርክር እየተደረገ ይገኛል፡፡ የድንበር ከተማዋ ብራውና ግን አሁንም ቢሆን ከሂትለር ጋር ተያይዛ መታሰቧ የሚቀር አልሆነም፡፡
news-46969296
https://www.bbc.com/amharic/news-46969296
ከተለያየ ጎሳ የተጋቡ የጂግጂጋ ጥንዶች ስጋት ላይ ነን እያሉ ነው
በሶማሌ ክልል ዋና ከተማ ጂግጂጋ ባለፈው ሚያዚያ ወር ትዳር የመሰረቱት ጥንዶች ከከተማዋ እንዲለቁ በሃላፊዎች እየተገደዱ እንደሆነ ለቢቢሲ ገልጸዋል።
የሶማሌ ክልላዊ መንግሥት ግን ከሌላ ጎሳ ጋር ትዳር የመሰረቱ ጥንዶች ላይ ምንም አይነት ችግር ችንዲገጥማቸው እንደማይፈቅድና ይህንን ተግባር እየፈጸሙ ያሉት ሰዎች የክልሉን መንግሥት የማይወክሉ መሆናቸውን ገልጿል። ሃዋ አብዱልቃድር ሙስታሂል ከሚባል አካባቢ ነው ወደ ጂግጂጋ የመጣችው። እሷ እንደምትለው ከሌላ ጎሳ ጋር ተጋብተው ለሚኖሩ ጥንዶች ከቤተሰብና ዘመዶች ራቅ ብሎ የከተማ ህይወት መኖር የተሻለ ይሆናል በሚል እሳቤ ነው ወደ ጂግጂጋ የመጣችው። • የዚምባብዌ ወታደሮች ዘዴያዊ ማሰቃየት ተጠቅመዋል ተባለ • የአልጀሪያዋ ቁንጅና አሸናፊዋ ዘረኝነት እንደማይበግራት ገለፀች ''ወደ ጂግጂጋ ስመጣ በጣም ደስ ብሎኝ ነበር። በከተማዋ ብዙ ከሌላ ጎሳ የተውጣጡ ጥንዶች በአንድ ላይ ሲዳሩ ከእነሱ መሃል ነበርኩ። ቤት ተሰጥቶንም ነበር። አሁን አሁን ግን ከቤታችሁ እናስወጣችኋለን የሚሉ ማስፈራሪያዎች በርክተዋል።'' በሶማሌ ክልል የጎሳ አወቃቀር እጅግ አስቸጋሪ ከሚባሉት መካከል ነው። ከተለያዩ ጎሳዎች የመጡ ጥንዶች ትዳር ሲመሰርቱ መመልከት የተለመደ አይደለም። ከፍተኛ ቦታ የሚሰጣቸው ጎሳዎች ወደታች ወርደው ከሌላ ጎሳ ማግባት አይችሉም፤ ደፍረው ቢያደርጉትም ብዙ የእንገላችኋለን ማስፈራሪያዎች ይከተላሉ። በጎረቤት ሃገር ሶማሊያ የሚገኝ አንድ ግለሰብ ከፍ ያለ ቦታ ካለው ጎሳ ከተገኘች ሴት ጋር ትዳር በመመስረቱ በእሳት ተቃጥሎ እንዲሞት ተደርጎ ነበር። የቀድሞው የሶማሌ ክልል ፕሬዝዳንት አብዲ ሞሃመድ ኦማር በጎሳዎች መካከል ያለውን ልዩነትና መከፋፈል ለመቀነስ በማለት ባለፈው ሚያዚያ ወር ላያ ከተለያዩ ጎሳዎች የተገኙ 29 ጥንዶችን አንድ ላይ ሰርግ ሥነ ሥርዓታቸውን እንዲፈጽሙ አድርገው ነበር። • የብሔር ግጭት የሚንጣት ሀገር • በእርጥብ ሳርና ቅጠል ጥቃትን ያስቆሙ አባቶች ሁሉም ጥንዶች ከሰርጋቸው በኋላ በዋና ከተማዋ የመኖሪያ ቤት የተሰጣቸው ሲሆን ቃል ተገብቶላቸው የነበረው የሥራ ዕድል ግን እስካሁን ተግባራዊ እንዳልተደረገላቸው ገልጸዋል። የቀድሞው ፕሬዝዳንት ከስልጣናቸው ከለቀቁ በኋላ ግን በአዲስ መልክ የተዋቀረው የክልሉ መንግሥት ቃል ተገብቶላቸው የነበረውን ነገር ለመፈጸምም ሆነ ደህንነታቸውን ለመጠበቅ እያደረገው ያለ ነገር እንደሌለም ለቢቢሲ ተናግረዋል።
news-46503849
https://www.bbc.com/amharic/news-46503849
ቢዮንሴ በህንድ ለቱጃር ልጅ ለሆነችው አምባኒ ፒራማል ሰርግ ዘፈነች
አሜሪካዊቷ ዘፋኝ ቢዮንሴ በህንድ ታዋቂ ለሆነው ቱጃር ሙኬሽ አምባኒ ሰርግ ላይ መዝፈኗ ተዘግቧል።
ቢዮንሴ በሰርጉ ላይ በህንድ የናጠጠ ሃብታም ልጅ የሆነችው ኢሻ አምባኒ ከህንዳዊው ቢሊዮነር ልጅ አናንድ ፒራማል ጋር በዚህ ሳምንት ትጋባለች። ለሰርጉ ከመጡት ታዋቂ ሰዎች መካከል ቢዮንሴ አንዷ ስትሆን ሂላሪ ክሊንተንም ከሰርጉ በፊት ያለውን ዝግጅት እንደታደሙ ተገልጿል። በባለፈው ሳምንት ሙሽራዋ የታዋቂዋ ተዋናይት ፕሪያንካ ቾፕራና አሜሪካዊው ዘፋኝ ኒክ ጆናስ ሰርግ ላይ ሚዜ ነበረች። •በህንድ ግማሽ ብርጭቆ ውሃ እየተሸጠ ነው •ሶሪያውያን ስደተኞች በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ይህ ቅንጡ መሆኑ የተዘገበለት ሰርግ ለረቡዕ የተቆረጠ ሲሆን ቅድመ ዝግጅቱ ግን ቅዳሜና እሁድ እንደተጀመረም ተገልጿል። የተቀናጣና የደመቀ ሰርግ ይሆናል ተብሎ በሚጠበቀው በዚህ ሰርግ ላይ በአሜሪካ የፕሬዚዳንትነት ዕጩ የነበሩት ሂላሪ ክሊንተንን ጨምሮ ታዋቂዋ የሚዲያ ግለሰብ አሪያና ሃፊንግተን ሰርጉን ይታደማሉ። •ጥቁር ለመሆን የሚጥሩት ነጭ እንስቶች ሚዲያዎች እንደዘገቡት እንግዶቹን ለማመላለስም 100 የሚሆኑ የግል አውሮፕላኖች እንደተመደቡ ነው። ታዋቂ ጦማሪዎች፣ የመዝናኛ ፀሐፊዎች ስለ ፌስቲቫሉ በኢንስታግራም ላይ እየፃፉም እንደሆነ ተገልጿል። ቢዮንሴ ከሰርጉ በፊት እሁድ እለት ሳንጌት ተብሎ በሚጠራው ዝግጅት ላይ የሙዚቃ ስራዎቿን ያቀረበች ሲሆን፤ ፎቶዎቿንም በኢንስታግራም አጋርታለች። ለዚህ የሙዚቃ ዝግጅት ምን ያህል እንደተከፈላት ግልፅ ባይሆንም፤ የሙሽራዋ አባት ሙከሺ አምባኒ 47 ቢሊዮን ዶላር አንጡራ ኃብት እንዳላቸው ተዘግቧል።
news-55891049
https://www.bbc.com/amharic/news-55891049
የሚያንማር መፈንቅለ መንግሥት፡ አሁን ለምን? በቀጣይስ?
በቀድሞዋ በርማ በአሁኗ ሚያንማር ወታደሩ ሥልጣን መቆጣጠሩ ተሰምቷል።
ወታደሮች ሥልጣን መቆጣጠራቸውን ይፋ ያደረጉት የሲቪል መንግሥት አባላትን በቁጥጥር ሥር ማድረጋቸውንተከትሎ ነው። የኖቤል ሰላም ሽልማት ተሸላሚዋ ኦንግ ሳን ሱ ቺ እና ሌሎች የፖለቲካ መሪዎች ተለቅመው ወዳልታወቀ ሥፍራ ተወስደዋል። ይህ መፈንቅለ መንግሥት በአገሪቷ ዜጎች ዘንድ ከፍተኛ ፍርሃትን ፈጥሯል። በርማ ወደ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት እንደምትሸጋገር ተስፋን ሰንቀው ለነበሩት ዜጎች የሳን ሱ ቺ እና ሌሎች ሲቪል ፖለቲከኞች እስር የዲሞክራሲ ተስፋን ያጨለመ ሆኗል። ላለፉት አምስት ዓመታት በአንድ ወቅት ታግዶ የነበረው የብሔራዊ ዲሞክራሲ ሊግ (ናሽናል ሊግ ፎርዲሞክራሲ) ከ25 ዓመታት በኋላ የተካሄደውን ምርጫ በማሸነፍ እአአ 2105 ላይ መንበረ ስልጣኑን ተረክቦ ነበር። ፓርቲው ሁለተኛ ዙር የሥልጣን ዘመኑን መጀመር ሲገባው ነበር ዛሬ ንጋት ላይ መፈንቅለ መንግሥት የተፈጸመው። በሚያንማር በወታደሩ እና በሲቪል አስተዳደሩ መካከል ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ውጥረት ተከስቶ ነበር። እነ ሳን ሱ ቺ ከመታሰራቸው በፊት የመንግሥት ቴሌቪዥን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አውጆ ነበር። ሚያንማር የዲሞክራሲያዊ ማሻሻያዎችን ማድረግ እስከጀመረችበት 2011 ድረስ በጥብቅ ወታደራዊ መንግሥት ነበር ስትመራ የቆየችው። ባለፈው ሕዳር በተደረገ ምርጫ የሳን ሱ ቺ ፓርቲ 'ናሽናል ሊግ ፎር ዲሞክራሲ' መንግሥት ለመመሥረት ሚያስችለውን የመቀመጫ ቁጥር ማግኘት ችሎ ነበር። ሆኖም ወታደሮቹ ምርጫው ተጭበርብሯል ሲሉ ቆይተዋል። ከሁለት ወራት በፊት ተካሂዶ በነበረው ምርጫ የሳን ሱ ቺ ፓርቲ ባለፈው ህዳር በተደረገ ምርጫ 83% መቀመጫ አሸንፎ ነበር። ይህም ለሳን ሱ ቺ መንግሥት ሕዝብ ይሁንታን መስጠቱን የሚያሳይ ተደርጎ ነበር የተወሰደው። የአገሪቱ ጦር ግን ምርጫው ተጭበርብሯል ሲል ቆይቷል። የሂዩማን ራይትስ ዎች የእስያ ምክትል ዳይሬክተር ፊል ሮበርትሰን ግን ጦሩ ምርጫው ተጭበርብሯል ሲል የቆየው ምርጫው ለመጭበርበሩ የሚያረጋግጥም አንድም ማስረጃ ሳያቀርብ ነው ይላል። ጦሩ ይህን መሰል ወቀሳዎቸን ሲያቀርብ የነበረው መፈንቅለ መንግሥት ለማከናወን ሁኔታዎችን ሲያመቻች ነው የሚሉ በርካቶች ናቸው። ፊል ሮበርትስ ጦሩ አገሪቷን በመቆጣጠሩ በርማ ከተቀረው ዓለም ነጥሎ ሊገዛ እንደሚችል ስጋታቸውን ይገልጻሉ የሚያንማር ጦር ዛሬ የሆነው ምን ነበር? ዛሬ [ሰኞ] ወታደሮች የአገሪቱን ሥልጣን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠራቸውና መሪያቸውም ኮማንደር ሚነ ኦንግ ሌይንግ መሆናቸውን ተናግረዋል። በርካታ ወታደሮች በአገሪቱ ዋና ከተማ ናይፒታው እና በሌላኛዋ ትልቋ ከተማ ያንጎን ይታያሉ። የሞባይልና ኢንተርኔ አገልግሎት እንዲሁም ስልክ በስፋት የተቋረጠባቸው ዋና ዋና ከተሞች ላይ ሲሆን የአገሪቱ ብሔራዊ ቴሌቪዥን ሥርጭት ለማድረስ እክል ገጥሞኛል በማለት ተቋርጧል። በርካታ ወታደሮችም በተለያዩ ቦታዎች እየሄዱ የሲቪል አስተዳደሩ ሚኒስትሮች የነበሩ ሰዎችን በቁጥጥር ሥርእንዳዋሉ ቤተሰቦቻቸው ተናግረዋል። የቢቢሲዋ የደቡብ ምሥራቅ ኢሲያ ወኪል እንደምትለው ከሆነ ሳን ሱ ቺ በአገሪቱ ዜጎች ዘንድ ትልቅ ተቀባይነት አላቸው። ሰፊ የሕዝብ ድጋፍ ያላትን ሳን ሱ ቺን የመሰሉ ፖለቲከኞችን ማሰር ትልቅ ውሳኔ ነው። ይህ ምርጫ የወታደራዊ መንግሥት አስተዳደር ካበቃበት ከ2011 ወዲህ ሲካሄድ ለ2ኛ ጊዜ ነው። ነገር ግን ይህን ምርጫ ወታደሩ ሳይቀበለው ቀርቶ ነበር። ይህን ተከትሎም ምናልባት ወታደሩ መፈንቅለ መንግሥት ያደርግ ይሆናል የሚል ፍርሃት ነግሶ ቆይቶ ነበር። ኦንግ ሳን ሱ ቺ ማን ናቸው? ሳን ሱ ቺ የበርማ የነጻነት አባት የሚባሉት የጄኔራል ኦንግ ሳን ሴት ልጅ ናት። አባቷ የተገደሉት እሷ ገና የ2 ዓመት ልጅ ሳለች ነበር። የተገደሉትም በርማ ከእንግሊዝ ነጻነቷን ከመቀዳጀቷ ጥቂት ቀደም ብሎ በፈረንጆቹ በ1948 ነበር። ሳን ሱ ቺ በአንድ ወቅት ለዲሞክራሲና ሰብዓዊ መብት ትልቅ ተምሳሌት ተደርጋ ነበር የምትታየው። ምክንያቱም ምሕረት አያውቁም ከሚባሉት የምያንማር ወታደራዊ ኃይሎች በተጻጻራሪ በመቆም በአገሪቱ ዲሞክራሲ እንዲሰፍን በመታገል ረዥም ዓመታት አሳልፋለች። ይህን ተከትሎም በ1991 የኖቤል የሰላም ሽልማትን ማሸነፍ ችላ ነበር። ሽልማቱን ያሸነፈችውም በቁም እስር ላይ ሳለች ነበር። ሳን ሱ ቺ ለ15 ዓመታት በእስር ከቆየች በኋላ በ2010 ነጻ ተደርጋለች። በ25 ዓመታት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ በተደረገ ምርጫም ፓርቲዋ ትልቅ ድል አግኝቶ ወደ ሥልጣን መምጣት ችሎ ነበር። ሆኖም የአገሪቱ ሕገ መንግሥት ሳን ሱ ቺ የአገሪቱ ፕሬዝዳንት እንድትሆን አይፈቅድም። ምክንያቱም ልጆቿ የውጭ ዜጎች ስለሆኑ ነው። በዚህም የተነሳ መንግሥትን የምትመራው ከጀርባ ሆና ነው። ሳን ሱ ቺ አሁን 75 ዓመት ሆኗታል። የሰላም ኖቤል አሸናፊ የነበረችው ሳን ሱ ቺ በአገሯ የሮሒንጋ ሙስሊሞች ላይ ለደረሰው ግፍና መከራ ቸልተኝነት በማሳየቷ ከበርካታ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ያገኘቻቸው ክብርና እውቅናዎችን ተነጥቃለች። ባለፈው ዓመት በዓለም አቀፉ ፍርድ ቤት ሔግ ቀርባ ለዚህ ምላሽ እንድትሰጥ በተደረገበት ጊዜ በሮሒንጋ ሙስሊሞችላይ የደረሰውን ግፍ ተገቢነቱን ለማሳየት መሞከሯ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተሰጥቷት የነበረውን ክብር የሚያጠለሽ ሆኖ ተገኝቷል። ሆኖም በአገሯ ውስጥ ሳን ሱ ቺ በቡድሃ ብዙኃን ዘንድ ሰፊ ተቀባይነት አላት።
50922449
https://www.bbc.com/amharic/50922449
በርኖስና ባና -የመንዝ ባህላዊ ልብስ
ነዋሪነቷን አዲስ አበባ ያደረገችው ሠላማዊት ገብሬ የበርኖስ ሥራን ከአባቷ እንደተማረች ትናገራለች። አባቷ ከዓመታት በፊት በርኖስ በማሠራት ወደ አዲስ አበባ እያስመጡ ይሸጡ ነበር። መርካቶ መንዝ በረንዳ ወይንም 4ኛ ፖሊስ ጣቢያ የሚባለው አካባቢም መሸጫ ሱቅ ነበራቸው።
በዚህ ወቅት ነው ሠላማዊት ስለበርኖስ ብዙ ነገሮችን የተማረችው። በርኖስ የሚሠራው ከበግ ጸጉር ቢሆንም ሁሉም የበግ ጸጉር ግን ለበርኖስ ሥራ አያገለግልም ትላለች። እንደበጎቹ መጠን ታይቶ ከአስር እስከ አስራ ሶስት የሚሆኑ ጥቁር በጎች ይመረጣሉ። • የኬንያ ዳኞችን አለባበስ የቀየረች ኢትዮጵያዊት • ሜድ ኢን ቻይና- የሀገር ባህል አልባሳቶቻችን "ለበርኖስ ሥራ የሚያገለግሉት በጎች የሪዝ በግ መሆን አለባቸው። ይህም በርኖሱ ለስላሳ መሆን ስላለበት ነው" ይላሉ የመንዝ ማማ ባህልና ቱሪዝም ጽህፈት ቤት የቅርስ ባለሙያ የሆኑት አቶ ታምሩ ፍቅረ። ጥቁር በጎች ሆነው ጸጉራቸው በተደጋጋሚ ከተቆረጠ ጸጉሩ ጠንካራ ስለሚሆን ሲለበስ ይኮሰኩሳል። የእነዚህ በጎች ጸጉር ጠንካራ ስለሆነ ባና ወይንም ዝተት ለሚባለውና እንደጋቢ ያለ በብርድ ወይንም በመኝታ ወቅት የሚለበስ ልብስ ይሠራበታል። "ባና ከማንኛውም በግ ጸጉር ይሠራል። ቀለሙም ዳልቻ፣ ነጭ ወይንም ጥቁር ሊሆን ይችላል። ለበርኖስ ግን ለስላሳ ሪዝ ያለው የጥቁር በግ ጸጉር ነው የሚያስፈልገው" ይላሉ ባለሙያው። ለበርኖስ ሥራ ጸጉራቸው የተመረጡት በጎች በደንብ ይታጠባሉ። ከዚያ እንዲደርቁ ይደረጋል። "ምንም እንዳይጎሳቆል እና ቆሻሻ እንዳይነካው ቁርበት ላይ ተደርጎ ጸጉሩ ይቆረጣል" ይላሉ አቶ ታምሩ። ቀጥሎ የሚከናወነው በእናቶች ፋቶው ይፋታል። ፋቶ ማለት ጸጉሩን ነጣጥሎ እንዲደርቅ ማድረግ ነው። የደረቀው የበግ ጸጉር እስኪልም ድረስ በደጋን ተነድፎ አመልማሎ ይሠራል። አመልማሎ ማለት እየተሽመለመለ ማድበልበል ማለት ነው። ቀጣዩ ሥራ የተድበለበለውን የበግ ጸጉር በእንዝርት መፍተል ነው። ፈትሉ በኳስ መልክ የሚዘጋጅ ሲሆን ኳሱን እየተረተሩ የማድራት ሥራው ይከናወናል። ከዚህ በኋላ ያለው ሥራ ሽመና ነው። ከጋቢ ወይንም ከነጠላ ጋር ተመሳሳይ በሆነ መልኩ የሽመና ሥራው ይከናወናል። የሽመና ሥራው አልቆ ከተጠናቀቀ በኋላ ንጹህ ውሃ ውስጥ ይረገጣል። "ጋቢ እንደማጠብ ነው የሚረገጠው። ጥቅጥቅ እንዲል ነው የሚረገጠው። ካልተረገጠ አይጠቀጠቀም። ሲረገጥም በየቀለሙ እየተለየ ነው። ጥቁሩ ከጥቁር ጋር ነጩ ከነጭ ጋር ብቻ ይረገጣል። ከተደባለቀ በርኖሱ ነጭ ይሆናል" ትላለች ሠላማዊት። • ባህልን በኤሌክትሮኒክ ሙዚቃ የቀመመው ሮፍናን • 'ኢትዮጵያዊነት' ከጄሰን ድሩሎ ጀርባ ያለው ቡድን ቀጣዩ ሥራ የተዘጋጀውን በርኖስ ወደ ልብስነት መቀየር ነው። አንዱ በርኖስ ወደ ልብስነት ሲቀየር ከአንድ ሰው በላይ አይሆንም። "በስፌት ወቅት ከሚለበሰው በርኖስ የሚተርፈው ቁርጥራጭ የጣውላ ወለል ላላቸው ቤቶች መወልወያነት ያገለግላል" "ቀደም ሲል ጀምሮ ለልብስነት የሚውለው በርኖስ ቀለም ጥቁር ብቻ ነው ይለኝ ነበር አባቴ" የምትለው ሠላማዊት "ሌላ ቀለም ካለው ግን እንደ ብርድ ልብስ ያገለግላል" ትላለች። በርኖስ በአንድ በኩል ወጣ ያለ ቅርጽ ያለው ባህላዊ ልብስ ነው። ይህም የጦር መሣሪያ ለመያዝ እንዲያመች ሆኖ የተሠራ መሆኑን ሠላማዊት ትናገራለች። በሠላማዊት ሃሳብ የሚስማሙት አቶ ታምሩ "አባቶቻችን ጀግኖች ናቸው። የጦር መሣሪያ በዛች ውስጥ ይይዙ ነበር። መሣሪያ ይያዙ አይያዙ አይታወቅም። መሣሪያ ለመደበቅ የሚጠቀሙባት ቀንድ መሰል ቅርጽ ያለው ነው" ብለዋል። በርኖስ በተለይ በመንዝ አካባቢ በስፋት የሚለበስ ባህላዊ ልብስ ነው። በሃዘንም ሆነ በደስታ ወቅት የሚለበስ ነው። "በተለያዩ አካባቢዎች ለሠርግም ሆነ ለሃዘን የሚለበስ ባህላዊ ልብስ ነው" የምትለው ሠላማዊት "የገና በዓል ሲከበር ደግሞ የገና ጨዋታም የሚከናወነው በዚሁ ልብስ ነው" ትላለች። ቀደም ሲል በርኖስ በስፋት ይለበስ ነበር። "በቀን እሰከ 30 የሚደርስ በርኖስ ከአባቴ ሱቅ ይሸጥ ነበር" የምትለው ሠላማዊት "ከበርኖስ በተጨማሪ እንደ ብርድ ልብስ የሚያገለግለው ባና ወደ አሥመራ ጭምር ይላክ ነበር" ትላለች። አይደለም በሌሎች አካባቢዎች በርኖስ በስፋት ይሠራበታል በሚባልበት መንዝ አካባቢ ጭምር ሥራው ተቀዛቅዟል። "አሁን ሰዉ ወደ ብርድ ልብስ ሄዷል። በርኖስ የሚለብሱ ሰዎች ስለሌሉ ሥራውን የሚሠሩ 10 የሚሆኑ ሰዎች ብቻ ናቸው" ይላሉ አቶ ታምሩ። በርኖስ የሚለብሱ ሰዎች ቁጥር ከማነሱም በላይ ሥራውም ረዥም ጊዜ የሚፈልግ እና አድካሚ ነው። "ይኮሰኩሳል" ትላለች ሠላማዊት "ይኮሰኩሳል። ስለሚኮሰኩስም ሰዉ መጠቀም ተወው። በፊት እንደብርድ ልብስ ከአንሶላ ጋር ይለበስ ነበር። እኛም ለብሰነው ነው ያደግነው። አሁን በብርድ ልብስ እየተቀየረ ነው። ዘመኑ የሻረው ይመስለኛል" ብላለች። ቀደም ሲል መርካቶ ሚሊተሪ ተራ በሚገኙ ሱቆች ውስጥ በብዛት የሚሸጥ የነበረው በርኖስ በአሁኑ ወቅት ከሁለት እና ሶስት ሱቆች በላይ ይህንን አይሸጡም። በተለያዩ የባህል ቁሳቁስ መሸጫ ሱቆች ውስጥም ቢሆን በርኖስም ሆነ ባና የመሸጥ ልምዱ እየቀዘቀዘ ይገኛል። "የሰሜን ሸዋ የባህል አለባበስ ሲነሳ በርኖስ በቀዳሚነት ይጠቀሳል" የሚሉት የዞኑ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ትዕግስት መኳንንቴ "በርኖስ በመንዝ ማማ ወረዳ በደንብ ይሠራል" ይላሉ። ባህሉን ለቀጣይ ትውልድ ለማስተላለፍ እና ሥራውን ሌሎችም እንዲያውቁት በማድረግ የማስፋፋት ሥራ እየተሠራ ነው ይላሉ። "ሌሎች ባህላዊ ቁሳቁሶችን የሚሠሩ እና ምንሊክ መስኮት በሚባለው አካባቢ ያሉ ሰዎች እንዲሠሩ ለማስተማር የቤት ሥራ ወስደናል" ብለዋል። በርኖስ የሚሠሩ ጥቂት ሰዎች መኖራቸው በራሱ እረፍት እንደሚሰጣት ሠላማዊት ትናገራለች። ሥራውን ለማጠናከር ደግሞ አንድ ፕሮጀክት ተቋቁሞ ቢሠራ ውጤታማ እንደሚሆን ታምናለች። "በፊት ሞላሌ ከተማ ላይ የባና ፕሮጀክት ነበር። ፕሮጀክቱ ተመሥርቶ ይንቀሳቀሱ በማህበር ተደራጅተው ይሠሩ ነበር። አባቴም በበርኖስ ንግድ እና ሥራ ላይ በተሠማራበት ወቅት ፕሮጀክቱ ነበር" ትላለች። ሠላማዊት ተመሳሳይ ፕሮጀክት ተቋቁሞ የበርኖስ ሥራ እንዲስፋፋ እና ከአባቷ ያገኘችው የበርኖስ ሥራ በቀጣይ ትውልድም ቀጥሎ ማየት ህልሟ ነው።
41021973
https://www.bbc.com/amharic/41021973
የ21ኛው ክፍለ ዘመን ነዳጅ. . . ውሃ!
የሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን ነዳጅ እየተባለ ይጠራል. . . ውሃ። የውሃ አቅርቦት የዓለማችንን መፃኢ ዕጣ ፈንታ እንደሚገለባብጠው ይነገራል። በሰላማዊ ወይም ሰላማዊ ባልሆነ መንገድ የዓለም ህዝቦች ለውሃ አቅርቦት ይፋለማሉ።
ለመኖር ወሃ ያስፈልገናል። እሱ ምንም ጥርጥር የለውም። ነገር ግን ውሃ ከዛ አልፎ የአንድን ሀገር ምጣኔ ሀብታዊ እንቅስቃሴ ሊገታው ወይም ደግሞ ሊያስመነድገው ይችላል። ከግብፅ እስከ ብራዚል ብንሄድ ታሪክ የሚነግረን ይሄንን ነው። አንዳንድ የውሃ አካላት የሀገራትን ድንበር ገደብ ሲወስኑ ሌሎች እንደ ወንዝ እና ሀይቅ የመሳሰሉ የውሃ አካላት ሁለት እና ከዚያ በላይ ሀገራት ይጋሯቸዋል። የናይል ወንዝ ብቻውን ደርዘን የአፍሪቃ ሀገራትን ያካልላል። ባለሙያዎች እንደሚስማሙት ከሆነ ሰዎች ለውሃ አቅርቦት መንገድ አበጅተው ባይሆን ኖሮ ዓለማችን ሰላም አልባ ትሆን ነበር። ለዚህም ነው በሚቀጥሉት አስርት ዓመታት ዓለማችን ያላትን የውሃ ሀብት በአግባቡ ካልተጠቀመች ነገሮች ባልታሰበ መልኩ ሊጓዙ ይችላሉ የሚሉት የዘርፉ ባለሙያች። በሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን ከሌላው ጊዜ በበለጠ የንፁህ ውሃ ምንጮች እየደረቁ መጥተዋል። የአየር ንብረት ለውጥ፥ የሕዝብ ቁጥር ዕድገት፥ እንዲሁም እያደገ ያለው ብሔርተኝነት የሰዎችን እርስ በርስ ሰላማዊ ግንኙነት አየፈተነው ይገኛል። በዚህ በኩል ደግሞ የዓለማችን የውሃ ፍላጎት እ.አ.አ. ከ2000 እስከ 2050 ባሉት ዓመታት በ55 በመቶ እንደሚያድግ ይገመታል። የውሃ ነገር ውሃ በዓለም ፖለቲካ ላይ የሚያሳድረው ተፅዕኖ የቅርብ ጊዜ ጉዳይ አይደለም። ከጥንት ጀምሮ የነበረ እንጂ። ብዙ ጊዜ የወንዝ መነሻ እና ከፍታ ቦታ ላይ የሚገኙ ሀገራት በታችኞቹ ሀገራት ላይ ተፅዕኖ ያሳድራሉ። እነዚህ የዓለማችን ክፍሎች ደግሞ ብዙ ጊዜ ውጥረት የነገሰባቸው ናቸው። በመካከለኛው ምስራቅ የሚገኘው የዮርዳንስ ወንዝ ፍልስጤም፥ ዮርዳኖስ እና እስራኤልን ጨምሮ በአካባቢው ለሚገኙ በርካታ ሀገራት የውሃ ምንጭ ነው። ኢትዮጵያ እና ግብፅ ደግሞ ከኢትዮጵያ ተነስቶ ማብቂያውን በግብፅ በኩል ሜዲትራንያን ውቅያኖስ ላይ ባደረገው ኣባይ ወይም በናይል ወንዝ ጉዳይ ለዘመናት ሲጎነታተሉ ኖረዋል። እ.አ.አ. በ2015 ዓ.ም. ኢትዮጵያ እና ግብፅ ሲጠናቀቅ በአፍሪካ ትልቁ እንደሚሆን በሚጠበቀው 'በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ' ዙሪያ እሰጥ እገባ ውስጥ ገብተው ነበር። ሀገራቱ ፍትሀዊ የውሃ ክፍፍል የሚያረጋግጥላቸውን ስምምነትም እስከመፈረም ደርሰዋል። በተመሳሳይ መልኩ ማሌዢያ እና ሲነንጋፖር ከዘጠና ዘጠኝ ዓመታት በፊት የፈረሙት ስምምነት ጆን ወንዝን በፍትሃዊ መልኩ ለመጠቀም የተስማሙበት ሰነድ ነው። የሃይድሮ ፖለቲካ ምሁር የሆኑት ዜንያ ታታ እንደሚናገሩት "ዕድሜ ለጆን ወንዝ ሲንጋፖር ዛሬ በፍጥነት እያደጉ ካሉ ሀገራት አንዷ ለመሆን በቅታለች።" • ኢትዮጵያ እና ግብፅ በአባይ ጉዳይ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኝ ፓሲፊክ የተባለ ተቋም የለቀቀው መረጃ እንደሚጠቁመው ከውሃ ጋር በተያያዘ ከክርስቶስ ልደት በፊት 2000 ዓ.ዓ. አንስቶ እስከ ዛሬ ድረስ በዓለማችን በርካታ ግጭቶች ተነስተዋል። እና እንዴት አድርገን ነው ባለንበት ሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን ፍትሃዊ የውሃ ሀብት ክፍፍልን ማረጋገጥ የምንችለው? የዚህ ጥያቄ መልስ የውሃ ሀብት ካላቸው ሀገራት ይልቅ ውሃ እና ምግብ አምርተው ወደሌሎች ክፍለ ዓለማት የሚልኩ ሀገራት ጫንቃ ላይ ይወድቃል። የውሃ ሀብት ክፍፍል "ስለ ሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን ውሃ ስናወራ ሶስት ነገሮችን ከግምት ማስገባት ይኖርብናል" ይላሉ የኦሬጎን ዩኒቨርሲቲ የመልክኣ ምድር ፕሮፌሰሩ አሮን ዎልፍ። "የመጀመሪያው ጉዳይ የውሃ እጥረት ነው። የንፁህ መጠጥ ውሃ እጥረት ልክ እንደ ኤች አይ ቪ እና ወባ በርካቶችን ሊቀጥፍ ይችላል። ሁለተኛው ደግሞ አሱን ተከትሎ የሚመጣው ፖለቲካዊ ቀውስ ነው። ለምሳሌ በሶሪያ ድርቅ ባስከተለው ጉዳት በርካቶች ፈልሰዋል፥ የምግብ ዋጋ ከተገቢው በላይ ንሯል እንዲሁም ሀገሪቱ ከገባችበት ቀውስ እንዳትወጣ ምክንያት ሆኗታል።. . . . . . ሶስተኛው ጉዳይ ግን ከሁለቱ የተለየ እና ብዙ ትኩረት ያልተሰጠው ጉዳይ ነው" ይላሉ አሮን። እሱም የድንብር አቋራጭ የውሃ አካላት ጉዳይ። ማለትም ሁለት እና ከዚያ በላይ ሀገራትን የሚያዋስኑ የውሃ አካላት በላይኛው እና በታችኛው ሀገራት መካከል የውሃ አጠቃቀም መብትን በተመለከተ ሊፈጠር የሚችለው አምባጓሮ አስጊ ነው። ትልቅ ፈተና 'የውሃ ጦርነት' የሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን መለያ ይሆናል እየተባለ ቢነገርም እርግጥ አስካሁን ፈታኝ የሆነ ነገር አላስተዋልንም። ነገር ግን በእስያ እና በአፍሪቃ እየተስተዋለ ያለው የሕዝብ ዕድገት ተፈጥሯዊ ሀብታችን ላይ አደጋ እየጣለ ይገኛል። የዓለማችን ሙቀት መጨመርም አንዳንድ የውሃ ምንጮች እንዲደርቁ ምክንያት እየሆነ ነው። ውሃ ለግጭት መነሻ ነጥብ ሊሆን እንደሚችለው ሁሉ በአግባቡ ትቅም ላይ ከዋለ ለዓለማቀፋዊ ዕድገት ትልቅ መሰረት ሊሆንም ይችላል። ለምሳሌ አፍጋኒስታን በቀጣናዋ ካሉ ሀገራት በላይኛው ተፋሰስ የምትገኝ ሀገር ነች። በጦርነት ስትታመስ የነበረችው አፍጋኒስታን አሁን ላይ የካቡል ወንዝን በፍትሃዊ መልኩ በመጠቀም በማደግ ላይ ትገኛለች። ለዚህም ነው የዘርፉ ተመራማሪዎች ከሀይድሮ ፖለቲካ ይልቅ ሀይድሮ ዲፕሎማሲ አዋጭ ነው እያሉ የሚገኙት። የተሻለ ክፍያ ለገበሬው የዘርፉ በላሙያዎች አንድ ነገር ጠንቅቀን እንድንረዳ ይፈልጋሉ። ውሃ የሚገኘው በወንዞች፥ ሀይቆች ወይም ውቅያኖሶች ብቻ አይደለም። በመሬት ውስጥም አንጂ። ገበሬው እህል ለማምረት በሚጠቀምበት ለም አፈር ውስጥ። ገበሬው ከብቶቹን ለግጦሽ በሚያሰማራበት መስክ ውስጥ። ቨርችዋል ዋተር ወይም 'ምናባዊ ውሃ' እየተባለ የሚጠራው ይህ ሀብት በስንዴ ወይም በበሬ ስጋ መልክ ከላኪ ሀገራት ወደ ተቀባዮቹ ይላካል። በኣውሮፓ ብቻ አርባ በመቶ የሚሆን 'ምናባዊ ውሃ' ከተቀረው ዓለም አህጉሪቱን ይቀላቀላል። ነገር ግን በዚህ ሂደት ውስጥ ትልቅ ቦታ ያላቸው አርሶ አደሮች የሚያገኙት ገቢ እጅግ ያነሰ ነው። በዓለማችን መቶ ስድሳ የሚሆኑ ሀገራት ከውጭ በሚገቡ የምግብ ምርቶች ላይ ጥገኛ ናቸው። የውሃ ሀብት ባለቤት የሆኑት እንደ አሜሪካ እና ካናዳ ያሉ ሀገራት ምግብ አምርተው ለሌሎች ሀገራት በቅናሽ ዋጋ ይሸጣሉ። ጆን አንተኒ አለን በለንደን ኪንግስ ኮሌጅ የግብርና ምሁር ናቸው። "ዓለማችን ሰላም ልትሆን የቻለችው በቨርችዋል ዋተር ወይም 'ምናባዊ ውሃ' ምክንያት ነው" ይላሉ አለን። "ወደ ሃገራት የሚገባው ውሃ በምግብ መልክ ከሌላ ሀገር የተገዛ ነው" በማለት ያክላሉ ። "ሃይድሮ ዲፕሎማሲ የክፍለ ዘመናችን ያለተዘመረልት ጀግና ነው ምክንያቱም የዓለማችንን አንፃራዊ ሰላም እያስጠበቀልን ነው" ሲሉ ያስረግጣሉ ምሁሩ። አንድ ብርጭቆ ውሃ ጨልጠን ጥማችንን ስንቆርጥም ሆነ እህል ስናበቅልበት ውሃ የዓለም ፖሊተካ ሚዛን ጠባቂ መሆኑን ልናስብ ግድ ይላል። ውሃ ለዘመናት የነበረ፥ ያለ እና የሚኖር ሀብታችን ነውና።
news-41683115
https://www.bbc.com/amharic/news-41683115
ብክለት የዓለምን ድሃ ህዝብ እየጨረሰ ነው?
በአውሮፓውያኑ 2015 ከአካባቢ ብክለት ጋር በተያያዘ ምክንያት 9 ሚሊዮን ሰዎች እንደሞቱ 'ዘ ላነሴት ' የተባለው የጤና መጽሄት ባወጣው ሪፖርት አረጋግጧል።
እነዚህ ሞቶች ሁሉም ሊባል በሚችል ሁኔታ የተከሰቱት አነስተኛና መካከለኛ ገቢ ባላቸው ሃገራት ነው። በሀገራቱ ከሚመዘገቡት ሞቶች የአካባቢ ብክለት እስከ 25 በመቶ የሚሆነውን ይሸፍናል። ባንግላዴሽና ሶማሊያ ደግሞ ሁኔታው ከሁሉም ቦታ የተባባሰባቸው ሀገራት ናቸው። የአየር ብክለት፤ ከብክለት ጋር ከሚያያዙ ሞቶች 2/3ኛውን በመሸፈን ከፍተኛ ተጽእኖ እየፈጠረ ነው። ከእነዚህ ሞቶች መካከል ብዙዎቹ የተከሰቱት በልብ በሽታ፤ በእዕምሮ የደም ዝውውር ማቆም( ስትሮክ) እና የሳንባ ካንሰር በሽታዎች ነው። ብሩናይ እና ስዊድን ደግሞ ከብክለት ጋር የተያያዘ ሞት መጠን አነስተኛ የሆነባቸው ሀገራት ሆነዋል። '' ብክለት አሁን ለአካባባቢ ፈተና ሆኗል፤ በጣም እየተስፋፋ ያለና ከባድ የሰው ልጅ የጤናና ደህንንነት ስጋት ነው።'' ይላሉ የጥናቱ ፀሃፊ ፊሊፕ ላንድሪጋን። ከእነዚህ ዋነኛው ስጋት የሆነው የአየር ብክለት የ6.5 ሚሊዮን ሰዎችን ህይወት በአጭሩ ይቀጫል። ይሄ ደግሞ በቤት ውስጥ እንጨት በማንደድና በከሰል ምክንያት፣ ከውጪ ደግሞ በጋዝ ልቀት የሚከሰት ነው። በሚከተለው የውሃ ብክለት ደግሞ 1.8 ሚሊዮን ሰዎችን ሲሞቱ ከእነዚህ 800,000 የሚሆኑት የሞቱት ከሥራ ቦታ ጋር በተያያዘ ብክለት ነው። ከሞቱት 92% የሚሆነው የተከሰተው በድሀ ሃገራት ሲሆን፤ ችግሩ የተባባሳው ደግሞ ለከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ልማት እየሰሩ ባሉት ሃገራት ነው። በተመዘገበው ሞት ብዛት ደረጃም ህንድ አምስተኛ፣ ቻይና ደግሞ አስራ ስድስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። በዩናይትድ ኪንግደም ከተመዘገቡ 50,000 ሞቶች 8% የሚሆነው በብክለት ምክንያት የተከሰተ ነው። ይህም ከ188 ሀገራት 55ኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል። በብሪታንያ የሳንባ ተቋም የሚሰሩት ዶክተር ፔኒ ዉድስ እንደሚሉት በዩናይትድ ኪንግደም ከምዕራብ አውሮፓ ሀገራትም ሆነ ከአሜሪካ በላይ ችግሩ እየተባባሰ መጥቷል '' ምናልባትም መርዛማ ጭስና ንጥረ ነገሮችን ወደ አየር በሚለቁ የነዳጅ መኪኖች ላይ ጥገኛ መሆናችን በተለይም ህጻናትና አዛውንቶችን ለሳንባ በሽታ እያጋለጣቸው ነው'' ብለዋል። በአሜሪካ ደግሞ 5.8% ማለትም የ155,000 ሰዎች ሞት ከብክለት ጋር የተገናኘ ሆኗል። ፀሃፍቱ እንደሚገልጹት የአየር ብክለት የድሃ ሀገራት ህዝቦችና በበለጸጉ ሀገራት የሚገኙ ድሆችን ክፉኛ እያጠቃ ነው። እናም ብክለት በዘመናችን በህይወት የመኖር፣ የጤና ፣ የደህንነት እንዲሁም የህጻናትና ሌሎች ተጋላጭ ሰዎች ክብካቤ ማግኘትን የመሰሉ መሰረታዊ መብቶችን አደጋ ላይ ጥሏል።
news-43616202
https://www.bbc.com/amharic/news-43616202
ቻይና ከአሜሪካ በሚመጡ ምርቶች ላይ የሶስት ቢሊዮን ዶላር ቀረጥ ጫነች
ከአሜሪካ ወደ ቻይና በሚገቡ ወይንና የአሳማ ስጋ የመሳሰሉት 128 የምርት አይነቶች ላይ ቻይና 25% ቀረጥ ጫነች።
ይህ ውሳኔም የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዚሁ ወር ከውጭ በሚገቡ ብረትና አሉሚኒየም ምርቶች ላይ ቀረጥ መጨመራቸውን ተከትሎ ነው። ሶስት ቢሊዮን ዶላር የሚገመቱ ምርቶች ላይ ተፅእኖ የሚያመጣው ይህ ውሳኔም ከዛሬ ጀምሮ ተግባር ላይ ይውላል። ውሳኔውንም አስመልክቶም ቤጂንግ የቻይንን ጥቅም ለማስከበር እንዲሁም አዲሱ የአሜሪካ ቀረጥ ያስከተለውን ኪሳራ ለማስመለስ እንደሆነ ተናግረዋል። ቻይና ቀደም ባሉት ጊዜያት የንግድ ጦርነት እንደማትፈልግ ብታሳውቅም ኢኮኖሚዋ ሲጎዳ ግን እጇን አጣጥፋ እንደማታይ ገልፃ ነበር። ትራምፕ በበኩላቸው የንግድ ጦርነት ጠቃሚነት ላይ አስምረው ለአሜሪካም ማሸነፍ ቀላል ነው ብለዋል። የአሜሪካ ባለስልጣናት በበኩላቸው ከቻይና ወደ አሜሪካ የሚገቡ በአስር ቢሊዮን ዶላር ምርቶች ላይ ቀረጥ ለመጨመር እቅድ እየነደፉ እንደሆነ የቢቢሲው ክሪስ በክለር ከዋሽንግተን ዘግቧል። በቻይና ባለው ኢፍትሀዊ የንግድ ስርዓት ብዙ የአሜሪካ ኩባንያዎች እንደተጎዱ ገልፆ ይህ ግን በአሁኑ ወቅት ወደ ንግድ ጦርነት ተቀይሯል ብሏል። የትኞቹ ምርቶች ይጎዳሉ? ካሉት ምርቶች በተጨማሪ የአሜሪካው አሉሚኒየምና የአሳማ ስጋ ተጨማሪ 25% ቀረጥ ይጫንባቸዋል። ከዚህም በተጨማሪ ኦቾሎኒ፣ የደረቁ ፍራፍሬዎች እንዲሁም የወይን ምርቶች ላይ 15% ጭማሪ ቀረጥ ተጭኖባቸዋል።
news-50512844
https://www.bbc.com/amharic/news-50512844
ፓኪስታን፡ ሴቶችን የማያሳትፈው በሴቶች ላይ የሚመክረው ስብሰባ ቁጣ ቀሰቀሰ
'አርትስ ካውንስል' የተባለው የፓኪስታን ማኅበራዊ ተቋም ምንም አይነት ሴቶችን ያላሳተፈ በሴቶች መብትና ተሳትፎ ላይ ያተኮረ ውይይት ለማድረግ በማሰቡ ከፍተኛ ውግዘት እየደረሰበት ነው።
ካራቺ በተባለችው ከተማ ሊካሄድ የነበረው ውይይት፤ በማኅበራዊ ሚዲያዎች በደረሰበት ከፍተኛ ጫና ምክንያት አዘጋጆቹ የውይይቱን ርእስ እንዲቀይሩ አስገድዷቸዋል። • ፈቲያ መሐመድ፡ ከዐረብ ሃገር ኑሮ ወደ ሚሊየነርነት • እርጉዟ የሰደድ እሳት ተከላካይ አዘጋጆቹ በተለያዩ ዘርፎች ያሉ ውሳኔ ሰጪ ወንዶች ስለ ሴቶች ምን ያስባሉ? የሚለውን ለማወቅ ነው ውይይቱ ላይ ሴቶች ያልጋበዝነው ቢሉም የፓኪስታን የሴቶች መብት ተሟጋቾችና የማኅበረሰብ አንቂዎች ጉዳዩን እንደ ንቀት እንቆጥረዋለን ብለዋል። ወንዶች በብዛት ሁሉንም ነገር በሚወስኑባት ፓኪስታን፤ ሴቶችን ያላሳተፈው ውይይት በአገሪቱ ላለው የወንዶች የበላይነት በቂ ማሳያ ነው ተብሏል። በውይይቱ ከሚሳተፉ ባለሙያዎች መካከል ብቸኛዋ ሴት የነበረችው ኡምዛ አል ካሪም ስሟ መጨረሻ ላይ መጠቀሱንም ብዙዎች አልወደዱትም። ከተለያዩ ዘርፎች የተወጣጡ ናቸው የተባሉት ወንድ ተሳታፊዎችም በሴቶች ስም የራሳቸውን አጀንዳ ለማራማድ በመስማማታቸው ሊያፍሩ ይገባል በሚል በማኅበራዊ ሚዲያዎች ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሟቸዋል። አንድ ፓኪስታናዊ በትዊተር ገጹ ላይ ባሰፈረው መልእክት ''ለሴቶች እኩልነት እሠራለው የሚሉ ወንዶች በዚህ ውይይት ላይ በመሳተፋቸው ሊያፍሩ ይገባል'' ብሏል። ብቸኛዋ የውይይቱ ሴት ተሳታፊና የመድረክ መሪ ኡምዛ አል ካሪም በበኩሏ፤ ''የውይይቱ አላማ በትልልቅ የመገናኛ ብዙሀን የሚገኙ ኃላፊዎችና ሌሎች ውሳኔ ሰጪ ወንዶች ስለሴቶች መብትና እኩልነት ያላቸውን ግንዛቤ ለመረዳት ነበር'' ብላለች። ''የእነሱን አስተያየት ማወቅ የፈለግነው በተለያዩ ማኅበራዊ ኃላፊነቶች ላይ ስለሚገኙ የሰዎችን ሃሳብ መቀየር ስለሚችሉ ነው።'' • በጃፓን ሴት ሠራተኞች መነጽር እንዳያደርጉ መከልከላቸው ጥያቄ አስነሳ በውይይቱ ከሚሳተፉ ወንዶች መካከል አንዱ የሆነው የሰብአዊ መብት ተሟጋቹ ጂብራን ናሲር እንድሳተፍ የተጠራሁበት ውይይት ዋና ርዕሰ ጉዳይ አሳሳች ነበር ብሏል። ''በደረሰኝ መረጃ መሠረት ወንዶች ስለሴቶች ያላቸውን የተሳሳተ አመለካከት እንዴት መቀየር ይችላሉ? በሚለው ርዕስ ላይ ውይይት እንደሚደረግ ነበር የማውቀው'' በማለት ስህተት እንደተፈጠረ ለማስረዳት ሞክሯል።
news-52519537
https://www.bbc.com/amharic/news-52519537
ኮሮናቫይረስ፡ የትኞቹ የአፍሪካ አገራት በኮሮናቫይረስ ምርመራ ይመራሉ?
ኮሮናቫይረስ ምን ያህል ተዛምቷል አልተዛመተም የሚለውን በትክክል ለመረዳት በርካታ ቁጥር ያላቸውን ሰዎች መመርመር ከፍተኛ ሚና ይጫወታል።
በአፍሪካ ያለውን የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምላሽ በማስተባበር ላይ የሚገኘው የአፍሪካ የበሽታዎች ቁጥጥርና መከላከል ማዕከል በአህጉሪቷ ያለው የምርመራ ሁኔታ በተለያዩ ሃገራት ዘንድ ልዩነት ያለው መሆኑን ጠቅሶ ፤ ክፍተትንም እንደሚያሳይ ከሰሞኑ አሳውቋል። በአህጉሪቷ ውስጥ በከፍተኛ ሁኔታ እየመረመሩ ያሉ ሃገራት የትኞቹ ናቸው ወደኋላስ የቀሩት? በአህጉሪቷ ውስጥ ያሉ ትንንሽ አገራት ከትልልቆቹ ጎረቤቶቻቸው ጋር በሚወዳደሩበት ወቅት በርካታ ሰዎችን በመመርመር ተሳክቶላቸዋል። ለምሳሌ ያህል ሞሪሺየሽና ጂቡቲ የመረመሩት ከህዝባቸው ቁጥር ጋር ሲነፃፀር ከፍተኛ ደረጃ የሚባል ነው። ጋናም በበኩሏ ባከናወነቻቸው ምርመራዎች ምስጋናን እየተቸራች ሲሆን፤ መንግሥቷም አስገዳጅ መመሪያዎቹ ሲነሱ ቫይረሱን ለመቆጣጠር እንደሚረዳ ተናግረዋል። ደቡብ አፍሪካም ቢሆን በከፍተኛ ሁኔታ ምርመራዎችን እያከናወነች ሲሆን እስካሁንም ባለው ከሁለት መቶ ሺ በላይ የላብራቶሪ ምርመራዎችን አድርጋለች። ነገር ግን ይህ አሃዝ እንደ ደቡብ ኮሪያ፣ ጣልያንና ጀርመን ካሉ ሃገራት ጋር ሲነፃፀር ዝቅተኛ ነው። በተለይም በአህጉሪቷ በህዝብ ቁጥሯ በአንደኝነት በምትመራው ናይጄሪያ የምርመራ ቁጥር አናሳ ነው ተብሎ ቢተችም መንግሥቷ ግን ቫይረሱ ከተገኘባቸው ግለሰቦች ጋር ንክኪ ወይም ግንኙነት ያላቸው ላይ ነው ትኩረቴ ብሏል። በናይጄሪያ የቢቢሲ ዘጋቢ ቺቺ ኢዙንዱ እንደሚናገረው ባለስልጣናቱ የምርመራ ቁጥርን የማሳደግ እቅድ አላቸው ብሏል። "መንግሥት ያለመው በቀን 5ሺ ሰዎችን መመርመር ቢሆንም አንድ ሺህ ሰዎችን እንኳን እየመረመሩ አይደለም" በማለትም ያለውን ክፍተት ያስረዳል። በአንዳንድ ሃገራት እንደ ኤርትራና አልጄሪያ ባሉት ደግሞ ምን ያህል ምርመራ እንደተካሄደ መረጃ የለም። አንዳንዶች በተለያዩ ምክንያቶች የምርመራ ቁጥራቸውን መረጃ መስጠት ቢደብቁም አንዳንድ ሃገራት ደግሞ ለመርመር አቅሙ የላቸውም። ለምሳሌ የታንዛንያው ፕሬዚዳንት ማጉፉሊ እንዲህ አይነት የምርመራ መረጃዎችን ይፋ ማድረግ በሕዝቡ ዘንድ ፍራቻን ይፈጥራል ብለዋል። ሃገራቸው የተመረጡ መረጃዎችን ሲሆን ለህዝብ ይፋ የምታደርገው አንዳንድ ጊዜም ከቫይረሱ ያገገሙት ላይ ማተኮርን መርጣለች። የምርመራን አቅም ለማሳደግ ያሉ እክሎች ምንድንናቸው? የምርመራ ሂደቶችን ለማከናወን የሚያስፈልጉ ኬሚካሎችን በበቂ ሁኔታ ማግኘት አስቸጋሪ ነው። ምክንያቱም በርካታ የአፍሪካ ሃገራት ኬሚካሎቹን ስለማያመርቱ ባለው የአለም አቀፉ አቅርቦት ለመግዛት ውድድር ውስጥ መግባታቸው ጥገኛ አድርጓቸዋል። የአፍሪካ በሽታዎች ቁጥጥርና ክትትል ማእከል ሰራተኛ የሆኑት ጆን ንኬንጋሶንግ " አለምአቀፋዊ ትብብርና መረዳዳት መፈራረሱ አፍሪካን ከምርመራ ገበያ ጨዋታ ውጭ እንድትሆን አድርጓታል" ብለዋል አክለዋል ምንም እንኳን የአፍሪካ ሃገራት ለዚህ የሚሆን ገንዘብ ቢኖራቸውም " ሰባ የሚሆኑት አገራት ምንም አይነት የህክምና ቁሳቁሶችን ወደ ውጭ መላክ ላይ ጥብቅ የሚባል ገደብ ጥለዋል" ይህም ሁኔታ አስፈላጊ የሚባሉ የህክምና ቁሳቁሶችን ለአህጉሪቷ ማግኘት አዳጋች አድርጎታል። ከዚህም በተጨማሪ ሃገራቱ የጣሏቸው የእንቅስቃሴ ገደብ መመሪያዎች መመርመሪያ ጣቢያዎች ሄደው እንዳይመረመሩ እክል ሆኗል ተብሏል። ከዚህ ሁሉ በላይ ግን በለንደን የትሮፒካል ህክምና ተባባሪ ፕሮፌሰር የሆኑት ንጎዚ ኤሮንዱ የህክምና ቁሳቁስ እጥረት ዋነኛውና አፅንኦት ሊሰጠው የሚገባው ጉዳይ ነው ይላሉ። "የመርመሪያ መሳሪያዎችም ሆነ ሂደቱን ለማከናወን የሚረዱ ኬሚካሎችም በበቂ ሁኔታ የሉም" ይላሉ የናይጄሪያ የበሽታ ቁጥጥር ማዕከል የኮሮናቫይረስን ለመርመር የሚያገለግለሉ አስራ ስምንት ላብራቶሪዎች ቢኖሩትም የመርመሪያ መሳሪያ እጥረት እንዳለበት አሳውቋል። ኬንያም ከሰሞኑ የመርመሪያ መሳሪያ እጥረት እንደ ምራቅ ናሙና መውሰጃ፣ የኬሚካል እጥረት እንዳጋጠማት አሳውቃለች። አንድ የኬንያ ባለስልጣን ከሰሞኑ እንደተናገሩት በአገሪቷ ያለው የመርመሪያ መሳሪያ ቁጥር አምስት ሺህ ብቻ ሲሆን 24 ሺህ መመርመሪያ መሳሪያ እንጠብቃለን ብለዋል። ከዚህም በተጨማሪ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ምክንያቶችም የመርመር ሁኔታው ላይ ተፅእኖ ሳያደርሱ አልቀረምም ተብሏል። "በአንዳንድ ማህበረሰብ ውስጥ ኮሮናቫይረስ ተገኘበት ማለት ለአድልዎና መገለል ሊያጋልጥ ይችላል" የሚሉት ረዳት ፕሮፌሰሯ ንጎዚ ኤሮንዲ " ሊመረጡ የሚፈልጉ የአካባቢውም መሪዎችም ሰዎች እንዲመረመሩ ላያበረታቱ ይችላሉ" ብለዋል። የአፍሪካ ህብረትና የአፍሪካ በሽታዎች ቁጥጥርና ክትትል ማዕከልም በጋራ በመሆን የምርመራ አቅምን ለመጨመር፣ ከህሙማን ጋር ንክኪ ያላቸው ላይ የሚደረጉ ክትትሎችና ምርመራዎችንም ለማፋጠን አዲስ ጅማሮ አቋቁመዋል። በዚህም ጅማሮ መሰረት በአህጉሪቷ ውስጥ አንድ ሚሊዮን ሰዎች የሚመረመሩበትም እቅድ ተይዟል። የኮሮናቫይረስ በእስያና በአውሮፓ በቅድሚያ በመከሰቱ እንዲሁም ኢቦላን የመሰለ ወረርሽኝን በመቋቋም ልምድ ላካበቱት የአፍሪካ ሃገራት ወረርሽኙን ለመካላከል ጊዜ ሰጥቷቸዋል
50739166
https://www.bbc.com/amharic/50739166
ሎዛ አበራ በአንድ ጨዋታ ሰባት ግቦችን አስቆጠረች
ለማልታው ቢርኪርካራ እግር ኳስ ቡድን የምትጫወተው ኢትዮጵያዊቷ እግር ኳሰኛ ሎዛ አበራ ቡድኗ ትናንት ከሂበርኒያንስ ጋር ባደረገው ጨዋታ ሰባት ግቦችን በስሟ ማስመዝገብ ችላለች።
ጨዋታው በቢርኪርካራ 17 ለምንም አሸናፊነት የተጠናቀቀ ሲሆን ቡድኑ በ19 ነጥብ ሊጉን በአንደኛነት እየመራው ይገኛል። ሰባት ልጆች ላፈሩት እናት እና አባቷ አምስተኛ ልጅ የሆነችው ሎዛ ተወልዳ ያደገችው የከንባታ ጠምባሮ ዞን ዋና ከተማ በሆነችው ዱራሜ ነው። • «የኔ ትውልድ ታሪክ እንደሚሠራ እምነት አለኝ» ሎዛ አበራ • የአውሮፓን እግር ኳስ የሚዘውረው ሃብታሙ 'ደላላ' • የሆንግ ኮንግን የዘር መድልዎ የሚፋለሙ አፍሪካዊያን እግር ኳስ ተጫዋቾች ባደገችበት ሠፈር ካሉ ወንድ እኩዮቿ ጋር እየተጋፋች ኳስን ተጫውታለች። የሎዛ ፕሮፌሽናል ኳስ ተጫዋችነት ጉዞ የተጀመረው የከንባታ ዞንን ወክላ ስትጫወት ባይዋት መልማዮች አማካይነት ነው። ብዙም ሳትቆይ ሎዛ የሐዋሳ ሴቶች እግር ኳስ ቡድንን ተቀላቀለች። ከሐዋሳ ጋር ዋንጫ ባታነሳም እዚያ በቆየችባቸው ሁለት ተከታታይ ዓመታት የክለቡ ኮከብ ጎል አስቆጣሪ ነበረች። ሐዋሳን ከለቀቀች በኋላ በደደቢት አራት ዓመታትን ያሳለፈችው ሎዛ በሁሉም ዓመታት በተከታታይ ኮከብ ጎል አስቆጣሪ ነበረች።። ለሶስት ተከታታይ ዓመት ደግሞ የሴቶች ፕሪሚዬር ሊግ ሻምፒዮን ሆናለች ከደደቢት ጋር። በአሁኑ ሰአት በማልታ ደሴት ከፍተኛ ሊግ ላይ ለሚሳተፈው ቢርኪርካራ የምትጫወተው ሎዛ በትዊተር ገጿ ላይ ባሰፈረችው መልእክት ''ዛሬ በነበረን ጨዋታ በማልታ ሊግ ላይ በአንድ ጨዋታ ብቻ ሰባት ጎል በማስቆጠር ሌላ ታሪክ መፃፍ እና መስራት ስለቻልኩ በጣም ደስ ብሎኛል፤ ከዚህ በፊት ኢትዮጵያ ላይ በአንድ ጨዋታ ብቻ ዘጠኝ ጎል አግብቼ ነበር'' ብላለች።
news-57306936
https://www.bbc.com/amharic/news-57306936
"የኤርትራ ወታደሮች ከኢትዮጵያ መውጣት ጀምረዋል" ቢልለኔ ስዩም
በትግራይ ክልል የተከሰተውን ጦርነት ተከትሎ ወደ ኢትዮጵያ ግዛት ገብተዋል የተባሉት የኤርትራ ወታደሮች መውጣት መጀመራቸው ተገለጸ።
ቢልለኔ ስዩም እና ጌዲዮን ጢሞቲዮስ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር ፕሬስ ሴክሬታሪያት ቢልለኔ ስዩም ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደተናገሩት በበርካታ ወገኖች ከትግራይ ክልል እንዲወጡ ሲጠየቁ የነበሩት የኤርትራ ወታደሮች ከኢትዮጵያ ግዛት "መውጣት ጀምረዋል" ብለዋል። ሰባት ወራትን ባስቆጠረው የትግራይ ክልል ቀውስ ውስጥ ተፈጽመዋል በተባሉ ጾታዊ ጥቃቶችና ግድያዎችን ጨምሮ በከባድ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ሲከሰሱ የቆዩት የኤርትራ ወታደሮች ወደ ኢትዮጵያ ግዛት ዘልቀው የገቡት "የደኅንነት ስጋት ስለነበራቸው" እንደሆነ ተገልጾ ነበር። በትግራይ ክልል የተከሰተው ቀውስ መቋጫ እንዲያገኝ የሚወተውቱት የተለያዩ አገራትና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች በተደጋጋሚ ከሚያነሷቸው ጥያቄዎች መካከል የኤርትራ ወታደሮች ከኢትዮጵያ እንዲወጡ የሚጠይቀው ይገኝበታል። ይህንንም ተከትሎ የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ከጥቂት ወራት በፊት ወደ ኤርትራ ተጉዘው ከአገሪቱ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር ከተወያዩ በኋላ ወታደሮቻቸው ከኢትዮጵያ እንደሚወጡ የተገለጸ ቢሆንም አስካሁን ድረስ በይፋ የተገለጸ ነገር አልነበረም። አሁን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቃል አቀባይ በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ የኤርትራ ወታደሮች ከኢትዮጵያ ግዛት መውጣት መጀመራቸውን አመልክተዋል። በትግራይ ስላለው ሁኔታ በተሰጠው መግለጫ ላይ ምን ተባለ? ዛሬ ሐሙስ ግንቦት 26/2013 ዓ. ም በጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽህፈት ቤት ውስጥ በተካሄደ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ የጽህፈት ቤቱ ፕሬስ ሴክሬታሪያት ቢልለኔ ስዩምና የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕጉ ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) በትግራይ ክልል ውስጥ ስለተከሰተውና አሁን ስላለው ሁኔታ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በዚህም መሠረት በክልሉ ስላለው የጸጥታ ሁኔታ፣ የእርዳታ አቅርቦት፣ ተፈጸሙ ስለተባሉ ሰብአዊ መብት ጥሰቶችና በመንግሥት በኩል እየተወሰዱ ስላሉ እርምጃዎች ሁለቱ ባለሥልጣናት ማበራሪያ ሰጥተዋል። የጠቅላይ ሚንስትሩ ጽህፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪ ቢልለኔ ስዩም በመግለጫው መንግሥት አሁን ላይ ወታደራዊ እርምጃ እየወሰደ ያለው በሁለት አካባቢዎች ብቻ መሆኑን ቢያመለክቱም እነዚህ አካባቢዎች የትኞቹ እንደሆኑ አልጠቀሱም። የዕርዳታ አቅርቦት በትግራይ ክልል በአንድ ዙር ለ4.5 ሚሊዮን ነዋሪዎች፣ በሁለተኛ እና ሦስተኛ ዙር ደግሞ ለ4.3 ሚሊዮን ሰዎች ሰብዓዊ እርዳታ ማድረስ እንደተቻለ ገልጸዋል። የተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋሞች በትግራይ እርዳታ የሚሹ ነዋሪዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን እንዲሁም ክልሉ የረሃብ አደጋ እንደተጋረጠበትም መግለጻቸው ይታወሳል። ቃል አቀባዩዋ በበኩላቸው መንግሥት ከእርዳታ ሰጪ አጋር ድርጅቶች ጋር በመሆን በ93 ወረዳዎች እርዳታ እየተሰጠ ነው ብለዋል። ከእነዚህ መካከል 14 ወረዳዎች በመንግሥት የተቀሩት ደግሞ በረድዔት ድርጅቶች ድጋፍ እየተደረገላቸው ነው ተብሏል። በክልሉ ያለውን ሁኔታ በማስመልከት የተለያዩ አገሮች ያሳዩትን አቋም "የኢትዮጵያን ክብር ያልጠበቀ" ሲሉ ገልጸውታል። የኢትዮጵያ መንግሥት አሜሪካን ጨምሮ የተለያዩ አገሮች በውስጥ ጉዳይ ጣልቃ እየገቡ ነው ሲል በተደጋጋሚ መውቀሱ አይዘነጋም። በክልሉ እየተደረገ ባለው ሰብዓዊ እርዳታ በ5.2 ሚሊዮን ብር 166 ሺህ ሜትሪክ ቶን ምግብ ተከፋፍሏል ብለዋል። የዓለም ምግብ ፕሮግራም፣ ሪሊፍ ሶሳይቲ ኦፍ ትግራይን ጨምሮ 6 የረድዔት ድርጅቶች ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር በመተባበር እርዳታ እያቀረቡ እንደሚገኙም አክለዋል። "ረሃብ እንደ ጦርነት መሣሪያ አየዋለ ነው የሚለው ክስ ተቀባይነት የለውም" ሲሉም የዓለም አቀፍ ድርጅቶች እና የመብት ተሟጋቾችን ክስ አጣጥለዋል። የተለያዩ አገራትና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች በትግራይ ክልል ያለው የእርዳታ አቀርቦት በሚፈለገው ሁኔታ እየተከናወነ ባለመሆኑ ቁጥሩ ከፍ ያለ ሕዝብ ለረሃብ ይጋለጣል በሚል ስጋታቸውን እየገለጹ ነው። በጤና ድጋፍ ረገድ 72.9 ሚሊዮን ብር እንደተመደበና 12 አምቡላንስ መሠማራታቸውን ጠቅሰው "የህክምና አገልግሎት መስጫ ሙሉ በሙሉ ወድሟል የሚለው ትክክል አይደለም" ብለዋል ቢልለኔ። በሌላ በኩል የግብርና ሚንስትር ዘርና ማዳበሪያ ለማከፋፈል እንዲሁም የክልሉን አርሶ አደር ለመደገፍ 10 ሚሊዮን ብር መመደቡን ጠቅሰዋል። ትምህርትን ዳግመኛ ለማስጀመር ደግሞ 95 ሚሊዮን ብር መመደቡን ቢልለኔ ጠቅሰዋል። የወንጀል ምርመራ በሌላ በኩል የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕጉ ጌድዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) በበኩላቸው በጋዜጣዊው መግለጫ ላይ በሕግ በኩል እየተወሰዱ ስላሉ እርምጃዎችና ተፈጸሙ ከተባሉ የመብት ጥሰቶች አንጻር ስለተደረጉ ምርመራዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ዐቃቤ ሕጉ "ህወሓት በአፋር፣ በአማራ፣ በቤንሻንጉል እና በኦሮሚያ ክልሎች የሚያስታጥቃቸው እና የሚደግፋቸው ኃይሎች የአገር ሰላም እያናጉ ነው" ብለዋል። በትግራይ ክልል ውስጥ ጦርነቱ በተቀሰቀሰበት ጊዜ በሰሜን ዕዝ ላይ "የተቀነባበረ ጥቃት ተፈጽሟል" በማለት በተያያዥም የኤሌክትሪክ እና የቴሌኮም መስመሮች በህወሓት አመራር መቋረጣቸውን አስታውሰው "ብዙዎቹ በወንጀል የሚጠረጠሩት ታስረዋል" ብለዋል። ተጠርጣሪዎቹ ሕገ መንግሥትን በመጣስ፣ በሽብርተኛነት እና በሌሎችም ወንጀሎች እንደሚጠየቁ በመግለጫቸው ላይ አመልከክተዋል። በወሲባዊ ጥቃት፣ ተዋጊ ባልሆኑ ሰዎች ያልተመጣጠነ ኃይል በመጠቀም የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አባላት ላይ የቀረበውን ክስ በተመለከተም ምርመራ ተደርጎ እርምጃ እተወሰደ መሆኑን አመልክተዋል። በዚህም መሠረት 28 ወታደሮች ክስ እንደተመሠረተባቸው እና በወሲባዊ ጥቃት የተጠረጠሩ 25 ወታደሮችም ላይም ክስ እንደተከፈተ ጌድዮን (ዶ/ር) ተናግረዋል። በሌላ በኩል በማይካድራ የ250 የዓይን እማኞች ተጠይቀውና የፎረንሲክ ምርመራ በከተደረገ በኋላ ከ200 በላይ ሰዎች እንደተገደሉ እንዲሁም የወንጀሉ ተሳታፊ የተባሉ 23 ተጠርጣሪዎች መያዛቸውን አመልክተዋል። በዚሁ ጥቃት ላይ ተሳትፈዋል የሚባሉ "ብዙዎቹ ግን ወደ ሱዳን ሸሽተዋል" ሲሉም አክለዋል። የአክሱም ግድያን በተመለከተ፤ ከ100 የዓይን እማኞች እና የህክምና ማስረጃ በተገኘ መረጃ መሠረት "100 ንጹሃን መሞታቸውን ደርሰንበታል። አብዛኞቹ ህወሓት ያስታጠቃቸው፣ ሁለት ቀን የሰለጠኑ ኢ-መደበኛ ተዋጊ ናቸው" ብለዋል ዐቃቤ ሕጉ። በአክሱም ከተገደሉት መካከል 40 የሚሆኑት ውጊያ ውስጥ ያልነበሩ እንደሆኑ ጠቅሰው፤ ምርመራቸው ንጹሃን እንደተገደሉና መሠረተ ልማት ላይም ጉዳት እንደደረሰ እንደሚያሳይም ተናግረዋል። በትግራይ ክልል ንጹሀን ላይ ደርሰዋል በተባሉት ጥቃቶች የኤርትራ ወታደሮች እጅ አለበት? በሚል ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄ፤ "በአንዳንዶቹ ወንጀሎች አሉበት" ሲሉ ጌድዮን (ዶ/ር) ምላሽ ሰጥተዋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ የኤርትራ ወታደሮች ከኢትዮጵያ መቼ እንደሚወጡ የተጠየቁት ቢልለኔ፤ ጥያቄው ለሚመለከተው አካል እንደቀረበ ገልጸው "በመከላከያ ሚንስትር ሪፖርት መሠረት ሂደቱ ተጀምሯል" ብለዋል።
news-55876528
https://www.bbc.com/amharic/news-55876528
ህንድ አርሶ አደሮች የረሃብ አድማ በመቱባቸው አካባቢዎች ኢንተርኔት አቋረጠች
ህንድ በቅርቡ የተሻሻለውን የግብርና ህግ በመቃወም አርሶ አደሮች የረሃብ አድማ እየመቱባቸው ባሉ አካባቢዎች የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲቋረጥ አድርጋለች።
አርሶ አደሮቹ በመዲናዋ ደልሂ ሶስት ቦታዎች ላይ ተቃውሟቸውን በረሃብ አድማ እየገለፁ ነው ተብሏል። መንግሥት በበኩሉ "የህዝቡን ደህንነት ለመጠበቅ" በሚል የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲቋረጥ እንዳደረገና ይኸም እስከ እሁድ ድረስ ይቀጥላል መባሉ ተገልጿል። በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ አርሶ አደር ተቃዋሚዎች በህንዷ ደልሂ ከሰፈሩና ተቃውሟቸውን ማሰማት ከጀመሩ ከወር በላይ አስቆጥረዋል። የአርሶ አደሮቹ የስራ ማህበራትና መንግሥት የሚያደርጉት ድርድር ያለ ፍሬ ተቋጭቷል ተብሏል። በዚህ ሳምንት ማክሰኞች በተፈጠረ የትራክተር ትእይንት ግጭት ያስከተለ ሲሆን በዚህም አንድ ተቃዋሚ ሞቷል በርካታ ፖሊሶች ተጎድተዋል። አንዳንድ ተቃዋሚዎች የደልሂ ታሪካዊ ቦታ የሚባለውን ሬድ ፎርትን ተቆጣጥረው የነበረ ሲሆን ፖሊስም በመግፋት ከአካባቢው እንዳስለቀቃቸው ተሰምቷል። በትናንትናው ዕለት፣ ቅዳሜ የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዳሳወቀው አርሶ አደሮቹ የተሰባሰቡባቸው ሲንጉ፣ ጋዚፑርና ቲክሪ ግዛቶች ኢንተርኔት መቋረጡን አስታውቀዋል። የአርሶ አደሮቹ መሪዎች በበኩላቸው የአንድ ቀኑ የረሃብ አድማ የታቀደው ህንዳውያን የነፃነት ታጋይ ብለው ከሚጠሩት ማህተመ ጋንዲ የሙት ዓመት መታሰቢያ ጋር ቀኑ እንዲገጥም ነው። "የአርሶ አደሮች አንቅስቃሴ ሰላማዊ ነው፤ በሰላማዊነቱ ይቀጥላል" በማለት የህብረቱ መሪ ዳርሻን ፓል ተናግረዋል። የኢንተርኔት መቋረጡ በርካታ ተቃዋሚዎችን እንዳበሳጫቸው ሮይተርስ በዘገባው አስነብቧል። ሳንዲ ሻርማ የተባለ አርሶ አደር ባለስልጣናቱ ፍርሃት ለመንዛት እየተጠቀሙበት እንደሆነ ሲናገር ሌላኛው ብሃቬሽ ያዳቭ የተባለ አርሶ አደር ደግሞ "ዲሞክራሲን" እየገደሉት ነው ብሏል። አርሶ አደሮቹ ተቃውሞ የሚያደርጉባቸው አካባቢዎች መታወቁን ተከትሎ በተፈጠረ ውጥረት መንግሥት ኢንተርኔት ማቋረጡን አስታውቋል። በያዝነው ሳምንት አርብ ማንነታቸው ያልተገለፁ ሰዎች ሲንጉ በሚባል አካባቢ አርሶ አደሮቹ ለቀው እንዲሄዱ መንገራቸውን ተከትሎ ግጭቶች ተነስተዋል ተብሏል። አርሶ አደሮቹ እንደሚሉት ግለሰቦች ድንጋይ ከመወርወር በተጨማሪ ድንኳኖቻቸውን ከጥቅም ውጭ እንዳደረጉት ተናግረዋል። በርካታ ሰዎችም ተጎድተዋል ተብሏል። የህንድ ሚዲያ እንደዘገበው ግለሰቦቹ የአካባቢው ነዋሪዎች ሲሆኑ አርሶ አደሮቹን የከባቢውን ሰላም በመረበሽና ምጣኔ ኃብቱን ጉዳት ውስጥ ከታችኋል በማለት እየወነጀሏቸው ይገኛሉ። አርሶ አደሮቹ አገሪቷ በቅርቡ የተሻሻለው ሕግ ከጥቅማችን የሚቃረን ነው ይሉታል። በሕንድ ማኅበረሰብ ውስጥ ከእጅ ወደ አፍ በሆነ ኑሮና በድህነት ከሚኖሩ መካከል አርሶ አደሮች ዋነኞቹ ናቸው። ከዚህ ቀደም የመንግሥት ፖሊሲዎች በነፃ ገበያ እንዳይጎዱም ሲጠብቃቸው ነበር። ያ ግን አሁን ተቀይሯል። አዲሱ ሕግ ኮርፖሬሽኖችንና ከፍተኛ ገንዘብ ያላቸውን የሚጠቅምና ደሃ አርሶ አደሮችን አዘቅት ውስጥ የሚከት ነው ይላሉ። ከዚህ ቀደም መንግሥት የግብርና ዘርፉን ገበያውን ይቆጣጠረው የነበረ ሲሆን፤ በአሁኑ ጊዜ ግን እሱ ቀርቶ አርሶ አደሮቹ በቀጥታ ከግል ሻጮች ጋር ዋጋ መደራደር ይችላሉ። አዲሱ ሕግ ከዚህ ቀደም ነጋዴዎች እህል ማከማቸት በወንጀል ይቀጣ የነበረውን በማሻሻል ማከማቸት ይችላሉ ይላል። በዚህም በወረርሽኝ ወቅት ነጋዴዎች ዋጋ እንዲጨምሩ የሚያስችል ዕድል ሰጥቷል። በሕንድ ከ86 በመቶ በላይ የሚሆኑት አርሶ አደሮች አነስተኛ መሬት ወይም ከሁለት ሄክታር በታች ያላቸው ናቸው። ከዚህም ጋር ተያይዞ ኑሮ ከእጅ ወደ አፍ በሆነበት ሁኔታ ጠቀም ባለና ለኑሯቸው በሚሆን ዋጋ ምርታቸውን ለትልልቅ ኩባንያዎች ለመሸጥ የመደራደሪያ አቅሙ የለንም ይላሉ። የግሉ ዘርፍ በከፍተኛ ሁኔታ የዘርና የማዳበሪያን ዋጋ በመጨመር ኑሯቸውን ከባድ አድርጎታል። ከዚህ ቀደም መንግሥት ዝቅተኛ የዋጋ ድጋፍ የሚል ፖሊሲ የነበረው ሲሆን መንግሥት ሩዝና ስንዴ ለሚያመርቱ አምራቾች የሚሰጠው የዋጋ ነበረው። በአዲሱም ሕግ ይህንንም ድጋፍ ያጣሉ ተብሏል። መንግሥት በበኩሉ የግል ተቋማትን በግብርና ዘርፉ እንዲሳተፉ የፈቀደው ይህ ማሻሻያ አርሶ አደሮችን አይጎዳም በማለት ይከራከራል። ይህ ግን ከአርሶ አደሮቹ ዘንድ ተቀባይነትን አላገኘም። አርሶ አደሮቹን ሳያሳትፍ የወጣ ሕግ ነው በሚል አመፁን አቀጣጥሎታል።
news-42400040
https://www.bbc.com/amharic/news-42400040
ለቤተሰብ ምግብ ወይስ ለህክምና ይክፈሉ?
ለቤተሰብ ምግብ፣ ለህፃናት ህክምና፣ ልጆች መፀዳጃ ቤት መጠቀም እንዲችሉ ከመክፈልና መሰል ጉዳዮች የቱን ላድርገው ለየቱ ላውጣ ብሎ መጨነቅ በኬንያ ያሉ የድሆች መንደሮች ውስጥ የሚኖሩ በርካታ እናቶች እጣ ነው።
ፒስ፤ የሱሳን ምቡላና ባለቤቷ አራተኛ ልጅ ነች። እነ ሱሳን የሚኖሩት ሲናይ የሚባል የናይሮቢ የተጨናነቀ መንደር ውስጥ ነው። መኖሪያ ቤታቸው አንድ ክፍል ሲሆን በአንድ አግዳሚ ሶፋ ከፍለውተል። ከጎረቤቶቻቸው ጋር ሲነፃፀር የነሱሳን ቤት ጥሩ የሚባል ነው። የተጨናነቀው የነሱሳን መንደር ውሃ የለውም። የንፅህና አገልግሎትም ብርቅ ነው። በየቤቱ ውሃ ማግኘት የዕለት ከዕለት ትልቁ ጉዳይ ነው። ህክምና ደግሞ ቅንጦት ነው። ሃያ አምስት በመቶ የሚሆኑ ኬንያዊያን የሆነ አይነት የጤና መድህን ሽፋን አላቸው። ቀሪዎቹ ግን ወደ ሃኪም ቤት ሲሄዱ የሚከፍሉ ናቸው። ይህ ደግሞ ብዙዎችን ለድህነት እንደዳረገ የኬንያ ጤና ጥበቃ ፌደሬሽን ይገልፃል። ለብዙዎች ለጤና ሽፋን መቆጠብ፣ ወይም ቅድመ ክፍያ የሚቻል አይደልም። እድሜ ለሱሳን የሞባይል የጤና ሽፋን ይሁንና ፒስ መከተብ የቻለች የሱሳን ብቸኛ ልጅ ነች። "በሌሎቹ ልጆቼ ጊዜ ከባድ የገንዘብ ችግር ነበረብኝ። ለህክምና ምንም መክፈል አልችልም ነበር" በማለት ታስታውሳለች ሱሳን። "የቅድመ ወሊድ ክትትልና የተለያዩ ምርመራዎችን ለማድረግ ወደ ክሊኒክ መሄድ አልችልም ነበር። በፒስ እርግዝና ጊዜ ግን በሞባይል ቁጠባዬ አማካኝነት ክሊኒክ መሄድ ችያለሁ"ትላለች። ኬንያ ውስጥ ኤም-ፔሳ የሚባል በሞባይል ክፍያ መፈፀም የሚያስችል ሥርዓት አለ። ኤም-ፔሳ 19 ሚሊዮን ተጠቃሚዎች አሉት። ሱሳን ተጠቃሚ የሆነችበት የጤና ሽፋን ኤም-ቲባ ደግሞ በኤም-ፔሳ ስር የሚሰራ ነው። ብዙ ኬንያዊያን ድንገተኛ የጤና ችግር ሲያጋጥማቸው ከጓደኞቻቸውና ከዘመዶቻቸው ገንዘብ ያሰባስባሉ፤ አልያም ያላቸውን ንብረት እንደሚሸጡ የሳፋሪኮም ዋና ሥራ አስኪያጅ ቦብ ኮሊሞር ይናገራሉ። "ስለዚህ የኤም-ቲባ ተጠቃሚዎች ትንሽ ገንዘብ ቆጥበው ለጤና ሽፋን ብቻ እንዲጠቀሙ እድል ሰጥቷል" ይላሉ ኮሊሙር። ይህ ብቻም ሳይሆን ተጠቃሚዎች ለሌሎች የጤና ሽፋን ይውል ዘንድ ገንዘብ ማስተላለፍ ይችላሉ። "መጀመሪያ እዚህ ሥርዓት ውስጥ ስገባ በጣም ተጠራጥሬ ነበር። ደጋግሜ ሂሳቤን እመለከት ነበር። በመጨረሻ ግን ገንዘቤ እንዳለና ቁጠባዬ እንደቀጠለ አየሁ" ትላለች ሱሳን። አንዱ ከአንዱ እየሰማ አሁን በሲናይ የተጨናነቁ መንደሮች ብዙዎች የኤም-ቲባ ተጠቃሚ ሆነዋል። የኤም-ቲባ አካሄድን በተመለከተ የኬንያ የህክምና ባለሙያዎች ቦርድ አባል የሆኑት ዶ/ር ኔሊ ቦሲር ለቢቢሲ "ምናልባትም ይህ ሀምሳ በመቶ ለሚሆነው ህዝባችን የሚያዋጣ መንገድ ነው" ብለዋል። ነገር ግን ብቸኛው መንገድ ነው አይሉም። ቢሆንም ግን ጤና ለሁሉም ሽፋን ላይ ለመድረስ ዓይነተኛ መንገድ ነውም ይላሉ። በሌላ በኩል ደግሞ ይህ ዘዴ ጤና ነክ መረጃዎችን ለመሰብሰብ እንደሚጠቅም ይናገራሉ። እሳቸው እንደሚሉት በዚህ መልኩ የተደራጀ መረጃ መግኘት ተችሏል። መረጃዎቹ የሰዎችን ህክምና የማግኘት ልማድ፣ ለምሳሌ ወባን ለማከም ምን ያህል ይፈጃል የሚሉና መሰል መረጃዎች እነደሚገኙ ተጠቁሟል። ይህ ደግሞ በአገር አቀፍ ደረጃ ለማቀድና ፖሊሲ ለማውጣት እንዲሁም የተለያዩ የጤና ጉዳዮችን በተሻለ ለመመለከት ያስችላል። ሁለት ዓመት ከማይሞላ ጊዜ በፊት ኪብራ ከሚባለው የናይሮቢ የተጨናነቀ መንደር ከኤም-ቲባ ጋር የሚሰራው አንድ ክሊኒክ ብቻ ነበር። አሁን ግን በመሰል የተጨናነቁ መንደሮች የሚገኙ 549 ክሊኒኮች ከኤም-ቲባ ጋር እየሰሩ ነው። ይህ ደግሞ እንደ ሱሳን ያሉ ድሆች ተጠቃሚ እንዲሆኑ አስችሏል።
news-56236703
https://www.bbc.com/amharic/news-56236703
ትግራይ፡ የቢቢሲ ዘጋቢ በኢትዮጵያ ሠራዊት በቁጥጥር ስር ዋለ
ግጭት በተካሄደበት የሰሜናዊ ኢትዮጵያዋ የትግራይ ክልል የቢቢሲ ዘጋቢ የሆነው ግርማይ ገብሩ በኢትዮጵያ ወታደሮች መታሰሩን ተከትሎ ቢቢሲ ስጋቱን ገለጸ።
የቢቢሲ ቃል አቀባይ እስሩን በተመለከተ "ስጋታችንን ለኢትዮጵያ መንግሥት ባለስልጣናት ገልጸን ምላሻቸውን እየተጠባበቅን ነው" ብለዋል። የግርማይንና የሌሎች መታሰርን በተመለከተ መግለጫ ያወጣው የጋዜጠኞች ደኅንነት ተቆርቋሪው ተቋም የሲፒጄ ተወካይ ሙቶኪ ሙሞ "የጋዜጠኞቹና አብረዋቸው የሚሰሩ ሰዎች እስር ያለጥርጥር እራስን ሳንሱር ማድረግና ፍርሃትን ይፈጥራል" በማለት የኢትዮጵያ ባለስልጣናት የታሰሩትን ሰዎች በመልቀቅ በትግራይ ውስጥ ያለውን ሁኔታ ያለፍርሃት መዘገብ እንዲቻል ጥሪ አቅርበዋል። ለቢቢሲ የትግርኛ ቋንቋ አገልግሎት የሚሰራው ግርማይ ገብሩ የተያዘው በክልሉ ዋና ከተማ መቀለ ውስጥ በሚገኝ ካፍቴሪያ ውስጥ ከሌሎች አራት ሰዎች ጋር ነው። የዓይን እማኞች ለቢቢሲ እንደተናገሩት አምሰቱ ሰዎች የተያዙት ወታደራዊ የደንብ ልብስ በለበሱ ግለሰቦች ሲሆን፤ በሁለት የወታደር ተሽከርካሪዎች በታጀበ መኪና መወሰዳቸውን ገልጸዋል። ግርማይን ጨምሮ አምሰት ሰዎች ለምን ተይዘው እንደተወሰዱ ግልጽ አይደለም። ቢቢሲ ባገኘው መረጃ መሰረት ሪፖርተሩ መቀለ ውስጥ ወደሚገኝ ወታደራዊ ካምፕ ተወስዷል። ህወሓትን ለማስወገድ በተወሰደው ወታደራዊ እርምጃ የፌደራል መንግሥቱ ኃይሎች የትግራይ ክልልን መቆጣጠራቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ካስታወቁ በኋላ ካለፈው ኅዳር ጀምሮ ክልሉ በወታደራዊ ዕዝ ስር ይገኛል። ወታደራዊ ግጭቱ የተባባሰው የህወሓት ኃይሎች ትግራይ ውስጥ በሚገኘው የሠሜን ዕዝ ጥቃት ከሰነዘሩ በኋላ ነበር። በውጊያው በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ሲገደሉ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩት ደግሞ ለመፈናቀል ተዳርገዋል፤ በተጨማሪም በክልሉ ተፈጽመዋል የተባሉ ግድያዎችና የሰብአዊ ቀውስ ሁኔታ አሳሳቢ እየሆነ ነው። ወደ ክልሉ ዓለም አቀፍ የመገናኛ ብዙሃን ለወራት እንዳይገቡ ከተከለከለ በኋላ የኢትዮጵያ መንግሥት የውጭ አገር ጋዜጠኞች ወደ ትግራይ ገብተው እንዲዘግቡ ባለፈው ሳምንት ፈቅዷል። የቢቢሲው ዘጋቢ የታሰረው ለአዣንስ ፍራንስ ፕሬስ (ኤኤፍፒ) እና ለፋይናንሻል ታይምስ የሚሰሩ ሁለት ሌሎች ጋዜጠኞቹን የሚያግዙ ባለሙያዎች (ፊክሰር) መታሰራቸው ከተነገረ ከቀናት በኋላ ነው። ሌላ ታምራት የማነ የተባለ የአገር ውስጥ ጋዜጠኛም ባልታወቀ ምክንያት በወታደሮች ተይዟል። ባለፈው ሳምንት አንድ የኢትዮጵያ ገዢ ፓርቲ ባለስልጣን "አሳሳች በሆኑ ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ላይ መንግሥት እርምጃ ይወስዳል" ሲሉ አስጠንቅቀው ነበር። ኤኤፍፒ እና ፋይናንሻል ታይምስ ወደ ትግራይ በመሄድ ዘገባ እንዲሰሩ በኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣንና በሠላም ሚኒስቴር ፈቃድ አግኝተው ነበር። "በፍጹም ብርሃኔ ላይ የቀረበ ይህ ነው የሚባል ክስ አልተነገረንም። ከመገናኛ ብዙሃን ጋር መተባበሩ ለመታሰሩ ምክንያት ሊሆን አይገባም፤ ስለዚህም በአስቸኳይ እንዲለቀቅ እንጠይቃለን" ሲሉ የኤኤፍፒ ግሎባል ኒውስ ዳይሬክተር ፊል ቼትዊንድ ባወጡት መግለጫ ጥሪ አቅርበዋል። ፋይናንሻል ታይምስ ባወጣው አጭር መግለጫ የታሰሩትን ጋዜጠኞቹን የሚያግዙ ባለሙያዎች (ፊክሰር) ለማስለቀቅ "የሚቻለውን ሁሉ እርምጃ" እየወሰደ መሆኑን ገልጿል። ምንም እንኳን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ በኅዳር ወር አጋማሽ ላይ የመንግሥት ሠራዊት የክልሉን ዋና ከተማ መቆጣጠራቸውን ተከትሎ ድል መቀዳጀታቸውን ቢያውጁም በክልሉ ውስጥ ግጭቶች የቀጠሉ ሲሆን የተጣለው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አልተናሳም።
news-50025471
https://www.bbc.com/amharic/news-50025471
አሜሪካ በቱርክ ላይ ማዕቀብ ልትጥል እየተሰናዳች ነው
ቱርክ በሶሪያ በኩርዶች ይዞታ ሥር የሚገኙ አካባቢዎች ላይ ጥቃት መፈፀሟን እንድታስቆም አሜሪካ ላይ ጫና እየበረታባት ነው።
የመከላከያ ሚኒስትሩ ፀኃፊ ማርክ ኤስፐር "ጠበቅ ያለ ርምጃ" ሊወሰድ እንደሚችል ሲያስጠነቅቁ፤ የገንዘብ ሚኒስትሩ ፀኃፊ ስቴቨን ሙንቺን በበኩላቸው አዲስ ማዕቀብ ሊጣል የሚችልበትን ዕድል ተናግረዋል። መከላከያ ሚኒስትር ፀኃፊው አክለውም ፕሬዝዳንት ኤርዶጋን " መዘዙ ብዙ የሆነ ርምጃ" እንደወሰዱ በመናገር ድርጊቱ " የአይ ኤስ ወታደሮች ታስረውበት ያለውን ሥፍራ አደጋ ላይ የሚጥል ነው" ሲሉ አስጠንቅቀዋል። • ቱርክ ከሶሪያ ጋር በሚያዋስናት ድንበር ላይ በፈፀመችው ጥቃት በርካቶች ተገደሉ • አሜሪካ ቱርክ ሶሪያ ላይ ጥቃት እንድትፈፅም ይኹንታዋን እንዳልሰጠች ገለፀች • ግብጽ በአባይ ላይ ያለኝን መብት ለመከላከል ኃይሉም ቁርጠኝነቱም አለኝ አለች የገንዘብ ሚኒስትሩ በበኩላቸው ፕሬዝዳንት ትራምፕ ቱርክ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ ለመጣል የሚያስችል ረቂቅ እንዲዘጋጅ ማዘዛቸውን ተናግረዋል። "ከፈለግን የቱርክን ኢኮኖሚ ቀጥ እናደርገዋለን" ሲሉ አክለዋል። ፕሬዝዳንት ትራምፕ "ቱርኮች የሰው ሕይወት እንዲቀጥፉ አንፈልግም፤ ማዕቀብ መጣል ካለብን እናደርገዋለን" ብለዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የዲሞክራቶችና ሪፐብሊካን ሕግ አውጪዎቹ በጋራ ተቀምጠው ቱርክ ላይ ጫና የሚደረግበትን ጉዳይ እየተነጋገሩ ነው። ፕሬዝዳንት ትራምፕ ጦራቸውን ከሥፍራው ለማውጣት መወሰናቸው ቱርክ ወታደሮቿን ወደ ሥፍራው አሰማርታ ጥቃት እንድትከፍት እድሉን ሰጥቷታል ሲሉ የሚከስሱ አሜሪካውያን ቁጥርም ቀላል አይደለም። የቱርክ ፕሬዝዳንት ጣይብ ኤርዶጋን ግን ወታደራዊ ዘመቻው እንደሚቀጥል ተናግረዋል። እንደተባበሩት መንግሥታት ከሆነ የቱርክ ጦር ጥቃት ከከፈተበት ረቡዕ እለት ጀምሮ ከ100 ሺህ በላይ ሰዎች ቤት ንብረታቸውን ጥለው ሸሽተዋል። በአካባቢው እየደረሰ ያለው ቀውስ እየበረታ በሄደበት በአሁን ሰዓት የአሜሪካ ጦር የቱርክ ጦር ጥቃት እንዳሳሰበው መናገር ጀምሯል። አርብ ዕለት ፔንታጎን እንዳለው በሰሜናዊ ሶሪያ አቅራቢያ በሚገኝ የጦር ካምፑ አቅራቢያ ከቱርክ የተተኮሰ መሣሪያ ወድቋል። የባህር ኃይሉ ካፒቴን ብሩክ ዴዋልት እንዳሉት ደግሞ አካባቢው "የአሜሪካ ጦር እንዳለበት ይታወቃል።" ካፒቴኑ"ሁሉም የአሜሪካ ጦር ባልደረቦች ላይ ጉዳት አለመድረሱን አረጋግጠናል" ብለዋል በመግለጫቸው ላይ፤ "አሜሪካ ከቱርክ የምትፈልገው ወዲያውኑ ራሳችንን ወደ መከላከል የምንገባበት ነገር እንዳይከሰት ነው" ሲሉም አስጠንቅቀዋል። ቱርክ ግን ሆን ተብሎ የተደረገ አይደለም ስትል አስተባብላለች። በኩርዶች የሚመራው የሶሪያ ዲሞክራሲያው ኃይል ጦር በቀጠናው የአሜሪካ ዋነኛ አጋር ነበር። አሁን ግን ከቱርክ ምድር ጦርና አየር ኃይል ከፍተኛ ጥቃት እየደረሰበት ይገኛል። ቱርክና ሶሪያ በሚጋሩት 120 ኪሎ ሜትር በሚሸፍነው ድንበር ላይ ጥቃቱ እንደተከፈተ ማወቅ ተችሏል። በርካታ የሶሪያ ዲሞክራሲያው ኃይል ጦር እና የሌሎች አማፂያን ጦር ታጣቂዎች መገደላቸውን ለማወቅ ተችሏል። ቱርክ ላይ የሚጣለው ማዕቀብ ባለሥልጣናቷ ላይ ሊሆን እንደሚችል እየተነገረ ሲሆን ይህንን ጥቃት ይደግፋሉ የሚባሉ ባንኮችም እጣው ሊደርሳቸው እንደሚችል የዲሞክራቶችና የሪፐብሊካን ተወካዮች ተናግረዋል። ፕሬዝዳንት ኤርዶጋን በበኩላቸው "ከግራም ከቀኝም ይህንን ጉዳይ አቁሙ የሚል ማስፈራሪያ እየደረሰን ነው" በማለት " ነገር ግን ከአቋማችን ፈቀቅ አንልም" ብለዋል።
55004607
https://www.bbc.com/amharic/55004607
ትግራይ፡ ከግጭቱ ጋር ተያይዞ በፌስቡክ እየተዘዋወሩ ያሉ የተጭበረበሩ ምሥሎች
በትግራይ ክልል ካለው ሁኔታ ጋር ተያይዞ የሚወጡ መረጃዎች በምሥልና በቪዲዮዎች የታገዙ ናቸው። ሁሉም ታዲያ ትክክለኛ ናቸው ማለት አይደለም።
የቢቢሲ የመረጃ አጣሪ ቡድን በብዛት በማኅበራዊ የትስስር ገጾች የተጋሩ ሐሰተኛ መረጃዎችን እንደሁልጊዜው ሁሉ ነቅሶ አውጥቷቸዋል። 1. የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የተሳሳተ ፎቶ ጠቅላይ ሚኒስትርዐቢይ አሕመድ በወታደራዊ ዩኒፎርም ይታያሉ። ስልክ እያወሩ ይመስላሉ። ጦር አውድማ ላይ ተገኝተው መመርያ እየሰጡም ይመስላል። ይህን ምሥል በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቃል አቀባይ የሆኑት አቶ ታዬ ደንደአ ስም የሚገኝ የፌስቡክ ገጽ ተጠቅሞታል። አቶ ታዬ ደንደአ የተጠቀሙት ይህ ምሥል የተጭበረበረ ነው። በሳቸው ገጽ ሦስት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ፎቶዎች ይታያሉ። ይህ የአቶ ታዬ ገጽ ላይ ያለውን ፎቶዎቹን የያዘው መረጃ ከአንድ ሺ ሰዎች በላይ አጋርተውታል። ነገር ግን በሪቨርስ ኢሜጅ ፍለጋ ከፎቶዎቹ አንዱ የተጭበረበረ እንደሆነ ደርሰንበታል። ይህም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስልክ እያወሩ ጦርነቱን እየመሩ መስለው የሚታዩበት ፎቶ ነው። ፎቶው ከዚህ በፊት አገልግሎት ላይ የዋለ ነው። ይኸው ፎቶ ለመጀመርያ ጊዜ ስለ አሜሪካ ሰራዊት በሚያወሳ ዜና ላይ አገልግሎት ላይ ውሎ ያውቃል። ዋናውን የፎቶ ቅጂ እዚህ ጋ ማየት ይቻላል። ፎቶዎቹን ያስተያይዋቸው። ይህ ፎቶ አንድ ወታደር ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድን እንዲመስል ተደርጎ የተቀነባበረ ነው። የቱባው (ኦሪጅናሉ) ፎቶ ምንጭ የት ነው በሚል ቢቢሲ ፍለጋ አድርጎ በጌቲ ኢሜጅ ቋት ውስጥ አግኝቶታል። ወደ ጌቲ ኢሜጅ የገባውም በኦክቶበር 2017 ነው። ፎቶው የተወሰደበት ትክክለኛ አድራሻም ዩክሬን ውስጥ ነው። ስለ ጉዳዩ ይበልጥ የተሟላ መረጃ ለመስጠት አቶ ታዬ ደንደአ አረዶ ጋር ደውለን ነበር። ለምን የተጭበረበረ ምሥል እንደተጠቀሙ ለመጠየቅ። ሆኖም አልተሳካልንም። ፎቶው የተወሰደበት ትክክለኛ አድራሻም ዩክሬን ውስጥ ነው። 2. ተመቶ የወደቀው አውሮፕላን ተንቀሳቃሽ ምሥል አንድ ተንቀሳቃሽ ምሥል በስፋት በማኅበራዊ የትስስር ገጾች እየተጋራ ነው። ይህም የኢትዮጵያ የጦር አውሮፕላን ተመትቶ ከሰማይ ላይ ሲከሰከስ የሚያሳይ ነው። አውሮፕላኑ በትግራይ ክልል ጥቃት ሲያደርስ እንደተመታ ተደርጎ ነው የቀረበው። ይህ ተንቀሳቃሽ ምሥል ሐሰተኛ እንደሆነ ደርሰንበታል። የዚህ የተጭበረበረ ቪዲዮ ምንጭ የት ነው በሚል ባደረግነው ፍተሻ አርማ ከሚባል የሚሊተሪ ቪዲዮ ጌም የተቀናበረ እንደሆነ አውቀናል። የዚህ የተጭበረበረ ቪዲዮ ምንጭ የት ነው በሚል ባደረግነው ፍተሻ አርማ ከሚባል የሚሊተሪ ቪዲዮ ጌም የተቀናበረ እንደሆነ ታውቋል ሐሰተኛ ቪዲዮ ለመሆኑ ምልክቶችን ማየት ይቻላል። ለምሳሌ ከጀርባው የሚታየው ሰማያዊ ቀለም የተዘበራረቀ መሆኑ፣ እንዲሁም አውሮፕላኑ ከመከስከሱ በፊት የሚታየው ጭስ ስለ መጭበሩ ምልክት ይሰጣል። የዚህ ተንቀሳቃሽ ምሥል ትክክለኛው መነሻ በጃፓንኛ ምሥሎችን የሚጭን አንዳንድ ጊዜም የእንግሊዝኛ ትርጉም የሚያስቀምጥ የዩትዩብ ቻናል እንደሆነ ደርሰንበታል። አሁን ወደ ኢትዮጵያ ተቀናጅቶ እየተጋራ ያለው ተንቀሳቃሽ ምሥል ከዚህ የጃፓን ዩትዩብ ቻናል የተወሰደ ሲሆን፤ በተወሰነ መልኩ ማሻሻያ ተደርጎበታል። ይኸውም የቪዲዮው መግቢያና መጨረሻ ላይ በጃፓንኛ የተጻፉ ነገሮችን እንዲወጡ ተደርገዋል። አንዳንዶቹ ትክክለኛ ቪዲዮዎች በዚህ ምሥል ላይ እንደተጨማሪ ገብተዋል። ምሥሎቹ ትክክለኛ ናቸው። ነገር ግን ከኢትዮጵያ የተገኙ አይደሉም። ምንጫቸው በ2016 በዮርዳኖስ አየር ኃይል ኤፍ 16 ሲከሰከስ የሚያሳየው ትክክለኛ ምሥል ነው። 3. ከኢትዮኤርትራ ጥቃት ጋር በተያያዘ አሁን በሰሜን ኢትዮጵያ ካለው ሁኔታ ጋር ምንም ተያያዥነት የሌላቸው ሌሎች በርከት ያሉ የተጭበረበሩ ምሥሎች ማኅበራዊ ሚዲያው ላይ እየተጋሩ ይገኛሉ። አንዳንዶቹ ከሌላው ዓለም ተወስደው የተቀናበሩ ናቸው፤ አንዳንዶቹ ምሥሎች ደግሞ ጦርነቱ ከመጀመሩ በፊት የነበሩ ናቸው። ለምሳሌ አንድ የፌስቡክ ገጽ አለ። የማእከላዊው መንግሥት እየወሰደ ያለውን እርምጃ የሚደግፍ ነው። የሚጠቀመው ምሥል ግን ከኡስቤኪስታን የተወሰደ ነው። ይህ ምሥል ከኡስቤኪስታን የተወሰደ ነው የወታደራዊ አውሮፕላን ሮኬቶችን ሲተኩስ የሚያሳዩ ምስሎችን ተጠቅሟል። ምስሎቹ በትግራይ እየሆነ ያለውን ሁኔታ የሚያሳዩ መስለው ቀርበዋል። ይህም በብዙ ሺ ሰዎች ተጋርቷል። ሐሰት ነው። ምሥሎቹን በደንብ ላጤናቸው "Uz Air Force A. Pecchi" የሚል ጽሑፍ ማየት ይችላል። Uz ኡዝቤኪስታን በምሕጻር ቃል ሲወከል ነው። A.Pecchi የሚለው ደግሞ የፎቶ አንሺው ስም ነው። አንቶኒ ፔቺ ነው ሙሉ ስሙ። በዚህ ዓመት ጃንዋሪ ይህ ፎቶ አንሺ እነዚህን ምሥሎች በራሱ የፌስቡክ ገጽ ላይ አጋርቷቸው ነበር። 4. ከባሕርዳርና ጎንደር ጥቃት ጋር በተያያዘ አንዳንድ ሰዎች ወደ ባሕርዳርና ጎንደር የተተኮሱ ሮኬቶች ያደረሱትን ጉዳት ለማሳየት ሐሰተኛ ምስሎችን ተጠቅመዋል። ሌሎች ደግሞ ወደ አስመራ የተተኮሱ ሮኬቶች ያደረሱትን አደጋ ለማሳየት እነዚህን የተጭበረበሩ ምስሎት ተጠቅመዋል። ይህ ምሥል ግን ትክክለኛ ምንጩ በቻይና የተከሰተ ፍንዳታ ነው። የቻይና የወደብ ከተማ ቲያንጂን በ2015 በአንድ ኬሚካል ማከማቻ መጋዘን ላይ የደረሰ ፍንዳታን የሚያሳዩ ምስሎች ናቸው በጎንደር፣ በባሕር ዳርና በአስመራ የደረሱ ጉዳቶች መስለው እየቀረቡ ያሉት። ይህ ምሥል ትክክለኛ ምንጩ በቻይና የተከሰተ ፍንዳታ ነው ቢቢሲ ይህንን ጉዳት በጊዜው ዘግቦት ነበር። አንደኛው ምሥልም በዚያን ጊዜ ከተዘገበው ምሥል ቁርጥ እንድ ዓይነት እንደሆነ ማየት ትችላላችሁ። 5. አስመራ ላይ የተተኮሰ ሚሳኤል ቪዲዮ አንድ የፌስቡክ ገጽ በአስመራ ላይ የተደረገውን የሚሳይል ጥቃት የሚያሳይ ተንቀሳቃሽ ምሥል ነው በሚል ቪዲዮ አጋርቷል። ይህ የፌስቡክ ገጽ ጥቃቱ ሲፈጸም የሚያሳይ ቪዲዮ ነው ያለኝ በሚል 2 ሰዓት ሙሉ በቀጥታ ጥቃቱን የቀረጸው ይመስል ለተከታዮቹ አጋርቷል። ከሺ ጊዜ በላይ የተጋራው ይህ ቪዲዮ ከኤርትራ የተገኘ አይደለም። ቪዲዮው የተወሰደው በዚህ ዓመት በጃንዋሪ ወር ኢራን በኢራቅ የሚገኘውን የአሜሪካ የጦር ሰፈር በሚሳይል ስታጠቃ ከሚያሳይ ቪዲዮ ነው። ቪዲዮው የተወሰደው ባለፈው ዓመት በጥር ወር ኢራን በኢራቅ የሚገኘውን የአሜሪካ የጦር ሰፈር በሚሳይል ስታጠቃ ከሚያሳይ ቪዲዮ ነው ቢቢሲ በኢራቅ የተፈጸመውን ጥቃት በተመለከተ ዘገባ ሰርቶ ነበር። ጥቃቱ በኤርትራ እንደደረሰ አድርጎ ካጋራው የፌስቡክ ገጽ ጋር ምን ያህል አንድ እንደሆነ አይቶ መረዳት ይቻላል።
news-55499520
https://www.bbc.com/amharic/news-55499520
ትራምፕ ለአሜሪካውያን 2 ሺህ ዶላር እንዲሰጥ ያቀረቡት ሃሳብ ውድቅ ሆነ
የዩናይትድ ስቴትስ ሴኔት የሪፐብሊካኖች መሪ የሆኑት ሚች ማክኮኔል ትራምፕ በኮሮናቫይረስ ምክንያት ኪሳቸው ለተጎዳ አሜሪካዊያን የሚሰጠው ገንዘብ ከፍ ይበል ሲሉ ያቀረቡትን ሃሳብ ውድቅ አደረጉ።
ከሌላው ጊዜ በተቃራኒ ኮንግረሽናል ዴሞክራቶችና አንዳንድ ሪፐብሊካን የትራምፕን ሃሳብ ደግፈው ድምፅ ሰጥተዋል። የአሜሪካ ሕዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ለአሜሪካዊያን በነብስ ወከፍ 2 ሺህ ዶላር ይሰጣቸው ብሎ አፅድቋል። ነገር በሪፐብሊካኖች የበላይነት የተያዘው የአሜሪካ የላይኛው ምክር [ሴኔት] ሃሳቡን ውድቅ አድርጎታል። የምክር ቤቱ የሪፐብሊካኖች መሪ ድጎማውን ወደ 2 ሺህ ከፍ ማድረግ 'ሌላ ዕዳ ውስጥ ነው የሚዘፍቀን' ብለዋል። ትራምፕ የአሜሪካ ምጣኔ ሃብት እንዲነቃቃ አያይዘው የጠየቁትም ገንዘብ ውድቅ ሆኖባቸዋል። ኮንግረሱ ከዚህ ቀደም በኮሮናቫይረስ ምክንያት ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው አሜሪካዊያን በነብስ ወከፍ 600 ዶላር እንዲሰጣቸው ወስኗል። ነገር ግን ፕሬዝደንት ትራምፕ ድጋፉ 2 ሺህ ዶላር ካልሆነ አልፈርምም ብለው ካንገራገሩ በኋላ ባለፈው እሁድ ፊርማቸውን አሳርፈዋል። ፕሬዝደንቱ ፊርማቸውን ያሳርፉ እንጂ ድጎማው ከለፍ ማለት አለበት የሚለውን ጥያቄያቸውን አላቋረጡም ነበር። ለወትሮም ከፕሬዝደንቱ ጋር ዓይንና ናጫ የሆኑት ዴሞክራት የሕዝብ እንደራሴዎች የትራምፕን ሃሳብ ደግፈው ድጎማው ወደ 2 ሺህ እንዲያድግ ሲሉ በአብላጫ ድምፅ አፅድቀው ነበር። ቢሆንም ትራምፕን ደግፈው በመናገር የሚታወቁት የላይኛው ምክር ቤት የሪፐብሊካኖች መሪ ሚች በዚህ ሃሳብ አልስማማም ሲሉ ተደምጠዋል። አሜሪካ ውስጥ በኮሮናቫይረስ ምክንያት የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከ3250 ሺህ በላይ ደርሷል። ከቀናት በፊት በተከበረው የፈረንጆቹ ገና እና በመጭው አዲስ ዓመት ሳቢያ ይህ ቁጥር የበለጠ ሊያሻቅብ ይችላል የሚል ፍራቻ አለ። አልፎም እጅግ በፍጥነት እየተላለፈ ነው የተባለለት አዲስ የኮሮናቫይረስ ዝርያ አሜሪካ ገብቷል። የዚህን ዝርያ መጀመሪያ ወደ አሜሪካ መግባት ይፋ ያደረገችው የኮሎራዶ ግዛት ናት። ካሊፎርኒያ ደግሞ ቫይረሱ እዚህም ታይቷል ብላለች። ሰውዬው ለምን ድጎማ ከፍ እንዲል አልፈለጉም? የኬንታኪ ሴናተር የሆኑት ሚች የዴሞክራቶችን ሃሳብ ውድቅ አድርገው አሜሪካዊያን 2 ሺህ ዶላር ሳይሆን 600 ዶላር ይሰጣቸው ብለዋል። "ምክረ ሃሳቡ ሴኔቱን አልፎ ይፀድቃል ብሎ ማሰብ ከባድ ነው" ብለዋል ሚች። በሕዝብ ተወካዮችና በሴኔቶች ፊት ንግግር ያደረጉት ሚች "ሰኔቱ በፍጥነት ገንዘብ ተበድሮ ይህን ድጎማ በማፅደቅ ለዴሞክራቶችና ለሃብታም ጓደኞቻቸው አይሰጥም" ብለዋል። በምትኩ ፕሬዝደንት ትራምፕ የጠየቋቸው ሌሎች ሃሳቦች እንዲፀድቁ የጠየቁት ሚች ከዴሚክራቶች መረረ ያለ ተቃውሞ ገጥሟቸዋል። አንደኛው ሃሳብ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎችን የሕግ ከለላ መንፈግ ሲሆን ሌላኛው ትራምፕ ምርጫው ተጭበርብሯል ሲሉ ያቀረቡት ያልተረጋገጠ ክስን የሚያጣራ ቡድን ማቋቋም ነው። ድጎማው ከፍ ይበል ሲሉ ድምፃቸውን የሰጡት 'ሊበራሉ' ሴናተር በርኒ ሳንደርስ "እኛ እየጠየቅን ያለነው ድምፅ እንድናገኝ ብቻ ነው። ምንድን ነው ችግሩ?" ሲሉ ተደምጠዋል። በሴኔቱ የዴሞክራቶች መሪ የሆኑት ቻክ ሹመር "መሪ ማክኮኔል ለአሜሪካውያን የ2 ሺህ ዶላር ቼክ ይሰጣቸው ብለን ያቀረብነውን ሃሳብ ሲገድሉብን እያየን ነው። ይህን ብር በርካታ ሚሊዮን አሜሪካውያን እጅግ ይፈልጉታል" ብለዋል። የሕዝብ እንደራሴዎችን አፈ ጉባዔዋ ናንሲ ፔሎሲ ደግሞ "እኚህ ሪፐብሊካኖች ሕዝቡ ሲያዝኑ እያዩ ዝም ማለት ይችሉበታል" ሲሉ አማረዋል። አንዳንድ ቀንደኛ የሚባሉ ሪፐብሊካኖችም የትራምፕን ሃሳብ ደግፈው ድጎማው ወደ 2 ሺህ ዶላር ከፍ እንዲል ጠይቀዋል። የአሜሪካ መንግሥት ለኤጎቼ ይሁን ያለው ድጎማ አንድ ጊዜ ከሚከፈል 600 ዶላር በተጨማሪ ለሥራ አጦች የሚሰጥና የቤት ኪራይ መክፈል ለተሳናቸው የሚሆን ነው።
news-51868474
https://www.bbc.com/amharic/news-51868474
ኮሮናቫይረስ ፡ በየደቂቃው በዓለም ዙሪያ ኮቪድ-19 የሚይዛቸውና የሚሞቱ ሰዎች ቁጥርን የሚያሳይ ካርታ
ከቻይናዋ ሁቤይ ግዛት ተነስቶ ሰው ከማይኖርበት አንታርክቲክ ውጪ ሁሉንም የዓለማችንን አህጉራትን ያዳረሰው የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ በአሁኑ ወቅት የምድራችን ዋነኛ የጤና ስጋት ሆኗል።
ኮቪድ-19 በመባል የሚታወቀው ይህ ወረርሽኝ የመተንፈሻ አካልን የሚያጠቃ ሲሆን፤ መጀመሪያ ትኩሳት ቀጥሎም ደረቅ ሳል ከሳምንት በኋላ ደግሞ የትንፋሽ ማጠርን ያስከትላል። እስካሁን በቫይረሱ ከ62 ሚሊዮን በላይ ሰዎች የተያዙ ሲሆን ከ1 ሚሊዮን 400 ሺህ በላይ የሚሆኑ ደግሞ ህይወታቸውን አጥተዋል። እስካሁን ባለው ሁኔታ ወረርሽኙን ለመቆጣጠር የሚያስችል ክትባትም ሆነ መድኃኒት አልተገኘም። በየደቂቃው በዓለም ዙሪያ ባሉ አገራት ውስጥ በኮቪድ-19 የሚያዙ፣ ከበሽታው የሚያገግሙና በቫይረሱ ምክንያት ለህልፈት የሚዳረጉ ሰዎችን አሃዝ ቀጥሎ ከተቀመጠው ዝርዝር ላይ ይመልከቱ። የኮሮናቫይረስ ምልክቶች ምንድናቸው? የኮሮናቫይረስ ሁለት ዋነኛ ምልክቶች ከፍተኛ ትኩሳትና ደረቅ ሳል ናቸው። በአንዳንድ ታማሚዎች ላይ እነዚህ ምልክቶች ወደ ትንፋሽ ማጠር ይወስዳሉ። ደረቅ ሳል ሲባል በጣም ጠንካራ የሆነ አንዳንድ ጊዜ ለአንድ ሰዓት የሚቆይ ነው። ከዚህ በፊት ደረቅ ሳል ካለብዎ የኮሮናቫይረስ ሳል በጣም ለየት ያለና ከባድ መሆኑን ማስተዋል ይችላሉ። ከፍተኛ ትኩሳት የሚባለው ደግሞ የሰውነት ሙቀት መጠን ከ37.8 ዲግሪ ሴልሲየስ ሲልቅ ነው። ይህ ትኩሳት ሰውነት እንዲግል ወይም ደግሞ ከፍተኛ ብርድና መንቀጥቀጥ እንዲሰማን ያደርጋል። ከእነዚህ ሁለቱ ዋነኛ ስሜቶች ባለፈ ራስ ምታትና ተቅማጥ አንዳንድ የበሽታው ታማሚዎች ያሳይዋቸው ምልክቶች ናቸው። የማሽተትና የመቅመስ አቅም ማጣትም ምልክቶች ሆነው ተመዝግበዋል። ምልክቶቹ ቫይረስ ሰውነት ውስጥ በገባ በአምስት ቀናት ሊታዩ ይችላሉ። የዓለም ጤና ድርጅት ዘገባ ምልክቶቹ እስከ 14 ቀናት ድረስ ሳይታዩ ሊቆዩ እንደሚችሉ ያስረዳል።
news-47944675
https://www.bbc.com/amharic/news-47944675
ዘንድሮ በዓለም ላይ የኩፍኝ ወረርሽኝ በሦስት እጥፍ ጨምሯል- የተባበሩት መንግሥታት
በዓለማችን ላይ በ2019 የመጀመሪያ ሦስት ወራት ብቻ የተመዘገቡ የኩፍኝ ሕሙማን ቁጥር ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወራት ጋር ሲነፃፀር በሦስት እጥፍ መጨመሩን የዓለም ጤና ድርጅት ተናገረ።
የዓለም አቀፉ የጤና ድርጅት መረጃዎች እንደሚያሳዩት "በአስደንጋጭ መልኩ እየተዛመተ" መሆኑን ነው ይህ የተባበሩት መንግሥታት አካል የሆነው ድርጅት እንዳስታወቀው ያሉት መረጃዎች መላው ዓለም የኩፍኝ ወረርሽኝ ሊያጋጥመው እንደሚችል የሚያሳዩ ናቸው። ወረርሽኙ በአፍሪካ በ700 በመቶ ጭማሪ ነው ያጋጠመው። • በኢትዮጵያ የኩፍኝ ክትባት ያልተከተቡ ህፃናት ቁጥር ከፍተኛ ነው • አለማችን የኩፍኝ ወረርሽኝ እንደሚያሰጋት አለም አቀፉ ጤና ድርጅት አስጠነቀቀ ድርጅቱ አክሎም ትክክለኛው የታማሚዎች ቁጥር ከዚህ ሊበልጥ ይችላል ሲል ስጋቱን አስቀምጧል፤ ለዚህም ምክንያት ብሎ ያቀረበው በዓለም ላይ ከ10 ታማሚዎች መካከል ሪፖርት የሚደረገው የአንዱ ብቻ መሆኑን ነው። ኩፍኝ ተላላፊ የሆነ በሽታ ሲሆን አንዳንድ ጊዜ ለከፋ የጤና ችግር ሊያጋልጥ ይችላል። በወረርሽኙ ክፉኛ ከተጠቁ ሃገራት መካከል ዩክሬን፣ ማዳጋስካር፣ እና ሕንድ ይገኙበታል። በማዳጋስካር ብቻ ከመስከረም ወር ጀምሮ 800 ሰዎች በኩፍኝ ምክንያት ሕይወታቸውን አጥተዋል። ወረርሽኙ ብራዚልን፣ ፓኪስታንና የመንንም "በርካታ ታዳጊ ሕፃናትን ለሞት በመዳረግ" አጥቅቷል። • እያነጋገረ ያለው የአማራ ክልል የቤተሰብ ዕቅድ ደብዳቤ በአሜሪካና በታይላንድ በከፍተኛ ቁጥር ክትባት የማዳረስ ሥራ እየተሠራ መሆኑ ተዘግቧል። የተባበሩት መንግሥታት በበኩሉ ኩፍኝ ተገቢውን ክትባት ከተሰጠ "ልንከላከለው የምንችለው" ወረርሽኝ ቢሆንም የክትባት መድኃኒት እጥረት አለ ብሏል። የዓለም ጤና ድርጅትን የሚያስተዳድሩት ቴዎድሮስ አድሃኖምና ባልደረባቸው ለሲኤን ኤን እንደተናገሩት ዓለም በኩፍኝ ወረርሽኝ ስጋት ውስጥ ናት፤ ለዚህም ስለ ክትባቱ እርስ በእርሳቸው የሚጋጩና የተሳሳቱ መረጃዎች የእራሳቸውን አስተዋፅዖ አድርገዋል ብለዋል።
55822126
https://www.bbc.com/amharic/55822126
ባይደን እና ፑቲን በስልክ ተወያዩ
ፕሬዝደንት ጆ ባይደን ከሩሲያው አቻቸው ቭላድሚር ፑቲን ጋር በነበራቸው የመጀመሪያ የስልክ ጥሪ በምርጫ ላይ ተጽእኖ መፍጠር ዙሪያ ላይ ማስጠንቀቂያ ሰጡ።
ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን እና ፕሬዝደንት ጆ ባይደን ሁለቱ መሪዎች በነበራቸው የመጀመሪያው የስልክ ውይይት በአሁኑ ወቅት በሩሲያ እየተካሄደ ስላለው መንግሥታዊ ተቃውሞ እና ስለ አሜሪካ-ሩሲያ ኒውክለር ስምምነት የተነሱ አጀንዳዎች እንደነበሩ የሩሲያ መንግሥት መግለጫ አመልክቷል። በመግለጫው እንደተገለጸው ሁለቱ መሪዎች ወደፊት ግንኙነታቸውን ለማስቀጠል ስለመስማማታቸው ተገልጿል። ጆ ባይደን ምክትል ፕሬዝደንት ሆነው ያገለገሉበት የኦባማ አስተዳድር፤ ክሬምሊን ክሬሚያን በኃይል ስትይዝ፣ ምስራቅ ዩክሬንን ስትወር እና በሶሪያ ጉዳይ ጣልቃ ስትገባ ማስቆም ባለመቻሉ ሲተች ቆይቷል። ሁለቱ መሪዎች ምን ተነጋገሩ? "ፕሬዝደንት ባይደን የአሜሪካን ብሔራዊ ፍላጎት እንዲሁም ከሩሲያ ጋር ያላትን ግነኙነት ሊጎዳ በሚችል ነገር ላይ አስተዳደራቸው ጠንካራ አጸፋዊ እርምጃ እንደሚወስድ አስታውቀዋል" ብሏል የባይደን አስተዳደር የሁለቱ አገራት መሪዎች ያደረጉትን ውይይት ተከትሎ ባወጣው መግለጫ። ውይይቱን በማስመልከት የሩሲያ ባለስልጣናት በበኩላቸው "ሩሲያ እና አሜሪካ ግነኙነታቸውን ማሻሻላቸው የሁለቱም አገራት ብሔራዊ ጥቅም የመከበር ፍላጎትን ያሳካል፤ ሁለቱ መሪዎች ግነኙነትን አሻሽሎ ለማስቀጠል እንዲሁም ለዓለም ደህንነት እና መረጋጋት ያላቸው ልዩ ኃላፊነት ላይ ከመግባባት ደርሰዋል" ይላል። በአጠቃላይ በሩሲያ እና አሜሪካ መሪዎች መካከል የነበረው የስልክ ውይይት "ግለጽ" ነበር ይላል የክሬምሊን መግለጫ። ሁለቱ አገራት በጦር ክምችታቸው ውስጥ በሚኖራቸው ሚሳኤል እና ሚሳኤል ማስተኮሻ ብዛት ላይ በኦባማ ዘመን ተደርሶ የነበረውን ስምምነት ዳግም ለማደስ መስማማታቸውም ተጠቅሷል። ፕሬዝደንት ትራምፕ ይህን ስምምነት ለማሰቀጠል ፍላጎት አልነበራቸውም። ባይደን ከክሬምሊን ጋር የተወያየቱ የአሜሪካ ሴኔት የአንቶኒ ብሊንከን የውጪ ጉዳይ ሚንስትርነት ሹመትን ባጸደቀበት ቀን ነው። አንቶኒ ብሊንከን ማይክ ፖምፔዮን እንዲተኩ በ78 ድጋፍ፣ በ22 ተቃውሞ ሹመታቸው ጸድቆላቸዋል። ባይደን ከሩሲያው መሪ ጋር ውይይት ካደረጉ በኋላ በዋይት ሃውስ በመገኘት በአሜሪካ የአስተዳደር ስርዓት ውስጥ የዘር መድሎ ያስቀራሉ ያሏቸውን ውሳኔዎችን አስተላልፈዋል። ፕሬዝደንት ባይደን የፍትሕ ቢሮው የግል ኩባንያዎች የፌደራል ማረሚያ ቤቶችን እንዲያስተዳድሩ የገባውን ውል እንዲሻሽል ትዕዛዝ አስተላለፈዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ምክትል ፕሬዝደንት ካማላ ሃሪስ የኮሮናቫይረስ ሁለተኛ ዙር ክትባት ወስደዋል። ካማላ በምርጫ ቅስቀሳቸው ወቅት በትራምፕ አስተዳደር ሥር ሊመረት የሚችል የኮቪድ ክትባት ውጤታማነት ላይ በሰጡት አስተያየት ተተችተው ነበር። ካማላ ሃሪስ የወሰዱት ሞደርና ሰራሹ ክትባት በትራምፕ አስተዳደር ለሕዝብ እንዲሰጥ ፍቃድ ያገኘ ክትባት ነው።
44299022
https://www.bbc.com/amharic/44299022
በሰሜን ሸዋ ዞን አንጎለላና ጠራ ወረዳ ሰርቲ ቀበሌ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ18 ሰዎች ህይወት አለፈ
አደጋው ለሐይማኖታዊ በዓል ጻድቃኔ ማሪያም ሄደው የነበሩ ምዕመናንን አሳፍሮ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ የነበረ የህዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ከአዲስ አበባ ወደ ደብረ ብርሀን ሲጓዝ ከነበረ ሚኒባስ ጋር በመጋጨቱ የደረሰ ነው።
በአደጋው ወዲያውኑ የ13 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ 5ቱ ሆስፒታል ከደረሱ በኋላ ህይወታቸው ማለፉን የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የሚዲያ አስተባባሪ የሆኑት ዋና ኢንስፔክተር መንገሻ አውራሪስ ለቢቢሲ ገልፀዋል። ከሟቾቹ መካከል አራቱ ሴቶች መሆናቸውን የአንጎለላ ጠራ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ የሆኑት ዋና ኢንስፔክተር ዳግም አጣለ ነግረውናል። አውቶቡሱ ዳገት እየወጣ ሚኒባሱ ደግሞ ቁልቁለት እየወረደ እንደነበር የተናገሩት ኢንስፔክተሩ በስፍራው ለአደጋ የሚያጋልጥ እይታን የሚከለክል ምንም ነገር እንዳልነበር አስረድተዋል። ነገር ግን አውቶቡሱ መንገዱን ለቆ በቀኝ መስመር መሄድ ሲገባው በግራ መስመር ላይ እየተጓዘ እንደነበር ተናግረዋል፤ በአደጋውም በሚኒባሱ ተሳፋሪዎች ሙሉ በሙሉ ህይወታቸው እንዳለፈም ጨምረው ገልፀዋል። አደጋው ትናንት ማክሰኞ ከቀኑ 10፡30 ላይ እንደደረሰ የገለፁት ዋና ኢንስፔክተር መንገሻ በበኩላቸው እስከ ምሽቱ 4፡00 ሰዓት ድርስ የአደጋው ተጎጂዎችን ለማውጣት መንገድ ተዘግቶ እንደነበር አስታውቀዋል። ኢንስፔክተሩ በክልሉ የሚደርሱ አብዛኞቹ የትራፊክ አደጋዎች ከፍጥነት ወሰን በላይ በማሽከርከር እንደሆነም ተናግረዋል። በክልሉ ለአደጋ አስጊ በሆኑ ቦታዎች አደጋዎች ሲከሰት አይታዩም የሚሉት ኢንስፔክተር መንገሻ አሽከርካሪዎች ከፍጥነት ወሰን በላይ ማሽከርከራቸው ለሚደርሱ አደጋዎች ከፍተኛውን ድርሻ ይይዛል ብለዋል። ኮሚሽኑ በክልሉ የሚደርሱ የትራፊክ አደጋዎችን ለመቀነስ ከተለያዩ አካላት ጋር እየሰራ እንደሆነ ጠቅሰው የፍጥነት መቆጣጠሪያ ራዳር እጥረት እንዳለባቸውም አመልክተዋል።
news-48332380
https://www.bbc.com/amharic/news-48332380
ጎግል፡ ሁዋዌ አንድሮይድን እንዳይጠቀም ገደብ ጣለ
ጎግል የስልክ አምራቹ ሁዋዌ ላይ የተወሰኑ የአንድሮይድ መተግበሪያዎችን መጠቀም እንዳይችል እገዳ ጣለ።
በዚህ ውሳኔ መሠረትም የተሻሻሉ የሁዋዌ ስማርት ስልኮች በርካቶች የሚጠቀሟቸውን የጎግል መተግበሪያዎችን መገልገል አይችሉም ማለት ነው። ይህ ውሳኔ የመጣው የትራምፕ አስተዳደር ሁዋዌን የአሜሪካ ኩባንያዎች ፈቃድ ካላገኙ በስተቀር አብረውት መስራት እንዳይችሉ በሚል ዝርዝር ውስጥ ስሙን ካሰፈረው በኋላ ነው። ጎግል ባወጣው መግለጫ "ጎግል የአስተዳደሩን ትዕዛዝ በመፈፀምና ያለውን ተፅእኖ በመገምገም ላይ ነው።" ብሏል። ሁዋዌ ግን በጉዳዩ ላይ አስተያየት ከመስጠት ተቆጥቧል። •አፕል ስልኮች በዝግታ እንዲሰሩ በማድረጉ ይቅርታ ጠየቀ • ዋትስአፕን በመጠቀም የስለላ መተግበሪያ ተጭኖ ነበር ተባለ ይህ ውሳኔ ለሁዋዌ ተጠቃሚዎች ምን ማለት ነው? ሁዋዌ ከዚህ በኋላ የጎግልን የደህንነት መጠበቂያ ማሻሻያዎችንና የቴክኒክ ድጋፍ አያገኝም። እንዲሁም አዳዲስ ምርቶቹ እንደ ዩ ቲዩብና ካርታዎች የመሳሰሉትን መተግበሪያዎች መጠቀም አይችሉም። አሁን የሁዋዌ ስማርት ስልኮችን እየተጠቀሙ ያሉ ግን መተግበሪያዎቻቸውን ማሻሻል እንዲሁም የጎግል ፕሌይ አገልግሎቶችን ማግኘት ይችላሉ። ነገር ግን ጎግል አዲስ የአንድሮይድ መተግበሪያ የሚለቅ ከሆነ ሁዋዌ በስልኮቹ ላይ መጠቀም እንዲችሉ ማድረግ አልተፈቀደለትም። በሙያው ላይ የተሰማሩ ባለሙያዎች "በሁዋዌ የደንበኞች አገልግሎት ላይ ትልቅ ተፅዕኖ ይኖረዋል" ሲሉ ስጋታቸውን ገልፀዋል። • ዋትስአፕ ሲጠቀሙ እንዴት ራስዎን ከጥቃት መከላከል እንደሚችሉ ያውቃሉ? ባለፈው ሳምንት የትራምፕ አስተዳደር ሁዋዌን ከአሜሪካ ተቋማት ጋር ካለ መንግሥት የፈቃድ አገልግሎት ማግኘት ከማይችሉ ድርጅቶች ዝርዝር ውስጥ ስሙን አስፍሮታል። የሁዋዌ ባለስልጣናት የድርጅታቸው ስም አገልግሎት ማግኘት ከማይችሉ ድርጅቶች ዝርዝር ውስጥ መግባቱን እንዳወቁ ለጃፓን መገናኛ ብዙኃን በሰጡት ቃለምልልስ "አስቀድመን ተዘጋጅተንበታል" ብለዋል። ሁዋዌ ከተለያዩ የምዕራብ ሀገራት የሁዋዌን ስልኮች ቻይና ለስለላ ትጠቀምባቸዋለች በሚል ጥያቄ እየተነሳበት ሲሆን ድርጅቱ ግን ክሱን አጣጥሎታል።
news-46894993
https://www.bbc.com/amharic/news-46894993
ኮማንድ ፖስቱ በምዕራብ ኢትዮጵያ 835 ታጣቂዎችን በቁጥጥር ስር አዋለ
በምዕራብ ኢትዮጵያ ታጥቀው የአካባቢውን ሰላም ሲያውኩ ነበሩ ያላቸውን 835 ታጣቂዎች በቁጥጥር ስር ማዋሉን የምዕራብ ኢትዮጵያ ኮማንድ ፖስት በዛሬው መግለጫው አስታውቋል።
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልልና በምዕራብ ኦሮሚያ አካባቢዎች የተከሰተውን ግጭት ለመከላከል የተቋቋመው ይህ ኮማንድ ፖስት ከአካባቢው ፖሊስ ከሚሊሻና ከዕቃግምጃ ቤት ተዘርፈው የነበሩ በርካታ ዘመናዊና የቆዩ የጦር መሳሪያዎች፤ መኪኖችና የተለያዩ እቃዎችን መያዙን አስታውቋል። •ኦነግ ከመንግሥት ጋር ያደረኩት ስምምነት አልተከበረም አለ •"ጫትን ማገድ ፈፅሞ የሚቻል አይደለም" ዶ/ር ዘሪሁን መሃመድ ሰላምን የማስፈን ስራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል፤ የሰላም እንቅፋት የሚሆኑ ግለሰቦችንም ህብረተሰቡ ለመንግሥትና ለኮማንድ ፖስቱ አስፈላጊውን ጥቆማ እንዲያደርግ ኮማንድ ፖስቱ አሳስቧል። ከሰሞኑም በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የግል ተቋማት ዝርፊያና የማቃጠል ሙከራዎችን በሚመለከት የተጋነነ መረጃ እየተሰጠ መሆኑን መግለጫው አትቶ ተዘረፉ የተባሉ ባንኮች ብዛት፣ የተዘረፈው የገንዘብ መጠንና የዘራፊዎቹን ማንነት በቀጣይ ለህዝቡ ግልፅ እንደሚያደርግ አስታውቋል። ከሰሞኑ በምዕራብ ኦሮሚያ ላይ የአየር ጥቃት ተደርጓል በሚል የወጣው መረጃም ሐሰት እንደሆነ ገልፆ ሄሊኮፕተሮቹ በተለያዩ ቦታዎች የተሰማራውን የሰራዊት ክፍል ለማገልገል፣ አመች ባልሆኑና ፈጣን አገልግሎት ለመስጠት እያገዙ እንደሆነ ጠቅሶ የሎጅስቲክ አቅርቦት ከመስጠት የዘለለ ለአየር ኃይል ውጊያ የሚያበቃ ነገር እንደሌለ አስታውቋል። "የአየር ኃይሉ በሂሊኮፕተር ሆነ በአውሮፕላን ተኩስ እንደከፈተ ነው የሚራገበው። ለዚህ የሚያበቃ የጠላት ኃይል ይቅርና ከመከላከያ አነስተኛ የእግረኛ ኃይል ጋር ፊት ለፊት የሚገጥም ፀረ-ሠላም ኃይል አልገጠመንም" ብሏል •"ትጥቅ ትግል ወደ ዴሞክራሲ አያመራም" አቶ ሌንጮ ለታ ኮማንድ ፖስቱ ጨምሮ ማህበረሰቡ የፀጥታ ኃይሉን በቅርበት እየደገፈ እንደሚገኝ አስታውቋል። በኮማንድ ፖስቱ በወንጀል ተጠርጥረው የተያዙ ሰዎችን በተመለከተ ከፌደራል የተላኩ አቃቢ ህግ እና መርማሪ ባለሙያዎች ወደ ቦታው እንደሄዱና ወደ ስራ ለመግባት የሚያስችላቸውን የቅድመ ሁኔታ ያጠናቀቁ በመሆኑ በቅርብ ጊዜ ስራ እንደሚጀምሩ በመግለጫው አስታውቋል፡፡
news-56555600
https://www.bbc.com/amharic/news-56555600
ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ ሸቀጦችን የጫኑ መርከቦች በሱዊዝ ቦይ መቆማቸው ተነገረ
ካለፈው ማክሰኞ ጠዋት ጀምሮ ለአንድ ሳምንት ለሚደርስ ጊዜ ተዘግቶ በቆየው የግብጹ ሱዊዝ መተላለፊያ ላይ ሁለት ወደ ኢትዮጵያ የሚመጣ ጭነት የያዙ መርከቦች መቆማቸውን የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አገልግሎት ድርጅት ገለጸ።
መርከቧን ለማንቀሳቀስ ጥረት በተደረገበት ጊዜ የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሮባ መገርሳ ለቢቢሲ እንደተናገሩት የተለያዩ ጭነቶችን ይዘው በሜዲትራኒያን ባሕር በኩል ወደ ጂቡቲ በማምራት ላይ የነበሩ መርከቦች መተላለፊያው በመዘጋቱ ጉዟቸው ተስተጓጉሏል። የሱዊዝ መተላላፊያ ቦይን ዘግታው የነበረችው ግዙፍ መርከብ ለመንቀሳቀስ እንዳትችል ካደረጋት የባሕር ዳርቻው አሸዋ ውስጥ የፊተኛ ክፍሏን ለቀናት በተደረገ ጥረት ዛሬ ለማውጣት ተችሎ አብዛኛው ክፍሏ በባሕሩ ላይ እየተንሳፈፈ በመሆኑ በጥቂት ሰዓታት ውስጥ መርከቦች ወደ መድረሻቸው መጓዝ ይጀምራሉ ተብሏል። ነገር ግን ከ350 በላይ ጭነት የያዙ መርከቦች በሁለቱም የመተላለፊያ መስመሩ ላይ ተሰልፈው በመጠባበቅ ላይ በመሆናቸው መርከቦቹን ተራ በተራ ማስተላለፍ እንደሚያስፈልግ ተነግሯል። የኢትዮጵያ ሁለቱ መርከቦች ጭነታቸውን ይዘው ወደ ሱዊዝ ቦይ የደረሱት ረቡዕና ሐሙስ ዕለት እንደሆነ የገለጹት አቶ ሮባ ቢያንስ ለአምስት ቀናት ባሉበት ለመቆም መገደዳቸውን ገልጸዋል። ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ ሸቀጦችን ከጫኑት ሁለት መርከቦች መካከል አንደኛው ንብረትነቱ የኢትዮጵያ ሲሆን ሌላኛው ደግሞ በኪራይ አገልግሎት የሚሰጥ የሌላ አገር መርከብ እንደሆነ ታውቋል። አሶሳ የተባለችው መርከብ ከቱርክ የጥቁር ባሕር የተለያዩ ሸቀጦችን የያዙ ኮንቴይነሮችን ጭነት በመያዝ እየተጓዘች የነበረ ሲሆን፣ ሌላኛዋ የኪራይ መርከብ ደግሞ ከሰሜን ምዕራብ የአፍሪካ ጫፍ ከምትገኘው ከሞሮኮ በሜዲትራኒያን ባሕር በኩል ማዳበሪያ ይዛ በመምጣት ላይ እንደነበረች ዋና ሥራ አስፈጻሚው ለቢቢሲ ገልጸዋል። መርከቦቹ የሚበላሽና ጊዜ የሚያልፍባቸው ሸቀጦችን እንዳልጫኑ የተናገሩት አቶ ሮባ መገርሳ ጭነቶቹን ለማራገፍ ከተያዘላቸው ጊዜ መዘግየት ውጪ ብዙም ችግር እንደማይገጥም ተናግረዋል። እንዲህ አይነቱ መዘግየት ደግሞ በባሕር መተላለፊያዎችና በወደቦች ላይ ወረፋ የመጠበቅ ሁኔታ ሲኖር የሚያጋጥም ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ወደ አገር ውስጥ የምታስገባው ነዳጅ በሱዊዝ ቦይ በኩል የሚያልፍ ባለመሆኑ በነዳጅ አቅርቦት ላይ እክል እንዳላጋጠመ የኢትዮጵያ የነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ለአገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን መግለጹ ይታወሳል። ኢትዮጵያ አብዛኛውን የነዳጅ ፍጆታዋን የምታገኘው ከመካከለኛው ምሥራቅ ከቀይ ባሕር ባሻገር ከሳዑዲ አረቢያ እና ከባሕረ ሰላጤዋ አገር ኩዌት ስለሆነ የሱዊዝ መተላለፊያ ላይ የተፈጠረው ችግር በአገሪቱ የነዳጅ አቅርቦትና ሥርጭት ላይ የሚፈጥረው ተጽእኖ እንደሌለ ተገልጿል። ኤቨር ጊቭን የተባለች ግዙፍ የጭነት መርከብ የጉዞ መስመሯን ስታ አግድም መተላላፊያውን በመዝጋቷ በዓለም ላይ በርካታ የንደግድ መርከቦች የሚተላለፉበትን ሱዊዝ ቦይን ዘግታ መቆየቷ ይታወሳል። በዚህም ሳቢያ ከ367 በላይ የጭነት መርከቦች ማለፊያ አጥተው በመተላለፊያው ሰሜናዊና ደቡባዊ መግቢያ ላይ በመቆማቸው በየቀኑ 9.6 ቢሊየን ዶላር የሚያወጡ ሸቀጦች ወደ መድረሻቸው ለመሄድ ሳይችሉ ለቀናት ተስተጓጉለዋል። አንዳንድ መርከቦችም ወደኋላቸው በመመለስ በደቡብ አፍሪካ በኩል ቀናት የሚፈጅ ጉዞን ለማድረግ መገደዳቸው ተነግሯል። የመተላላፊያ መስመሩ በመዘጋቱ ሳቢያ ከባሕረ ሰላጤው አገራትና ከመካከለኛው ምሥራቅ አካባቢ ወደ አውሮፓ የሚሄደው የነዳጅ አቅርቦት በመስተጓጎሉና ይህም ችግር ለሳምንታት ይዘልቃል ተብሎ ተሰግቶ ስለነበረ የነዳጅ ዋጋ ላይ ጭማሪን አስከትሏል። ባለቤቷ ጃፓናዊ የሆነውና 200 ሺህ ቶን የምትመዝነው ግዙፏ ኤቨር ጊቭን መርከብ ባለፈው ማክሰኞ የሱዊዝ መተላለፊያን የዘጋችው በአካባቢው በተከሰተ ከባድ አሸዋ አዘል አውሎ ነፋስ ሳቢያ መስመሯን ስታ የፊት ክፍሏ አሸዋ ውስጥ በመስመጡ ነበር። መርከቧ ጭነቷ ከባድ ከመሆኑ የተነሳ ከያዘችው መካከል 20 ሺህ ኮንቴይነር በማንሳት ክብደቷን ለመቀነስ እየተዘጋጁ ነበር። መርከቧን ከመተላለፊያው ለማንሳት የሳምንታት ሥራ ሊጠይቅ ይችላል ተብሎ ተሰግቶ ነበር። የመተላለፊያውን መከፈት ከሚጠብቁት ከ350 በላይ መርከቦች መካከል ጥቂቱ
news-50107235
https://www.bbc.com/amharic/news-50107235
ዛሬ በመቀሌ ሊካሄድ የነበረ ሠላማዊ ሰልፍ በፖሊስ ተበተነ
'ህድሪ ሰብ' በተባለ ማህበር ዛሬ ቅዳሜ መቀሌ ከተማ ውስጥ ሊካሄድ ተጠርቶ የነበረው ሠላማዊ ሰልፍ ህጋዊ አይደለም ተብሎ በፖሊስ ተበተነ።
ይህ ሠላማዊ ሰልፍ የተጠራው የትግራይ ክልል የከፍተኛ የትምህርት ተቋም ተማሪዎች ችግር ያጋጥማቸዋል ወደተባሉ ቦታዎች እንዲሄዱ እንዳይደረግ በክልሉ መንግሥት ላይ ግፊት ለማድረግ እንደነበረ ተነግሯል። ሠላማዊ ሰልፉን የጠራው ማህበር ሊቀ መንበር መሃሪ ዮሐንስ ለቢቢሲ እንደተናገሩት ስለሰልፉ ለማሳወቅ ለመቀሌ ከተማ ከንቲባ ጸሐፊ ደብዳቤ ማስገባታቸውንና ግልባጩንም ለዞኑ ፖሊስ ለማስገባት ሙከራ ባደረጉበት ወቅት አንቀበልም መባላቸውን ተናግረዋል። • በመቀሌ ከተማ ፆታዊ ጥቃትን በመቃወም ሊደረግ የነበረው ሰልፍ ተከለከለ • የትግራይ ክልል አዲስ ገቢ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ወደ አማራ ክልል አንደማይልክ አስታወቀ ሊቀ መንበሩ በተጨማሪ ሠላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ መንግሥት ሁኔታዎችን እንዲያመቻች ማሳወቅ እንጂ የመፍቀድና የመከልከል ህጋዊ መብት የለውም ብለዋል። ዛሬ ጠዋት ሠላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ ሮማናት ተብሎ በሚጠራው የመቀሌ ከተማ አደባባይ መሰባሰብ በጀመሩበት ጊዜ ፖሊሶች ወደ ስፍራው መጥተው ሰልፉ ህጋዊ ስላልሆነ በመግለጽ እንዲያስቆሙ መታዘዛቸውን በመግለጽ ሰልፈኞቹ እንዲበተኑ ማድረጋቸውን የሰልፉ አስተባባሪዎች ተናግረዋል። አስተባባሪዎቹም ከፖሊስ ጋር ግብግብ መፍጠር ተገቢ ባለመሆኑ ሰልፉን ለማካሄድ ለሁለተኛ ጊዜ ለፖሊስ የማሳወቂያ ደብዳቤ እንደሚያስገቡ ተናግረዋል። • "ሰልፍ የዜጎች መሰረታዊ መብት ነው" መስፍን ነጋሽ • ተማሪዎች በተመደቡበት ዩኒቨርስቲ ብቻ ነው መማር የሚችሉት- የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የመቀሌ ከተማ ምክትል ከንቲባ ስለተከለከለው ሠላማዊ ሰልፍ ተጠይቀው "ሰልፉ ሊከለከል አይገባም። ቢሆንም የጸጥታውን ሥራ በተመለከተ ማን ተጠይቆ ምን መልስ ተሰጠ? የሚሉትን ጥያቄዎች መመለስ ይገባል" ብለዋል። የሠላማዊ ሰልፍ ማሳወቂያ ደብዳቤውን ተቀብሎ ወደሚመለከተው አካል ያላቀረበ ግለሰብ ካለ እንቀጣለን" ያሉት አቶ አቶ ብርሐነ፤ ለፖሊስ ቀርቦ ነበር የሚለው ቅሬታን ተከትሎ ፖሊስ የመከልከል መብት ስለሌለው ተቀባይነት እንደሌለው ገልጸዋል። ሠላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ተጠይቆ ሲከለከል በዚህ ሳምንት ውስጥ ይህ ለሁለተኛ ጊዜ ሲሆን፤ ከቀናት በፊት በሴቶች ላይ የሚፈጸም ጾታዊ ጥቃትን ለማውገዝ በተመሳሳይ መቀሌ ውስጥ ሠላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ጥያቄ ቀርቦ እንደተከለከለ መዘገባችን ይታወሳል።
44843674
https://www.bbc.com/amharic/44843674
ኤርትራዊያን ሊያዩ የሚሿቸው አምስት ለውጦች
በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ሰላም ወርዷል፤ የሁለቱ ሃገራት ፍቅርም እየጠነከረ መጥቷል። በጦርነት እና ሰላም እጦት ሲቆራቆዙ የከረሙት ሁለቱ ሃገራት ወደ ሰላም መድረክ በመጡበት በዚህ ጊዜ ኤርትራውያን በርካታ ጉዳዮች ተለውጠው ማየትን ይሻሉ።
የኤርትራው ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ በሃገራቸው ለሚታየው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸው አለመስማማት ዋነኛ ምክንያት እንደሆነ ሲያቀርቡ ቆይተዋል። ኤርትራ ለ20 ዓመታት ያክል ባልተቋረጠ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ውስጥ ከርማለች፤ በተለይ ደግሞ ከድንበር ጦርነቱ በኋላ። አሁን ላይ ግን ነገሮች እየተቀየሩ ይመስላሉ። • የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ አዲስ አበባ ገቡ • ስለ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ምን ያህል ያውቃሉ? ሐምሌ 01/2010 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ ታሪክ ሰሩ፤ ከ20 ዓመታት በኋላ አሥመራን በመጎብኘት የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ መሆንም ቻሉ። ይህን ተከትሎም ሁለቱ ሃገራት በዲፕሎማሲውም ሆነ በምጣኔ ሃብት ዘርፍ ተባብረው ለመሥራት ስምምነት ላይ ደርሰዋል። ሐምሌ 07/2010 ዓ.ም ሌላ ታሪክ፤ ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ ከ20 ዓመታት በኋላ አዲስ አበባን ረገጡ። ታዲያ እነዚህ ሁሉ በአጭር ጊዜ ይሆናሉ ተብለው ያልተጠበቁ ክስተቶች እውን እየሆኑ ባሉበት በዚህ ወቅት ኤርትራውያንን ሰቅዞ የያዘ አንድ ጉዳይ አለ፤ የሁለቱ ሃገራት ስምምነት ለኤርትራ ምን ትርፍ ይኖረዋል የሚል። ተንታኞች በኤርትራ ቢያንስ አምስት ጉዳዮች ለውጥ ይሻሉ ይላሉ። ሕገ-መንግሥት ኤርትራ ነፃ ከወጣች ብዙም ጊዜ ሳይሆናት ነው የሕገ-መንግሥት ኮሚሽን በማቋቋም አዳዲስ ሕግጋትን ማርቀቅ የጀመረቸው። ከሦስት ዓመታት በኋላም ሕገ-መንግሥቱ ለሃገሪቱ ብሔራዊ ጉባዔ ቀረበ፣ ከዓመት በኋላ የድንበር ጦርነቱ ተነሳ፤ ሕገ-መንግሥቱም በእንጥልጥል ቀረ። በ1992 ዓ.ም የአልጀርሱ ስምምነት በሚፈርምበት ወቅት ሚኒስትሮች፣ ወታደራዊ አመራሮችና አንዳንድ ባለሥልጣናት ሕገ-መንግሥቱ መተግበር እንዲጀምር ጠየቁ። • ወደ አሥመራ ለመጓዝ ማወቅ የሚገባዎ 6 ነጥቦች • የፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ አቀባበል በፎቶ ነገር ግን የኤርትራ መንግሥት ጥያቄያቸውን ችላ አለው፤ አልፎም ይህን ጥያቄ ካነሱት መካከል 11 ሰዎች የገቡበት ጠፋ። ኤርትራ እስከዛሬ ድረስ ሕገ-መንግሥት የላትም። ለ25 ዓመታት ኤርትራን የገዙት ኢሳያስ አፈወርቂም 'የሕግ ያለህ' የሚላቸው ሕግ ሳይኖራቸው ዘለቁ። የኤርትራ ነገርም ምርጫ የለ፤ የሥልጣን ገደብ የለ፤ ሕገ-መንግሥት ሆነ። ሕገ-መንግሥት ወይም በትግርኛው አጠራር 'ቅዋም' ለኤርትራ ሕዝብ ቀዳሚ ቦታ የሚሰጠው ጉዳይ መሆኑ ግን አልቀረም። ሕገ-መንግሥቱ ተግባራዊ ሆነ ማለት ፓርቲዎች በነፃ የሚንቀሳቀሱባት እና ነፃ ምርጫ የሚካሄድባት ሃገረ ኤርትራ እውን ትሆናልች ማለት ነውና። ነፃ መገናኛ ብዙሃን ወርሃ መስከረም 1993 ላይ የኤርትራ መንግሥት ሁሉም በግል የሚተዳደሩ ጋዜጦች የሕገ-መንግሥት ትግበራንና ዴሞክራሲያዊ ሽግግርን በርዕስነት በማንሳታቸው እንዲዘጉ ወሰነ። ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች ጥበቃ ኮሚቴ (ሲፒጄ) ቢያንስ 10 ጋዜጠኞች በወቅቱ ለእሥር እንደተዳረጉ መዘገቡ ይታወሳል። ሰቲት፣ ዘመን፣ ቀስተ-ደበና፣ ፂጌና፣ መቃልህ እና አድማስ የተባሉ ጋዜጦች ድጋሚ ገበያ ላይ እንዳይታዩ ከተፈረደባቸው መካከል ነበሩ። • ፕሬዝዳንት ኢሳያስ የኢትዯጵያና የኤርትራ ሕዝቦች አንድ ናቸው አሉ • "ኢትዮጵያና ኤርትራን የሚለያቸው የለም" ኢሳያስ አፈወርቂ አሁን ላይ ኤርትራ ውስጥ አገልግሎት እየሰጡ ያሉ መገናኛ ብዙሃን ሁሉም በመንግሥት የሚተዳደሩ ናቸው። የኤርትራ ቴሌቪዥን፣ ራድዮ ድምፂ ሓፋሽ እና በትግርኛ፣ አረብኛ፣ እንግሊዝኛና ትግረ ቋንቋዎች የሚሰራጩ ጋዜጦች ገበያውን ያለተቀናቃኝ ተቆጣጥረውታል። የሰብዓዊ መብት አያያዝ ተመልክቶ ከሚወጡ ዘገባዎች አብዛኛዎቹ ኤርትራን በነፃ መገናኛ ብዙሃን ረገድ 'ጨቋኟ' ሃገር ሲሉ ይጠሯታል። 'የአፍሪቃ ሰሜን ኮሪያ' በሚል ቅፅል ስም በማጀብ። ኤርትራውያን ይህ ስም ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ተፍቆ ማየት ይሻሉ። የሃይማኖት ነፃነት ኤርትራ ውስጥ እውቅና የተሰጣቸው አራት ሃይማኖቶች ብቻ ናቸው፤ የኦርቶዶክስ ክርስትና፣ የሱኒ እስልምና፣ የሮማ ካቶሊክ ቤተ-ክርስትያን እና የኤርትራ ኢንቫጄሊካል-ሉቴራን ቤተ-እምነት። ከእነዚህ ውጭ ያሉት ሕገ-ወጥ ናቸው ተብሎ ስለሚታሰብ አማኞች ለክስ የተጋለጡ ናቸው። የሃይማኖት ነፃነት ላይ የሚሠራ አንድ የአሜሪካ ድርጅት ኤርትራ ውስጥ በሺዎች የሚቆጠሩ በሃይማኖታቸው ምክንያት ለእሥር እንደተዳረጉ የዘገበው በቅርቡ ነበር። የጄሆቫ ምስክሮችን ማደን የተጀረመው ኤርትራ ነፃ በወጣች ማግስት ሲሆን፤ ዋነኛ ምክንያት የነበረው ደግሞ ለኤርትራ ነፃነት ድምፃችንን አንሰጥም ማለታቸው ነበር። በምድራዊ ፖለቲካ እና ብሔራዊ አገልግሎት ላይ ለመሳተፍ ካላቸው ቁጥብነት በመነሳት የእምነቱ ተከታዮች ዜግነት፣ የመኖሪያ መታወቂያ ካርድ እና የሥራ ፈቃድ አይሰጣቸውም። ይህም ጉዳይ ሌላው ኤርትራዊያን ተቀይሮ ሊያዩት የሚሹት መብት ነው። የብሔራዊ አገልግሎት ፍፃሜ ብሔራዊ አገልግሎት ኤርትራ ውስጥ ተግባራዊ መሆን የጀመረው ከ1987 ጀምሮ ነው። መባቻው ላይ ሁሉም ዜጎች ለ18 ወራት ብሔራዊ አገልግሎት ይሰጡ ዘንድ ታዘዘ፤ የ6 ወራት ወታደራዊ ሥልጠናን ጨምሮ። ከ1994 ጀምሮ ግን የአገልግሎት ጊዜው ገደብ አልባ እንዲሆን ተደረገ። ወጣት ኤርትራዊያን 11ኛ ክፍልን እንዳጠናቀቁ ወደሳዋ የማቅናት ግዴታ አለባቸው። እዚያም 12ኛ ይጨርሱና ወታደራዊ ሥልጠናውን ይቀላቀላሉ፤ መቼ እንደሚጨርሱ ግን ይፋ የሆነ ቀነ-ገደብ አልተቀመጠላቸውም፤ አንዳንዶችም ለዓመታት ያገለግላሉ። በወታደራዊ ሕግጋት ሥር የሚቆዩት እኚህ ወጣቶች እንቅስቃሴያቸውም የተገደበ ነው። ብሔራዊ አገልግሎት አንድ ሰሞን ለኤርትራዊያን የኩራት ምንጭ ነበር፤ አሁን ግን በርካታ ወጣቶች ሃገሪቱን ጥለው ይሸሹ ዘንድ ምክንያት ሆኗል። የፖለቲካ እሥረኞችን መፈታት መቀመጫቸውን አውሮፓ እና ሰሜን አሜሪካ ያደረጉ ኤርትራዊያን እንደሚስማሙት ኤርትራ ውስጥ ለውጥ መታየት የሚጀምረው የፖለቲካ እሥረኞች ሲፈቱ እንደሆነ ነው። የዚሁ ጉዳይ አንደምታ እስከ ብሔራዊ የጋራ መግባባት ድረስ ሊያደርስ እንደሚችል በርካቶች ያምናሉ። ጂ-15 ተብለው ስለሚጠሩት የፖለቲካ እሥረኞች ብዙ የተባለ ሲሆን ስማቸው ያልገነነ ሺዎች አሁንም ከፍርግርጉ ጀርባ ይገኛሉ። እሥር ቤቶቹም ደረጃቸው እጅጉን የወረደ ተብለው ሲብጥለጠሉ ይሰማል። እሥረኞችን መፍታት ለኤርትራ ለውጥ ትልቅ ማሳያ ተደርጎ የሚወሰደውም ለዚህ ነው።
news-56121976
https://www.bbc.com/amharic/news-56121976
ኢራናዊው የጁዶ ስፖርት ተወዳዳሪ በእስራኤል
ከእስራኤላዊ ተወዳዳሪ ጋር እንዳይፎካከር የተሰጠውን ትዕዛዝ ችላ ብሎ ከተወዳደረ በኋላ ወደ ኢራን ለመመለስ ፈቃደኛ ያልነበረው ኢራናዊው የጁዶ ተወዳዳሪ ለውድድር እስራኤል ገባ፡፡
በጎርጎሮሳዊያኑ 2019 በጃፓን በተካሄደው የጁዶ ዓለም ሻምፒዮና ላይ የተከሰተውን ትዕይንት ተከትሎ ሳኢድ ሞላኤ ለሕይወቴ እሰጋለሁ ማለቱ ይታወሳል። ከክስተቱ በኋላ እስራኤልን እንደ ጠላት የምትቆጥረው ኢራን በዓለም አቀፉ የጁዶ ፌዴሬሽን (አይ ጄ ኤፍ) ታገዳለች፡፡ ተወዳዳሪው በቴል አቪቭ ጨዋታዎች ላይ መገኘቱን "ታሪካዊ" ሲሉ የእስራኤል መገናኛ ብዙሃን ገልጸውታል፡፡ ሳኢድ በቴል አቪቭ ለሁለት ቀናት በሚቆየው ውድድር ላይ ሞንጎሊያን ይወክላል፡፡ ሳኢድ እሁድ እስራኤል ደርሷል። በቶኪዮው ውድድር ኢራን ከእስራኤላዊው የጁዶ ተወዳዳሪ ሳጊ ሙኪ ጋር ነበር ሳኢድ እንዳይወዳደር ያገደችው። ሙኪ ሁለቱ ተወዳዳሪዎች ተቃቅፈው ያሉበትን ፎቶ በማህበራዊ ድራምባዎች "እንኳን ደህና መጣህ ወንድም ዓለም" ከሚል መልዕክት ጋር አስፍሯል። ሁለቱ ስፖርተኞች በቴል አቪቭ ጨዋታዎች ሊጋጠሙ የሚችሉበት ዕድል አለ። "ይህ ለዓለም ትልቅ መልዕክት ነው፡፡ ይህ ኢራንን ወደ እስራኤል ይበልጥ ሊያቀርባት የሚችል ነገር ነው። ስፖርት በቀላሉ ሰዎችን እንዴት እንደሚያገናኝ እና ድንበር እንደሚሰብር ያሳያል" ሲል ሙኪ ለእስራኤል ራዲዮ ተናግሯል፡፡ የእስራኤል ስፖርት 1 ድረ-ገጽ ጉዳዩን "ታሪካዊ" ብሎ በመነሻ ገጹ አስፍሮታል። በእስራኤል በጣም ታዋቂ ከሆኑ የዜና አውታሮች አንዱ የሆነው ኔት ደግሞ ሳኢድን በቴላቪቭ ለመወዳደር በመወሰኑ "ደፋር" እና "ጀግና" ሲል ገልጾታል፡፡ የቶኪዮ ጨዋታዎች መጠናቀቅን ተከትሎ ጀርመን ያቀናው ኢራናዊው የጥገኝነት መብት የተሰጠው ሲሆን ከጎርጎሮሳዊያኑ መጋቢት 2020 ጀምሮ በዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ሞንጎሊያን ወክሎ እንዲወዳደር ተፈቅዶለታል፡፡ ቀደም ሲል ወደ ኢራን ከተመለሰ "በቤተሰቦቼ እና በራሴ ላይ ምን ሊሆን ሳስብ እንደሚችል እፈራለሁ" ብሏል፡፡ ኢራን በቴል አቪቭ በሚካሄደው ውድድር መሳተፉን ለሚገልጸው ዜና በንቀት መልሳለች፡፡ "ይህ ክብር አይደለም። እስከመጨረሻው ከእርሱ ጋር የሚቆየው በግንባሩ ላይ የተጻፈ የውርደት እድፍ ነው። ምክንያቱም ጀርባውን ለትውልድ አገሩ እሳቤዎች ላይ አዙሯል " ብለዋል የኢራን የጁዶ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አራሽ ሚሬስማኤሊ፡፡ ኢራን የሳኢድን ውንጀላ "የሐሰት ጥያቄዎች" ናቸው ብላ በመጥቀስ ለዓለም አቀፉ የጁዶ ፌደሬሽን ይግባኝ ብላለች፡፡ የኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ የእስራኤልን ህልውና የማይቀበል ሲሆን እና ስፖርተኞቹም በዓለም አቀፍ ውድድሮች የእስራኤል ተፎካካሪዎቻቸውን እንዳይገጥሙ ታዘዋል፡፡
news-44601782
https://www.bbc.com/amharic/news-44601782
በእናቱ ኢትዮጵያዊ የሆነው ግለሰብ በእንግሊዝ በሽብር ተጠርጥሮ ተያዘ
በእንግሊዝ ዌስትሚኒስትር ውስጥ የሽብር ጥቃት ለመፈጸም ሲያቅድ የነበረና ለታሊባን ፈንጂዎችን ሲሰራ የነበር አንድ እንግሊዛዊ የቧንቧ ሰራተኛ ፍርዱን እየተጠባበቀ ነው።
ካሊድ አሊ የ28 ዓመት ወጣት ሲሆን፤ በሚያዚያ 2017 ዓ.ም ሶስት የስለት መሳሪያዎችን ይዞ በቁጥጥር ስር ውሏል። ክሱን የሚከታተሉት ዓቃቤ ህጎች እንደሚሉት ካሊድ አሊ ፖለቲከኞችን፤ ፖሊሶችንና ሰላማዊ ሰዎችን ለመግደል እቅድ ነበረው ብለዋል። ካሊድ ከፖሊስ ጋር በነበረው ቃለ ምልልስ ለእንግሊዝ ባለስልጣናት መልዕክት ማስተላለፍ ፈልጎ እንደሆነና በቁጥጥር ስር ሲውል ይዟቸው የነበሩት የስለት መሳሪያዎች ግን የራሱን ደህንነት ለመጠበቅ እንደሆነ ገልጿል። በመጪው ሃምሌ ለፍርድ የሚቀርበው ካሊድ በእናቱ ኢትዮጵያዊ በአባቱ ሶማሊያዊ ሲሆን ላለፉት አራት ዓመታት ፖሊስ እያንዳንዱ እንቅስቃሴውን ሲከታተለው ነበር። ቤተሰቦቹ በ1992 ወደ እንደግሊዝ የመጡ ሲሆን፤ ስምንት ልጆችን ወልደዋል። ካሊድ ኤድመንተን ከተማ ውስጥ አድጎ የጋዝ ምህንድስና እና የቧንቧ ስራ አጥንቷል። ከቅርብ አመታት ወዲህ ግን በሃይማኖት እና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ማተኮር እንደጀመረ ተገልጿል። ኢትዮጵያዊት እናቱ ባለፈው ዓመት በመኝታ ቤቱ ውስጥ አራት የስለት መሳሪያዎች እንዳገኘች ለፖሊስ ተናግራ ነበር። ካሊድ አሊ በ2011 ወደ አፍጋኒስታን የተጓዘ ሲሆን፤ ለአምስት ዓመታት ቦንብ ሲሰራ እንደነበር ተገልጿል። በ2016 ቱርክ ውስጥ የሚገኘው የእንግሊዝ ኤምባሲ ውስጥ ተገኝቶ ፓስፖርቱ ስለጠፋበት ጊዜያዊ የጉዞ ሰነድ እንዲዘጋጅለት ጠይቆ ነበር። ወደ ሃገሩ እንግሊዝ በዛኑ ዓመት ሲመለስም በሄትሮው አየር ማረፊያ በፖሊስ ተይዞ ጥያቄ ተደርጎለታል። በዚያኑ ወቅት የጣት አሻራውና የዘረመል ናሙናው በፖሊስ ተይዞ ነበር። ናሙናው ለአሜሪካው የወንጀል ምርመራ ቢሮ 'ኤፍ ቢ አይ' ተላልፎ የተሰጠ ሲሆን፤ በናሙናው መሰረት አፍጋኒስታን ውስጥ በተሰሩ 42 ተቀጣጣይ ፈንጂዎች ላይ የካሊድ የጣት አሻራ ተገኝቷል። በቁጥጥር ስር ከዋለ በኋላ ካሊድ አፍጋኒስታን በነረው ቆይታ የእንግሊዝ ወታደሮችን ሲዋጋ እንደነበር ገልጿል። ከ300 መቶ በላይ ፈንጂዎችን ደግሞ በእጁ ሰርቶ እንዳበረከተ ገልጿል።
news-53713057
https://www.bbc.com/amharic/news-53713057
አፍጋኒስታን፡ ምክር ቤቱ 400 የታሊባን እስረኞችን ለመፍታት ወሰነ
የአፍጋኒስታን ከፍተኛ ምክር ቤት ከባድ ወንጀሎችን በመፈፀም ተከሰው የነበሩ 400 የታሊባን እስረኞችን ለመፍታት የቀረበውን ሃሳብ አፀደቀ።
ሎያ ጂርጋ ተብሎ የሚጠራው ምክር ቤት ውሳኔው የተላለፈው የሰላም ድርድር እንዲጀመር ለማስቻል እንደሆነ አስታውቋል። አሜሪካ በአገሪቷ ያለው ወታደሮቿ ቁጥር በመጭው ሕዳር ወር ከ5 ሺህ በታች እንደሚሆን ካስታወቀች በኋላ ታሊባን በአፍጋኒስታንና በውጭ ዜጎች ላይ ጥቃት መፈፀምን ጨምሮ በሌሎች ወንጀሎች የተከሰሱ እስረኞቹ እንዲፈቱለት ሲጠይቅ ነበር። በዚህ ዓመት መጀመሪያ ላይም አሜሪካና ታሊባን ለ19 ዓመታት የዘለቀውን ግጭት ለመፍታት የሰላም ስምምነት ለማካሄድ መስማማታቸው ይታወሳል። የአሜሪካና የታሊባን አደራዳረዎችም ከአፍጋኒስታን መንግሥት ጋር ወደሚያደርጉት የሰላም ድርድር ከመግባታቸው በፊት 5 ሺህ የታሊባን እስረኞች እንዲፈቱ ተስማምተው ነበር። በዚህም መሠረት በሺዎች የሚቆጠሩ እስረኞች የተፈቱ ሲሆን የቀሩት 400 እስረኞች ብቻ ነበሩ። ከእነዚህ መካከል 150 የሚሆኑት የሞት ፍርድ የሚጠባባቁ መሆናቸውን ኤኤፍፒ ዘግቧል። ምክር ቤቱም እነዚህ እስረኞች እንዲፈቱ የወሰነው "የሚደረገውን የሰላም ስምምነት ሂደት ለመጀመርና እንቅፋቶቹን ለማስወገድ እንዲሁም ደም መፋሰሱን ለማስቆም" እንደሆነ ገልጿል። ውሳኔውም በፕሬዚደንት አሽራፍ ጋኒም ይፈረማል ተብሏል። በመንግሥትና በታሊባን መካከል የሚደረገው ድርድርም በሚቀጥለው ሳምንት ዶሃ እንደሚጀመር አንድ የምዕራቡ ዓለም ዲፕሎማት ለሮይተርስ የዜና ወኪል ተናግረዋል። ይሁን እንጅ የእስረኞቹ መፈታት ጉዳይ በነዋሪዎችና በሰብዓዊ መብት ተሟጋች ቡድኖች ዘንድ አወዛጋቢ ሆኗል። በሁለቱ ወገኖች መካከል ላለፉት 19 ዓመታት በዘለቀው ጦርነት ከ32 ሺህ በላይ ንፁሃን ዜጎች መሞታቸውን ባለፈው ዓመት የካቲት ወር ላይ የወጣ የተባበሩት መንግሥታት ሪፖርት አመልክቷል። ፕሬዚደንት አሽራፍ ጋኒም ከጎርጎሳውያኑ 2014 ጀምሮ ከ45 ሺህ በላይ የፀጥታ ኃይል አባላት መገደላቸውን በዚያው ዓመት ተናግረዋል። ታሊባን ከ19 ዓመታት በፊት ከሥልጣን የተወገደው የመስከረም አንዱን ጥቃት ተከትሎ በአሜሪካ በተመራ ወረራ ሲሆን ቡድኑ ከየትኛውም ጊዜ በበለጠ አሁን ላይ ተጨማሪ ግዛቶችን ለመቆጣጠር ቀስ በቀስ የቀድሞ ጥንካሬውን አግኝቷል። ቅዳሜ ዕለት የአሜሪካው መከላከያ ሚኒስትር ማርክ ቲ ኤስፐር በአፍጋኒስታን የሚኖራቸው ወታደሮች ቁጥር በመጭው ህዳር ወር ከ5 ሺህ ዝቅ እንደሚል ተናግረዋል። ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕም ህዳር ወር ላይ ከሚካሄደው ፕሬዚደንታዊ ምርጫ በፊት የወታደሮቹን ቁጥር ወደ 4 ሺህ ዝቅ ማድረግ እንደሚፈልጉ የተናገሩት ባለፈው ሳምንት ነበር።
52059441
https://www.bbc.com/amharic/52059441
ኮሮናቫይረስ፡ ኮቪድ-19ን ለመከላከል የኢትዮጵያ ዝግጁነት ምን ይመስላል?
በኢትዮጵያ የመጀመሪያው በኮቪድ-19 [ኮሮናቫይረስ] ተያዘ ሰው ከተገኘ በኋላ የተለያዩ የመከላከል እርምጃዎችን ስትወስድ ቆይታለች። ከእነዚህም መካከል ከባህር ማዶ ለሚመጡ መንገዶኞች ለ14 ቀናት በተዘጋጁ ሆቴሎች ውስጥ በራሳቸው ወጪ እንዲቆዩ መመሪያ አስተላልፋለች።
ይህንንም ተከትሎ በስካይ ላይት ሆቴል ያረፉና ስማቸው እንዳይገለፅ ያልፈለጉ አንድ ግለሰብ ስላሉበት ሁኔታ ለቢቢሲ አጋርተዋል። ከአውሮፓ በናይሮቢ በኩል አድርገው ከመጡ ጥቂት ቀናት እንዳለፋቸው የሚናገሩት እኚህ ግለሰብ ወደ ኢትዮጵያ ለመምጣት አውሮፕላን ከመሳፈራቸው በፊት 1630 ዩሮ እንዲከፍሉ ተጠይቀው መክፈላቸውን ይናገራሉ። • በየደቂቃው በኮሮናቫይረስ የሚያዙና የሚሞቱ ሰዎች ቁጥርን የሚያሳይ ካርታ በወቅቱ ከእርሳቸው ጋር የነበሩ መንገደኞችም ሆኑ እርሳቸው ሌሎች ረከስ የሚሉ ሆቴሎች ስለመዘጋጀታቸው እንዳልተነገራቸው የገለፁት ግለሰቧ ስካይ ላይት ሆቴል ውድ መሆኑን ገልጸዋል። ግለሰቧ እንደሚሉት ምንም እንኳ ቫይረሱን ለመከላከል ከአካላዊ ንክኪ መራቅ አንዱ መንገድ ቢሆንም ኢትዮጵያ ውስጥ ቦሌ አየር ማረፊያ በደረሱበት ወቅት በርካታ ሰዎች ተጠጋግተው ይታዩ እንደነበር ያስታውሳሉ። በሆቴሉ የከፈሉት ምግብን ጨምሮ መሆኑን የሚናገሩት ግለሰቧ ከክፍላቸው መውጣት ስለማይቻል በሆቴሉ ውስጥ ምን ያህል እንግዳ መኖሩን ለማወቅ እንዳልቻሉ ለቢቢሲ ገልፀዋል። በየዕለቱም የጤና ባለሙያዎች እየመጡ ናሙና እንደሚወስዱ ተናግረው፣ የሆቴሉ አስተዳደር በርካታ ሰው በመኖሩ ሆቴሉ መጨናነቁን እንደነገራቸው ለቢቢሲ ተናግረዋል። ኮቪድ-19ን ለመከላከል የኢትዮጵያ ዝግጁነት በሚመለከት በቢቢሲ የተጠየቁት በጤና ጥበቃ ሚኒስትር የሕክምና አገልግሎቶች ዳይሬክተር ጄነራል የሆኑት አቶ ያዕቆብ ሰማን፤ ሲመልሱ ከባህር ማዶ ለሚመጡ ሰዎች ለለይቶ ማቆያነት እንዲያገለግሉ ተብሎ ስምንት ሆቴሎችና የተወሰኑ ትምህርት ቤቶች ተመርጠው መዘጋጀታቸውን ገልፀዋል። እነዚህ ስፍራዎች 5ሺህ ሰው የመያዝ አቅም አላቸው ያሉት አቶ ያዕቆብ፤ በሚቀጥሉት ሳምንታት ማቆያዎቹ እስከ 21 ሺህ ሰዎች የመያዝ አቅም እንዲኖራቸው እንደሚደረግ ለቢቢሲ ገልፀዋል። የቫይረሱ ምልክትን ለሚያሳዩ እና ቫይርሱ ካለበት ሰው ጋር ንክኪ እንዳለባቸው ለሚጠረጥሩ ሰዎች ደግሞ የተዘጋጁ 1ሺህ 200 አልጋዎች መኖራቸውን ጨምረው ያስረዳሉ። በቫይረሱ ምክንያት ከባድና መካከለኛ ምልክቶች ለሚያሳዩ የተዘጋጁ 343 ለመተንፈስ የሚረዱ (ሜካኒካል ቬንትሌተሮች) መሳሪያዎች የተዘጋጁ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ 301 በደንብ እንደሚሰሩ ተረጋግጧል ብለዋል። 19 ለመተንፈስ የሚረዱ (ሜካኒካል ቬንትሌተሮች) መሳሪያዎች በአዲስ አበባ ከፍተኛ ተጋላጭነት አለው ተብሎ በተለየ ስፍራ ዝግጁ ሆነው እንደሚጠባበቁ የሚናገሩት ዳይሬክተሩ፤ አንድ መሳሪያ ደግሞ ወደ ሐረር ተልኳል ሲሉ ገልጸዋል። አቶ ያዕቆብ አዲስ የተገዙ ለመተንፈስ የሚረዱ መሳሪያዎች መኖራቸውን ገልፀው፤ አዲስ ከተገዙት ሜካኒካል ቬንትሌተሮች መካከል አስራ አንዱ አዲስ አበባ በሚገኘው ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል ገብተው ከአልጋ ጋር ተገጥመው ለአገልግሎት ዝግጁ ሆነዋል ሲሉ ለቢቢሲ አረጋግጠዋል። ስምንቱ ደግሞ እንዲሁ አዲስ አበባ በሚገኘው ቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ገብተው ተገጥመዋል በማለት ከአዳዲሶቹ ቬንትሌተሮች ወደክልል የተላከው አንድ ብቻ ሲሆን እርሱም በሐረር ከተማ ወደሚገኘው ሕይወት ፋና ሆስፒታል ነው ብለዋል። "የሌሎችን አገራት ተሞክሮ ስናየው የት ቦታ በብዛት አንደሚከሰት መገመት አይቻልም። ስለዚህ እስካሁን ድረስ እያጠናን፤ እየሰራን ነበር። ነገር ግን እኛ ከሌሎች የበለጠ የመጋለጥ አደጋ አለው ብለን የወሰድነው አዲስ አበባን ነው" በማለት "ግን ደግሞ እንደ ጣልያን ከትንሽ ከተማ እንዲሁም ከክልል ሊጀምር ይችላል" ብለዋል አቶ ያዕቆብ ከቢቢሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ። ሆኖም ክልሎች በሙሉ የህክምና ማዕከል እያቋቋሙ አንደሆኑ እና በቅርቡ ያጠናቅቃሉ ብለው እንደሚጠብቁም አቶ ያዕቆብ አመልክተዋል። ከዚህም በተጨማሪ መንግሥት የ1500 ተጨማሪ ሜካኒካል ቬንትሌተሮችን ግዥ ከቻይና ለመፈፀም ውሳኔ ላይ መድረሱንና ቬንትሌተሮቹ በሒደት በሚቀጥለው ወር ውስጥ ይመጣሉ ተብለው እንደሚጠበቁም ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ እስካሁን ድረስ ኮቪድ-19 የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 16 መድረሱ ይታወቃል።
news-56471329
https://www.bbc.com/amharic/news-56471329
ጠ/ሚ ዐቢይ በትግራይ የሰብዓዊ መብት ጥሰት የፈፀሙ እንደሚጠየቁ ገለፁ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ትግራይ ውስጥ ከተካሄደው ዘመቻ ጋር ተያይዞ ተፈጸሙ የተባሉት በደሎች "የተጋነኑ ቢሆኑም" የሰብዓዊ መብት ጥሰት ተፈጽሟል አሉ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ ማክሰኞ፣ በተወካዮች ምክር ቤት ቀርበው በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ማብራርያ በሰጡበት ወቅት እንደተናገሩት፣ ትግራይ ውስጥ የሰብአዊ መብት ጥሰትና በደሎች መፈጸማቸውን የሚያመለክቱ መረጃዎች መኖራቸውን ጠቅሰው መንግሥታቸው የድርጊቱ ፈጻሚዎች ላይ እርምጃ ይወስዳል ብለዋል። "እኛ ወታደሩን የላክነው ወንጀለኞችን እንዲቆጣጠር እንጂ እንዲደፍር አይደለም። በዚህ ወንጀል የተሰማራ ወታደር ካለ በሕግ ተጠያቂ ይደረጋል" ብለዋል። ነገር ግን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በትግራይ ክልል ውስጥ ተፈጸሙ የተባሉትን የመብት ጥሰቶች በተመለከተ "ከፍተኛ ግነት እና ፕሮፖጋንዳ አለ" በማለት "የሚጋነነውን ነገር እንዳለ ሆኖ በትግራይ ክልል የሰብዓዊ መብት ጥሰት ተፈጽሟል" በማለት "የተፈጸመው ጥፋት አንድ እንኳን ቢሆን ተጠያቂነት ይኖራል" ሲሉ ተናግረዋል። ከዚህ አንጻር ከአገር መከላከያ ሠራዊት አመራሮች ጋር ግምገማ ማድረጋቸውን የጠቀሱት ጠቅላእ ሚኒስትር ዐብይ "እንዲጠብቃቸው የተሰማራውን ሴቶች የደፈረና ሌላ ጉዳት ያደረሰ ማንኛውም ኃይል ተጠያቂ ይሆናል" ብለዋል። የኤርትራ ሠራዊት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ከምክር ቤቱ አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች መልስና ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ከትግራይ ክልል ግጭት ጋር ተያይዞ በተደጋጋሚ ሲነሳ ለነበረው የኤርትራ ሠራዊት ተሳትፎ ምላሽ ሰጥተዋል። በዚህም የኤርትራ ሠራዊት በድንበር አካባቢ "የደኅንነት ስጋት እንዳለበት" ገልጾ በዚያው አካባቢ ሠራዊቱ እንዳለ ያስረዱት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ፣ ለዚህም ምክንያቱ በኢትዮጵያ ሠራዊት ላይ በህወሓት የተፈጸመው ጥቃት እንደሆነ ተናግረዋል። ጨምረውም የኢትዮጵያ ሠራዊት ከጀርባው ጥቃት እየተፈጸመበት የድንበር አካባቢውን መጠበቅ አስቸጋሪ ስለሆነበት የህወሓት ኃይሎችን ለመዋጋት ወደ ሌሎች የትግራይ አካባቢዎች በመንቀሳቀሱ ክፍተት እንደተፈጠረና የኤርትራ መንግሥትም በዚህ ክፍተት ጥቃት እንዳይፈጸምበት በመስጋቱ ወደ ስፍራዎቹ መግባቱን ገልጸዋል። ነገር ግን ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኤርትራ ሠራዊት በየትኞቹ የኢትዮጵያ አካባቢዎች እንደሚገኝ አልተናገሩም። ቢሆንም ግን የኢትዮጵያ ሠራዊት ሌላውን ተልዕኮ ሲያጠናቅቅና አካባቢዎቹን መቆጣጠር ሲችል በቀጣዩ ቀን የኤርትራ ኃይሎች ከስፍራው እንደሚወጡ ተናግረዋል። ትግራይ ውስጥ በኤርትራ ሠራዊት ተፈጸሙ ከተባሉ ግድያዎችና የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ጋር በተያያዘ አሜሪካንና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትን ጨምሮ የተለያዩ አገራትና ዓለም አቀፍ ተቋማት ሠራዊቱ ከክልሉ እንዲወጣ በተደጋጋሚ ሲተይቁ ቆይተዋል። "የኤርትራ መንግሥት ለሚያቀርበው የደኅንነት ስጋት ዋስትና መስጠት አንችልም" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ "ምክንያቱም ከኋላ የሚወጋን ኃይል አለ" ሲሉ ተናግረዋል። በተለያዩ ዓለም አቀፍ የመብት ተሟጋቾችና ድርጅቶች በተደጋጋሚ በሚወጡ ሪፖርቶች ላይ የኤርትራ ሠራዊት በትግራይ ክልል ውስጥ አስከፊ የሰብአዊ መብት ጥሰት፣ ግድያና ዘረፋዎችን መፈጸሙ ሲገለጽ መቆየቱ አይዘነጋም። ከዚሁ ጋር በተያያዘ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የኤርትራ ወታደሮች የኢትዮጵያን ድንበር አልፈው የሚያደርሱትን ጥፋቶች መንግሥታቸው ፈጽሞ አይቀበለውም ብለዋል። ይህንን በሚመለከት ከኤርትራ መንግሥት ጋር መነጋገራቸውን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ የኤርትራ መንግሥት ወታደሮቹ አደረሱት ስለሚባለው በደሎችና ዘረፋን በተመለከተ ጥፋቱን በሚፈጽሙ ወታደሮቹ ላይ እርምጃ እንደሚወስድ መግለጹን ተናግረዋል። ቀደም ሲል የኢትዮጵያም ሆነ የኤርትራ መንግሥት የኤርትራ ሠራዊት በኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ ስለመገኘቱ የሚወጡ ሪፖርቶችን ሲያስተባብሉ እንደነበር ይታወሳል። በጥቅምት ወር መጨረሻ ላይ ቀውሱ በተከሰተበት ጊዜ ከኤርትራ በኩል ስለተደረገላቸው ድጋፍ የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ "የመከላከያ ሠራዊት ክህደት በተፈጸመበት በወቅት የኤርትራና ሕዝብ እና መንግሥት ድጋፍ ሰጥቷል" በማለት በዚህም የኤርትራ መንግሥት "የምን ጊዜም የኢትዮጵያ ባለውለታ ነው" በማለት አመስግነዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም የኤርትራ መንግሥት፣ የኤርትራ ዕጣ ፈንታ ከኢትዮጵያ እና ከትግራይ ሕዝብ ጋር የተሳሰሰረ መሆኑን እንደሚያምን ገልፀዋል። ሰብአዊ እርዳታ በትግራይ ክልል በተካሄደው ጦርነት ወቅት በርካታ መሠረተ ልማቶች መውደማቸውን የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን መልሶ ለመገንባት መንግሥት ከአንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ ማውጣቱን ተናግረዋል። አክለውም በግጭቱ ምክንያት ተፈናቅለው የሰብዓዊ እርዳታ ጠባቂ ለሆኑ 4.2 ሚሊዮን ለሚደርሱ ሰዎች ከ92 በላይ የእርዳታ መስጫ ጣብያዎች መንግሥት ከፍቶ እርዳታ እያረበ መሆኑን ገልጸዋል። ከዚሁ ጋር በማያያዝም በርካታ የውጭ እርዳታ ሰጪዎች ክልሉ ላልተገደበ የተራድኦ አቅርቦት ክፍት ይሁን ሲሉ የቆዩ ቢሆንም ከተከፈተ በኋላ ግን ገብተዉ እርዳታ እየሰጡ አለመሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አንስተዋል። የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ግጭቱ ከተቀሰቀሰ በኋላ በትግራይ ክልል 30 ሺህ የሚደርሱ እስረኞች ሆን ተብሎ መፈታታቸውን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከእነዚህ መካከል 10 ሺህ የሚሆኑት በመቀሌ ውስጥ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። የመከላከያ ሠራዊት የተለያዩ የትግራይ ከተሞችን ከተቆጣጠረ በኋላ በአንዳንድ ያልተደራጁ ግለሰቦች ጥቃቶች እንደተጸጸመበት ያስታወሱት ጠቅላይ ሚኒስተሩ ይህንን ተከትሎ በተፈጠረ ቁጣ የተከሰቱ ችግሮች አሉ ብለዋል። በክልሉ በተደረገው "የሕግ ማስከበር ዘመቻ" ወቅት የተለያዩ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ያቀረቧቸው ጥቃቶችና በደሎች መፈፀማቸውን የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ይህንንም ከመከላከያ ከፍተኛ ኃላፊዎች ጋር በመሆን መገምገማቸውን ተናግረዋል። ከአገር መከላከያ ሠራዊት አባል ሆኖ በትግራይ ውስጥ የመድፈርና የዘረፋ ወንጀል የፈፀመ "ማንኛውመ ወታደር በሕግ ይጠየቃል" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ "ጀግኖችን እንሸልማለን ጥፋተኞችን በሕግ እንጠይቃለን" ብለዋል። ኦነግ-ሸኔ በአንዳንድ የአገሪቱ አካባቢዎች በሰላማዊ ሰዎች ላይ ከሚፈጸሙ ጥቃቶችና ግጭቶች ጋር በተያያዘ ስሙ የሚነሳው ኦነግ-ሸኔ የተባለውን ታጣቂ ኃይል ጠቅላይ ሚኒስትሩ "የሰው ጠላት ነው" በማለት ከማንም በላይ በርካታ ኦሮሞዎችን ገድሏል ብለዋል። "ኦነግ-ሸኔ እየገደለ ያለው አማራን ብቻ አይደለም፤ ኦነግ-ሸኔ ከሁሉም በላይ የገደለው አሮሞን ነው።" ቡድኑን የህወሓት ተላላኪ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ "ቡድኑ ሰው የሚድገል የሰው ጠላት እንጂ ብሔርን ለይቶ ብቻ የሚገድል አይደለም" ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም በትግራይ "የሕግ ማስከበር እርምጃ በተወሰደበት ወቅት 300 የሚደርሱ የኦነግ-ሸኔ አባላት ሲሰለጥኑ ተገኝተዋል" ብለዋል። በዚህ ዓመት ለሁለተኛ ጊዜ ወደ ምክር ቤቱ የቀረቡበት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ፤ በዛሬው የምር ቤቱ ስብሰባ በአገሪቱ የ10 ዓመት የልማት ዕቅድ ላይ እንዲሁም በተለያዩ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ከተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች መልስና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
52989991
https://www.bbc.com/amharic/52989991
የስዊድኑን ጠቅላይ ሚኒስትር የገደላቸው ማን እንደነበር ይፋ ሆነ
ይህ በዓለም ላይ ምስጢር ሆነው ከቆዩ እጅግ አስገራሚ ግድያዎች አንዱ የሆነው የሲዊዲኑ ጠቅላይ ሚንስትር የግድያ ወንጀል አንዱ ነው፡፡
በአመዛኙ በስዊድናዊያን ዘንድ ተወዳጅና እጅግ አወዛጋቢ ጠቅላይ ሚኒስትር የነበሩት ኦሉፍ ፓልማ የተገደሉት እንደ አውሮጳዊያኑ በ1986 ነበር፡፡ ከ34 ዓመት በኋላ ፖሊስ ገዳያቸው ማን እንደሆነ አውቂያለሁ ብሏል፤ ዛሬ። ነፍሰ ገዳዩ ሰው ስቲግ ኢንግስትሮም የሚባል ሰው ሲሆን አሁን በሕይወት የለም፡፡ ራሱን በገዛ እጁ ያጠፋውም በ2000 ዓ. ም ነበር፡፡ ይህ ሰው በቅጽል ስሙ "ስካንዲያ ማን" ይባል የነበረው ሲሆን በሕይወት ሳለ ፖሊስ ጠርጥሮ አስሮት ነበር፡፡ ዋና አቃቢ ሕግ ክሪስተር ፒተርሰን ዛሬ ከደቂቃዎች በፊት ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት ስዊድንን ለ34 ዓመታት ሰቅዞ የያዛት ጉዳይ እነሆ ፍጻሜውን አግኝቷል፡፡ የሚገርመው ገዳዩ በዚያ ዘመን ሰውየው ሲገደሉ አይቻለሁ ብሎ ምስክርነት ሰጥቶ ነበር። የያኔው ጠቅላይ ሚኒስትር ፓልማ የተገደሉት ከባለቤታቸው ጋር በሕዝብ ሲኒማ ቤት ገብተው ፊልም አይተው ሲወጡ በጎዳና ላይ ነበር፡፡ ፓልማ አጀብና የፖሊስ ጥበቃ የማይፈልጉና እንደ ተራ ዜጋ በጎዳና ይንቀሳቀሱ የነበሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ነበሩ፡፡ ሰውየውን የገደላቸው ጥቁር ኮት ያደረገ የስካንዲኒቪያን መልክና ገጽታ የነበረው ረዥም ሰውዬ እንደነበር ግድያውን አጠናቆ ሲሄድ የተመለከቱት ቢያንስ 20 ሰዎች መስክረው ነበር፡፡ በ34 ዓመታት ውስጥ ከ10ሺህ ሰዎች በላይ ከግድያው ጋር በተያያዘ በፖሊስ ሲመረመሩ ነበር፡፡ ገዳዩ ማን ነበር? ስቲግ ኢንግስትሮም ወይም በቅጽል ስሙ ስካንዲያ ተብሎ የሚጠራው ግለሰብ አዲስ ተጠርጣሪ አይደለም። ይህ ቅጽል ስም የተሰጠው ደግሞ ይሰራበት የነበረው መሥሪያ ቤት ስሙ ስካንዲያ ስለሚባል ነበር፡፡ ስካንዲያ ኢንሹራን ኩባንያ የሚገኘው ደግሞ ጠ/ሚኒስትሩ ከተገደሉበት ጎዳና አቅራቢያ ነው፡፡ ያቺ ጠ/ሚኒስትሩ የተገደሉባት አርብ ምሽት ላይ እሱ በዚህ መሥሪያ ቤት ውስጥ አምሽቶ ይሰራ እንደነበር ፖሊስ ደርሶበታል፡፡ ይህ ሰው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሲገደሉ ባይኔ በብረቱ አይቻለሁ ብለው በገዛ ፈቃዳቸው ለፖሊስ ምስክርነት ከሰጡ 20 ሰዎች መካከል አንዱ ነው፡፡ በመጨረሻም ራሱን በገዛ እጁ ያጠፋው በ2000 ዓ. ም በፈረንጆች ነበር፡፡ ይህ ሰው ጠቅላይ ሚኒስትሩን ሳይገድላቸው አልቀረም ብሎ መጀመርያ የጠረጠረው ቶማስ ፒተርሰን የተባለ ጋዜጠኛ ነበር፡፡ በኋላም ፖሊስ ምርመራ ጀምሮበት ነበር፡፡ ምርመራው ተጠናክሮ የቀጠለው ግን ሰውየው ራሱን ካጠፋ ከ18 ዓመታት በኋላ ነው፡፡ ይህ ሰው ጠቅላይ ሚኒስትሩን የገደላቸው ግራ ዘመም አመለካከታቸውን አይወድላቸው ስለነበረ ነው ተብሏል፡፡ ጋዜጠኛው ይህን ሰው ሊጠረጥር ያስቻለው ምስክር በሰጠበት ወቅት ወደ ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር የቀረብኩት ነፍሳቸው ካልወጣች ልረዳቸው ፈልጌ ነው ሲል መዋሸቱን ተከትሎ ነበር፡፡ ፖሊስ ይህን ተከትሎ ባደረገው ምርመራ ደግሞ ሰውየው የጦር መሣሪያ አተኳኮስ ልምምድ ማድረጉን ደርሶበት ነበር፡፡ ከገዳዩ ጋር በትዳር የኖረችውና በኋላም ፍቺ የጠየቀችው ሴት በ2018 ፖሊስ ጠርቶ እንደመረመራት ለስዊድን ጋዜጣ ተናግራ ነበር፡፡ ገዳዩ እሱ ይሆናል ብለሽ ትገምቻለሽ ወይ ተብላ ተጠይቃ የነበረችው የቀድሞው ባለቤቱ፣ እረ እሱ በጣም 'ቦቅቧቃ ነው'፤ ዝምብ እንኳ የመግደል ድፍረት ያለው ሰው አይደለም" ስትል ተናግራ ነበር፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትር ፓልማ ግድያ ዙርያ በመቶዎች የሚቆጠሩ ፊልሞች፣ መጻሕፍትና የመድረክ ሥራዎች የቀረቡ ሲሆን በስዊድን አገር ለሦሰት ዐሥርታት እጅግ አነጋጋሪ ጉዳይ ሆኖ ዘልቋል፡፡ የቀድመው ጠቅላይ ሚኒስትር ኦሉፍ ፓልማን ያስገደሏቸው የደቡብ አፍሪካ አፓርታይድ ሥርዓት ባለሥልጣናት ናቸው የሚል ጠንካራ እምነት ነበር፡፡ ምክንያቱም ፓልማ የማንዴላና የኤኤንሲ ደጋፊ ነበሩና ነው። በኚህ ጠቅላይ ሚኒስትር ዙርያ ዘለግ ያለ ንባብ ይህንን ማስፈንጠሪያ ነክተው ያገኛሉ፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ባለቤት ወ/ሮ ሊዝቤት ፓልማ የሞቱት ከ2 ዓመት በፊት የባለቤታቸውን ገዳይ ሳያውቁ ነው፡፡ ባለቤታቸው በተገደሉበት ምሽት ግን አብረዋቸው ነበሩ፡፡ ይህ ለ34 ዓመታት ሚስጥር ሆኖ ስለቆየው ታሪክ ተጨማሪ ለማንበብ፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ማን እንደገደላቸው ከ34 ዓመታት በኋላ ይፋ ሊሆን ነው
47539621
https://www.bbc.com/amharic/47539621
እንግሊዝ ቦይንግን ከበረራ ካገዱት ሃገራት ተቀላቀለች
የእንግሊዝ ሲቪል አቪዬሽን መሥሪያ ቤት የቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላኖችን ለጥንቃቄ ከበረራ አገደ።
ለጊዜው የሲልክኤር 6 ማክስ 8 አውሮፕላኖች ከበረራ ታግደዋል ይህን እንዲወስኑ ያደረጋቸውም በኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ ማክስ 8 አውሮፕላንን መከስከስ ተከትሎ፤ በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ሁለተኛው የቦይንግ አውሮፕላን በመሆኑና የ157 ሰዎች ሕይወት በመጥፋቱ ነው። አውሮፕላኑን ከበረራ በማገድ እንግሊዝ ማሌዥያን፣ ሲንጋፖርን፣ ቻይናንና አውስትራሊያን ተቀላቅላለች። የሃገሪቱ ሲቪል አቪዬሽን መሥሪያ ቤት ላልተወሰነ ጊዜ እገዳው እንደሚቀጥል አሳውቋዋል። ትዊ የተሰኘው አየር መንገድና የኖርዌይ አየር መንገድ ሁለቱም የቦይንግ ማክስ 8 አውሮፕላን ተጠቃሚዎች ናቸው። "የእንግሊዝ ሲቪል አቪዬሽን መሥሪያ ቤት ነገሮችን ከቅርብ ሲቆጣጠር የነበረ ሲሆን ለጊዜው ከመረጃ ሳጥኑ በቂ መረጃ ባለመገኘቱ ለጥንቃቄ ሲባል አውሮፕላኖቹን ከማብረርም ሆነ በእንግሊዝ ከባቢ አየር እንዳይበሩ አግደናል" የሚል መግለጫ ሰጥተዋል። የትዊ አየር መንገድ መግለጫ ያሏቸውን የቦይንግ ማክስ 8 አውሮፕላኖች እንዳገዱ ይነግራል። "ከእረፍት የሚመለሱ ተሳፋሪዎች በሙሉ በሌላ አውሮፕላን እንዲመለሱ አድርገናል" ያለው ሲቪል አቪየሽኑ ወደ እረፍት ለሚሄዱ ተሳፋሪዎቻቸውም ይህንኑ እንዳመቻቹ አሳውቀዋል። የኖርዌይ አየር መንገድም የዚህን አውሮፕላን በረራዎች በሙሉ ማገዱንና በተሳፋሪዎች ዘንድ ለተፈጠረው ችግር በሙሉ ይቅርታ ጠይቋል። ቦይንግ 737 ማክስ 8 ሞዴል በ 6 ወር ጊዜ ውስጥ ሁለቴ የመከስከስ አደጋ ቢያጋጥበውም የአሜሪካ የፌደራል አየር መንገድ አስተዳደር ግን አውሮፕላኑ ለመብረር ብቁ ነው ሲል ማረጋገጫ ሰጥቷል። ከአዲስ አበባ ተነስቶ ወደ ኬንያ በመብረር ላይ የነበረው ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሆነው ቦይንግ 737 ማክስ 8 አውሮፕላን ካኮበኮበ ከ6 ደቂቃዎች በኋላ ባጋጠመው የመከስከስ አደጋ 157 ሰዎች ህይወታቸው ማለፉ ይታወሳል። • "የሞተው የኔ ያሬድ ነው ብዬ አላሰብኩም" የካፕቴን ያሬድ የ11 አመት ጓደኛ • ኢትዮጵያ አየር መንገድ ዛሬም ስኬታማ ነው አደጋው በጥቅምት ወር ተከስክሶ የ189 ሰዎች ህይወት የቀጠፈው የላየን ኤር 737 ማክስ 8 ቀጥሎ ሁለተኛው ነው። አንዳንድ አየርመንገዶች የአውሮፕላኑን ሞዴል ፕሌኖቻቸውን ምርመራው እስኪጠናቀቅ ድረስ እንዳይበሩ አስጠንቅቀዋል። ነገር ግን ሰኞ ማምሻ ላይ የአሜሪካው ፌደራል አየርመንገድ አስተዳደር መስሪያ ቤት አውሮፕላኑ ለበብረር ብቁ ነው፤ ምንም የደህንነት ስጋት የለበትም ብሏል። ቻይና፥ ኢንዶኔዥያና ኢትዮጵያ ሰኞ ዕለት ተመሳሳይ ሞዴል አውሮፕላኖቻቸውን እንዳይበሩ አዘዋል። የአርጀንቲናው ኤሮላይነስ፥ የሜክሲኮው ኤሮሜክስኮ እና የብራዚል ጎል አየር ምንገዶችም በተመሳሳይ ሞዴል ፕሌኖች የሚደረጉ በረራዎችን አቋርጠዋል። ማክሰኞ የሲንጋፖር ሲቪል አቬሽን ባለስልጣናት "ሁሉንም የተለያዩ የቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን ሞዴሎች ወደ ሲንጋፖር እና ከሲንጋፖር ወደ ሌላ ቦታ እንዳይበሩ በጊዜያዊነት ከልክለናል" ብለዋል። እገዳው ከምሸት 3 ሰአት ጀምሮ ይተገበራል። ቦይንግ ሞዴሉ ለመብረር አስተማማኝ ነው ካለ በኋላ ሌሎች አየርመንገዶች ቦይንግ 737 ማክስ 8 ማብረርን ቀጥለዋል። ከአደጋው በኋላ የቦይንግ አለማቀፍ የገበያ ድርሻ 12.9 በመቶ መውረዱ ተሰምቷል። ስለአደጋው እስካሁን የምናውቀው • 149 መንገደኞችንና 8 የበረራ ሰራተኞችን አሳፍሮ ይጓዝ የነበረው ET 302 ቦይንግ 737 ማክስ 8 አውሮፕላን ከጠዋቱ 2፡38 ከቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ተነሳ። • ከ6 ደቂቃ በኋላ ከአብራሪዎቹ ጋር ይደረግ የነበረው ግንኙነት ተቋርጦ ቢሾፍቱ አካባቢ አውሮፕላኑ የመከስከስ አደጋ አጋጠመው። • የአውሮፕላኑ አብራሪ ችግር ስላጋጠመው ወደ አዲስ አበባ ለመመለስ ጠይቆ እንዲመለስ ተነግሮት እንደነበር ታውቋል። • ለ60 ዓመታት የዘለቀው የኢትዮጵያ አየር መንገድና የቦይንግ ግንኙነት • ቦይንግ 737 ማክስ 8 ከአራት ወራት በፊት የተገዛ ሲሆን የኢትዮጵያ አየር መንገድ የዚህ አይነት ስድስት አውሮፕላኖች አሉት። • አውሮፕላኑ እሁድ ጠዋት ከጆሃንስበርግ በረራው ሲመለስ ምንም አይነት የበረራ ችግርን የሚመለከት መረጃ እንዳልነበርና ከሶስት ሰዓት በላይም መሬት ላይ ቆይቶ እንደነበር ተገልጿል። • ዋና አብራሪው ያሬድ ሙልጌታ ከ 8 ሺህ ሰዓት በላያ ያበረረ ፓይለት ሲሆን ረዳት አብራሪው አህመድ ኑር ሞሃመድ ደግሞ 2 መቶ ሰዓት ያበረረ ፓይለት እንደሆነ ታውቋል።
news-49706007
https://www.bbc.com/amharic/news-49706007
አሜሪካ ሳዑዲ ላይ ለተፈጸመው ጥቃት ኢራንን ተጠያቂ አደረገች
የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊው ማይክ ፖምፔዮ ቅዳሜ ዕለት የሳዑዲ ነዳጅ ማውጫ ተቋማት ላይ ለተሰነዘረው የድሮን ጥቃት ኢራንን ተጠያቂ አድርገዋል።
የሁቲ አማጺያን ትናንት ሳዑዲ ላይ ለተፈጸመው ጥቃት ኃላፊነቱን እንወስዳለን ቢሉም ማይክ ፖምፔዮ ግን አጣጥለውታል። የሳዑዲ አረቢያ የሃይል ሚንስቴር እንዳስታወቀው የተሰነዘረው ጥቃት የሳዕዲ አረቢያን የድፍድፍ ነዳጅ የማምረት አቅም በግማሽ ቀንሶታል። የዘርፉ ባለሙያዎች እንደሚሉት ይህ ሳዑዲ ላይ የተፈጸመው ጥቃት በዓልም አቀፍ ደረጃ የነዳጅ ዋጋ ላይ የዋጋ ልዩነት ሊያስከትል ይችላል። • የየመን አማፂያን የሁዴይዳን ወደብ ለቀው እየወጡ ነው • በየመን ከአየር ላይ አውቶብስ ላይ በደረሰ ጥቃት 29 ህፃናት ተገደሉ ከምዕራባውያን መንግሥታት ድጋፍ የሚያገኘው ሳዑዲ መራሹ ኃይል በየመን እየተደረገ ባለው ጦርነት ለየመን መንግሥት ድጋፍ የሚያደርግ ሲሆን፤ ኢራን ደግሞ ለሁቲ አማጽያን ድጋፍ ታደርጋለች። የአሜሪካው የውጪ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊው ማይክ ፖምፔዮ ''የድሮን ጥቃቱ ከየመን ስለመነሳቱ የሚያሳይ ምንም አይነት ማስረጃ የለም። ሁሉም መንግሥታት ኢራን በዓለም የኢንርጂ ምንጭ ላይ የሰነዘረችውን ጥቃት ማውገዝ አለበት'' ብለዋል። የሁቲ ቃል አቀባይ በበኩላቸው ከ10 በላይ የድሮን ጥቃቶች መሰንዘራቸውን እና ወደፊትም ተመሳሳይ ጥቃቶች ሳዑዲ ላይ እንደሚሰነዘሩ ተናግረዋል። ቃል አቀባዩ መቀመጫውን ቤሩት ላደረገው የቴሌቪዥን ጣቢያ ሲናገሩ "ይህ ትልቅ ኦፕሬሽን ማሳከት የቻልነው በሳዑዲ አረቢያ በሚገኙ የተከበሩ ሰዎች ድጋፍ ጭምር ነው" ሲሉም ተደምጠዋል። ጥቃቱ ያስከተለውን ጉዳት በተመለከተ ከሳዑዲ መንግሥት ባለስልጣናት የተሰጠ መግለጫ ባይኖርም፤ የሳዑዲ አልጋ ወራሽ ልዑል ሞሐመድ ቢን ሰልማን ከፕሬዝደንት ትራምፕ ጋር ባደረጉት የስልክ ንግግር "ሳዑዲ ለዚህ መሰል የሽብር ጥቃት ምላሽ ለመስጠት ዝግጁ መሆኗን" ነግረዋቸዋል። ዋይት ሃውስ ሳዑዲ እራሷን መከላከል እንድትችል አሜሪካ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ስለመሆኗ ትራምፕ ለሳዑዲ ባለስልጣናት አስታውዋል። • የሁቲ አማጺያን ወደ ሳዑዲ ሚሳዔል ተኮሰች የሁቲ አማጺያን እነማን ናቸው? በኢራን መንግሥት ድጋፍ የሚደረግላቸው የሁቲ አማጽያን የየመንን መንግሥት እና የሳዑዲ መራሹን ኃይል ሲፋለሙ ቆይተዋል። ፕሬዝደንት አብደራቡህ ማንሱር ከመዲናዋ ሰነዓ በሁቲ አማጽያን ተባረው ከወጡበት ጊዜ ጀምሮ የመን ላለፉት 4 ዓመታት በጦርነት ስትታመስ ቆይታለች። ሳዑዲ ከመዲናዋ የተባረሩትን ፕሬዝደንት በመደገፍ በሁቲ አማጽያን ላይ በየቀኑ ማለት በሚቻል መልኩ የአየር ጥቃቶችን ትፈጽማለች። የሁቲ አማጽያን በበኩላቸው ሚሳኤሎችን ወደ ሳዑዲ ያስወነጭፋሉ።
news-50583016
https://www.bbc.com/amharic/news-50583016
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ለማህጸን ለካንሰር መከላከያ ክትባት ከሚሰጡ ጥቂት አገራት አንዷ ናት
የማህጻን በር ጫፍ ካንሰር በመላው ዓለም ለሴቶች ሞት ምክንያት ከሆኑት የካንሰር አይነቶች መካከል አራተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
አንጀሊን ኡሳናሴ ከየማህጻን በር ጫፍ ካንሰር የዳኑ በአፍሪካ ግን ይህ በሽታ ከየትኛውም የዓለማችን ክፍል በተለየ መልኩ በከፍተኛ ደረጃ ገዳይ ነው፤ ምንም እንኳ ቀድሞ መከላከል ቢቻልም። በሩዋንዳ የተጀመረው በሽታውን የመከላከል እንቅስቃሴ ውጤትማ መሆኑን ተከትሎ ሌሎች የአፍሪካ አገራት የሩዋንዳን ተመሳሌት መከተል ጀምረዋል። አንጀሊን ኡሳናሴ በሩዋንዳ መዲና ኪጋሊ ትኖራለች። የ67 ዓመት አዛውንቷ አንጀሊን በማህጻን በር ጫፍ ካንሰር ህይወቷ እንዴት እንደተቀየረ ታስታውሳለች። ልክ የዛሬ ሁለት ዓመት ገደማ ነበር ድንገት በሙታንታዋ ላይ ደም የተመለከተችው። የ67 ዓመት ሴት መቼም የወር አበባ ልታይ አትችልም። እንዲህ አይነት ምልክት በእራሷ ላይ ካየች ዓመታት አልፈዋል። "በአቅራቢያዬ ወደሚገኝ የጤና ተቋም ሄድኩኝ። ከዚያም ሃኪሞች የማህጻን በር ጫፍ ካንሰር ምረመራ እንዳደርግ ነገሩኝ። የምረመራ ውጤቱ ሲመጣ በሽታው እንዳለብኝ አሳየ። በጣም ተደናገጥኩ። ልቀበለው አልቻልኩም። የምሞት መሰለኝ" በማለት የነበረውን ሁኔታ ታስታውሳለች። አንጀሊን በሽታውን በጊዜ ማወቋ እና የህክምና ዕርዳታ ማግኘቷ ህይወቷን እንደታደረገው ታምናለች። ዛሬ ላይ ቢሆን ግን አንጀሊን ይህ በሽታ ባልያዘት ነበር። ምክንያቱም በመላው ሩዋንዳ የተጀመረው የቅድመ ማህጻን በር ጫፍ ካንሰር ምረመራ እና ክትባት በታደጋት ነበር። ለማህጻን በር ጫፍ ካንሰር በሽታ መከሰት በግብረ ሥጋ ግንኙነት የሚተላለፈው ሂዩማን ፓፒሎማ ቫይረስ (ኤችፒቪ) አብዛኛውን ጊዜ እንደ ምክንያት ይጠቀሳል። • አስጊነቱ እየጨመረ ያለው ካንሰር ምንም እንኳ በአፍሪካ ይህ በሽታ ከፍተኛ ሞት የሚያስከትል ቢሆንም 10 አገራት ብቻ ናቸው የማህጻን በር ጫፍ ካንሰር ክትባትን ለዜጎቻቸው የሚሰጡት። ከእነዚህም መካከል ኢትዮጵያ አንዷ ተጠቃሽ አገር ናት። በአፍሪካ ኢትዮጵያን ጨምሮ 10 ሃገራት ብቻ ናቸው የማህጻን በር ጫፍ ካንሰር ክትባትን ለዜጎቻቸው የሚሰጡት። በምዕራብ አፍሪካ ውስጥ ከሚገኙ አገራት ለዜጎቿ ክትባቱን በብቸኝነት የምታቀርበው ሴኔጋል ናት። በምሥራቅ አፍሪካ ደግሞ ኬንያ፣ ኡጋንዳ፣ ታንዛኒያ፣ ኢትዮጵያ እና ሩዋንዳ ለዜጎች ክትባቱን ስለሚያቀርቡ በማህጻን በር ጫፍ ካንሰር የሚከሰተው ሞት ከሌሎች የአህጉሪቱ ቀጠና ጋር ሲነጻጸር ዝቅ ያለ ነው። ሩዋንዳ ከስምንት ዓመታት በፊት የጀመረችው ዘመቻ አዎንታዊ ውጤት አስገኝቶላታል። ከ10 ሴቶች 9 ሴቶች ክትባቱን ማግኘት ችለዋል። ይህ ውጤት ግን ያለፈተና አልነበረም የመጣው። ክትባቱ የሚያስወጣው ከፍተኛ ገንዘብ እስከ ለክትባቱ ያሉ የተሳሳቱ አመለካከቶች ሩዋንዳዊያን የተሻገሯቸው ጋሬጣዎች ናቸው። "አሁንም ቢሆን የማህጻን በር ጫፍ ካንሰር በሽታ እርግማን ነው በማለት ወደ ሃኪም ከማቅናት ይልቅ ወደ ጠንቋዮች ጋር የሚሄዱ ሴቶች አሉ" በማለት አንጀሊን ትናገራለች። ከዚህ በተጨማሪ በበሽታው ምክያት 'ማህጸናችን እንዲወጣ ሊደረግ ይችላል' የሚለው ስጋት በርካታ ሴቶች ወደ ህክምና እንዳይሄዱ ይገድባቸዋል። የኤችፒቪ ክትባት በሽታው በወጣቶች መካከል እንዳይስፋፋ በከፍተኛ ደረጃ ያደርጋል መንግሥት የማኅበረሰብ መሪዎችን፣ አብያተ ክርስቲያናትን፣ የመንደር መሪዎችን፣ የጤና ሰራተኞችን፣ ትምህርት ቤቶችንና የመገናኛ ብዙኃንን በመጠቀም በክትባቱ ዙሪያ የሚነዙ አፈታሪኮችን ለማስወገድ ዘመቻ አካሂዷል። ተማሪ ለሆኑት ልጃገረዶች በትምህርት ቤት ለማይማሩት ደግሞ በየቤታቸው ክትባቱን እንዲያገኙ ተደርጓል። የጤና ባለስልጣናትም ክትባቱ በተፈለገበት ቦታና ጊዜ ሁሉ በበቂ ሁኔታ በፍጥነት እንዲገኝ አድርገዋል። የኤችፒቪ ክትባት በሽታው በወጣቶች መካከል እንዳይስፋፋ በከፍተኛ ደረጃ ያደርጋል ኅብረተሰቡ በስፋት እንዲከተብ የሚያስችለው የመጀመሪያው የክትባት ዘመቻ ከተጀመረ ከስምንት ዓመታት በኋላ ክትባቱ የሩዋንዳ መደበኛ የክትባቶች ዝርዝር ውስጥ እንዲገባ ተደርጓል። ምንም እንኳን ሩዋንዳ ያገኘችውን ውጤት የሚያሳይ መረጃ ባይኖርም ተመሳሳይ ዘዴን የተጠቀሙ አገራት ውስጥ በሚገኙ ወጣቶች ላይ የኤችፒቪ በሽታ መስፋፋት በከፍተኛ ደረጃ ቀንሷል። • “እዚህ ደረጃ የደረስኩት በእርሷ ብርታት ነው” አርቲስት ደመረ ለገሰ አውስትራሊያ ከ1991 (እአአ) ጀምሮ ሴቶች የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ ማደረግ የተጀመረ ሲሆን ከ12 ዓመት በፊት ደግሞ ክትባቱ መስጠት ተጀምሯል። የአውስትራሊያ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ክስተት መጠን ከአንድ መቶ ሺህ ሴቶች ሰባት ብቻ ነው፤ ይህም በዓለም ላይ ከሚታየው አማካይ ቁጥር በግማሽ ያመነሰ ነው። በቀጣዩ የፈረንጆች ዓመት ደግሞ ዓመታዊው የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር አዲስ ክስተት በአንድ መቶ ሺህ ሴቶች ወደ ስድስት ዝቅ ይላል ተብሎ ይጠበቃል። 'በየቀኑ ዘጠኝ ሴቶች ይሞታሉ' የሩዋንዳን እርምጃ በመከተል ሌሎች የአፍሪካ አገራት በአሁኑ ጊዜ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ለመከላከል ጥረት እያደረጉ ነው። በጥቅምት ወር የኬንያ መንግሥት ከዓለም አቀፍ ለጋሾች ጋር በመተባበር የኤችፒቪ ክትባትን ከመደበኛ የክትባት አይነቶች ጋር እንዲሰጥ ማድረግ ጀምሯል። በዚህም ዘመቻ እድሜያቸው 10 ዓመት የሆናቸው 800 ሺህ ታዳጊ ሴቶችን በየዓመቱ ለመከተብ ፍላጎት አለው። "ኬንያ ውስጥ በየቀኑ በማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምክንያት ዘጠን ሴቶች ይሞታሉ። ይህንንም ለመከላከል ነው ለልጃገረዶች ክትባት ለአዋቂ ሴቶች ደግሞ ምርመራ የሚደረገው" ሲሉ ናይሮቢ ውስጥ በሚገኘው የአጋ ካን ዩኒቨርስቲ ሆስፒታል ውስጥ የጽንስና የማህጸን ፕሮፌሰር የሆኑት ማርሊን ተመርማን ይናገራሉ። የጡት ካንሰር 12 ምልክቶች ምንም እንኳን ዓለም አቀፍ የጤና ባለስልጣናት ክትባቱ ካለበት ቀላል የጎንዮሽ ችግር በስተቀር ደህንነቱ የተጠበቀና ውጤታማ እንደሆነ ቢገልጹም አንዳንዶች አሁንም ጥርጣሬ አላቸው። "ስለክትባቱ የምሰማው ነገር ስላስፈራኝ የአስር ዓመቷ ልጄን እንድትከተብ አላደረግኩም። ሲከተቡ ሽባ ሊሆኑ ወይም የደም መርጋት ሊያጋጥማቸው እንደሚችል የሚገልጹ ወሬዎች አሉ። ስለክትባቱ ምንም አይነት ትምህርት አልተሰጠንም" የምትለው በኬንያዋ የባሕር ዳርቻ ከተማ ሞምባሳ ነዋሪ የሆነችው እናት ቦንጄ አትማን ናት። ሃይማኖታዊ ስብስብ የሆነው የኬንያ የካቶሊክ ዶክተሮች ማህበር ግን ክትባቱን ለታዳጊ ልጃገረዶች መስጠት አስፈላጊ አይደለም በማለት ሴቶች ክትባቱን እንዳይወስዱ ጥሪ አቅርቧል። ኤችፒቪንም ለመከላከል ከወሲብ መታቀብ ወይም በአንድ የትዳር አጋር መወሰንን እንደመፍትሄ አቅርቧል። ሩዋንዳ ውስጥ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰርን ለማስወገድ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ ቀጥሏል። • የዘር ከረጢት ካንሰር ከአባት ጅን ጋር የተያያዘ ነው "ዘመቻውን በጀመርንበት ወቅት ከፍ ባለ የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ሴቶች ክትባቱን አላገኙም ነበር። አሁን ትኩረታችን በ30 እና በ49 እድሜ ውስጥ የሚገኙ ሴቶችን መመርመር ነው" ይላሉ ዶክተር ኡዊንክዊነዲ። አንጀሊን ሌሎች ስለበሽታው ያለቸውን ግንዛቤ ለማስፋትና ማግኘት የሚገባቸውን ህክምና እንዲወስዱ ለማበረታታት የራሷን የካንሰር ታሪክ በመንገር ጥረት እያደረገች ነው። "የምችል ቢሆን ኖሮ፤ ሁሉንም አሰልፌ ምርመራ እንዲያደርጉ ሃኪም ጋር እወስዳቸው ነበር" ትላለች።
news-48652222
https://www.bbc.com/amharic/news-48652222
ህንድ አሜሪካን ይጎዳል የተባለ የንግድ ታሪፍ ልታስተዋውቅ ነው
ህንድ ከእሁድ ጀምሮ የለውዝና የአፕል ምርቶችን ጨምሮ 28 የአሜሪካ ምርቶች ላይ አዲስ ታሪፍ ልታስተዋውቅ መሆኑን ገልፃለች።
አዲሱ ታሪፍ ህንድ የብረትና አሉሚኒየም ምርቶችን ወደ አሜሪካ በምትልክበት ወቅት ለጫነችባት ከፍተኛ ግብር ምላሽ ነው ተብሏል። አሜሪካ ግብሩን ዝቅ አድርጊ ብትባል በእምቢተኝነቷ ቀጥላለች። በዚህ ወር ፕሬዚዳንት ትራምፕ አሜሪካ ለህንድ በንግዱ ዘርፍ የምታደርግላትን የተለየ ጥቅማጥቅም እንደምታቆም ገልፀው ነበር። •ኢሳያስን ለመጣል'#ይበቃል' የተሰኘው የኤርትራውያን እንቅስቃሴ •ኢኮኖሚያዊ ተቃውሞና ያስከተለው ውጤት በምላሹም ህንድ እስከ 120% የሚደርስ ታሪፍ በአሜሪካ ምርቶች እንደሚጫን በባለፈው አመት ህንድ አስታውቃ የነበረ ቢሆንም በውይይቶች ምክንያት አተገባበሩ ዘግይቶ ነበር። በባለፈው አርብ ግን የህንድ የገንዘብ ሚኒስትር ለሰፊው ህዝብ ጥቅም ሲባል ውሳኔው ተግባራዊ እንደሚሆን አሳውቀዋል። በአሜሪካና በህንድ ያለው የሁለትዮሽ የንግድ ግንኙነት በባለፈው አመት 142 ቢሊዮን ዶላር የነበረ ሲሆን ይህም ከአስራ ሰባት አመት በፊት ከነበረው ቁጥር ጋር ሲወዳደር ሰባት እጥፍ ነው ተብሏል። ነገር ግን 5.6 ቢሊዮን ዶላር የሚሆነው የህንድ ወጪ ንግድ አሜሪካ ከቀረጥ ነፃ አድርጋላት የነበረ ሲሆን አሜሪካ ይህንን የንግድ ግንኙነት ማቆሟ ጋር ተያይዞ ከፍተኛ ተፅእኖ ሊያደርስ እንደሚችል ተንታኞች ይናገራሉ። •የትራምፕ እና የለንደኑ ከንቲባ ሳዲቅ ካህን እሰጣገባ የትራምፕ አስተዳደር "ኢፍትሐዊ" የንግድ ስርአትን ለማስተካከል በሚል እንቅስቃሴያቸው ነው እንዲህ አይነት የንግድ መጠቃቀም ግንኙነት እንዲቀሩ ያደረጉት። ይህንንም ተከትሎ በሁለቱ ኃገራት ያለው የንግድ ግንኙነት የሻከረ ሲሆን በባለፈው አመትም ህንድ ለዚህ ምላሽ የሚሆን የታሪፍ ጫናን አስተዋውቃለች። ትራምፕ በበኩላቸው ህንድ ከኢራን ነዳጅ እንዲሁም ከሩሲያ ኤስ 400 ሚሳይል ለመግዛት የያዘችውን እቅድ የማታቆም ከሆነ ማእቀብ ይጣልባታል ሲሉ አስፈራርተዋል። •የቴክኖሎጂ ፈጣሪዎች ልጆቻቸው 'ሞባይል' እንዳይጠቀሙ የሚያግዱት ለምን ይሆን? የህንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሱብራሃማንያም ጃይሻንካርና አቻቸው ማይክ ፖምፔዮ ጃፓን በሚካሄደው የጂ-20 ጉባኤ ላይ የሚወያየዩ ሲሆን፤ ፕሬዚዳንት ትራምፕና ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በቅርቡ ተገናኝተው እንደሚወያዩ ይጠበቃል።
news-42186655
https://www.bbc.com/amharic/news-42186655
በኢትዮጵያ 76 በመቶ የሚሆኑት ወጣት ሴቶች ስለ ኤችአይቪ እውቀት የላቸውም ተባለ
በኢትዮጵያ ባለፈው የፈረንጆች ዓመት በተደረገ ጥናት እድሜያቸው ከ15-24 የሚሆኑ ወጣቶች ስለኤች አይቪ ያላቸው ግንዛቤ አነስተኛ እንደሆነ ታውቋል።
በተለይም ደግሞ በዚህ የእድሜ ክልል ከሚገኙ ሴቶች 76 በመቶ የሚሆኑት የኤች አይቪ መተላለፊያ እና መከላከያ መንገዶችን አያውቁም። ወንዶች ቢሆኑ እውቀቱ ያላቸው 39 በመቶ ብቻ ናቸው። በፌደራል የኤች አይቪ መከላከያ እና መቆጣጠሪያ ፅህፈት ቤት የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ዳንኤል በትረ ለዚህ የተለያዩ አካላት ኃላፊነታቸውን አለመወጣታቸውን ምክንያት ያደርጋሉ። እነዚህ አካላትም የህዝብ ምክር ቤቶች፣ የሐይማኖት ተቋማት፣ ቫይረሱ በደማቸው የሚገኝ ግለሰቦች ማህበራት፣ የመገናኛ ብዙሃን፣ የጎሳ መሪዎችና አጋር ድርጅቶች ናቸው። መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ስለ ኤች አይቪ ኢድስ በንቃት በሚያስተምሩበት ወቅት የዛሬዎቹ ወጣቶች ጨቅላ ህፃናት ነበሩ። አሁን ግን ስለኤች አይቪ በማይወራበት ጊዜ ለአካለ መጠን በመድረሳቸው ለቫይረሱ ተጋላጭ ሆነዋል ይላሉ አቶ ዳንኤል። ኢትዮጵያ፡ የኤች.አይ.ቪ ኤድስ ወረርሽኝ አዲስ ስጋት ፈጥሯል "እነዚህ ወጣቶች በአብዛኛው በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች፣ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ በትላልቅ የአበባ እርሻዎች፣ በፋብሪካዎች እና በኃይል ማመንጫ ግንባታዎች ላይ የሚገኙ ናቸው።" እናም በኢትዮጵያ ከአፍላ ወጣቶች ግንዛቤ ማነስ ጋር በተያያዘ የኤች አይቪ ስርጭትም በዚሁ የእድሜ ክልል ከፍተኛ ምጣኔ ይታይበታል ። አቶ ዳንኤል ጨምረው እንደገለፁት በኤች አይቪ የሚሞቱ ሰዎች እንደሀገር በከፍተኛ ሁኔታ መቀነስ ዝምታንና መዘናጋትን ፈጥሯል። በተቃራኒው ደግሞ በወጣቶች መካከል ለኤች አይቪ የሚያጋልጡ ሁኔታዎች ጨምረዋል። ስለዚህ ምንም እንኳ ዛሬ የስርጭት መጠኑ አነስተኛ ቢሆንም የአጋላጭ ሁኔታዎች እየጨመረ መምጣት ግን ነገ የስርጭት መጠኑ እንዲጨምር ያደርገዋል። አቶ ዳንኤል "መዘናጋቱ ነገ ትልቅ ዋጋ ሊያስከፍለን ይችላል" በማለት የሁኔታውን አሳሳቢነት ይገልፃሉ። ከነዚህ ወጣቶች ባሻገር ለኤች አይቪ ይበልጥ ተጋላጭ የሆኑት እና የስርጭት መጠኑ ከፍ ያለው በወሲብ ንግድ ስራ ላይ በተሰማሩ ሴቶች፣ የረጅም ርቀት መኪና አሽከርካሪዎች እና በማረሚያ ቤት የሚገኙ ግለሰቦች ላይ ነው። ችግሩ ይህ ብቻ አይደለም፤ በየጊዜው የኤች አይቪ ምርመራ እና ክትትል የሚያደርጉ ሰዎች ቁጥርም አነስተኛ ነው ሲሉ አቶ ዳንኤል ሃሳባቸውን ያጠናክራሉ። ከዚህም በተጨማሪ ምንም እንኳን የትምህርት ሚኒስቴር ከአንደኛ ደረጃ ጀምሮ በቋንቋ፣በሥነ-ዜጋ፣ በሥነ-ሕይወት የሥርዓተ ትምህርቶች ውስጥ ቢካተትም የተጠበቀውን ያህል ለውጥ እንዳልመጣ አቶ ዳንኤል ይገልፃሉ። በየአመቱ ህዳር 22 የሚከበረው የፀረ ኤች አይቪ ቀን የዘንድሮ መሪ ቃል "አሁንም ትኩረት ለኤች አይቪ መከላከል" የሚል ነው።
52627585
https://www.bbc.com/amharic/52627585
ከጎረቤት አገራት ጋር የሚዋሰኑ ክልሎችና የኮሮና ወረርሽኝ ስጋት
በኢትዮጵያ የኮሮናቫይረስ የተያዘ የመጀመሪያው ግለሰብ ከተገኘ ሁለት ወራት ተቆጥረዋል። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ ሲሆን በተለያዩ አካባቢዎች ቫይረሱ የተያዙ ሰዎች እየተገኙ ነው።
በተለይ ኢትዮጵያ ከጎረቤት አገራት ጋር በምትዋሰንባቸው አካባቢዎች በቫይረሱ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር መጨመር ደግሞ አሳሳቢ ሆኗል። "ስጋቱ ይህ ነው ብሎ መግለጽ ይከብዳል" ያሉት የመተማ ወረዳ የጤና ጥበቃ ጽህፈት ኃላፊ አቶ በቃሉ እውነቱ ". . . በጣም ከባድ ነው። ቁጥሩ መጨመሩ አስፈሪ ነው። ከሱዳን በማሽላ አጨዳ እና በጥጥ ለቀማ ተሠማርተው ብዙዎች እየገቡ ነው። ከሚያዝያ 22 ጀምሮ 360 ሰዎችን ለይቶ ማቆያ አስገብተናል" ብለዋል። እስካሁን ድረስ ከፌደራል እና ከክልል ምንም ድጋፍ ያለመኖሩን ጠቅሰው "የእነሱ ድጋፍ ካልተጨመረበት ከባድ ነው። በቀን 100 ወይም 200 የቀን ሠራተኛ ይገባል። . . . ። እስካሁን የመጣልን ነገር የለም" ብለዋል። በተመሳሳይ ስጋት እንዳለባቸው የገለጹልን ደግሞ የባቲ ወረዳ አስተዳዳሪ የሆኑት አቶ ሞሃመድ አብዱ ናቸው። • "ምዕራባውያን ለአፍሪካ ሃገር በቀል መድኃኒቶች ንቀት አለባቸው" ሲሉ የማዳጋስካሩ ፕሬዚዳንት ተቹ • ዉሃን ለ11 ሚሊዮን ነዋሪዎቿ የኮቪድ-19 ምርመራ ልታደርግ ነው • የኮሮናቫይረስ ክራሞት በኢትዮጵያ፡ ከመጋቢት እስከ ግንቦት "በጣም ስጋት አለን. . . " ያሉት አቶ ሞሃመድ ቀደመው ወደ ሥራ መግባታቸውንና አፋር እና አማራ ክልል ድንበር ላይ የሙቀት ልየታ በአግባቡ እየሠሩ መሆኑን አስታውቀዋል። ለህብረተሰቡ መረጃ በመስጠት ከጅቡቲ የተመለሱ ሰዎችን እንዲጠቁም በማድረግ እየሠሩ መሆናቸውንም ጨምረው ገልጸዋል። "የክልል እና የፌደራል መንግስት እገዛ የለም። ሰሞኑን ለሱፐርቪዥን (ለቁጥጥር) መጥተው ነግረናቸዋል። ቦታው ስትራቴጂክ ነው ምስራቅ አማራን ጠቅላላ የሚያገናኝ ዋና መንገድ ነው" ሲሉ ገልጸዋል አቶ ሞሃመድ። እንደ አቶ ሞሃመድ ከሆነ ሌላው ስጋት ከጅቡቲ የሚመጡ ሰዎች መረጃ መደበቃቸው ነው። ይህ ደግሞ ሥራቸው ላይ እንቅፋት ሆኗል። ከጀቡቲ ወደ ኢትዮጵያ ድንበር በእግር በመሻገር ወደ ከተሞች የሚገቡ መኖራቸውን አቶ ሞሃመድ ጨምረው ያስረዳሉ። "ከዚያ ወደ ከተማ መጥቶ ከሚሴ መኪና ተሳፍሮ ይመጣል። የጉዞ ታሪክ ሲጠየቅ ከሚሴ ወይም ከሎጊያ ምናምን ይላል። ከጅቡቲ ነው የመጣሁት ብሎ አይናገርም። ይሄን ማወቅ ስለማይቻል ጎጥ እና ቀበሌ ወይም ከተማቸው ሲገቡ ሰዎች ጥቆማ ይሰጣሉ። በዚያ ጥቆማ ማቆያ እያስገባን ነው።" አብዛኛዎቹ ሲመጡ የጉዞ ታሪክ ሲጠየቁ ከሚሴ ወይም ሎጊያ ይላሉ እንጂ ከጅቡቲ አይሉም በማለት ያለው ክፍተት የፈጠረውን ችግር ያስረዳሉ። የሶማሌ ክልልም ከጎረቤት አገራት በሚመጡ ሰዎች ተመሳሳይ ስጋት መፈጠሩን የክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ዩሱፍ መሐመድ በተለይ ለቢቢሲ ገልጸዋል። "ከፍተኛ ስጋት አለ። እስካሁን ያስመዘገብናቸው 22 በኮሮናቫይረስ የተያዙ ሰዎች ከጎረቤት አገራት የመጡ ናቸው። ለይቶ ማቆያ ላይ ያገኘናቸው ናቸው።" ብለውናል። ሌላው ስጋት ያንዣበበት የአፋር ክልል ነው። የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ ያሲን ሃቢብ "ጥሩ አይደለም። ስጋቶች አሉ" ሲሉ ይናገራሉ። ከጅቡቲ የሚመለሱ ሰዎች አሁንም እንዳሉ ጠቅሰው "540 ሰዎች በለይቶ ማቆያ ውስጥ ይገኛሉ" ሲሉ የስጋቱን ደረጃ ያስቀምጣሉ። በለይቶ ማቆያ ውስጥ ያሉትን ለ14 ቀናት ከማቆየት ሌላ በክልሉ ሥራ በጀመረው ቤተ ሙከራ ምርመራ አድርገው፣ ከቫይረሱ ነጻ የሆኑትን ወደ ቀያቸው እንደሚመልሱ ይናገራሉ። እስካሁንም 241 ናሙና ተወስዶ 238ቱ ነጻ መሆናቸው ሲረጋገጥ ቀሪዎቹ ቫይረሱ ተገኝቶባቸዋል። "ስጋቱን አውቆ የክልሉ መንግሥት ሁሉም ከፍተኛ አመራር በ34 ወረዳ እና 5 ከተማ አስተዳደሮች ላይ ተመድበው እየሠሩ ነው" ብለዋል። ስለወረርሽኙ ትምህርት ከመስጠት ባለፈ በአፋር ህዝብ ዘንድ ያለው መረጃ የመለዋወጥ ባህልን ተጠቅመው "ህዝቡ በእግር የሚገቡትን ሰዎች በመለየት ትልቅ ድጋፍ እና ትብብር እያደረገ ነው። በዚሁ ከ21 በላይ ሰዎች ተጠቁመው ከእነዚያ መካከል አንዱ በቫይረሱ መያዙ ተረጋግጧል። ህዝብ በጣም ትልቅ አገልግሎት እየሰጠ ነው" ብለዋል። በትግራይ ክልል ቫይረሱ እንዳለባቸው ከተረጋገጠባቸው ሰዎች መካከል አብዛኛዎቹ አሸከርካሪዎች እና ረዳቶች መሆናቸው በዚህ ረገድ ምን እየተሠራ እንደሆነ ጠይቀን ነበር። "በክልል ደረጃ ምርመራ ጀምረናል" ያሉን ዶ/ር የሱፍ "ሾፌሮች እና ረዳቶች ለብቻቸው ለይቶ ማቆያ እንዲዘጋጅላቸው የሚያርፉበት እና የሚመገቡበት ሆቴል ለብቻ ተለይቶ ጥንቃቄ እየተደረገ ዕቃ ማመላለሱንም እንዲያከናውኑ የተወሰነ ውሳኔ ስላለ እሱን ተግባራዊ እናደርጋለን" ብለዋል። አቶ ያሲን በበኩላቸው የአሸከርካሪዎችን እና ረዳቶቻቸውን ሙቀት ከመለካት ባለፈ መኪኖቻቸውም መድኃኒት እንዲረጩ እየተደረገ መሆኑነን ገልፀዋል። "ጋላፊ ላይ ሙቀት ልየታ አለን። ከ14 በላይ ሾፌሮች ማቆያ አስገብተናል። ሙቀታቸው ከፍ ያለባቸውን ሰዎች ለ14 ቀናት እንዲቀመጡ በማድረግ መርምረን ነጻ መሆናቸውን አረጋግጠን እንዲወጡ እናደርጋለን። ሙሉ ለሙሉ መንገዱን መዝጋት የአገሪቱ ጉሮሮ ስለሆነ አደገኛ ነው" ሲሉ ለቢቢሲ ገልጸዋል። ዶ/ር የሱፍ እንዳሉት ከተለያዩ አካላት ድጋፍ እያገኙ ሲሆን፣ ያለውን ድጋፍ ለማስቀተል እና ክፍተቶችን ለመሙላት መነጋገራቸውን አስታውቀዋል። "ማን ምን መስራት አለበት በሚል እስካሁን ቴክኒካል እና የቁሳቁስ ድጋፍ ሲያደርጉ ነበር። ይህ ግን በቂ እንዳልሆነ እና ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ካለው የድንበር አካባቢ እንቅስቃሴ እና የቦርደር ስፋት አኳያ ጎረቤት ሃገራት ቁጥሩ ከመጨመር አንጻር ትልቅ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ተስማምተናል" ብለዋል። ከፌደራል መንግሥት የባለሙያ እና ቁሳቁስ ድጋፍ እንደሚደረግላቸው የገለጹት አቶ ያሲን በበኩላቸው "በሁሉም ረገድ ድጋፎች አሉ። ግን በቂ ነው፤ አጥጋቢ ነው ሳይሆን ጊዜው አደገኛ ስለሆነ ያሉትን ድጋፎች በመያዝ እኛም ክልሉ በመደበው በጀት ያሉትን ግብአቶች ለማሟላት ከፍተኛ ጥረት እያደረግን ነው" ሲሉ ገልጸዋል።
44521619
https://www.bbc.com/amharic/44521619
በደቡብ ክልል ሦስት ከተሞች በተፈጠሩ ግጭቶች 15 ሰዎች መሞታቸው ተገለፀ
በደቡብ ብሔሮችና ብሔረሰቦች ክልላዊ መንግስት አስተዳደር ውስጥ በሚገኙት የወልቂጤ፣ሀዋሳ እና ወላይታ ሶዶ ከተሞች በተፈጠሩ ግጭቶች 15 ሰዎች መሞታቸውን የክልሉ መንግስት አስታውቋል።
የክልሉ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ሰለሞን ሃይሉ ለሀገር ውስጥ የዜና ተቋማት እንደተናገሩት በግጭቱ ከሰዎች ህይወት መጥፋት በተጨማሪ "ግምቱ ያልታወቀ ንብረት ወድሟል፤ ከ2500 በላይ ሰዎችም ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል" ብለዋል። ግጭት በወልቂጤ ሰኔ 6 / 2010 ዓ.ም በወልቂጤ ከተማ የተፈጠረው ግጭት መንስኤ በከተማው እየተካሄደ ካለው የስፖርት ውድድር ጋር በተገናኘ የጉራጌ እና የአጎራባች ቀቤና ብሄረሰብ አባላት መካከል የተፈጠረው አለመግባባት እንደሆነ በወቅቱ የከተማዋ ነዋሪዎች ለቢቢሲ መናገራቸው አይዘነጋም። ለመረጋጋት የፀጥታ ሃይሎችን ጣልቃ ገብነት ባስፈለገው በዚህ ግጭት የሁለት ሰዎች ህይወት መጥፋቱን የክልሉ የኮሚዩኒዮኬሽን ጉዳይ ኃላፊ ተናግረዋል ። ለዘመናት በመልካም መግባባት የቆዩት የጉራጌ እና የቀቤና ብሄር አባላት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የወልቂጤ ከተማ ይገባኛል ጥያቄ ልባቸውን እያሻከረው ስለመሆኑ በጉራጌ ዞን የመስቃን ወረዳ የኮሚዩኒኬሽን ጉዳይ ባልደረባ ሬድዋን መሀመድ በወቅቱ ለቢቢሲ ተናግረዋል። የሀዋሳ ከተማ ግጭት ሰኔ 5/ 2010 ዓ.ም የሲዳማ ብሄር የዘመን መለወጫ በዓል በሀዋሳ ከተማ በሚከበርበት ዕለት በተነሳ ግጭት እና ቀጥለው በመጡ ሁለት ቀናት በተፈጠሩ ውጥረቶች 10ሰዎች ህይወታቸው ማለፉን፣9ሰዎች ከባድ ፣80 ደግሞ ቀላል ጉዳት እንደደረሰባቸው የክልሉ መንግስት የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ አስታውቋል። ከ50 በላይ ብሄረሰቦች የሚኖሩበት የደቡብ ብሄር ብሄረሰቦቹ ክልል ለተለያዩ የብሄር እና ጎሳ ግጭቶች እንግዳ ባይሆንም ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በሲዳማ እና ወላይታ ብሄሮች መካካል የተፈጠረ ቁርሾ የውጥረት ምንጭነቱ እንደጎላ ነዋሪዎች ለቢቢሲ ተናግረዋል። የወላይታ ሶዶ ከተማ ግጭት በሀዋሳው ግጭት ማግስት ሰኔ 8 /2010 ዓ.ም "የወላይታ ህዝብ ላይ እየደረሰ ያለው ብሄር ተኮር የነፍስ ማጥፋት እና ንብረት ማውደም ይቁም" የሚል እና ሌሎች መፈክሮችን የያዙ ሰልፈኞች ወደ ጎዳና ወጥተዋል። ሆኖም ሰላማዊው ሰልፍ ከቆይታ በኋላ ወደ ግጭት ተለውጧል ። ማሪያም ሰፈር ከሚባለው ስፍራ የተነሱ ሰልፈኞች በመጀመሪያ 'ጥቅማችንን እያስጠበቀ አይደለም!' ያሏቸውን የዞን አስተዳዳሪ ለማጥቃት ወደ መኖሪያ ቤታቸው እንዳቀኑ ፣ በመንገዳቸው ላይ ያገኟቸውን የግብርና መምሪያ፣የገጠር ቴክኖሎጂ ተቋማትን ፣ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲን ጨምሮ የተለያዩ የመንግስት እና የግል ተቋማት ላይ ጉዳት እንዳደረሱ የዐይን መስክሮች በምስል እና ቪዲዮ አስደግፈው ለቢቢሲ ገልፀዋል። በዚህ ግጭት 3 ሰዎች ህይወታቸውን እንዳጡ የክልሉ መንግስት አስታውቋል። ዶ/ር አብይ እንደ አስታራቂ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ከአጭር የሶማሊያ ቆይታቸው መልስ ከኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ጋር በነበራቸው ቆይታ ግጭት በተፈጠረባቸው ስፍራዎች ለሚኖሩ ዜጎች የሰላም ጥሪ አቅርበዋል። በቀጣይ ቀናትም ወደ ስፍራው በማምራት ከህብረሰቡ ጋር ውይይት ለማድረግ ስለማቀዳቸውም አስታውቀዋል።
news-49253081
https://www.bbc.com/amharic/news-49253081
ሙዚቀኛው የፓርላማ አባል በኡጋንዳው ፕሬዝዳንት ላይ በመሳለቁ ተከሰሰ
የኡጋንዳ ፓርላማ አባልና ታዋቂ የፖፕ ሙዚቀኛ ቦቢ ዋይን በአገሪቱ ፕሬዝዳንት ላይ በመሳለቅና ፕሬዝዳንቱን በማስቆጣት ክስ ተመሰረተበት።
ይህ አዲስ ክስ በቦቢ ዋይን ላይ ከዚህ በፊት ከቀረበበት ክስ ላይ ተጨማሪ ነው። ከአንድ ዓመት በፊት በሰሜናዊ ኡጋንዳ በምትገኘው የአሩዋ ከተማ ውስጥ ፕሬዝዳንቱ የምርጫ ቅስቀሳ በሚያደርጉበት ጊዜ የፓርላማ አባሉና አብረውት የነበሩ ደጋፊዎቹ በፕሬዝዳንቱ መኪኖች ላይ ድንጋይ ወርውረዋል በሚል ተይዞ ነበር። • ኡጋንዳ የዋትስአፕ ተጠቃሚዎችን ቀረጥ ልታስከፍል ነው • ለጎዳና ተዳዳሪዎች ገንዘብ ወይም ምግብ መለገስ ተከለከለ ሙዚቀኛውና የፓርላማ አባሉ ቦቢ ዋይን በቀረበበት ክስ ጥፋተኛ ሆኖ ከተገኘ እስከ እድሜ ልክ እስራት ሊቀጣ እንደሚችል ተነግሯል። ዋይንና በርካታ ባልደረቦቹ እስር ቤት በቆዩበት ወቅት ማሰቃየት እንደተፈጸመባቸው ቢናገሩም ባለስልጣናት ግን ክሱን ያስተባብላሉ። ትክክለኛ ስሙ ሮበርት ኪያጉላኒይ የሆነው ቦቢ ዋይን አሁን ከቀረበበት ክስ በተጨማሪ ባለፈው ዓመት በሞባይል ገንዘብ የማስተላለፍ አገልግሎትና በማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ላይ ግብር በሚጥለውን ሕግ ላይ ተቃሞን በማካሄዱ በሌላ ፍርድ ቤት ክስ ቀርቦበታል። ሙዚቀኛው የፓርላማ አባል ቦቢ ዋይን ለሰላሳ ዓመታት ስልጣን ላይ የቆዩትን የአገሪቱን ፕሬዝዳንት በመቃወም በኩል ዋነኛው ሰው ሲሆን፤ በቅርቡም ከሁለት ዓመት በኋላ በሚካሄደው የፕሬዝዳንትናት ምርጫ ላይ በተፎካካሪነት እንደሚቀርብ አሳውቋል።
news-54046096
https://www.bbc.com/amharic/news-54046096
"ሰንደቅ አላማችንን ነፃ ለማውጣት እንታገላለን" የአውስትራሊያ ቀደምት ህዝቦች
ጥቁር፣ ቀይ ፣ ነጭ የአውስትራሊያ ቀደምት ህዝቦች (አቦርጂን) ሰንደቅ አላማ ነው።
የአቦርጂን ሰንደቅ አላማ ጥቁሩ፣ ህዝብን፤ ቀዩ ከመሬት ጋር ያላቸውን ትስስር እንዲሁም ቢጫው የአለም ማዕከል የሆነችውን ፀሃይን የሚወክል ነው። አውሮፓውያን በቅኝ ግዛት መሬታቸውን ነጥቀው በርካታ ቀደምት ህዝቦችን ጨፍጭፈዋል፤ በርካቶችም በአገራቸው እንደ ባርያና ሁለተኛ ዜጋ እንዲቆጠሩ ሆነዋል። ለዚያም ነው የቅኝ ግዛት፣ ወረራና "ህዝባችንን የጨፈጨፈ" ስርአት ተምሳሌት የሆነውን የአውስትራሊያን ሰንደቅ አላማ አይወክለንም የሚሉት። ይሄ ሰንደቅ አላማ በአውስትራሊያ በሚገኙ ድልድዮች፣ ህንፃዎችና በቲሸርቶችም ላይ ማየት የተለመደ ነው። ሰንደቅ አላማው በመጀመሪያ የተቃውሞ የነበረ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት ግን የአቦርጂን ህዝቦች መለያና በአገሪቱም ብሄራዊ ሰንደቅ አላማነት እውቅና ተሰጥቶታል። እናም በባለፈው አመት ይህንን ሰንደቅ አላማ መጠቀምም ሆነ መያዝ እንዲያቆሙ ሲነገራቸው አብዛኛዎቹን የአቦርጂን ህዝብ ግራ ያጋባው። በጣም ጥቂቶች ብቻ ናቸው ሰንደቅ አላማው ከቅጅና ተዛማች መብቶች ጋር ተያይዞ እክል እንደገጠመው የተረዱት። ሁኔታው በርካታዎችን አስከፍቷል፣ አስቆጥቷል። የቀደምት ህዝቦችን ወክለው የፓርላማ አባል የሆኑት የሆኑት ሊንዳ በርኔ ሰንደቅ አላማውን እጃቸው ላይ ተነቅሰውታል። እናም ሰንደቅ አላማውም ሆነ ምልክቱ "ታግቷል" ብለዋል። በከፍተኛ ሁኔታ ጫና የደረሰበት የአውስትራሊያ መንግሥትም የቅጅና ባለቤት መብቱን ሊቆጣጠር ቢፈልግም ህጋዊና ባህላዊ ችግሮች ገጥመውታል ተብሏል። ይህ እንዴት ተፈጠረ? ከበርካቶቹ ብሄራዊ ሰንደቅ አላማዎች ለየት ባለ ሁኔታ ይህ ሰንደቅ አላማ ባለቤትነቱ የመንግሥት አይደለም። ባለቤትነቱ ሃሮርልድ ቶማስ የተባለ አርቲስት ነው። ይህ የአቦርጂን አርቲስት ሰንደቅ አላማውን ዲዛይን ያደረገው በጎርጎሳውያኑ 1971 በነበረው የትግል እንቅስቃሴ ነው። አርቲስቱ የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ባለሙሉ መብት ነው፤ ይህንንም መብቱን ያረጋገጠው በ90ዎቹ በተደረገ የፍርድ ሂደት ነው። ከዚያም በኋላ በባለፉት አመታት ለተለያዩ ኩባንያዎች እንደገና እንዲያመርቱም ስምምነት ላይ ደርሷል። ከሁለት አመታት በፊት ዋም ከተባለ የልብስ አምራች ጋር አንድ ስምምነት ተፈራርመው ነበር። በዚህም ስምምነት መሰረት ኩባንያው ሰንደቅ አላማውን በልብሶች እንዲያትም፣ በተለያዩ ሚዲያዎችም ላይ እንዲጠቀም አለም አቀፍ ብቸኛ መብትም የሰጠ ነው። የአቦርጂን ሰንደቅ አላማ ከዚህ ቀደም እንደነበሩት ኩባንያዎች ሳይሆን ይሔኛው ኩባንያው ይህንን ስምምነትም ለማስከበር በከፍተኛ ሁኔታ ተንቀሳቅሷል። በርካታ ለትርፍ ያልቆሙ የአቦርጂን ድርጅቶችም ይህንን የተረዱት ኩባንያው ህጋዊ መፍትሄንም ጭምር በመጠቀሙ ነው። "ሰንደቅ አላማውን የያዙ ልብሶች ሽያጭ በሶስት ቀናት ውስጥ እንዳቆም የፍርድ ቤት ማስቆሚያ ወረቀት የያዙ ጠበቆች ነገሩኝ" በማለትም የጉንዲትጅማራዋ ላውራ ቶምሰን ትናገራለች። የአቦርጂን ሰንደቅ አላማ ያለባቸውን ቲሸርቶችን በመሸጥም ለህዝቡ የህክምና አገልግሎት እንዲውል የሚሰራ ድርጅትንም ትመራለች። በዚህ ህጋዊ ማስፈራሪያ የተቆጣችው ላውራ "ሰንደቅ አላማውን ነፃ እናውጣ" የሚል ዘመቻን ጀምራለች። በበይነ መረብም 150 ሺህ የተቃውሞ ፊርማ ማሰባሰብ ችላለች። ይህም በባለፈው አመት ለፓርላማው ቀርቦ ነበር። "አንድ ግለሰብ ወይም ድርጅት ሰንደቅ አላማው እንዴት የግሌ ነው ይላል? ሰንደቅ አላማው የአቦርጂን ህዝቦች ነው። የራሳቸውን ሰንደቅ አላማ ለመጠቀምስ ለምን ይከፍላሉ?" በማለት በወቅቱ ለቢቢሲ ተናግራ ነበር። "የህዝባችን የፅናት ምልክት ነው። የአውስትራሊያ ሰንደቅ አላማ የኛ ነው ብለን አናስብም ምክንያቱም የቅኝ ግዛት፣ የወረራና የግድያ ምልክት ነው ብለን ስለምናምን አይወክለንም" ብላለች። ሰንደቅ አላማውን ነፃ የማውጣት ዘመቻ የጀመረችው ላውራ ቶምፕሰን "ሰንደቅ አላማችን ከፍ አድርገን እዚህ ስፍራ ያደረስነው እኛ ነን" የምትለው ላውራ ዋም የተባለው ኩባንያም ሰንደቅ አላማውን በነፃ እንድትጠቀም ቢፈቅድላትም እምቢተኝነቷን አሳይታለች። የአቦርጂን ያልሆነ ኩባንያ የህዝቡ ማንነት መሰረት የሆነውን ምልከት በመዝበዝ ትርፍ ያከማቻል በማለትም ወቅሳለች። በባለፈው አመትም የአቦርጂን ፖለቲከኞችና ታዋቂ ግለሰቦች በሰንደቅ አላማው የተጣለውን የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ተቃውሞ ተቀላቅለዋል። በተለይም የአውስትራሊያው እግር ኳስ ሊግ ሰንደቅ አላማውን ለመጠቀም ለኩባንያው የመብት ክፍያ አልፈፅምም ማለቱ እንዲሁም የአገሪቱ ራግቢ ቡድንም በተመሳሳይ አልከፍልም ማለቱ ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆኗል። ቡድኖቹም ሰንደቅ አላማውን ነፃ እናውጣው የሚለውን ተቃውሞ ድጋፋቸውን አሳይተዋል። ለአቦርጂን ህዝቦች የኩራት ምልክት የሆነው ይህንን ሰንደቅ አላማ አውስትራሊያዊቷ የአጭር ርቀት ሯጭ ካቲ ፍሪማን የ400ና የ2000 ውድድሮችን በሲድኒ ኦሎምፒክ ካሸነፈች በኋላ የአቦርጂን እንዲሁም የአውስትራሊያን ሰንደቅ አላማ ይዛ ታይታለች። በዚህ ሳምንትም ምክር ቤቱ የሰንደቅ አላማውን ቅጅና ተዛማች መብቶች ጋር በተያያዘ እንዲጣራ ትእዛዝ አስተላልፏል። ከዚህም በተጨማሪ የአገሪቱ የህግ ባለሙያዎች የንግድ ኩባንያዎች ከአገራዊ ኩራት በፊት ትርፍን በማስቀደም ሰንደቅ አላማው ጥቅም ላይ እንዳይውል እክል ፈጥረዋል በማለትም ተቃውሟቸውን አሰምተዋል። መንግሥትም የተቻለውን በማድረግ ሰንደቅ አላማውን ነፃ እንዲያወጣም ጥሪያቸውን አሰምተዋል። በአውስትራሊያ የቅጂና ተዛማች መብቶች መሰረት አርቲስቱ ሃሮልድ ቶማስም ሆነ ኩባንያው ዋም ፈቃዱንም ሆነ እንደገና ለማምረት የሚጠየቀውን ክፍያ የመጠየቅ መብት አላቸው። በባለፈው ሳምንት የዋም መስራች ግለሰቦች ሰንደቅ አላማውን ለግል ጥቅማቸው ቢይዙት እንደማይከለክሉ ባወጡት መግለጫ አስታውቀዋል። ሆኖም የልብስ አምራቾች፣ ለንግድ ተግባራት ማዋልና ድርጅታቸውን ለማስተዋወቅ የሚጠቀሙ ሰዎች በተለየ መንገድ ይታያሉ ብሏል መግለጫው። አርቲስቱ በበኩሉ የሰንደቅ አላማውን የባለቤትነት መብት ለኩባንያው የሰጠው ለጥበብ ስራው ተገቢው ክፍያ እንዲሰጠውና በውጭ አገራት የሚገኙ ኩባንያዎችም ሆነ ድርጅቶች አጓጉል ትርፍ እንዳያጋብሱ በማለት ነው። አርቲስቱ ቢቢሲን ለማናገር ፈቃደኛ ባይሆን ለአንድ አቦርጂን ሬድዮ በሰጠው ቃለ ምልልስ "ሰንደቅ አላማውን ሸጧል" በሚል ከፍተኘ ውግዘት እየደረሰበት እንደሆነ ነው። "ይህ ፍፁም ውሸት ነው" ማለቱንም ካማ ሬድዮ ዘግቧል። ህ ዝቡን ክዷል የሚባለውንም ስም ማጥፋት ዘመቻ ነው ብሏል። የአውስትራሊያ ቀደምት ህዝቦች ሚኒስቴር ቃለ አቀባይ ኬን ዋያት እንደተናገሩት" አርቲስቱ ከየትኛው ኩባንያ ጋር የንግድ ስምምነት ይፈፅም አይፈፅም የሚለውን ጉዳይ መንግሥት መንገር አይችልም" ብለዋል። ሆኖም የአገሪቱ ሚዲያዎች እንደዘገቡት መንግሥት የሰንደቅአላማውን መብት ከአርቲስቱ ለመግዛት ፍላጎት አሳይቷል ብለዋል።
news-48565610
https://www.bbc.com/amharic/news-48565610
በሁዋዌ ስልኮች ላይ በቅድምያ የሚጫኑ መተግበሪያዎችን እንዲቆሙ ተደረገ
ፌስቡክ መተግበሪያዎቹ በቅድምያ የሁዋዌ ስልኮች ላይ እንዳይጫኑ እርምጃዎችን መውሰዱን ሮይተርስ ዘገበ።
እገዳው የፌስቡክን ዋና መተግበሪያ የሚያካትት ቢሆንም በስሩ የሚተዳደሩትንም ዋትሳፕንና ኢንስታግራምንም ይጨምራል። አሜሪካ፤ ከወራት በፊት የአሜሪካ ግዙፍ ኩባንያዎች ለደህንነት ሲባል ከሌሎች የቴሌኮም አገልግሎት አቅራቢዎች ጋር እንዳየይሰሩ ላቀረበችው ጥሪ የተወሰደ እርምጃ ነው። የሁዋዌ የእጅ ስልክ ያሏቸው ሰዎች በቅድምያ ተጭነው የተሰጧቸውን መተግበሪያዎች እንደቀድሞው መጠቀም ይችላሉ። ለእነርሱም ከፌስቡክ በየጊዜው መረጃዎች እንዲደርሳቸው እንደሚደረግም ተናግረዋል። ፌዴሬሽኑ፡ «የቡና እና መቀለ ደጋፊዎች ባሉበት ጨዋታ ሊካሄድ አይችልም» የፌስቡክን ውሳኔ ተከትሎ ከሁዋዌ የተሰጠ ምላሽ የለም። ይህ ውሳኔ በእርግጥ በቅድምያ የተጫኑ መተግበሪያዎችን እንጂ የሁዋዌ ስልክ ያላቸውን ሰዎች መተግበሪያዎችን ማውረድም ሆነ መጠቀም አያግድም። ትኩረት እየሳበ የመጣው የሴቶች እግር ኳስ የዓለም ዋንጫ ወደፊት ግን ጉግል ከ'ፕሌይ ስቶር' ማለትም ከመተግበሪያ ማዕቀፍ የሁዋዌ ስልኮችን ቢያግድ ለሁዋዌ ስልክ ተጠቃሚዎች አስቸጋሪ ይሆናል። ይህ ውሳኔ ለሁዋዌ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንደማለት ነው።በዚሁ ሳምንት ነበር ከነሐሴ ጀምሮ የጉግልን አንድሮይድ ሶፍትዌር ከመጠቀም እንደታገደ የታወቀው። «የኔ ትውልድ ታሪክ እንደሚሠራ እምነት አለኝ» ሎዛ አበራ አሁንም ግን በ'ፕሌይ ስቶር' ያሉ የጉግል መተግበሪያዎች በሙሉ የሁዋዌ የስልክ ቀፎዎች ላይ ይሰራሉ። ሌሎች ሃገራትም በሁዋዌ መሣሪያዎች ላይ ገደቦች ብቻ ሳይሆን እገዳም እያደረጉ ነው።
news-44315979
https://www.bbc.com/amharic/news-44315979
መንግሥት ልዩ ፖሊስን እንዲበትን አምነስቲ ጠየቀ
በሶማሌና ኦሮሚያ ክልሎች ውስጥ የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን ይፈፅማል ያለውን የልዩ ኃይል ፖሊስን መንግሥት እንዲበትን የሰብአዊ መብት ተቆርቋሪው አምነስቲ ኢንተርናሽናል ባወጠው መግለጫ ጥሪ አቅርቧል።
አምነስቲ እንዳመለከተው በአጎራባች የኦሮሚያ ክልል ውስጥ በመግባት ግድያን ይፈፅማሉ ያለቸውን የሶማሌ ክልል ልዩ የፖሊስ ኃይልን የኢትዮጵያ መንግሥት በአስቸኳይ እንዲያስወጣና እንዲበትን ጠይቋል። በሶማሌ ክልል የፀረ-ሽብር ልዩ ኃይል ሆኖ የተቋቋመው የዚህ ቡድን አባላት በዚህ ሳምንት በሶማሌ ክልል ይኖሩ የነበሩ ሰዎችን 48 ቤቶች በማቃጠል ወደ ኦሮሚያ ክልል እንዲሸሹ ማድረጉን ጠቅሷል። መግለጫው ጨምሮም የኢትዮጵያ መንግሥት ይህን የልዩ ፖሊስ ክፍልን በአስቸኳይ በመበተን ለዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ህጎች ተገዢ በሆነ የፖሊስ ኃይል እንዲተካም ጠይቋል። የአምነስቲ ኢንተርናሽናል የምሥራቅ አፍሪካ፣ የአፍሪካ ቀንድና የታላላቅ ሃይቆች ዳይሬክተር የሆኑት ጆዋን ኒያኑኪ እንዳሉት "የልዩ ኃይሉ አባላት እንደፈለጉ በህዝብ ላይ ግፍ እንዲፈፅሙ መፈቀድ የለበትም" ብለዋል። ባለፈው ሳምንት ልዩ ኃይሉ በምሥራቃዊ ኦሮሚያ ጭናቅሰን ወረዳ ውስጥ በሚገኙ አራት መንደሮች ላይ በፈፀመው ጥቃት 5 አርሶ አደሮች ሲገደሉ 50 የሚጠጉ ቤቶች በእሳት ተቃጥለዋል። በዚህም ሳቢያ ነዋሪዎች ነፍሳቸውን ለማትረፍ መኖሪያቸውን ጥለው መሄዳቸውን የአምነስቲ ሪፖርት አመልክቷል። "የመንግሥት ባለሥልጣናት ይህ ጥቃት እንዲያበቃ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል" ያሉት ጆዋን ኒያኑኪ "ለዚህ ደግሞ የመጀመሪያው እርምጃ መሆን ያለበት ፖሊስ የሰብአዊ መብቶችን እንዲያከብር ማድረግና በጥቃቱ ተሳታፊ የሆኑትን በነፃና ገለልተኛ ምርመራ በመለየት ተጠያቂ እንዲሆኑ ማድረግ ያስፈልጋል" ብለዋል። ልዩ የፖሊስ ኃይሉ ባለፈው ዓመት ኦሮሚያ ክልል ውስጥ በተፈፀመ ጥቃት በመቶዎች ለሚቆጠሩ ሰዎች ሞትና ከአንድ ሚሊዮን ለሚልቁ ሰዎች መፈናቀል ምክንያት መሆኑን የብሔራዊ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ያወጣው ሪፖርት ያመለክታል። አምነስቲ ኢንተርናሽናል በማጠቃለያው በአካባቢው ላለው ውጥረት ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት፤ የኦሮሚያንና የሶማሌ ክልሎችን ድንበር ለይቶ ለማስቀመጥ በ1996 በተካሄደውን ህዝበ-ውሳኔ የተገኘውን ውጤት የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ተግባራዊ እንዲያደርጉ አሳስቧል። ይህንን ሪፖርት ተከትሎ የኢትዮጵያን መንግሥት ባለሥልጣናትን ምላሽ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።
news-55099412
https://www.bbc.com/amharic/news-55099412
ዝነኛዋ ሞዴል ሐሊማ በሃይማኖት ምክንያት ከፋሽን ዓለም ራሷን አገለለች
ከሶማሊያዊ ቤተሰብ የተገኘችው አሜሪካዊቷ ዝነኛ ሞዴል ሐሊማ አደን በሃይማኖት ምክንያት በፋሽን ኢንዱስትሪው ላለመቆየት ወስኛለሁ ስትል አስታወቀች።
ዝነኛ ሞዴል ሐሊማ አደን ለዚህ ውሳኔ ያበቃት የፋሽን ሥራ ከሃይማኖቴ እሴቶች ጋር ስለሚቃረን ነው ብላለች። የ23 ዓመቷ ሐሊማ በዝነኛዎቹ የብሪታኒያ ቮግ፣ የአረቢያ ቮግና አሉር መጽሔቶች ሽፋን ላይ ለመውጣት የበቃች ገናና ሞዴል ነበረች። በኢኒስታግራም ሰሌዳዋ ላይ ለአድናቂዎቿ በተወችው ማስታወሻ እንዳለችው የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ቤት እንድትውል ባደረጋት ጊዜ ከራሷ ጋር ስለሕይወቷ ለማሰላሰል እንደቻለች ጠቅሳ “እንደ አንዲት ሙስሊም የኔ እሴቶች ምንድናቸው?” በሚል አእምሮዋ ጥያቄ ማንሳቱን አውስታለች። ከሃይማኖቷ አስተምህሮ የሚቃረኑ የሞዴሊንግ የሥራ እድሎች ሲቀርቡላት መቀበሏ የራሷ ጥፋት እንደሆነና በዚህ ረገድ ማንንም መውቀስ እንደማትሻ አብራርታለች። ሒጃብ የምትለብስ ሙስሊም ሞዴል የሚገጥማትን ፈተናዎችን በማስታወሻዋ ጠቃቅሳለች። በኢንዱስትሪው የሙስሊም ሴት ሞዴል እጥረት መኖሩን ጠቅሳ ይህ መሆኑ ደግሞ ሒጃብ መልበስ ለአንዲት ሙስሊም ያለውን ትርጉሙ በፋሽን ኢንዱስትሪው የሚረዳ ሰው እንዳይኖር አድርጓል ትላለች። የኢኒስታግራም መልእክቷን ተከትሎ በርካታ አስተያየቶች የተሰነዘሩ ሲሆን ዝነኞቹ ሞዴሎችና የሥራ ባልደቦቿ ቤላ፣ ጂጂ ሐዲድ እና ሪሐና አበረታተዋታል። ሐሊማ የተወለደችው በኬንያ ስደተኞች ካምፕ ውስጥ ሲሆን ከሶማሊያ ስደተኛ ቤተሰቦች ነበር የተገኘችው። በ6 ዓመቷ ወደ አሜሪካ አቅንታለች። በ18 ዓመቷ የሞዴል ወኪል ግዙፉ አይኤምጂ ኩባንያ ለሞዴልነት መልምሏታል። በኋላም ለወይዘሪት ሜኔሶታ የቁንጅና ውድድር ላይ የመጨረሻ ዙር መድረስ ችላ ነበር። በቁንጅና ውድድሩ ታሪክ ሒጃብ ለብሳ የተወዳደረች የመጀመርያዋ ሴት ስለነበረችም ትልቅ ትኩረት መሳብ ችላ ነበር። ከዚያ በኋላ በትልልቅ የፋሽን መድረኮች በመቅረብ ከሒጃብ ጋር እምብዛም ገላጣ ያልሆኑ ወግ ያላቸው (modest) አለባበሶችን በማስተዋወቅ እውቅናን አትርፋለች። የአቀንቃኟን ሪሐና “ፌንቲ ቢዩቲ” እንዲሁም የካንዬ ዌስትን “ዩዚ” ብራንዶችን ያስተዋወቅችውም ሐሊማ ነበረች፤ በዚህም ዝናዋ ጨምሮ ነበር። በኢኒስታግራም መልእክቷ ሪሐና ለሰጠቻት ድጋፍና ሒጃብ ለብሳ እንድትሰራ ስላበቃቻት ምስጋናዋን አቅርባላታለች። ሞዴል ሐሊማ በፋሽን ኢንዱስትሪው ቆይታዋ ከሃይማኖታዊ አስተምህሮቷ ሊያሰናክሏት የሚችሉ በርካታ አጋጣሚዎች እንደነበሩ ጠቅሳለች። ከነዚህም መሐል ሂጃብ ሳትለብስ ፋሽን ሞዴሊን ለመስራት መስማማትና በቀን አምስት ጊዜ ጸሎት ለማድረስ አለመቻሏ ናቸው። ከህሊናዋ የማይታረቁ ተግባሮች ውስጥ በመሳተፏ ሆቴል ውስጥ ገብታ ብቻዋን ታለቅስ እንደነበር ጠቅሳለች። “እውነቱ በፋሽን ኢንዱስትሪ ቆይታዬ ደስተኛ አልነበርኩም” ስትል ደምድማለች።
news-42869381
https://www.bbc.com/amharic/news-42869381
ሩሲያ የአሜሪካንን ምርጫ ኢላማ ልታደርግ እንደምትችል የሲአይኤ ሃላፊ ተናገሩ
የሲአይኤ ዳይሬክተር ማይክ ፖምፒዮ በተያዘው የአውሮፓውያን ዓመት አጋማሽ ላይ የሚደረገውን የአሜሪካ ምርጫ ሩሲያ ኢላማ ታደርጋለች የሚል ስጋት መኖሩን ገለፁ።
ሩሲያ በአሜሪካና በአውሮፓ ላይ የምትሰነዝረው ጥቃት እየቀነሰ አለመሆኑንም ጠቁመዋል። ሲአይኤ ባለፈው ዓመት በተደረገው የአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ሩሲያ ጣልቃ ገብታለች ብሎም ያምናል። በተጨማሪም ዳይሬክተሩ ሰሜን ኮሪያ በጥቂት ዓመታት ውስጥ አሜሪካ ላይ የሚሳኤል ጥቃት የመሰንዘር አቅም ይኖራታል ብለው እንደሚያምኑም ተናግረዋል። በሌላ በኩል ማይክ ፖምፒዮ ትራምፕ ለፕሬዝዳንትነት ብቁ ነኝ ብለው አያምኑም ነበር የሚለውን አስተያየት ውድቅ አድርገዋል። "የዓለም ምርጡ የስለላ ድርጅት ነን። ለአሜሪካ ህዝብ ስንል ምስጢር እንሰርቃለን" ብለዋል ፖምፒዮ ለቢቢሲ። በያዙት ሃላፊነት አንድ ዓመት ያስቆጠሩት ፖምፒዮ ሥራቸው የሲአይኤን አቅም ማሳየት እንዲሁም የድርጅቱን ሸክም ማቅለል እንደሆነም ገልፀዋል። ምንም እንኳ ሽብርተኝነትን በመዋጋት ረገድ ትብብር ቢኖራቸውም፤ ፖምፒዮ ሩሲያን በቀዳሚነት የሚመለከቷት በአደገኝነቷ ነው። ሩሲያ አውሮፓና አሜሪካ ላይ የምታደርገው ጥቃትም ይህ ነው በሚባል መልኩ እየቀነሰ እንዳልሆነም አስረድተዋል። በመጭው ምርጫ ሩሲያ ጣልቃ ትገባለች የሚል ስጋት ቢኖራቸውም ግን ምርጫውን ነፃና ፍትሃዊ በማድረግ አገራቸው እርምጃውን እንደምትገታው እምነታቸውን ገልፀዋል። በትራምፕ ብቃት ላይ በርካታ ጥያቄዎችን ስላስነሳው 'ፋየር ኤንድ ፊዩሪ' መፅሃፍ ተጠይቀውም መፅሃፉ ትራምፕን የሳለበት መንገድ የተሳሳተ ነው ብለዋል። "ግራ የገባው ነው። መፅሃፉን አላነበብኩትም የማንበብ ሃሳቡም የለኝ" ብለዋል ፖምፒዮ።
news-53951022
https://www.bbc.com/amharic/news-53951022
የሰውን አንጎል ከማሽን ጋር የሚያገናኘው መሣሪያ
ኤለን መስክ የሰው ልጆችን አንጎል ከማሽን ጋር ቀጥታ ግንኙነት እንዲኖረው የሚያስችል አሠራርን ሊያሳይ ነው።
ይህም ለሰው ልጆች የላቀ ችሎታ የሚያጎናጽፍ ሂደት ነው። የሰው ልጆች አንጎል ላይ ምርምር በሚያደርገው የኤለን ተቋም ኒውራሊንክ ውስጥ በሰው ላይ ምርምር የተጀመረው አምና ነበር። ኤለን የሚያሳየው ሂደት ሰዎች በአዕምሯቸው ስልክ ወይም ኮምፒውተር የሚቆጣጠሩበት ነው። ኤለን እንደሚለው፤ የረዥም ጊዜ እቅዱ ለሰው ልጆች ላቅ ያለ ብቃት መስጠት ነው። ሰዎች፤ ከሰው ሰራሽ ክህሎት (አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ) ጋር መተሳሰር እንዳለባቸው ያምናል። ይህም ሰው ሰራሽ ክህሎት ከሰው ልጆች በልጦ ሰዎችን እንዳያጠፋ ይረዳል ሲል ያስረዳል። ኒውራሊንክ የተመሠረተው እንደ ጎርጎሮሳውያኑ 2017 ላይ ነው። ሳይንቲስቶችን ሲመለምልም ነበር። ተቋሙ እየሠራው ያለው መሣሪያ ከ3,000 በላይ ኤሌክትሮዶች የያዘ፣ ከሰው ልጅ ጸጉር የቀጠነ ገመድ ጋር የተያያዘም ነው። መሣሪያው ከ 1,000 በላይ ኒውሮኖችን ማንቀሳቀስ ይችላል። አምና ከተቋሙ የወጣ መግለጫ እንደሚጠቁመው በመሣሪያው ኮምፒውተርን በአንጎል መቆጣጠር እንዲቻል ዝንጀሮዎች ላይ ሙከራ ተደርጎበታል። በየደቂቃው 192 ኤሌክትሮዶችን አንጎል ውስጥ የሚከት ሮቦትም ተሠርቷል። የፒትስበርግ ዩኒቨርስቲ ተባባሪ ፕሮፌሰር ጄኔፈር ኮሊንገር፤ ኤለን እየሞከረ ያለው ነገር ለሕክምና ቴክኖሎጂ አስተዋጽኦ የሚያበረክት ይሆናል። “ኒውራሊንክ አስፈላጊው ግብዓት፣ ሳይንቲስቶች፣ ኢንጂነሮች አሉት። ሁሉም ለአንድ ግብ ስለሚሠሩ ውጤታማ የመሆን እድላቸው ሰፊ ነው።” ብለዋል። ሆኖም ግን በቴክኖሎጂ ውጤት ሕክምናን የሚያግዝ መሣሪያ ለመሥራት ጊዜ እንደሚወስድ ጠቅሰዋል። በፔልሰንቬንያ ዩኒቨርስቲ የሚሠሩት አሪ ቤንጃሚን ለቢቢሲ እንዳሉት፤ የሰው ልጆች አዕምሮ ውስብስብ መሆኑ መሣሪያውን የማዘጋጀት ሂደቱን ሊያከብደው ይችላል። “ኒውሮሊንኮች መረጃው አላቸው። ግን መተንተን ያስፈልጋቸዋል። አንጎል እንዴት እንደሚሠራ መሠረታዊ እውቀቱ የለንም። ይህም ፈተና ሊሆንባቸው ይችላል” ሲሉ አስረድተዋል። የስፔስኤክስ እና የተስላ ባለቤት የሆነው ኤለን፤ በሕዋ ጉዞ፣ በኤሌክትሪክ በሚሠራ መኪናና በሌሎችም ፈጠራዎች የበርካቶችን ቀልብ መግዛት ችሏል። በእርግጥ ትልልቅ ፕሮጀክቶችን ካስተዋወቀ በኋላ እውን ሆነው እስኪታዩ ጊዜ የወሰዱባቸው አጋጣሚዎች አሉ።
50931785
https://www.bbc.com/amharic/50931785
የንድፈ ሐሳብ ትምህርትን ወደ ተግባራዊ ዕውቀት ለመለወጥ የሚተጋው የፈጠራ ባለሙያ
ናኦል ዳባ ይባላል። የከፍተኛ ትምህርቱን በአሜሪካ ሲከታተል ቆይቶ ወደ ኢትዮጵያ ከተመለሰ ከአንድ ዓመት በላይ ሆኖታል።
ናኦል ዳባ ሕልሙና ዓላማው የፈጠራ ሥራውን ማጠናከርና በዘርፉ ላይ ፍላጎት ያላቸውን ወጣቶች መርዳት እንደሆነ ይናገራል። ናኦል ያጠናው ቲዮረቲካል ፓርቲክልስ ፊዚክስና ኢኮኖሚክስ ነው። ወደ አገር ቤት ከተመለሰም በኋላ ያሉትን ተጨባጭ ሁኔታዎች በማጥናት በሳተላይት ሳይንስ ዘርፍ ላይ ለመሥራት ከፍተኛ ፍላጎት አድሮብኛል ሲል ነግሮናል። በዚሁ መሰረት በቅርቡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት ኃላፊዎች በተገኙበት የፈጠራ ሥራውን አሳይቷል። ይህንን ፈጠራውን እውን ለማድረግ በብዙ ውጣ ውረድ ውስጥ ማለፉን የሚናገረው ናኦል፤ በተለይም የሳይንስና ኢኖቬሽን ሚኒስቴር፣ ዶ/ር ጌታሁን እንዳበረታቱት ያስታውሳል። ናኦል በሚኒስትር መሥሪያ ቤቱ ቴክኒካል ዘርፍ ላይ የሚሠሩ ሠራተኞች እንዳበረታቱት በማስታወስ፤ በአዕምሮው ውስጥ የነበረውን የፈጠራ ሐሳብ በግሉ ለመሥራት መወሰኑን ለቢቢሲ ተናግሯል። • የወንድሙን ገዳይ ለመበቀል ወደ ፈጠራ ሥራ የገባው ኢትዮጵያዊ • «ሰው ሲበሳጭ ማስታወሻ እይዝ ነበር» አዲስ ዓለማየሁ "በልቤ ውስጥ ያለውን የፈጠራ ሥራ በግሌ መተግበር ስፈልግ አንድ ነገር ወደ አዕምሮዬ መጣ፤ ይኸውም ለሳተላይት ዘርፍ ፍላጎት ያላቸው ተማሪዎችን አሰባስቤ እነሱን እያስተማርኩ ለምን ከእነርሱ ጋር አልሠራም የሚል ነበር፤ ከዚያ በኋላም ወጣቶቹን አሰባስቤ በሁለት ሳምንት አንዴ በቪዲዮ ኮንፍረንስ ማስተማር ጀመርኩ" በማለት የፈጠራ ሥራውን መጀመሩን ያብራራል፡፡ ከዚያም በኋላ ወጣቶቹን በንድፈ ሐሳብ ያስተማራቸውን ትምህርት ወደ ተግባር በመቀየር ትንሽ ሳተላይት (cubesat) ከተማሪዎቹ ጋር መሥራት መጀመሩን ይናገራል። ሥራውም ሰምሮለት ከሜቲዎሪዮሎጂ ኤጀንሲ ጋር በመሆን ትንሸ ሳተላይት ወደ ሰማይ አስወንጭፎ ተገቢውን መረጃ እና ምሥል ማሰብሰብ ችሏል። "ሳተላይቷ 37 ኪሎ ሜትር ወደ ላይ በመወንጨፍ የተለያዩ መረጃዎችንና የቪዲዮ ምሥሎችን ካሰባሰበች በኋላ በምዕራብ ሸዋ ወደ አምቦ አካባቢ አረፈች" ይላል ናኦል። ከዚያም በኋላ አንዲት ልጅ ሳተላይቷን መሬት ላይ አግኝታ ለአባቷ በመስጠቷንና ሊደብቋት ዳድተው እንደነበር ናኦል ያስታውሳል። "እኔ በጂፒኤስ እከታተላት ስለነበር የት እንዳረፈች በመለየቴ ደርሼባት ከሰባሰበችው መረጃ ጋር አግኝቻታለሁ።" • "ዓላማችን ችግሮችን ፈተን ገንዘብ ማግኘት ነው " የጠብታ አምቡላንስ ባለቤት • የፈረንሳይ ጦር ደራሲያንን "የወደፊቱን ተንብዩልኝ" አለ የትኛውም አዲስ ፕሮጀክት በሚሠራበት ሰዓት ጥቃቅን ያልተሟሉ ነገሮች ሊኖሩ ይችላሉ የሚለው ናኦል፤ ለመጀመሪያ ጊዜ በሠራው የሰው አልባ አውሮፕላንም ደስተኛ መሆኑን ይናገራል። "የመጀመሪያ ዓላማዬ ወጣቶቹን ምን ያህል አነሳስቻለሁ የሚል ነበር፤ በዚህ በኩል ከተለያዩ ሰዎች ባገኘሁት ግብረ መልስ እንደተሳካልኝ አረጋግጫለሁ። በሌላ በኩል ደግሞ ሰው አልባ አውሮፕላኗን ወደ ሰማይ በማስወነጭፍበት ሰዓት ሊኖሩ የሚችሉ ኃላፊነቶች በሙሉ ወስጄ ነበር በዚህም ተሳክቶልኛል" ይላል። ይህንን የሰው አልባ አውሮፕላን የሠራው በራሱ ወጪ መሆኑን የሚናገረው ናኦል፤ ውጤታማ በመሆኑ ለበለጠ ሥራ እንዳነሳሳው ይናገራል። "ብዙ ጊዜ የዚህ አገር ትምህርት በንድፈ ሐሳብ ላይ ያተኩራል። የኔ አላማ ደግሞ በንድፈ ሐሳብ የተማሩትን እንዴት በተግባር ማዋል እንደሚቻል ለማሳየት ነበር ተሳክቶልኛል" በየትኛውም የሥራ መስክ ውጤታማ ለመሆን በቅድሚያ ሥራውን መውደድ እንደሚያስፈልግ የሚናገረው ናኦል፤ እርሱም ለሥራው ያለውን ፍቅር ያብራራል። ከዚህም በተጨማሪ ምን ላይ ትኩረት ባደርግ የበለጠ ማሕበረሰቡን ልረዳ እችላለሁ የሚል የዘወትር ሃሳብ እንዳለው በመግለጽ ወጣቶችን እንዴት ልረዳ እችላለሁ የሚለውም የዘወትር ሃሳቡ መሆኑን ያብራራል። እነዚህ ሐሳቦች ለፈጠራ ሥራው እንዳነሳሱትም ጨምሮ ገልጧል። ይህንኑ ዓላማውን ከግብ ለማድረስ የሰው አልባ አውሮፕላን መሥራት ብቻ ሳይሆን፣ ለመሥራት የሚያስችል ድርጅትም ማቋቋሙን ይናገራል። በዚሁ መሠረት ኤን ጄት ማኑፋክቸሪንግ (NJT Manufacturing) የተሰኘ ኩባንያ አቋቁሟል። ኩባንያውም ሁለት ዋና ዋና ዓላማዎች አሉት የሚለው ናኦል፤ ቀዳሚው ዓላማ ሰው አልባ አውሮፕላንን በኢትዮጵያ ውስጥ ማምረት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በዘርፉ ፍላጎት ያላቸው ወጣቶችን በማሳተፍ ድጋፍ ማድረግ መሆኑን ያስረዳል። በተለይም ስለ ፈጠራ ማዕከሉ ሲያብራራ ወጣቶች የፈጠራ ሥራ የሚሠሩበት፣ ሰብረው የሚለማመዱበት፣ በአዕምሯቸው ያለው ወደ ተግባር የሚለውጡበት ነው ይላል። በተመሳሳይም ማዕከሉ ቴክኖሎጂን ከውጪ አገር በማስገባት ሰው አልባ አውሮፕላን በአገር ውስጥ የሚመረትበት መሆኑን ያስረዳል። እንደ ቻይና፣ እስራኤልና አሜሪካ ያሉ አገራት የሰው አልባ አውሮፕላን ቴክኖሎጂን ከአገራቸው ማስወጣት እንደማይፈልጉ የሚናገረው ናኦል፤ "እኛው በራሳችን የሚያስፈልጉን መሳሪያዎች ከውጪ በማስገባትና ሰብረን ቢሆን ተምረን በአገር ውስጥ ማምረት መቻል አለብን" ይላል። • "ይህ ፈጠራ ወደፊት ብዙ ነገሮችን እንደሚቀይር ከአሁኑ መናገር እችላለሁ።'' • በብርሃን ታስሰው የማይገኙት ሴት ኮሜዲያን የሰው አልባ አውሮፕላን ፈጠራ አዲስና ብዙ ጠቀሜታዎች እንዳሉት የሚናገረው ናኦል፤ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ሰዎች ይህንን ተረድተው በዘርፉ ቢሳተፉ ኢትዮጵያ ብዙ ጥቅሞች ልታገኝ እንደምትችል ያብራራል። ለወደፊት በሰው አልባ አውሮፕላን የእቃ ማመላለስ አገልግሎትና የግብርና ዘርፉን በሰው አልባ አውሮፕላን ቴክኖሎጂ ለመደገፍ እቅድ እንዳለው ይናገራል። በዓለም ላይ እንደ ቦይንግ ያሉ ትልልቅ ኩባንያዎች ከእንደነዚህ ዓይነት ትንንሽ ፈጠራዎች በመነሳት ትልልቅ ነገሮችን እንደሚሠሩ የሚያስታውሰው ናኦል፤ ኢትዮጵያም በዚህ ቴክኖሎጂ ላይ ትኩረት ማድረግ እንደሚያስፈልጋት ይናገራል። በኢትዮጵያ ውስጥ የሰው አልባ አውሮፕላንን አስመልክቶ ዝርዝር የሆነ የተቀመጠ ሕግ አለመኖሩን በመግለጽ ይህ በዘርፉ ላይ ለመሰማራት ፍላጎት ላላቸው አካላት እንቅፋት በመሆኑ እንደሚያሳስበው ያነሳል። ከዚህ ውጪ ቴክኖሎጂ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተቀያየረ ስለሚሄድ በኢትዮጵያም ሰው አልባ አውሮፕላንና ሳተላይት በብዙ መንገድ ሊረዱ ስለሚችሉ እነዚህ ቴክኖሎጂዎችን በአገር ውስጥ እንዲመረቱ ጽኑ ፍላጎት እንዳለው ለቢቢሲ ገልጧል።
news-53675952
https://www.bbc.com/amharic/news-53675952
ኮሮናቫይረስ፡ በየደቂቃው በዓለም ዙሪያ በኮሮናቫይረስ የሚያዙና የሚሞቱ ሰዎች ቁጥርን የሚያሳይ ካርታ
ከቻይናዋ ሁቤይ ግዛት ተነስቶ ሰው ከማይኖርበት አንታርክቲክ ውጪ ሁሉንም የዓለማችንን አህጉራትን ያዳረሰው የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ በአሁኑ ወቅት የምድራችን ዋነኛ የጤና ስጋት ሆኗል።
ኮቪድ-19 በመባል የሚታወቀው ይህ ወረርሽኝ የመተንፈሻ አካልን የሚያጠቃ ሲሆን፤ መጀመሪያ ትኩሳት ቀጥሎም ደረቅ ሳል ባስ ሲል ደግሞ የትንፋሽ ማጠርን ያስከትላል። እስካሁን በቫይረሱ ከ18.8 ሚሊዮን በላይ ሰዎች የተያዙ ሲሆን ከ700 ሺህ በላይ የሚሆኑ ደግሞ ህይወታቸውን አጥተዋል። እስካሁን ባለው ሁኔታ ወረርሽኙን ለመቆጣጠር የሚያስችል ክትባትም ሆነ መድኃኒት አልተገኘም። በየደቂቃው በዓለም ዙሪያ ባሉ አገራት ውስጥ በኮቪድ-19 የሚያዙ፣ ከበሽታው የሚያገግሙና በቫይረሱ ምክንያት ለህልፈት የሚዳረጉ ሰዎችን አሃዝ ቀጥሎ ከተቀመጠው ዝርዝር ላይ ይመልከቱ። በአገራት በዓለም ዙሪያ በበሽታው የተያዙ ሰዎች ሙሉውን ለመመልከት እባክዎን ብሮውዘርዎን ያሻሽሉ ምንጭ፡ ጆንስ ሆፕኪንስ ዩኒቨርስቲ፣ ብሔራዊ የኅብረተሰብ ጤና ተቋማት አሃዞቹ በመጨረሻ የተሻሻሉት 1 ዲሴምበር 2020 12:29 ከሰዓት ጂ ኤም ቲ+4 የኮሮናቫይረስ ምልክቶች ምንድናቸው? የኮሮናቫይረስ ሁለት ዋነኛ ምልክቶች ከፍተኛ ትኩሳትና ደረቅ ሳል ናቸው። በአንዳንድ ታማሚዎች ላይ እነዚህ ምልክቶች ወደ ትንፋሽ ማጠር ይወስዳሉ። ደረቅ ሳል ሲባል በጣም ጠንካራ የሆነ አንዳንድ ጊዜ ለአንድ ሰዓት የሚቆይ ነው። ከዚህ በፊት ደረቅ ሳል ካለብዎ የኮሮናቫይረስ ሳል በጣም ለየት ያለና ከባድ መሆኑን ማስተዋል ይችላሉ። ከፍተኛ ትኩሳት የሚባለው ደግሞ የሰውነት ሙቀት መጠን ከ37.8 ዲግሪ ሴልሲየስ ሲልቅ ነው። ይህ ትኩሳት ሰውነት እንዲግል ወይም ደግሞ ከፍተኛ ብርድና መንቀጥቀጥ እንዲሰማን ያደርጋል። ከእነዚህ ሁለቱ ዋነኛ ስሜቶች ባለፈ ራስ ምታትና ተቅማጥ አንዳንድ የበሽታው ታማሚዎች ያሳይዋቸው ምልክቶች ናቸው። የማሽተትና የመቅመስ አቅም ማጣትም ምልክቶች ሆነው ተመዝግበዋል። ምልክቶቹ ቫይረስ ሰውነት ውስጥ በገባ በአምስት ቀናት ሊታዩ ይችላሉ። የዓለም ጤና ድርጅት ዘገባ ምልክቶቹ እስከ 14 ቀናት ድረስ ሳይታዩ ሊቆዩ እንደሚችሉ ያስረዳል። ዝርዝር መረጃ *ከ100,000 ሰዎች መካከል የሞት ሙሉውን ለመመልከት እባክዎን ብሮውዘርዎን ያሻሽሉ ይህ ስዕላዊ መግለጫ ከጆንስ ሆፕኪንስ ዩኒቨርስቲ የሚወጣን መደበኛ መረጃ መሰረት ያደረገ ሲሆን፤ የየአገሩን ወቅታዊ አሃዝ ላያካትት ይችላል። ** ቀደም ያለው መረጃ የሦስት ቀናት አማካይ ነው። በበሽታው የተያዙ ሰዎች ቁጥር ላይ በሚደረግ ክለሳ ምክንያት፤ የዚህ ቀን አማካይ አሃዝን ማስላት አይቻልም። ምንጭ፡ ጆንስ ሆፕኪንስ ዩኒቨርስቲ፣ ብሔራዊ የኅብረተሰብ ጤና ተቋማት አሃዞቹ በመጨረሻ የተሻሻሉት፡ 4 ዲሴምበር 2020 1:27 ከሰዓት ጂ ኤም ቲ+4
news-50745003
https://www.bbc.com/amharic/news-50745003
#6 እሷ ማናት?: ለነፃነትም ለጥበብም ያልታከቱ እጆች
ንግስቲ ገብረመስቀል እባላለሁ። በኤርትራ የነጻነት ትግል ወቅት በበርሃ መምህርት ነበርኩኝ። ከነጻነት በኋላ በአንድ የመንግሥት ጽሕፈት ቤት በሰነዶች ምዝገባ [ዳታ ኢንትሪ] ባለሙያ ሆኜ ሰርቻለሁ።
ንግስቲ ገብረመስቀል እኤአ ከ1978 ጀምሮ በኤርትራ የነጻነት ትግል ውስጥ ተሳትፋለች የውስጥ ፍላጎቴ ግን ሌላ ነበር። የሸክላ ሥራዎችና እደ ጥበብን አብዝቼ እወድ ነበር። ይህ ስሜቴ እየገፋኝ ሲመጣም የመንግሥት ሥራን ትቼ ወደዚህ ገባሁ። እኤአ በ2003፣ በኤርትራ የጥልፍ ሥራ የተነቃቃበት ጊዜ ነበር፤ እኔም አቡጀዲ ላይ መጥለፍ ጀመርኩኝ። በዛን ወቅት በርካታ የሴቶችና የወንዶች የባህል ልብስ ሠራሁኝ። • እሷ ማናት?፡ ማየትና መስማት የተሳናት የመብት ተሟጋችና የሕግ ባለሞያዋ ሃበን ግርማ በፈርጥ ያጌጡ ጌጣጌጦችንም እሰራ ነበር። ልጆች ሆነን ለትግል ወደ በርሃ ከመውጣታችን በፊት ወላጆቻችን እንዲመርቁን በክር ሹራብ ሰርተን ሰጥተን ነበር የምንሄደው። በርሃ ላይም ሴት ታጋዮችን የእጅ ሞያ እንዲለምዱ፣ እዛው ባገኘነው ቀጭን ስልክ ሳይቀር በተለይ ደግሞ ለታጋይ እናቶች ለልጆቻቸው ካልሲ እንዲሰሩ እናስተምር ነበር። በዚህ መንገድ ያደገው ልምድ ለእኔም እንጀራ ሆኖኝ፤ አሥመራ ላይ ስሜን የተከልኩ ባለሙያ እንድሆን ረድቶኛል። የንግሥቲ የእጅ ውጤቶች የትግል ጓዶቼና የሚያውቁኝ ሰዎች ሥራዬ እንዲታውቅልኝም ሆነ ገበያ እንዳገኝ ወደ የተለያዩ ሥፍራዎች ሲሄዱ ምርቶቼን ይዘው በመሄድ እየሸጡ ያግዙኝ ነበር። 2005 ጥቅምት ወር ግን አንድ ትልቅ ነገር በሕይወቴ ተከሰተ። ከሁሉም የኤርትራ ዞኖች የተሰባሰብን 10 ሴቶች በአንዲት ክላውዲያ ዛምቦኒ የተባለች ጣልያናዊ መምህርት በኩል የሸክላ ሥራ ሥልጠና አገኘን። • እሷ ማናት?፡ ፈቲያ መሐመድ ከዐረብ ሃገር ኑሮ ወደ ሚሊየነርነት ለተከታታይ አስር ወራት ሥልጠና ከወሰድን በኋላ ተመልሼ እጄን አጣጥፌ መቀመጥ አልፈለግኩም። በአንድ ወር ውስጥ የሚያስፈልገኝን እቃ አሟልቼ ወደ ሥራ ገባሁ። በ2007 ላይ የሸክላ ሥራዎቼን ይዤ አሥመራ ከተማ ላይ በተዘጋጀው ዓውደ ርዕይ ላይ ለዕይታ አቀረብኩ። ያኔ ይዤው የወጣሁት ሥራ በሙሉ ተሸጠ። ያ ቀን የእንጀራ በሬን፣ ለሥራ ያለኝን ዓይኔን የከፈተ ሆነ። ትልቁ ሸክላ ሽጬ ያገኘሁት ገንዘብ 3 ሺ ናቅፋ [በአሁኑ የምንዛሬ ዋጋ 6320 ብር] ነበር። [ሳቅ] በወቅቱ ትልቋንና ውድ የነበረችው የሸክላ ሥራዬ በፈርጥና በኤርትራ ሰንደቅ ዓላማ ያጌጠች የአምፖል አቃፊ [ላምፕ] ነበረች። አልሸጥኳትም! ለፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት በስጦታ አበረከትኳት። 'ጣቶቻችን የተለዩ ናቸው' የሸክላ ሥራ በጭቃ የሚሠራ ስለሆነ ትክክለኛውን አፈር ማግኘትና መምረጥ ከባዱ ፈተና ነው። ጭቃውን ለማቡካት የሚያስፈልገው ጉልበት ደግሞ ሌላው ጭንቅ ነው። በእኔ አቅም ብቻ የሚሆን ስላልሆነ፤ የሚያግዘኝ ሰው ያስፈልገኝ ነበር። ይህ ሁሉ ከተለፋ፤ ሥራውን ሰርቶ ገበያው ሊወደው የሚችለው ቅርጽና መልክ መስጠቱ ላይ ሌላ ጉልበት ይጠይቃል። በዚህ መካከል የተሰራበት አፈር ትክክለኛ ካልነበረ ይሰነጠቃል። ያኔ የማነባውን እንባ በቃላት መግለጽ አልችልም። • እሷ ማናት?፡ ዘቢብ ካቩማ "ለዩኤን እሠራለሁ ብዬ አስቤ አላውቅም" እድለኛ ሆኜ ይሄኛውን ደረጃ ካለፍኩኝ፤ ሸክላውን በእሳት መጥበስ አለብኝ። 20 ሰው መያዝ የሚችል ጉድጓድ እቆፍራለሁ። ጉድጓዱ ላይ እሳት ለማቀጣጠል ውስጥ ገብቼ ነው የምሠራው። ዐይኔና አፍንጫዬ ያነባል፤ ፊቴ ከሰል ይለብሳል። ሥራው በጣም ከባድ ነው። በተለይ የመጨረሻው ደረጃ! ሸክላው ከእሳት ወጥቶ እስካይ ድረስ ያለኝ ስሜት ምጥ የተያዘች እናት የምትሰቃየው ስቃይ ያክል ነው። የሸክላ ሰራተኛ ትዕግስተኛና የሙያው አፍቃሪ መሆን አለበት። በፍቅር ስትሰራው ሌሊቱ ሁሉ ኩልል ያለ ንጋት ያክል ይሆናል። የሥራዎቼን ውጤት ሳይ ሁሌም እደሰታለሁ። አልቆ ሳይ የምደሰተው ደስታ ከቃላት በላይ ነው። በዚህ ሙያ ውስጥ 14 ዓመት ሆኖኛል። ለ12 ዓመታትም ሰርቼበታለሁ። ቀደም ብሎ ሰው ለዚህ ሙያ ክብር አልነበረውም፤ ሰዉ 'ደግሞ ለጭቃ ሥራ' እያለ ሲያጥላላው ነበር። አሁን ግን ብዙዎች ሕይወታቸውን የሚቀይሩበት ሥራ እየሆነ ነው። በእኔ ሥር 20 ወጣት ሴቶች ይገኛሉ። በየቀኑ በምንሠራው ሥራ ደስተኞች ነን። • እሷ ማናት?፡ የምሥራቅ አፍሪካ ማይክሮሶፍት ቢሮን የምትመራው ወጣት ኢትዮጵያዊት ለይምሰል አይደለም፤ ሴቶች ጣቶቻችን የተለዩ ናቸው። በቤታችን ውስጥ የምንሰራው ምግብ፣ የምናሳድጋቸው ልጆች፣ የቤታችን አያያዝ ማንነታችን የምናይበት መስታወታችን ናቸው። ቤትን ማስተዳደር ቀላል አይደለም። ከዚህም አልፎ በእነዛ ውብ ጣቶችዋ እደ ጥበብን የማትሰራ ሴት ልጅ አለች ካላችሁኝ ማመን ይከብደኛል። ሁሉንም ሴቶች ችሎታችሁን በአግባቡ በመጠቀም ለገበያ አቅርቡት እላለሁ። አቅምና ሙያ እያላት ቤት ውስጥ የምትቀመጥ ሴት ካለች ለእኔ ስንፍና ነው። ሴቶች ችሎታቸውና ጥበባቸውን አውጥተው ለመጠቀም ግን ሊበረታቱና ድጋፍ ሊያገኙ ይገባል። አቅምና ችሎታን ይዞ መቀመጥ ግን ተቀባይነት የለውም። ዓለም ላይ በተለያየ ሙያ ያለን ሴቶች ተቀራርበን ከሰራን ደግሞ ታሪካችን ይቀየራል። "ሴቶች ጣቶቻችን የተለዩ ናቸው"
51971610
https://www.bbc.com/amharic/51971610
ዓለምን ያስቆጣው የህንድ አስገድዶ መድፈር ወንጀል ተጠያቂዎች በስቅላት ተቀጡ
ከሰባት ዓመታት ገደማ በፊት በህንድ አንዲት የዩኒቨርሲቲ ተማሪን አውቶቡስ ውስጥ ለስድስት ደፍረው የገደሉት በስቅላት ተቀጡ።
ከስድስቱ ደፋሪዎች አንደኛው እስር ቤት ሳለ ራሱን ያጠፋ ፤ የ17 ዓመት ወጣት የነበረው ሌላኛው ሶስት ዓመት ታስሮ እንደ አውሮፓውያኑ 2015 ላይ የተፈታ በመሆኑ አሁን በስቅላት የተቀጡት አራቱ ናቸው። ህንድ ታዳጊውን ለሶስት ዓመት በእስር እንዲቆይ ያደረገችው ለታዳጊ የሚሰጠውን ከፍተኛ ቅጣት በመፍረድ ነው። • የአስገድዶ መደፈር ክሷን ለመከታተል የሄደችው ወጣት በእሳት ተቃጠለች • ሶማሊላንድ አስገድዶ መድፈርን በተመለከተ የመጀመሪያ ሕግ አወጣች • ሴት አስገድዳ ከወንድ ጋር ወሲብ ብትፈጽም፤ አስገድዶ መድፈር ይባላል? የ23 ዓመቷ የፊዚዮቴራፒ የዩኒቨርሲቲ ተማሪ የተደፈረችው በመንቀሳቀስ ላይ በነበረ አውቶቡስ ውስጥ ሲሆን ከጥቂት ቀናት በኋላ የሞተችውም ደፋሪዎቿ ባደረሱባት ከባድ ድብደባ ነበር። የወጣቷ መደፈር ድፍን ህንድን አስቆጥቶ የነበረ ሲሆን መንግሥትም ፀረ አስገድዶ መድፈር ህግ እንዲያወጣ አስገድዷል። ህንድ ጥፋተኞችን በስቅላት ስትቀጣ ከ2015 ወዲህ ይህ የመጀመሪያዋ ነው። ጥፋተኞቹ በስቅላት እንደተቀጡ የሟች እናት " የልጄን ፎቶ አቅፌ በመጨረሻም ፍትህ ማግኘታችንን ነገርኳት" ሲሉ ለመገናኛ ብዙሃን ተናግረዋል። አባቷም ከዚህ ወዲህ በአገሪቱ ፍትህ ስርዓት ላይ እምነት መጣል እንደሚቻል ሃሳባቸውን ገልፀዋል። አራቱ ወንጀለኞች በስቅላት ከተቀጡበት እስር ቤት ደጃፍ በርካታ ህንዳዊያን የተለያዩ መፈክሮችን ይዘው የነበረ ሲሆን ልክ ስቅላቱ መፈፀሙን እስር ቤቱ ሲያስታውቅ ብዙዎች ደስታቸውን ገልፀዋል። በስቅላት የተቀጡት አራቱ ደፋሪዎች ቅጣታቸው ወደ እድሜ ልክ እስራት እንዲቀነስላቸው ፊርማ በማሰባሰብ ቢጠይቁም ፍርድ ቤቱ ጥያቄያቸውን ውድቅ አድርጎታል።
news-51455302
https://www.bbc.com/amharic/news-51455302
የኮሮናቫይረስ በሽታን ምልክት ያሳዩ 14 ኢትዮጵያውያን ነፃ ሆነው ተገኙ
የኮሮናቫይረስ በሽታን ምልክት አሳይተው የነበሩ አስራ አራት ኢትዮጵያውያን ከላብራቶሪ ምርመራ በኋላ ነፃ መሆናቸው መረጋገጡን የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታውቋል።
ኢንስቲትዩቱ ይህንን ያሳወቀው በዛሬው ዕለት የኮሮናቫይረስን አስመልክቶ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ሲሆን አስራ አራቱ ግለሰቦች ወደ ለይቶ ማቆያ ስፍራም ተወስደው ነበርም ብሏል። •ኢትዮጵያውያን፡ የአስወጡን ድምጽ በጎሉባት የቻይናዋ ዉሃን •በኮሮናቫይረስ ሳይያዙ አይቀሩም ተብለው የተጠረጠሩ 4 ሰዎች በአዲስ አበባ ተገኙ በትናንትናውም ዕለት አንድ የተጠረጠረ ሰው በለይቶ ማቆያ ውስጥ የነበረ ሲሆን በኢንስቲትዩቱ የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ ውጤቱም ከቫይረሱ ነፃ መሆኑን በመረጋገጡ ከለይቶ ማቆያ ማዕከሉ እንዲወጣ መደረጉንም የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ኤባ አባተ ገልፀዋል። በበሽታው መስፋፋት ምክንያት በተፈጠረ ስጋት በርካታ አየር መንገዶች ወደ ቻይና የሚያደርጓቸውን በረራዎች ያቋረጡ ቢሆንም የኢትዮጵያ አየር መንገድ "በረራ ማቋረጥ በሞራልም በሥነ ምግባርም ተቀባይነት የለውም" በሚል የቀጠለ ሲሆን ለተጓዦችም አስፈላጊውን ምርመራና ክትትል እየተደረገ መሆኑን አየር መንገዱም ሆነ ኢንስቲትዩቱ አረጋግጠዋል። የቦሌ አየር ማረፊያን ጨምሮ በሁሉም አቅጣጫ ባሉ የሀገሪቱ መውጫና መግቢያ ድንበሮች የሙቀት ልየታ እየተደረገ መሆኑን የጠቀሰው ኢንስቲትዩቱ፤ ከጥር 14/2012- የካቲት 2/2012 ድረስ የኮሮናና የኢቦላ ቫይረስን ዝግጁነት በጋራ በማጣመር ከአንድ መቶ ሰባ ሁለት ሺህ በላይ መንገደኞች ምርመራ ተደርጓል። ከዚህም በተጨማሪ ከቻይና የሚመጡ መንገደኞችን ከሙቀት ልየታ በተጨማሪ የበሽታው ምልክት የታየባቸው መንገደኞችን የጤና ሁኔታ የመከታተል ሥራዎች በተጠናከረ መንገድ መቀጠሉን ዶክተር ኤባ አሳውቀዋል። •የኮሮናቫይረስ ስጋትና የኢትዮጵያ አየር መንገድ •በኮሮናቫይረስ ከተጠረጠሩ አራት አዲስ ሰዎች አንዱ በአክሱም እንደሚገኝ ተገለፀ ከቻይና የሚመጡ ሁሉንም ተጓዦች በአገር ውሰጥ በሚቆዩበት ወቅት አድራሻቸው ተመዝግቦ ለአስራ አራት ቀናት ክትትል የሚደረግባቸውን መንገድ እንደተዘረጋም ዶ/ር ኤባ በተጨማሪ ተናግረዋል። የኮሮናቫይረስ ከታየባቸው አገራት የመጡ መንገደኞች ወይም ንክኪ ያላቸው ሰዎች የሚያሳዩዋቸውን ምልክቶች እንደ ትኩሳት፣ ሳል፣ የትንፋሽ መቆራረጥ፣ የመተንፈስ ችግር ህብረተሰቡ ሲያይ በአስቸኳይ እንዲያሳውቅ የነፃ መስመሮች በዘረጋው መሰረትም ጥቆማዎች መጥተውለታል። እስካሁንም ባለው 39 ጥቆማዎች ለኢንስቲትዩቱ የድንገተኛ አደጋዎች ምላሽ ማስተባበሪያ ማዕከል መጥተው አስፈላጊውን ማጣራት አድርጌያለሁ ብሏል። እነዚህንም ክትትሎች ለማሳለጥ ለመገናኛ ብዙሀን ባለሙያዎች፣ ለሆቴል ባለሙያዎችና ከክልልና ከኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ለተውጣጡ ፈጣን ምላሽ ሰጪ ቡድን ስልጠና እየተሰጠ መሆኑንም አሳውቋል። ከዚህም በተጨማሪ የኢንዱስትሪ ፓርክ ባለባቸው በሁሉም ክልሎች ውስጥ የለይቶ ማቆያ ማዕከልና የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች ማስተባበሪያ ማዕከላትን ለመዘርጋት ኢንስቲትዩቱ በያዘው ዕቅድ መሰረት ወደ ሃዋሳ ከተማ የባለሙያዎች ቡድን የላከ ሲሆን ዝግቶችም እየተደረጉ ነው ብሏል። ከሁቤይ ግዛት፣ ውሃን ከተማ የተነሳው ኮሮናቫይረስ ለ1018 ሰዎች ህይወት መቀጠፍ እንዲሁም 43ሺ 108 ሰዎች በቫይረሱ መያዝ እንዲሁም 4053 ሰዎች ደግሞ ከበሽታው ማገገማቸውን የዓለም የጤና ድርጅት መረጃ ያሳያል።
news-56968687
https://www.bbc.com/amharic/news-56968687
ምርጫ 2013፡ ኢትዮጵያ ከአውሮፓ ሕብረት ጋር ያልተስማማቸው ሕብረቱ ሉዓላዊነትን የሚጻረር ጥያቄ በማቅረቡ ነው ተባለ
ኢትዮጵያ ምርጫ ለመታዘብ ካቀደው የአውሮፓ ሕብረት ጋር ያልተስማማቸው ሕብረቱ ሉዓላዊነትን የሚጻረር ጥያቄን በማቅረቡ ነው ሲሉ የውጪ ጉዳይ ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ተናገሩ።
የአውሮፓ ሕብረት ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ከስምምነት መድረስ ባለመቻሉ ወደ ኢትዮጵያ ለመላክ አስቦ የነበረውን የምርጫ ታዛቢ እንዲቀር መወሰኑን ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። ሕብረቱ የምርጫ ታዛቢ ልዑክ ለመላክ ከፍተኛ ጥረት ቢያደረግም ከኢትዮጵያ መንግሥት ባለስልጣናት ጋር የአውሮፓ ሕብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን የሚሰማራበት ቁልፍ መለኪያዎች /ፓራሜትርስ/ ላይ ከስምምነት መድረስ አልተቻለም ብሏል። ሕብረቱ ያልተሟሉ መስፈርቶች ያላቸው የምርጫ ታዛቢው ልዑክ ገለልተኝነት ማረጋገጥ አለመቻሉ እና ልዑኩ የራሱን መገናኛ ስርዓቶች ወደ አገር ማስገባት አለመቻሉ ናቸው። የውጪ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ማክሰኞ ረፋድ ላይ በጽህፈት ቤታቸው በሰጡት መግለጫ፤ የአውሮፓ ሕብረት የምርጫ ታዛቢ ልዑኩን ላለመላክ የወሰነው በሁለት ምክንያት ነው ብለዋል። ቃል አቀባዩ ሕብረቱ እና የኢትዮጵያ መንግሥት ሳይስማሙ የቀሩበት ጉዳዮች፤ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት የሚጻረሩ እና የአገሪቱን ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥሉ በመሆናቸው ከሕብረቱ ጋር ስምምነት ላይ ሳይደረስ መቅረቱን አብራርተዋል። የቴሌኮሚኒኬሽን ስርዓት አምባሳደር ዲና የመጀመሪያ፤ ሕብረቱ ወደ አገር ውስጥ ለማስገባት የጠየቀው የግንኙነት ስርዓት የአገሪቱን ሉዓላዊነት የሚጥስ ነው ብለዋል። ሕብረቱ 'ቪሳት' የሚባል ኢትዮጵያ የሌላት የቴሌኮሚኒኬሽን ስርዓት ወደ አገር ውስጥ ለመስገባት ጫና ማድረጉን ቃል አቀባዩ ተናግረዋል። ከዚህ ቀደም በነበሩ ምርጫዎች፤ የውጪ ታዛቢዎች ወደ አገር ሲገቡ መሰል የግንኙነት መሳሪያዎችን ለመጠቀም ጥያቄ ቀርቦ እንደማያውቅ አስታውሰዋል። "ታዛቢዎችም ሊጓዙባቸው የሚችሉባቸው ቦታዎች የአገሪቱ የቴሌኮሚኒኬሽን ስርዓት የተዘረጋባቸው ናቸው። እሱን መጠቀም ይችላሉ፤ ከዚህ ውጪ አገሪቱ የሌላትን የቴሌኮሚኒኬሽን ስርዓት ይዘን እንገባለን ማለት እኛ እናስተዳደራችሁ ማለት ነው" ብለዋል። 'የምርጫ ውጤት ይፋ ምናደርገው እኛ ነን' መንግሥት ከሕብረቱ ጋር ያልተስማማበት ሁለተኛው ነጥብ ሕብረቱ ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቀድሞ የምርጫውን ውጤት ይፋ የማደርገው እኔ ነኝ ማለቱ መሆኑን አምባሳደር ዲና ተናግረዋል። "ይህ በየትኛው አገር የማይታሰብ ነው" ያሉት አምባሰደር ዲና፤ የምርጫ ውጤትን መግለጽ ያለበት ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነው ብለዋል። "በቅድሚያ ምርጫው የሚያረጋግጥልን የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው። ከዚያ ቀጥሎ የምርጫ ቦርድ ነው" ብለዋል። ኢትዮጵያ ግንቦት 28 እና ሰኔ 5 2013 ዓ.ም. ለማካሄድ ላቀደችው ስድስተኛው አጠቃላይ ምርጫ ላይ ለመሳተፍ 42 የፖለቲካ ፓርቲዎች እጩዎችን ያስመዘገቡ ሲሆን መራጮችም እየተመዘገቡ ይገኛሉ። ስድስተኛው አገራዊ ምርጫ ላይ ጥላቸውን ከጣሉ ጉዳዮች መካከል አንዱ በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የሚቀሰቀሱ ብሔር ተኮር ግጭቶች ናቸው። በሌላ በኩል አምስት የአሜሪካ ሴናተሮች ኢትዮጵያ የምታካሂደው ምርጫ አሁን ባለበት ሁኔታ ዓለም አቀፍ መመዘኛዎችን አያሟላም ማለታቸው ይታወሳል። ሴናተሮቹ ይህን ያሉት በቅርቡ የፕሬዝደንት ጆ ባይደን አስተዳደር የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ሆነው ለተሾሙት አምባሳደር ጆፍሪ ፌልትማን በጻፉት ደብዳቤ ነው። ሴናተሮቹ ከሳምንታት በኋላ የሚካሄደው አገራዊ ምርጫ አሁን ባለበት ሁኔታ ነጻ፣ ሚዛናዊ እና ግልጽ ሆኖ ዓለም አቀፍ መመዘኛዎች አያሟላም ብለዋል። ሴናተሮቹ ምርጫውን በተመለከተ ይህን ማለታቸውን ተከትሎ የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስተያየትን ለማካተት ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም። ይሁን እንጂ ከዚህ ቀደም ብሔራዊ ምርጫ ቦርድም ይሁን መንግሥት ቀጣዩ ምርጫ ዲሞክራሲያዊ እና ተዓማኒነት ያለው ለማድረግ እየሰሩ መሆኑን በተደጋጋሚ ገልጸዋል።
news-53544126
https://www.bbc.com/amharic/news-53544126
ሴቶች የሚመሯቸው ኩባንያዎች የተሻለ አትራፊ መሆናቸውን አንድ ጥናት አመለከተ
ሴቶች በአመራርነት የሚሳተፉባቸው ተቋማት በወንዶች ብቻ ከሚመሩት የተሻለ ስኬታማ እንደሚሆኑ አንድ ጥናት አመለከተ።
ጥናቱ የተደረገው ለንደን ውስጥ በሚገኙ ኩባንያዎች ላይ ነው። 350 ግዙፍ ኩባንያዎች በዚህ ጥናቱ ተካተዋል። የጥናቱ መደምደሚያም አንድ ነገር አሳየ። በከፍተኛ አመራር ላይ ከሚቀመጡ ሦስት ሰዎች ቢያንስ አንዷ ሴት በሆኑባቸው ኩባንያዎች ውስጥ የተሻለ ምርት፣ የተሻለ ትርፍ ከመታየቱም ባሻገር በሴቶች የሚመሩ ኩባንያዎች ደንበኞቻቸውን ፍላጎት ማሟላት እንደቻሉ ተደርሶበታል። ጥናቱ እንዳስቀመጠው በወንድ ሥራ አስፈጻሚዎች ከሚመሩ ኩባንያዎች ይልቅ በሴቶች የሚመሩት የ10 እጥፍ ብልጫን አሳይተዋል፤ በትርፍም በምርትም። የሚገርመው ጥናቱ ላይ ከተሳተፉ 350 ኩባንያዎች ውስጥ 14ቱ ብቻ ናቸው በሴት ሥራ አስፈጻሚ የሚመሩት። ጥናቱን ያደረገው ዘፓይፕላይን የተሰኘ ድርጅት ነው። ከጠቅላላ ኩባንያዎቹ ውስጥ ደግሞ 15 እጅ የሚሆኑት በከፍተኛ አመራር ደረጃ አንዲት ሴት እንኳ አልተወከለችባቸውም። የጥናት ቡድኑ መሥራች እንዳረጋገጡት ሴት ሥራ አስፈጻሚዎች የሚመሯቸው መሥሪያ ቤቶች የደንበኞቻቸውን ፍላጎት ነቅሶ በማውጣትና ፍላጎትን በማሟላት የሚስተካከላቸው አልተገኘም። ከእነዚህ መቀመጫቸውን ለንደን ካደረጉ ኩባንያዎች መካከል ሴቶች በአመራር የሌሉባቸው ድርጅቶች 1.5 በመቶ የትርፍ ህዳግ ብቻ ነበር ያስመዘገቡት። ሴቶች በርከት ብለው በአመራር ደረጃ የሚገኙባቸው ኩባንያዎች በበኩላቸው የትርፍ ህዳጋቸው 15.2 በመቶ ያህል ደርሶ ታይቷል። ጥናቱ ከዚህ ሌላ በፋይናንስ ዘርፍ የሚገኙ ኩባንያዎች 96 ከመቶ የሚሆኑት በወንዶች እንደሚመሩ ደርሶበታል። ሴቶች በአመራር ደረጃ ከማይቀመጡባቸው ኩባንያዎች ውስጥ የኮንስትራክሽንና የችርቻሮ ንግድ ዋንኞቹ ሆነው ተገኝተዋል። የጥናት ቡድኑ መሥራች እንዳሉት በችርቻሮ ዘርፍ 80 ከመቶ ሴቶች ተሳታፊ ቢሆኑም በአመራር ደረጃ ግን ድርሽ አይሉም ወይም ዕድሉ አይሰጣቸውም። በጥናቱ ላይ የተሳተፉት የቀድሞው የዩናይትድ ኪንግደም ጠቅላይ ሚኒሰትር ቴሬሳ ሜይ እንደተናገሩት በእንግሊዝ ሴቶች በአመራር ደረጃ እንዳይሳተፉ የሚያደርጋቸው አንድም የረባ ምክንያት የለም። "እያንዳንዱ በእንግሊዝ ኩባንያ ያለ ወንድ ሥራ አስፈጻሚ የቦርድ ስብሰባው ላይ ከ10 ተሰብሳቢዎች 9ኙ ወንዶች መልሰው ሲያፈጡበት ራሱን መጠየቅ ይኖርበታል። ስለሴት ልጁም ማሰብ አለበት" ብለዋል ቴሬሳ ሜይ።
news-53963766
https://www.bbc.com/amharic/news-53963766
ኮሮናቫይረስ ፡ በአውሮፓ ከተሞች "ኮቪድ-19 ውሸት ነው" የሚሉ ተቃውሞዎች እየተካሄዱ ነው
ከአርብ ጀምሮ እየተካሄዱ ያሉ ሰልፎች መልከ ብዙ ቢሆኑም 'ጭራሽ ኮሮና የሚባል ቫይረስ ብሎ ነገር የለም፣ እየተጭበረበርን ነው' ብለው የሚያምኑ ሰልፈኞችም የተገኙበት ሆኗል፡፡
የብዙዎቹ ሰልፈኞች ጥያቄ ግን በኮሮና ምክንያት የተጣሉ ገደቦች ይነሱ የሚሉ ናቸው፡፡ በጀርመን በርሊን ሰፊ ተቃውሞ የተካሄደ ሲሆን ከዚሁ ጋር ተያይዞ 300 ሰዎች በቁጥጥር ሥር ውለዋል፡፡ የጀርመን ሰልፈኞች ያነሱት ተቃውሞ በዋናነት 'በኮሮናቫይረስ ምክንያት ጥብቅ የተደረጉ መመሪያዎች ይነሱልን መረረን' የሚል ነው፡፡ በጀርመን ለተቃውሞው 40ሺ የሚጠጉ ሰዎች አደባባይ ወጥተዋል፡፡ በአመዛኙ ሰላማዊ ሆኖ የቆየው ተቃውሞ በነጭ አክራሪዎች ነውጥ ምክንያት መልኩን እየቀየረ መጥቷል፡፡ ድንጋይና ጠርሙስ መወራወርም ተጀምሯል፡፡ በበርሊን ብቻ ሳይሆን በሌሎችም የአውሮፓ ከተሞች ተመሳሳይ ሰልፎች ተደርገዋል፡፡ በለንደን በዝነኛው ትራፋልጋር አደባባይ የወጡ ሰልፈኞች ብዙዎቹ "ኮሮናቫይረስ ብሎ ነገር የለም፤ እየተጭበረበርን ነው" የሚል ይዘት ያላቸው መፈክሮችን ይዘው ታይተዋል፡፡ በፓሪስ፣ በቪየና እንዲሁም በዙሪክ ይኸው ተቃውሞ በተመሳሳይ መንፈስ ቀጥሏል፡፡ በጀርመን የተካሄደው ተቃውሞ ፍትጊያ የበዛበትና ማኅበራዊ ርቀትን ለማስጠበቅ አስቸጋሪ እንደነበር ፖሊስ አምኗል፡፡ "ምንም ማድረግ አንችልም፡፡ የሚቻለውን ለማድረግ ሙክረናል፡፡ በሰልፈኞች መሀል የኮሮናቫይረስ ደንቦችን ማስጠበቅ ግን አልቻልንም" ብሏል ፖሊስ በትዊተር ገጹ፡፡ ፖሊስ በቁጥጥር ካዋላቸው ሰዎች መሀል አንዱ "ኮሮናቫይረስ ብሎ ነገር የለም፣ ዉሸት ነው የሚለውን መላምት በማራገብ የሚታወቀው አቲላ ሂልድማን" ይገኝበታል፡፡ ሂልድማን ለሰልፈኞች ድምጽ ማጉያ ይዞ ተከታታይ ንግግር ሲያደርግ ነበር፡፡ ሂልድማን በጀርመን እውቅ የምግብ አብሳይ ባለሙያ ሲሆን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የነጭ አክራሪዎችን አስተሳሰብ በመጋራት ከፍተኛ ተጽእኖ ፈጣሪ ሆኗል፡፡ "ኮሮናቫይረስ የሚባል ነገር የለም፤ ጀርመን ከቢልጌትስ መወገኗን ታቁም" የሚሉ አስተሳሰቦችን ማራመድ በመጀመሩ ብዙ ተከታዮችን አፍርቷል፡፡ ብዙዎቹ ሰልፈኞቹ ጭምብል ማጥለቅና ሌሎች ኮሮናቫይረስን ለመከላከል የሚወሰዱ መመርያዎች የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ስለሆኑ እንዳሻን እንሁን የሚል ጥያቄ ነው ያነሱት፡፡ ከሰልፈኞቹ መሀል እውቅ ሰዎችም ተገኝተውበታል፡፡ ለምሳሌ ሮበርት የጆን ኤፍ ኬኔዲ ልጅ ለሰልፉ ድጋፍ ከሰጡት መሀል ይገኝበታል፡፡ ሮበርት ኬኔዲ ጁንየር በሰው እጅ የተገደሉት የዝነኛው የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆን ኤፍ ኬኔዲ የወንድም ልጅ ሲሆን ክትባትን በመቃወም ከፍተኛ ተከታይ ያፈራ ሰው ነው፡፡ ሮበርት ኬኔዲ በርሊን ድረስ በመምጣት ሰልፉን ተቀላቅሏል፡፡ ጀርመን እስካሁን 242,000 ሰዎች በኮቪድ-19 እንደተጠቁባት እና ከ10ሺ ሰዎች በታች እንደሞቱባት ይታወቃል፡፡
news-47147338
https://www.bbc.com/amharic/news-47147338
የሴት ልጅ ግርዛት ምንድነው? የት እና ለምን ይፈጸማል?
የተባበሩት መንግሥታት በዓለማችን በህይወት ያሉ ወደ 200 ሚሊዮን የሚጠጉ ሴቶች እና ህጻናት ላይ የተለያየ ደረጃ የግርዛት ተግባራት ተፈጽሞባቸዋል ይላል።
'ገራዧ' ተብላ የምትታወቀው ይህች ሴት ሞምባሳ ኬንያ ውስጥ ሴቶችን ለመግረዝ የምትጠቀምበትን ምላጭ ይዛ። የሴት ልጅ ግርዛት በስፋት እየተፈጸመ ያለው ወደ 30 በሚጠጉ የአፍሪካ እና መካከለኛው ምስራቅ ሃገራት ሲሆን፤ በእስያ እና ደቡብ አሜሪካ በሚገኙ ሃገራትም የሴት ልጅ ግርዛት ይፈጸማል። የተባበሩት መንግሥታት እንደሚለው ከሆነ በአውሮፓ፣ ሰሜን አሜሪካ፣ አውስትራሊያ እና ኒው ዚላንድ የሚኖሩ ስደተኞች ህግን በመተላለፍ ሴት ልጆቻቸውን ያስገርዛሉ። የተባበሩት መንግሥታት በዓለም አቀፍ ደረጃ የሴት ልጅ ግርዛት እንዲቆም ጥሪ እያቀረበ ነው። የሴት ልጅ ግርዛት አካላዊ እና አእምሯዊ ጉዳቶችን ሊያስከትል እንደሚችል የቦረና ማህብረሰብ አባል የሆነችው ቢሻራ ሼህክ ሃሞ ትናገራለች። ''የተገረዝኩት የ11 ዓመት ልጅ ሳለሁ ነበር። አያቴ ግርዛት ንጹህ የሚያደርግ የሁሉም ሴት ልጅ ግዴታ እንደሆነ ትነግረኝ ነበር'' ትላለች ቢሻራ ሼክህ። የሴት ልጅ ግርዛት ምንድነው? የተባበሩት መንግሥትታት እንደሚለው በአፍሪካ፣ ኢሲያ እና መካከለኛው ምስራቅ ቢያንስ 200 ሚሊዮን የሚሆኑ በህይወት ያሉ ሴቶች እና ህጻናት ተገርዘዋል። የሴት ልጅ ግርዛት ሆነ ተብሎ የሴት ልጅን የመራቢያ ክፍል አካል መቁረጥ ማለት ነው። የዓለም ጤና ድርጅት ብዙ ጊዜ የሴት ልጅ ግርዛት ሲፈጸም የብልት ከንፈሮችን እና ቂንጥርን መቁረጥን ያካትታል ይላል። ኦምኒያ ኢብራሂም ግብጻዊት የፊልም ዳይሬክተር እና ጦማሪ ናት። ኦምኒያ ግርዛት በህይወቷ ላይ ከፍተኛ ጫና እንዳሳደረ ትናገራለች። ማህብረሰቡ ያስተማረኝ ''የሰውነት ክፍል የግብረ ስጋ ግንኙነት አካልና ይህ ደግሞ ሀጢያት መሆኑን ነው። አእምሮዬ ውስጥ ሰውነቴ ሀጢያት እንደሆነ ነበር የምረዳው'' ትላለች። ቢሻራ ሼክህ በግርዛት ምክንያት ከደረሰባት ችግር በመነሳት የሴት ልጅ ግርዛት እንዳይፈጸም የተለያዩ ቅስቀሳዎችን ታደርጋለች ቢሻራ ግርዛት እንዴት እንደተፈጸመባት ስታስታውስ፤ ''አራት ሴት ህጻናት አብረውኝ ተገርዘዋል። ዓይኔ ተሸፍኖ ነበር። ከዛ እጄን ወደኋላ አሰረች። ሁለት እግሮቼን ከፍተው ከያዙ በኋላ የብልቴን ከንፈር ቆርጣ ጣለች'' ስትል ታስታውሳለች። የግርዛት አይነቶች አራት አይነት የግርዛት አይነቶች አሉ። የሴት ልጅ ግርዛት ለምን ይከሰታል? በአንዳንድ የኬንያ ማያሳ ሴቶች ዘንድ ያልተገረዙ ሴቶች የትዳር አጋር አያገኙም ወይም ከበርካታ ሰዎች ጋር የወሲብ ግንኙነት ሊኖራቸው ይችላል የሚል እምነት አላቸው። የሴት ልጅ ግርዛት ከሚፈፀምባቸው የተሳሳቱ ምክንያቶች መካከል የማህብረሰብ አስተሳሳብ፣ ኃይማኖት፣ ከንጽህና ጋር የተያያዘ የተሳሳተ ዕምነት፣ ድንግልናን ለማቆየት በማሰብ፣ ሴት ልጅ ትዳር እንድታገኝ በማሰብ እና የወንድ ልጅ የወሲብ እርካታን ለመጨመር ይገኙበታል። በበርካታ ማህብረሰብ ዘንድ ሴት ልጅ የምትገረዘው ለትዳር እንደ ቅድመ ዝግጅት ስለሚወሰድ ነው። ምንም እንኳ ግርዛት ለንጽህና የሚያበርክተው አስተዋጽኦ በሳይንስ ባይረጋገጥም፤ ያልተገረዙ ሴቶች ጤነኛ እና ንጹህ ያልሆኑ ተደርገው በበርካታ ማህብረሰብ ዘንድ ይታሰባሉ። የሴት ልጅ ግርዛት የሚፈጸምባቸው ሃገራት የሴት ልጅ ግርዛት የት ይፈጸማል? የሴት ልጅ ግርዛት በበርካታ የዓለማችን ሃገራት የተከለከለ ተግባር ቢሆንም አሁንም በየቀኑ በተለያየ ሃገራት ይፈጸማል። የተባበሩት መንግሥታት እንደሚለው ምንም እንኳ የሴት ልጅ ግርዛት በ29 የአፍሪካ እና መካከለኛው ምስራቅ ሃገራት ውስጥ በህግ የተከለከለ ቢሆንም በ24 ሃገራት ውስጥ በስፋት እንደሚፈፀም ይጠቁማል። በአውሮፓ፣ ሰሜን አሜሪካ፣ አውስትራሊያ እና ኒው ዚላንድ የሚኖሩ ስደተኞች ህግን በመተላለፍ ሴት ልጆቻቸውን እንደሚያስገርዙም እኚህ መረጃዎች ያሳያሉ። በምዕራባውያን ሃገራት የሴት ልጅ ግርዛት የሚፈጸመው በጨቅላ ህጻናት ላይ በመሆኑ ጨቅላዎቹ ወደ ትምህርት ቤት ስለማይሄዱ እና ከእድሜያቸው አንጻር ሪፖርት ማድረግ ስለማይችሉ ተግባሩ እንደተፈጸመባቸው ማወቁ ከባድ መሆኑ ተጠቅሷል።
51610110
https://www.bbc.com/amharic/51610110
ሰሜን ኮሪያ ኮሮናቫይረስ እንዳይዛመት በመስጋት የውጭ ዜጎችን ማቆያ ጣብያ እያስገባች ነው
ሰሜን ኮሪያ የኮሮናቫይረስ ስርጭትን በመስጋት 380 ያክል የውጭ ዜጎችን በማቆያ ጣብያ ውስጥ ማስገባቷ ተነገረ።
አብዛኛዎቹ የውጭ ዜጎች ዲፕሎማቶች ሲሆኑ በዋና ከተማዋ ፒዮንግያንግ በሚገኝ ጣብያ ውስጥ ነው እንዲቆዩ የተደረገው ሲል የኮሪያ ማዕከላዊ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽንን ጠቅሶ ዮንሃፕ የዜና ወኪል ዘግቧል። 200 ገደማ የውጭ ዜጎች በቫይረሱ ምክንያት ከሚኖሩበት ግቢ ንቅንቅ እንዳይሉ ተደርገው እንደነበር፤ አሁን ግን እንደተለቀቁ ተነግሯል። ቢሆንም በርካቶች ወደ ማቆያ ጣብያዎች እየተጋዙ ነው። በሰሜን ኮሪያ፤ እስካሁን አንድም የተዘገበ የኮቪድ-19 ተጠቂ የለም። የውጭ አገር ዜጎቹ በለይቶ ማቆያው ጣብያው ለምን ያህል ጊዜ እንደሚቆዩ የተነገረ ነገር የለም። ጎረቤት አገር ደቡብ ኮሪያ 763 ሰዎች በቫይረሱ ተይዘው 7 ሰዎች ሞተዋል። 11 ወታደሮች በቫይረሱ መጠቃታቸውን ተከትሎ 7700 የደቡብ ኮሪያ ወታደሮች በማቆያ ጣብያ እንዲቆዩ መደረጉም ተሰምቷል። ቻይና የተከሰተው ኮሮናቫይረስ ወደ 29 አገራት ተዛምቷል። አውሮጳ ውስጥ በርካታ የኮሮናቫይረስ ተጠቂ ያላት አገር ጣልያን ናት። 152 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። ከ50 ሺህ በላይ ሰዎች ለሁለት ሳምንታት በለይቶ ማቆያ እንዲቆዩ መደረጉም አይዘነጋም። ኢራን ውስጥ ደግሞ 43 ሰዎች ተይዘው 8 ሰዎች ሞተዋል። ቻይና ውስጥ በቫይረሱ ምክንያት የሞቱ ሰዎች ከ2500 በልጧል። 77150 ሰዎች ደግሞ በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። ከቻይና ጋር ወደብ የምትጋራው ሰሜን ኮሪያ በቫይረሱ የተጠቃ ዜጋ ባይኖርባትም ስጋት ግን ሳይገባት የቀረ አይመስልም። ወደ ሰሜን ኮሪያ የሚያመራ ማንኛውም ዜጋ ለ30 ቀናት በለይቶ ማቆያ ይቆያል። ነገር ግን ወደ ሰሜን ኮሪያ የሚያመሩ የውጭ አገር ዜጎች ቁጥር እጅግ ውስን ነው። ስማቸውን እንዳይጠቀስ የፈለጉ አንድ ባለሙያ በሰሜን ኮሪያ የሚገኙት የምዕራባውያን አገራት ዜጎች ቁጥር ከ 200 አይዘልም ብለዋል። አልፎም የሰሜን ኮሪያ ባለሥልጣናት ለወትሮው በርካታ የውጭ አገር ዜጎች የሚሳተፈበት የፒዮንግያንግ ማራቶን ዘንድሮ እንዳይከናወን አዘዋል። ከቻይና ጋር ደንበር በምትጋራው የሰሜን ፒዮንጋን ግዛት የሚኖሩ 3000 ሰዎች የቅርብ ክትትል እየተደረገባቸው እንደሆነም ተዘግቧል።
51172201
https://www.bbc.com/amharic/51172201
ቻይና ውስጥ በተከሰተው ቫይረስ በሁለት ቀናት 139 ሰዎች ተያዙ
የቻይና ባለሥልጣናት አዲስ እየተዛመት ባለው ቫይረስ በሁለት ቀናት ውስጥ 139 ሰዎች መያዛቸውን አሳወቁ።
ቫይረሱ ተከስቷል የተባለው ዉሃን በተሰኘችው ግዛት ሲሆን ቫይረሱ ያለባቸው ሰዎች የተገኙት ግን ከግዛቲቱ ውጭ መሆኑ ጉዳዩን አሳሳቢ አድርጎታል። 200 ሰዎች እስካሁን በቫይረሱ የተያዙ ሲሆን 3 ሰዎች በመተንፈሻ አካሉ ቫይረስ ምክንያት ሕይወታቸው አልፏል። የዓለም ጤና ድርጅት ሰዎች በተመረመሩ ቁጥር አዳዲስ የበሽታው ተጠቂዎች ቁጥር መጨመሩ አይቀርም እያለ ነው። በሕክምናው አጠራር ኮሮናቫይረስ የተሰኘውና የመተንፈሻ አካላትን የሚያጠቃው ቫይረስ መጀመሪያ የታየው በቻይናዋ ውሃን ግዛት ነው። የእንግሊዝ የሕክምና ባለሙያዎች ግን ከሌሎች ባለሙያዎችና ከዓለም የጤና ድርጅት ጋር ሆነን ባደረግነው ምርምር በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር መንግሥት ከሚለው የላቀ መሆኑን ደርሰንበታል ይላሉ። ማዕከላዊ ቻይና የምትገኘው ዉሃን ግዛት ብቻ 136 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ሲረጋገጥ ሶስቱም የቫይረሱ ሰለባዎች እዛው የሚገኙ ናቸው። ዉሃን ግዛት ዘመድ ጠይቆ የመጣ አንድ የሼንዘን ግዛት ነዋሪ የመጀመሪያ በሽታው ከታየበት ውጭ ያለ የቫይረሱ ተያዥ ሆኗል። ዓለም አቀፉ የጤና ተቋም የበሽታው ምልክት የታየባቸው ሰዎች በፍጥነት እንዲመረመሩ ጥሪ አቅርቧል። የበሽታው መንስዔ የባሕር እንስሳት ሳይሆኑ እንዳልቀረ ግምት አለ። የቫይረሱ ከሰው ወደ ሰው የመዛመት አቅምም ደካማ ነው ተብሏል። የቻይና ጤና ቢሮ 'በሽታውን መቆጣጠር የሚቻል ነው' ቢልም የበሽታው ምንጭ፣ የመዛመት አቅም እና መከላከያ መንገዶች ገና በውል አለመታወቁ ሁኔታዎችን ያከብዳቸዋል ተብሏል። ቻይናዊያን በዚህ ሳምንት የሉናር አዲስ ዓመትን ያከብራሉ። ይህ ወቅት ደግሞ ብዙዎች ቤተሰብና ዘመድ ጥየቃ ከሥፍራ ሥፍራ የሚጓጓዙበት ነው። ኮሮናቫይረስ የሚል የሕክምና ስያሜ ያለው በቫይረስ የሚከሰት በሽታ የመተንፈሻ አካላትን የሚያጠቃ እንደ ጉንፋን ዓይነት የሆነ በሽታ ሲሆን ከበድ ሲል ግን ሊገድል እንደሚችል ባለሙያዎች ይናገራሉ። በፈረንጆቹ 2002 ቻይና ውስጥ 'ሳርስ' የተሰኘ ስም የተሰጠው በሽታ 774 ሰዎችን መግደሉ አይዘነጋም። አዲሱ በሽታም ከሳርስ ጋር ተመሳሳይነት አለው እየተባለ ነው።
56485880
https://www.bbc.com/amharic/56485880
ኤርትራ በአውሮፓ ሕብረት የተጣለባትን ማዕቀብ ተቃወመች
ኤርትራ በአውሮፓ ሕብረት በደኅንነት ተቋሟ ላይ የተጣለባትን ማዕቀብ "ውጤት የማያስገኝ" በማለት እንደማትቀበለው ገለፀች።
ሕብረቱ በኤርትራ ብሔራዊ ደኅንነት መስሪያ ቤት ላይ ማዕቀብ የጣለው ከከባድ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ጋር በተያያዘ ነው። የአውሮፓ ሕብረት ይህንን ማዕቀብ በደኅንንት ተቋሙ ላይ ለመጣል የወሰነው የኤርትራ ብሄራዊ የደኅንት መስሪያ ቤት ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ፈጽሟል በሚል ነው። በዚህም ተቋሙ በዘፈቀደ በተፈጸሙ ግድያዎች፣ በእንግልቶች፣ በሰዎች እስር እና መሰወር ጋር በተያያዘ በተፈጸሙ በደሎች ውስጥ እጁ አለበት በሚል ነው እገዳው የተጣለው። የሕብረቱን እርምጃ ተከትሎ የኤርትራ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በሰጠው ምላሽ የሕብረቱን ውሳኔን "ጥቃት እና ውጤት የማያስገኝ" እንደሆነ በመግለጽ እንደማይቀበለው ገልጿል። ጨምሮም ሕብረቱ እዚህ ውሳኔ ላይ ለመድረስ ሕጋዊም ሆነ የሞራል የበላይነት የለውም በማለት "ለሌላ ድብቅ አላማ ሲባል ኤርትራን ለማሸማቀቅ በሐሰት የተቀነባበረ ክስ ነው" ሲል አጣጥሎታል። የአውሮፓ ሕብረት ምን አይነት ማዕቀብ አንደጣለና ማዕቀቡን በዚህ ወቅት ለምን መጣል እንዳስፈለገ ዝርዝር መረጃ አልሰጠም። ሮይተርስ የዜና ወኪል እንደዘገበው አውሮፓ ውስጥ የኤርትራ ብሔራዊ ደኅንነት መስሪያ ቤት ንብረቶች ይታገዳሉ። ይህ ቢሮ የሚመራው በሜጀር ጀነራል አብርሃ ካሳ ሲሆን፤ ተጠሪነቱም ለአገሪቱ የፕሬዝዘዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጽህፈት ቤት ነው። የአውሮፓ ሕብረት ከኤርትራ በተጨማሪ በቻይና፣ በሊቢያ፣ በሩሲያ፣ በደቡብ ሱዳን እና በሰሜን ኮርያ ያለው የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች እንደሚያሳስቡት አስታውቋል። በሕብረቱ የተጣለው ማዕቀብ 11 ሰዎችና አራት ተቋማትን ያካተተ መሆኑም ተገልጿል። የአውሮፓ ሕብረት ሰብዓዊ መብቶች እንዲከበሩና የመብት ጥሰት የፈጸሙ ተጠያቂ እንዲሆኑ በማሰብ ማዕቀቡን መጣሉ ተዘግቧል። በኤርትራ እና በደቡብ ሱዳን የዘፈቀደ ግድያ እንዲሁም በሩሲያ የፓለቲካ ተቃዋሚዎች የሚደርስባቸውን እንግልት ሕብረቱ አውግዟል። በቻይና፣ በሊቢያ እና በሰሜን ኮርያ የዘፈቀደ ግድያ፣ የሰዎች መሰወር እና ስቃይንም ኮንኗል። በአውሮፓ ሕብረት፣ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ጥሰትን በሚመለከት ማዕቀብ የሚጥለው አካል ያስተላለፈው ውሳኔ ወደ አውሮፓ የሚካሄድ የጉዞ እገዳን ይጨምራል። የአውሮፓ ሕብረት አባላት ማዕቀብ ለተጣለባቸው አካላት በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ የገንዘብ ድጋፍ እንዳያደርጉም ዕገዳ እንደተጣለባቸው ተገልጿል። ይህንን ውሳኔ ያስተላለፈው የአውሮፓ ሕብረት የዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ክንፍ የተቋቋመው አምና ጥቅምት ወር ላይ ነበር። ኤርትራ በተለያዩ ዓለም አቀፍ የመብት ድርጅቶች በሰብአዊ መብቶች ጥሰትና በግድጃ የብሔራዊ ውትድርና አገልግሎት ምክንያት በተደጋጋሚ ወቀሳ ሲሰነዘርባት እንደቆች ይታወቃል።
news-51850790
https://www.bbc.com/amharic/news-51850790
አዲሶቹ ተሿሚ ሚንስትሮች እነማን ናቸው?
የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የተለያዩ የሚንስትር ሹመቶችን አጽድቋል። ፓርላማው የአራት ሚንስትሮችን ሹመት ያጸደቀ ሲሆን ሦስቱ ሚንስትሮች በሚንስትር ደረጃ ሲሾሙ የመጀመሪያቸው ነው።
ከግራ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ፣ አቶ ላቀ አያሌው፣ ዶ/ር ሊያ ታደሰ እና ወ/ሮ ፈልሰን አብዱላሂ በዚህም መሰረት አቶ ላቀ አያሌውን የገቢዎች ሚንስትር፣ ዶ/ር ሊያ ታደሰን የጤና ጥበቃ ሚንስትር፣ ወ/ሮ አዳነች አቤቤን ጠቅላይ አቃቤ ሕግ እና ወ/ሮ ፈልሰን አብዱላሂን የሴቶችና ሕጻናት ሚንስትር አድርጎ ሾሟል። ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ከአንድ ዓመት በላይ የገቢዎች ሚንስትር በመሆን ያገለገሉ ሲሆን በቅርቡ አምባሳደር ሆነው የተሾሙትን አቶ ብርሃኑ ጸጋዬን በመተካት ነው ጠቅላይ አቃቤ ሕግ ሆነው የተሾሙት። ተሿሚዎቹ በፓርላማው ፊት ያላቸው የሥራ ልምድና የትምህርት ደረጃ ተብራርቷል። በዚህም መሰረት የገቢዎች ሚንስትር ሆነው የተሾሙት አቶ ላቀ አያሌው በደጋ ዳሞትና ጃቢ ጠህናን ወረዳዎች በተለያዩ ኃላፊነቶች ሠርተዋል። በ1990ዎቹ መጀመሪያ አካባቢ በተደረገው የኢትዮ ኤርትራ ጦርነት በመሳተፍም በውትድርና ለሦስት ዓመታት አገልግለዋል። ከውትድርና መልስ በምዕራብ ጎጃም ዞን በተለያዩ የኃላፊነት ደረጃዎች ከሠሩ በኋላ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ በመሆን ለሦስት ዓመታት አገልግለዋል። የባህርዳር ከተማ ከንቲባ በመሆን ለሦስት ዓመት ተኩል የሠሩት አቶ ላቀ ከባህር ዳር ከንቲባነት በመቀጠል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ደረጃ የክልሉ ቴክኒክ ሙያና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ኃላፊ ሆነው ለሁለት ዓመታት ካገለገሉ በኋላ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሆነው በመሾም ከአንድ ዓመት በላይ አገልግለዋል። አቶ ላቀ 45 ዓመታቸው ሲሆን በሂሳብ አያያዝና በቢዝነስ አስተዳደር የመጀመሪያና የሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ተከታትለዋል። የጤና ጥበቃ ሚንስትር ሆነው የተሾሙት ዶ/ር ሊያ ታደሰ በ1991 ዓ. ም ከጂማ ዩኒቨርሲቲ በጠቅላላ ሃኪምነት የተመረቁ ሲሆን በ1998 ዓ. ም ደግሞ በማሕጸንና ጽንስ ስፔሻሊስትነት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ተመርቀዋል። የሥራ ልምዳቸውን በተመለከተ በፖሊስ ሆስፒታል፣ በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ኮሌጅ፣ አሜሪካን አገር በሚገኝ ተቋም በሃኪምነት፣ በረዳትነትና በአመራርነት በአጠቃላይ በተለያዩ ሞያዎችና ኃላፊነቶች ከ20 ዓመታት በላይ አገራቸውን አገልግለዋል። በተለያዩ አካባቢዎች የሰላም መድረኮችን በማካሄድም ያገለገሉ ሲሆን እስከ ዛሬ ደግሞ የኢትዮጵያ ጤና ጥበቃ ሚንስትር ዲኤታ ሆነው አገልግለዋል። ዶ/ር ሊያ በአሁኑ ወቅት 44 ዓመታቸው ነው። ምክር ቤቱ ለሴቶችና ሕጻናት ሚንስትር ሆነው እንዲሾሙ ያጸደቀላቸው ወ/ሮ ፌልሰን አብዱላሂ ደግሞ በእንግሊዝ ሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ በሳይኮሎጂ የማስተርስ ዲግሪያቸውን የተከታተሉ ሲሆን የመጀመሪያ ዲግሪያቸውንም በእንግሊዝኛ በዩኒቲ ዩኒቨርሲቲዎች ተከታትለዋል። ወ/ሮ ፈልሰን በአጎራባች ክልሎች በሰላም ዙሪያ ከወጣቶች ጋር በመሥራት ውጤት ማስገኘት የቻሉ ናቸው። በዚህ ተግባራቸውም የሰላም ሚንስቴር "የብሔራዊ የበጎ አድራጎት ፕሮግራም አምባሳደር" አድርጎ ሾሟቸዋል። ወ/ሮ ፈልሰን ዛሬ ከተሾሙት ሚንስትሮች በእድሜ ትንሿ ሲሆኑ 29 ዓመታቸው ነው። ባለፈው ዓመት ግማሽ ሚንስትሮችን ሴት ያደረጉት ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ ዛሬ ከተሾሙት ሦስት ሴት ሚንስትሮች መካከል ሁለቱ በሚንስትር ደረጃ ሲሾሙ ይህ የመጀመሪያቸው ነው።
46272301
https://www.bbc.com/amharic/46272301
የኖርዌይ ተራድዖ ድርጅት ባለፉት ሁለት ዓመታት ከሶማሌ ክልል 700 ሺህ ሰዎች ተፈናቅለዋል ሲል አስታወቀ
ከሐምሌ ወር ጀምሮ ባለው ጊዜ ብቻ ከ200 ሺህ በላይ ሰዎች ግጭት በመሸሽ ከሶማሌ ክልል መፈናቀላቸውን የኖርዌይ ተራድዒ ድርጅት ይፋ አድርጓል።
አብዛኛዎቹ ከኦሮሚያ ክልል ሲሆኑ፤ ከሶማሌ ክልል የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር 1.1 ደርሷል፤ በጎርፍ እና ድርቅ ምክንያት የተፈናቀሉትን ጨምሮ። በኢትዮጵያ ግጭትን በመሸሽ የሚፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ እንደሆነ የሚያትተው መግለጫው በሁለት ዓመታት ብቻ 700 ሺህ ሰዎች ከሶማሌ ክልል ተፈናቅለዋል። አብዛኛዎቹ የተፈናቀሉት ከኦሮሚያ ክልል ሲሆን፤ በጎርፍ እና ድርቅ ምክንያት የተፈናቀሉትን ጨምሮ 1.1 ሚሊዮን ደርሷል፤። የድርጅቱ የምስራቅ አፍሪቃ ተጠሪ ኤቬሊን አየሮ በኦሮሚያና ሶማሌ ክልሎች መካከል የተፈጠረው ግጭት ቁጥራቸው እጅግ የላቀ ነዋሪዎች ቀያቸውን ጥለው እንዲሰደዱ ምክንያት ሆኗል ይላሉ። ጥቂት እርዳታ ሰጭ ድርጅቶች ብቻ በሚገኙበት በዚህ አካባቢ አሁንም የተፈናቃዮች ቁጥር እንዳልቀነሰና የእርዳታ እጥረት እያጋጠመ እንደሆነ ኃላፊው ያክላሉ። «እርዳታ በጣም ያሻል፤ ከመርፈዱ በፊትተፈናቃዮቹ ሕይወትን የሚታደግ እርዳታ ይሻሉ።» ብለዋል • በሞያሌ በተከሰተ ግጭት የ19 ሰዎች ህይወት አለፈ ከምስራቅ ኦሮሚያ የተፈናቀሉት አርሶ አደር አብድራህማን ሞአሊም «ልብሳችንን ብቻ ይዘን ነው፤ ቀያችንን ጥለን የወጣነው» ይላሉ። አብድራህማን ቤተሰቦቻቸውን ይዘው ሶማሌ ክልል በሚገኘው ኮሎጂ በተሰኘ የመጠለያ ጣብያ የሚገኙ ሲሆን ጣቢያው ሌሎች 65 ሺህ ገደማ ሰዎች ተጠልለውበታል። «ከፍተኛ የሆነ የጤና ችግር አለ፤ ሕፃናት እየሞቱ ነው። የኩፍኝ እና የቲቢ በሽታ እየተንሰራፋ ነው። 3 ወይም 4 ሰው በቀን ሊሞትብን ይችላል» ይላሉ አብድራህማን። አዲሱ የሶማሌ ክልል አስተዳደር ለችግሩ መፍትሄ ለማበጀት የእርዳታ ድርጅቶች ወደ ክልሉ ገብተው የበኩላቸውን እንዲያበረክቱ ጥሪ እያቀረበ እንደሆነ የኖርዌይ ተራድዖ ድርጅት በመግለጫው አስታውቋል። • "በኢትዮጵያ 93 በመቶ የሚሆነው ሕዝብ መጸዳጃ ቤት የለውም" ከተፈናቃዮቹ መሃል 5 ሺህ የሚሆኑትን መልሶ ለማቋቋም እቅድ እንዳደለ ድርጅቱ ይፋ አድርጓል። ውሃ፣ መጠለያ እና ሌሎች እርዳታዎች ተፈናቃዮቹ በአፋጣኝ የሚሿቸው እንደሆኑ ነው ድርጅቱ ባወጣው መግለጫ ያሳውቀው። የኢትዮጵያ መንግሥት ለጉዳዩ ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ብናውቅም አፋጣኝ ምላሽ የሚሹ ጉዳዩች እንዳሉ ግን አይካድም ይላል የድርጅቱ ማሳሰቢያ። «ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው አለመረጋጋት በዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ ብዙ ትኩረት ዘንድ ያገኘ አይደለም፤ መንግሥት ለችግሩ ፖለቲካዊና ሰብዓዊ መፍትሄ ለመስጠት እየጣረ እንዳለው እናውቃለን። እርዳታ ሰጭ ድርጅቶች ግን አፋጣኝ ምላሽ በመስጠት ረደግ ሊሯሯጡ ይገባል» ይላሉ ኃላፊዋ። • ሕገወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውር መበራከት ምንን ያመለክታል?
news-45819960
https://www.bbc.com/amharic/news-45819960
ሴራሊዮን በቻይና ብድር አየር ማረፊያ አልገነባም አለች
አፍሪካዊቷ ሃገር ሴራሊዮን በብድር መልክ ቻይና እንድትገነባላት ተስማምታ የነበረውን የአየር መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ሰረዘች።
የቀድሞ ሴራሊዮን ፕሬዚዳንት ኤርነስት ባኢ ኮሮማ እና የቻይና ፕሬዚዳንት ዚ ጂንፒንግ 400 ሚሊዮን ዶላር ፈሰስ ይደረግበታል ተብሎ የነበረውን ይህንን ፕሮጀክት ስምምነቱን ተፈራርመው የነበሩት ከወራት በፊት በምርጫ ተሸንፈው ከሥልጣን የወረዱት የቀድሞ ፕሬዚዳንት ኤርነስት ባኢ ኮሮማ ነበሩ። በወቅቱ የዓለም ባንክ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይኤምኤፍ) ሃገሪቱን ልትወጣው የማትችለውን ዕዳ ይቆልልባታል ሲሉ አስጠንቅቀው ነበር። የሴራሊዮን ውሳኔ የተሰማው የአፍሪካ ሃገራት ለቻይና መክፈል ያለባቸው የዕዳ መጠን እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል የሚሉ ሪፖርቶች እየተሰሙ ባሉበት ወቅት ነው። የሃገሪቱ የአቪዬሽን ሚንስትሩ ካቢኔህ ካሎን ለቢቢሲ ሲናገሩ ሴራሊዮን በአሁኑ ሰዓት አዲስ አየር ማረፊያ ሳይሆን የሚያስፈልጋት ያላትን አየር ማረፊያ ማደስ ነው። • አፍሪካዊያን ሌሎች የአፍሪካ ሃገራትን መጎብኘት ለምን ይከብዳቸዋል? • "ካሜራ ፊት ስቀመጥ ዘርም፣ ዘመድም ፓርቲም የለኝም " ቤተልሔም ታፈሰ • የትግራይ ህዝብ ዴሞክራስያዊ ንቅናቄ- ትህዴን ማን ነው? ሴራሊዮን ከመዲናዋ ፍሪታዎን አቅራቢያ የሚገኝ አንድ አየር ማረፊያ ብቻ ነው ያላት። ከአየር ማረፊው ወደ ዋና ከተማዋ ዘልቀው መግባት የሚፈልጉ ተጓዦች ሄሊኮፕተር አልያም ጀልባ መጠቀም ግድ ይላቸዋል። የአቪዬሽን ሚኒስትሩ ጨምረው ለቢቢሲ እንደተናገሩት ቀጣዩ እቅዳቸው ከአየር ማረፊያው ወደ መዲናዋ የሚያስገባ ድልድይ መገንባት ነው። በሴራሊዮን የቻይና አምባሳደር የሆኑት ዉ ፔንግ ለቢቢሲ ሲናገሩ የአየር ማረፊያ ግንባታ ስምምነት መሰረዙ በሁለቱ ሃገራት መካከል የሚፈጥረው ቁርሾ የለም ብለዋል። ከዓለም ባንክ፣ ከአፍሪካ ልማት ባንክ እንዲሁም ጂ8 ተብለው የሚጠሩ እጅግ የበለጸጉ ሃገራት በድምሩ ለአፍሪካ ከሚሰጡት ብድር ሁሉ የቻይና የፍይናንስ አቅርቦታ ይበልጣል። የቻይናን አካሄድ የማይወዱ የዘርፉ ባለሙያዎች ቻይና ሆን ብላ የአፍሪካ ሃገራትን የብድር ማነቆ ውስጥ እየከተተች ነው ይላሉ። ቻይና ይህን አስተያየት አትቀበለውም።
news-55106408
https://www.bbc.com/amharic/news-55106408
በፈረንሳይ ፖሊሶችን ቪዲዮ መቅረፅ የሚከለክለው ረቂቅ ህግ ቁጣን ቀሰቀሰ
የፈረንሳይ ፖሊስ በመዲናዋ ፓሪስ አዲሱን የፖሊስ ደህንነት ረቂቅ ህግ ለመቃወም የወጡ ተቃዋሚዎችን ለመበተን አስለቃሽ ጋዝ በመጠቀም ላይ ነው። በረቂቁ ህግ መሰረት "ለመጥፎ ተግባር" ለማዋል ፖሊሶችን ፎቶ ማንሳትም ሆነ ቪዲዮ መቅረፅ ወንጀል ነው ይላል።
በዚህ የተቆጡ ፈረንሳያውያን ወደ ጎዳና ላይ የወጡ ሲሆን የተወሰኑትም ድንጋይና ተቀጣጣይ ነገር በፖሊስ መወርወራቸውን ተከትሎ ግጭት ተፈጥሯል ተብሏል። የጋዜጣ መሸጫ ኪዮስክና መኪኖች የተቃጠሉ ሲሆን በርካቶችም በቁጥጥር ስር ውለዋል። በፓሪስ 46 ሺህ የሚሆኑ ተቃዋሚዎች መውጣታቸውን የአገር ውስጥ ሚኒስትር የገለፀ ሲሆን በርካቶቹ በሰላማዊ መንገድ ተቃውሟቸውን ቢገልፁም የተወሰኑት ከፖሊስ ጋር ተጋጭተዋል። እስካሁን ድረስ 46 ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል፤ 20 ፖሊሶችም ተጎድተዋል። ህጉ የፕሬስ ነፃነትን ይቃረናል፤ የፖሊስ ጭካኔንም ለመዘገብ እክል ይፈጥራል ይላሉ ተቃዋሚዎች። "ረቂቅ ህጉ የፕሬስ ነፃነት ላይ እክል የሚፈጥር ነው። የማወቅና የማሳወቅ መብትን እንዲሁም ራስን በነፃነት የመግለፅ መብት ጋር የሚጣረስ ነው" በማለት ከተቃውሞ ሰልፈኞቹ መካከል መናገሩን አጃንስ ፍራንስ ፐሬስ ዘግቧል። መንግሥት በበኩሉ ፖሊሶች በበይነ መረብ ከሚደርስባቸው ትንኮሳና ጥቃት ለመጠበቅ ነው ይላል። ቅዳሜ እለት ከፓሪስ በተጨማሪ በፈረንሳዮቹ ቦርዶክስ፣ ሊሌ፣ ሞንትፔሊየር፣ ናንቴስና ሌሎች ከተሞችም የተቃውሞ ሰልፎች ነበሩ። በዚህ ሳምንት ሶስት ነጭ ፖሊሶች አንድ ጥቁር የሙዚቃ ፕሮዲውሰር በዘረኝነት ተነሳስተው ሲደበድቡት የሚያሳይ ቪዲዮ ወጥቶ ነበር. ሚሸል ዜክለር በፖሊስ ሲደበደብና በቡጡ ሲነረት የሚያሳይ ቪዲዮ በርካቶችን አስደንግጧል። የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ሁኔታውን "አሳፋሪ" ና "ተቀባይነት" የሌለው ያሉ ሲሆን በፖሊስና በዜጎች መካከል ያለው እምነትም እንደገና እንዲገነባ እቅድ እንዲቀርብ ጠይቀዋል። በቪዲዮው ላይ የሚታዩት ፖሊሶችም ከስራ ታግደው ምርመራ እየተከናወነባቸው ነው። በተለየ ዜና ፖሊስ በመዲናዋ ጊዜያዊ የስደተኞች መጠለያን ማፍረሱን ተከትሎ ከስደተኞችና ተሟጋቾች ጋር ግጭት ተፈጥሯል። በዚህም ላይ ፖሊስ ሙሉ ሪፖርት እንዲያቀርብ ትእዛዝ ተላልፏል። ረቂቅ ህጉ ለምን አወዛጋቢ ሆነ? በአገሪቱ ታችኛው ምክር ቤት ድጋፍ የወጣው ረቂቅ ህጉ ምክር ቤቱ እንዲያፀድቀው እየተጠበቀ ነቅ። ከረቂቅ ህጉ ውስጥ አንቀፅ 24 እንደሚያትተው በስራ ላይ ያሉ ፖሊሶች "አካላዊም ሆነ ስነ ልቦናዊ ጉዳት" ለማስከተል በሚል ፎቶ ማንሳትም ሆነ ቪዲዮ መቅረፅ በወንጀል ያስቀጣል ይላል። ህጉን ተላልፈው የተገኙም አንድ አመት እስርና 53 ሺህ 840 ዶላር ቅጣት ይጠብቃቸዋል። መንግሥት እንደሚለው ረቂቅ ህጉ ሚዲያም ሆነ ግለሰቦች የፖሊስን ጥቃት ሪፖርት የማድረግ መብታቸውን አይከለክልም፤ የረቂቅ ህጉ ዋና አላማ ለፖሊስ ጥበቃ ለመስጠት ነው በማለት ይከራከራል። ተቃዋሚዎች ግን እንደሚሉት ባለፈው ሳምንት እንደተፈፀመው ጥቁር ግለሰብ በፖሊስ ሲደበደብ የሚያሳይ ቪዲዮ አይጋለጥም ነበር ይላሉ። ረቂቅ ህጉ ከፍተኛ ትችን ማስተናገዱን ተከትሎ ጠቅላይ ሚኒስትር ጂን ካስቴክስ አንቀፅ 24ን ለማሻሻል ኮሚሽን አቋቁማለሁ ብለዋል።
news-57084284
https://www.bbc.com/amharic/news-57084284
ፈጠራ፡ 'አውሮፕላን' ሰርተው ለማብረር የሞከሩት ወንድማማቾች
በምስራቅ ወለጋ ከነቀምቴ በቅርብ ርቀት በምትገኘው የሲቡ ሲሬ ከተማ ነዋሪ የሆኑት ወንድማማቾች ከሰሞኑ የሰሯትን 'አውሮፕላን' ለማብረር ጥረት ማድረጋቸው የበርካቶች መነጋገሪያ ሆነዋል።
ወንድማማቾቹ ለሊሳ ዳንኤል እና ቢቂላ ዳንኤል ይባላሉ። ወጣቶቹ "ኦሮሚያ" ሲሉ የሰየሟትን 'አውሮፕላናቸውን' ለማብረር ሙከራ ማድረጋቸው የአከባቢ ሰዎች በታሪክ መዝገብ ለመጀመሪያ ጊዜ ባለ ሞተር አውሮፕላን ካበረሩት አሜሪካውያን ወንድማማቾች ኦርቪል እና ዊልበር ራይት ጋር አነጻጽረዋቸዋል። ወንድማማቾቹ የሰሯትን 'አውሮፕላን' ለማብረር ያደረጉት ጥረት ሳይሳካ ቀርቷል። 'አውሮፕላኗ' እንዴት ተሰራች? ወንድማማቾቹ የሰሯት 'አውሮፕላን' ወንድማማቾቹ የሰሯት 'አውሮፕላን' 2 ሜትር ርዝመት እና 4.5 ሜትር ከፍታ እንዳላት ይናገራሉ። ሁለት ሰዎችን የማሳፈር አቅም ያላት ይህች 'አውሮፕላን' የክንፎቿ ርዝመት ከአንዱ ጫፋ እስከ ሌላኛው ጫፍ 7 ሜትር ይሆናል። ቢቂላ እና ለሊሳ እንደሚሉት ከሆነ 'አውሮፕላኗን' ለመስራት ሦስት ዓመታት ፈጅቶባቸዋል። ከጥቂት ቀናት በፊት የበረራ ሙከራ ለማድረግ ያደረጉት ጥረት እንዳልተሳካ ይናገራሉ። ለዚህ ደግሞ ምክንያቱን "ሞተሩ ያረጀ ስለሆነ ከመሬት ተነስታ አልበረረችም" ሲሉ አስረድተዋል። ወጣቶቹ ሙከራቸው ባይሳካም ሰዎች እንዳበረቷቷቸው ይናገራሉ። ሙከራ ባደረጉበት ወቅት አደጋ ሊያጋጥም ይችላል በማለት ስጋት ገብቷቸው የነበሩ ሰዎች እንደነበሩም አልሸሸጉም። ወንድማማቾቹ አውሮፕላን የመሠረት ፍላጎት ከልጅነታቸው ጀምሮ የነበረ መሆኑን ለቢቢሲ ተናግረዋል። ከዚህ ቀደም ሰው ይዞ ሊበር የሚችል 'አውሮፕላን' ከመስራታችን በፊት "መብረር የሚችሉ ትናንሽ አውሮፕላኖችን" ሰርተናል ይላሉ። "ልጆች እያለን ትንንሽ አውሮፕላኖችን እንሰራ ነበር። እናታችን ታበረታታናለች። የሚያስፈልጉን ነገሮችን ትገዛልን ነበር። ዛሬ ላይ አእምሯቸን እያደገ፤ የትምህርት ደረጃችንም ከፍ እያለ ሲመጣ መስራት እንችላለን [ሰው ይዞ መብረር የሚችል] ብለን ተነሳን" ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል። "ፈጣሪ በሰጠን ሙያ አውሮፕላን ሠርተን ተሳክቶልናል" የሰሯትን 'አውሮፕላን' ኦሮሚያ ሲሉ የሰየሙት ወንድማማቾቹ፤ "ኦሮሚያ ወደፊት የራሷ የሆነ አቪዬሽን እንዲኖራት ምኞት ስላለን ነው" ብለዋል። ከምን ተሰራች? ቢቂላ እና ለሊሳ የሰሩት 'አውሮፕላን' በአካባቢያቸው ከሚገኙ ቁሳቁሶች እንደሆነ ይናገራሉ። ወጣቶቹ የሞተር ሳይክል ሞተር፣ ከዋንዛ ዛፍ የተገኘ እንጨት፣ በድጋፍ መልክ ከሰዎች ያገኙት አሮጌ የአውሮፕላን ጎማ እንዲሁም ከባጃጅ የተወሰዱ እቃዎችን በግብዓትነት መጠቀማቸውን ይናገራሉ። ከዚህ በተጨማሪም ከአልሙኒየም የተሠራ ቆርቆሮ፣ ስፖንጅ፣ በርካሽ ዋጋ የተገዙ ያረጁ የአውሮፕላን መቀመጫዎች ጥቅም ላይ መዋላቸውን ያስረዳሉ። "ቆርቆሮ እና ብርት እርስ በእርስ እየተፋፋቁ ድምጽ እንዳይፈጥሩ ስፖንጅ ተጠቅመናል" በብለዋል ወንድማማቾቹ። የዋርካ እንጨት ጠንካራ ስለሆነ እና ክብደት ስለሌለው ጥቅም ላይ ማዋላቸውን ይናገራሉ። ይህን ለመሠረት ክህሎቱን ከየት አገኛችሁት ተብለው ለተጠየቁት ጥያቄ ወንድማማቾቹ ኢንተርኔት እና መጽሃፍት ሲያጣቅሱ መቆየታቸውን ገልፀዋል። ዩቲዩብ ላይ ያሉ ቪዲዮችን በመመልከት እና ከኢንተርኔት ላይ መጽሃፍትን እያወረዱ ሲያነቡ መቆየታቸውን ያስረዳሉ። ወንድማማቾቹ እንደሚሉት ለሰሩት 'አውሮፕላን' አግባብ የሆነውን ሞተር ባለማግኘታቸው ከመሬት ተነስታ መብረር አልቻለችም። ወንድማማቾቹ የሰሯት 'አውሮፕላን'
57019408
https://www.bbc.com/amharic/57019408
ሕዳሴ ግድብ፡ የኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብጽ ባለሥልጣናት የሕዳሴ ግድቡን በሚመለከት የጎበኟቸው የአፍሪካ አገራት
ኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን በሕዳሴ ግድቡ ዙሪያ ኪንሻሳ ያደረጉት የሶስትዮሽ ድርድር ያለውጤት ከተጠናቀቀ በኋላ ከፍተኛ ባለስልጣኖቻቸውን ወደተለያዩ የአፍሪካ አገራት ልከዋል።
ሦስቱ አገራት ለዓመታት በሕዳሴ ግድብ ውሃ አሞላል እና አለቃቀቅ ጋር በተያያዘ ሲያደርጉት የነበረው ድርድር ይህ ነው የሚባል ውጤት አላመጣም። በህዳሴ ግድቡ ጉዳይ ለ3 ቀናት ሲካሄድ የነበረው የኪንሻሳው የሶስትዮሽ ውይይት ያለስምምነት ሲጠናቀቅ ሱዳን፣ ኢትዮጵያ በኪንሻሳው ውይይት ላይ "ስምምነት ላይ ለመድረስ የሚያስቸግር ግትር አቋም አራምዳለች" ብላ ስትከስ፣ ግብፅ ደግሞ "ኢትዮጵያ ሁሉንም የድርድር ሂደት አማራጮች ውድቅ ማድረጓን" አስታውቃለች። ኢትዮጵያ በበኩሏ ውይይቱ ያለስምምነት ለመጠናቀቁ ሱዳን እና ግብጽን ወንጅላለች። በባለፉት ሳምንታት የሶስቱ አገራት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ወደ ተለያዩ የአፍሪካ አገራት ያደረጉት ጉብኝት ዋነኛ ዓላማም የታላቁ የህዳሴ ግድብ ውዝግብ ሲሆን ትኩረት ያደረጉት ደግሞ የተባበሩት መንግስታት ድርጀት የጸጥታው ምክር ቤት ተለዋጭ አባል ሃገራትን ነው። ኒጀር፣ ቱኒዚያ እና ኬኒያ የወቅቱ የተመድ ተለዋጭ የጸታው ምክር ቤት አባላት ናቸው። ኢትዮጵያ መጪው ክረምት ሲገባ ሁለተኛ ዙር ሙሌቷን በእቅዷ መሰረት እንደምታከናውን አስታውቃለች። ነገር ግን ግብጽና ሱዳን ኢትዮጵያ ሁለተኛ ዙር ሙሌት ከማከናወኗ በፊት ስምምነት ላይ መደረስ አለበት ይላሉ። ይህንንም ተከትሎ ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብን ሁለተኛ ዙር ውሃ ሙሌት ከማካሄዷ በፊት ግብጽ እና ሱዳን ለመረጃ ልውውጥ ባለሙያዎች እንዲመድቡ ጠይቃለች። ኢትዮጵያ ወዴት አቀናች? የኢፌድሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ከውሃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚንስትሩ ዶ/ር ስለሺ በቀለ ጋር በመሆን ወደ ኒጀር አቅንተዋል። እነዚህ የኢትዮፕያ ከፍተኛ ባለሥልጣናት በኒያሚ ቆይታቸው ለፕሬዝዳንት ሞሐመድ ባዞም በህዳሴው ግድብ ዙሪያ ገለጻ ማድረጋቸውን የውሃ ሚኒስትሩ በትዊተር ገጻቸው ላይ ያሰፈሩት መልዕክት ያስረዳል። የውሃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚንስትሩ ዶ/ር ስለሺ በቀለ በትዊተር ሰሌዳቸው፤ ከኒጀር ፕሬዚዳንት እና ሚኒስትሮቻቸው ጋር በኒያሚ ውይይትና ጉብኝት ማድረጋቸውን ጠቅሰዋል። በጉብኝቱም በትግራይ ክልል ስላለው ወቅታዊ ሁኔታ፣ የህዳሴ ግድብ ድርድር እና የግንባታ ደረጃ፣ ቀጣዩ ምርጫና ከሱዳን ጋር ስላለው የድንበር ጉዳይ የኢትዮጵያን አቋም ማስረዳታቸውን አስታውቀዋል። "ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሄ ፍቱን መሆኑን ታምናለች" ብለዋል ሚንስትሩ። በሌላ በኩል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ወደ ደቡብ አፍሪካ በማቅናት ፕሬዚዳንት ሲሪል ራማፎሳ ጋር ተመሳሳይ ውይይት ማድረጋቸውን መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። ሱዳን ምን አከናወነች? የሱዳን የውጪ ጉዳይ ሚንስትር መሪያም አልሳዲቅ አልመሐዲ (ዶ/ር) በሕዳሴ ግድብ ዙሪያ የተለያዩ የአፍሪካ አገራት መሪዎችን አነጋግረዋል። የውጪ ጉዳይ ሚንስትሯ በቅድሚያ ያቀኑት ወደ ኬንያ ሲሆን ከፕሬዝደንት ኡሁሩ ኬንያታ፣ ከኬንያ የውጪ ጉዳይ ሚንሰትር ራይቼል ኦማሞ እና በናይሮቢ ከሚኖሩ የሱዳን ማህበረሰብ አባላት ጋር መወያየታቸውን ተገልጿል። ከፕሬዝደንት ኡሁሩ ጋር በነበራቸው ውይይት ከግድቡ ጋር በተያያዘ ሦስቱንም አገራት የሚያስማማ ስምምነት መደረስ አለበት የሚል አቋም ሱዳን እንዳላት አንጸባርቂያለሁ ብለዋል የውጪ ጉዳይ ሚንስትሯ በትዊተር ገጻቸው ላይ። የውጪ ጉዳይ ሚንሰትሯ ሩዋንዳ ተገኝተው ተመሳሳይ ውይይት ከፕሬዝደንት ፖል ካጋሜ ጋር አድርገዋል። ፕሬዝደንት ኡሁሩ እና ፕሬዝዳንት ካጋሜ ከሱዳኗ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ጋር በተገናኙበት ወቅት ከጠቅላይ ሚንስትር ሃምዶክ የተላከ መልዕክት ተቀብለዋል። የግብጽ ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ወደዴት አቀኑ? የግብጽ የውጪ ጉዳይ ሚንሰትር ሳሚ ሽኩሪ የግድቡን ድርድር በተመለከተ የአገራቸውን አቋም ለማንጸባረቅ ወደ ተለያዩ የአፍሪካ አገራት ጉዞ አድርገው ነበር። ሳሚ ሽኩሪ ከሳምንታት በፊት ወደ ወደ ኬንያ፣ ኮሞሮስ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ሴኔጋል፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኦፍ ኮንጎ እና ቱኒዚያ ተጉዘዋል። ኢትዮጵያ የሦስትዮሽ ድርድሩን በአፍሪካ ሕብረት በአደራዳሪነት እንዲቀጥል ፍላጎት አላት። በቀጣይ የክረምቱ ወራት ሁለተኛው የግድቡ ውሃ ሙሌት እንደምታካሂድ ይፋ ያደረገችው ኢትዮጵያ፤ በአፍሪካ ሕብረት የሚመራውን አደራዳሪ ቡድን ወደ ጎን ማድረግ፤ በሦስቱ አገራት መካከል አለመተማመንን ይፈጥራል ትላለች። ግብጽ እና ሱዳን በበኩላቸው ሶስቱ አገራት ከስምምነት ሳይደርሱ ሁለተኛው ዙር የውሃ ሙሌት መካሄድ የለበትም ይላሉ። ከዚህ በተጨማሪም አሜሪካ እና የአውሮፓ ሕብረት በአደራዳሪነት እንዲመሩ ፍላጎት አላቸው። የህዳሴ ግድብ በአምስት ዓመት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ የነበረው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እስካሁን ሲጓተት ቆይቶ በግንባታ ላይ አስር ዓመትን አስቆጥሯል። ተገንብቶ ሲያበቃ በግዝፈቱ ከአፍሪካ ቀዳሚ እንደሚሆን የተነገረው ግድቡ በአሁኑ ጊዜ ወደ 80 በመቶ የሚጠጋው የግንባታ ሥራው መጠናቀቁ የተገለጸ ሲሆን በሚቀጥለው ዓመት በከፊል የኤሌክትሪክ ኃይል ያመነጫል ተብሎ ይጠበቃል። ከአምስት ሺህ በላይ ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል እንደሚያመነጭ የተነገረለት ይህ ግድብ ተጠናቆ ሥራ ሲጀምር ከግማሽ በላይ ለሚሆነው የአገሪቱ ሕዝብ፣ ለኢንዱስትሪዎችና ለጎረቤት አገራት የኤሌክትሪክ ኃይል ያቀርባል ተብሎ ተስፋ ተጥሎበታል።